የአልኮል መጠጦችን በቴሌቪዥን፤ በሬዲዮ እና በግዙፍ የአደባባይ ሠሌዳዎች ማስተዋወቅን የሚከለክለው «የምግብ እና የመድኃኒት አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ» ከዛሬ ግንቦት 21 ቀን፤ 2011 ዓ.ም ጀምሮ ተፈጻሚ እንደሚኾን የጤና ጥበቃ ሚንሥትር ዐስታውቋል።
ከዚህ ቀደም በግዙፍ ሠሌዳዎች ላይ በአደባባይ የተሰቀሉ የአልኮል ማስታወቂያዎች እንዲነሱ ማሳሰቢያ ተላልፏል። ክልከላውን በማናቸውም መንገድ የሚተላለፉ አካላት ካሉ ኅብረተሰቡ በ«8482» ላይ ደውሎ እንዲጠቊም ሚንሥትር መሥሪያ ቤቱ ጥሪ አስተላልፏል። የኢትዮጵያ የምግብ እና የመድኃኒት አስተዳደር ፌስቡክ ገጽ ላይም ጥቆማ ማድረግ እንደሚቻል የጤና ጥበቃ ሚንሥትር ዶክተር አሚር አማን በማኅበራዊ መገናኛ ገጻቸው ላይ ጽፈዋል።
አንዳንድ የግል መገናኛ አውታሮች ከማስታወቂያ የሚያገኙት ገቢ እጅግ የሚቀንስ በመኾኑ የሠራተኛ ቅነሳ ሊያደርጉ እንደሚችሉ ገልጠዋል።
Via #DW
ፎቶ፦ የጤና ጥበቃ ሚንሥቴር ዶ/ር አሚር አማን ትዊተር ገጽ
ከዚህ ቀደም በግዙፍ ሠሌዳዎች ላይ በአደባባይ የተሰቀሉ የአልኮል ማስታወቂያዎች እንዲነሱ ማሳሰቢያ ተላልፏል። ክልከላውን በማናቸውም መንገድ የሚተላለፉ አካላት ካሉ ኅብረተሰቡ በ«8482» ላይ ደውሎ እንዲጠቊም ሚንሥትር መሥሪያ ቤቱ ጥሪ አስተላልፏል። የኢትዮጵያ የምግብ እና የመድኃኒት አስተዳደር ፌስቡክ ገጽ ላይም ጥቆማ ማድረግ እንደሚቻል የጤና ጥበቃ ሚንሥትር ዶክተር አሚር አማን በማኅበራዊ መገናኛ ገጻቸው ላይ ጽፈዋል።
አንዳንድ የግል መገናኛ አውታሮች ከማስታወቂያ የሚያገኙት ገቢ እጅግ የሚቀንስ በመኾኑ የሠራተኛ ቅነሳ ሊያደርጉ እንደሚችሉ ገልጠዋል።
Via #DW
ፎቶ፦ የጤና ጥበቃ ሚንሥቴር ዶ/ር አሚር አማን ትዊተር ገጽ
ሰላም የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የፌስ-ቡክ ገጻችን ተከታታዮች ይህ የናንተን የህግ ግንዛቤ ለማሳደግ በየሳምንቱ አርብ የምናቀርብላችሁ የህግ ማብራሪያ ሲሆን በዛሬው ጽሁፋችን በማህበራዊ ሚዲያዎች የጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ የማሰራጨት ድርጊት የሚያስከትለውን የህግ ተጠያቂነት በተመለከተ ሰፋ ያለ ማብራሪያ አቅርበንላችኋል መልካም ንባብ!
1. የማህበራዊ ሚዲያ ጽንሰ ሃሳብና በአገራችን ስላለዉ የአጠቃቀም ሁኔታ
በኢንተርኔት ላይ ከምንጠቀማቸው እጅግ በጣም ዝነኛ ከሆኑ መካነ ድሮች መካከል የማኀበራዊ ሚዲያዎች ይገኙበታል። ፌስቡክ ከቢሊዮን በላይ፣ ኢንስታግራም እና ትዊተር እያንዳንዳቸው በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተጠቃሚዎች አሏቸው። ማኀበራዊ ሚዲያዎች የተገነቡት የተለያዩ ሃሳቦችን፣ ፎቶግራፎችን እና የግል መረጃን ለማጋራት ነው። ይሁን እንጂ አሁን ላይ አገራችንን ጨምሮ በተለያዩ የአለመ አገራት ዉስጥ ሰዎች እነዚህን ድረገጾች ለታለመላቸዉ በጎ ተግባራት ከማዋል በተቃራኒዉ ለእኩይ ተገባረት ለምሳሌ የጥላቻ ንግግሮችን እና የሃሰት መረጃዎችን ለማሰራጨት ሲጠቀሙት ይሰተዋላል፡፡ በማህበራዊ ሚዲያዎች እየተስፋፉ የመጡት ኃላፊነት የጎደላቸው መልዕክቶችና የሐሰት ወሬዎች በተለይ እንደፌስቡክ ባሉ የማህበራዊ ድረ ገጾች አንድን ቡድን፣ ብሔር የሚያንቆለጳጵሱ፣ የሌላውን ብሔር ዝቅ የሚያደርጉ፣ የሚዘልፉ፣ የሚያዋርዱ ከፋፋይ አጀንዳዎች በሀገሪቱ ለሚከሰቱ ግጭቶች ምክንያት ናቸዉ፡፡
2. የማህበራዊ ሚዲያዎች አጠቃቀም ገደብ በኢትዮጵያ
የጥላቻ ንግግርና የሃሰተኛ መረጃ ስርጭት ለማህበራዊ ስምሪት፣ ለፖለቲካ መረጋጋት፣ ለሀገራዊ አንድነት፣ ለሰብዓዊ ክብር እና ለብዝሃነት ጠንቅ መሆኑን በመገንዘብ በተለይም በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ በህብረተሰቡ መካከል ያሉ መልካም እሴቶች በጥላቻ ንግግሮችና በሀሰተኛ መረጃ ስርጭት ምክንያት በከፍተኛ ደረጃ እየተሸረሸሩና ለሀገርም ስጋት እየደቀኑ በመሆናቸው በቅርቡ የጥላቻ ንግግርና የሃሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር አዋጅ ቁጥር 1185 ጸድቆ ስራ ላይ ዉሏል፡፡
በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት ዕውቅና ከተሰጣቸው መብቶች አንዱ አንቀጽ 29 ላይ የተደነገገው ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት ቢሆንም ይህ መብት በሕገ መንግሥቱ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ስምምነቶችም ጭምር ገደብ የሚጣልበት ነዉ፡፡ በመሆኑም ሰዎች ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብታቸውን ተግባራዊ ሲያደርጉ ሰብዓዊ ክብርን፣ የሌሎችን ደኅንነትና ሰላም አደጋ ላይ ከሚጥል ንግግር መቆጠብ ይኖርባቸዋል፡፡
የጥላቻ ንግግርና የሃሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በወጣዉ አዋጅ ስለ የጥላቻ ንግግርና ሃሰተኛ መረጃ ስርጭት ምንነት እንዲሁም ድረግቶቹን ፈጽሞ የተገኘ ሰዉ ስለሚቀጣዉ የወንጀል ቅጣት እንደሚከተለዉ እናያለን፡፡
የጥላቻ ንግግር ማለት በአንድ ሰዉ ወይም የተወሰነ ቡድን ማንነት ላይ ያነጣጠረ፣ ብሄርን፡ብሄረሰብንና ህዝብን፣ ሀይማኖትን፣ ዘርን፣ ጾታን ወይም አካል ጉዳተኝነትን መሰረት በማድረግ ሆን ተብሎ ጥላቻን፣ መድሎን ወይም ጥቃትን የሚያነሳሳ ንግግር ሲሆን ንግግሩ በቃል፣ በጽሑፍ፣ በምሥልና ሥዕል፣ በቅርጻ ቅርጽ እና በሌሎች ተመሳሳይ መንገዶች መልእክትን የማሰራጨት ተግባርን በመጠቀም የተደረገ ሊሆን ይችላል፡፡
በመሆኑም በአዋጁ አንቀጽ 4 እና 7(1) መሰረት የጥላቻ ንግግርን በብሮድካስት፣ በህትመት ወይም በማህበራዊ ሚዲያዎች ወይም በሌላ ተመሳሳይ ዘዴዎች አማካኝነት በጽሁፍ፣ በምስል፣ በድምጽ ወይም በቪዲዮ ማሰራጨት የተከለከለና ይህን የተከለከለዉን የጥላቻ ንግግር ማድረግ እስከ ሁለት አመት በሚደርስ ቀላል እስራት ወይም ከብር 100,000 ያልበለጠ መቀጮ ያስቀጣል፡፡ በጥላቻ ንግግሩ ምክንያት በግለሰብ ወይም በቡድን ላይ ጥቃት የተፈጸመ እንደሆነ ቅጣቱ ከአንድ አመት እስከ አምስት አመት የሚደርስ ቀላል እስራት ነዉ፡፡(አንቀጽ 7(2) በሌላ በኩል ደግሞ በአንቀጹ ንሁስ አንቀጽ 4 መሰረት ወንጀሉ የተፈጸመው ከአምስት ሺ በላይ ተከታይ ባለው የማህበራዊ ሚዲያ ገጽ ከሆነ ወይም በብሮድካስት አገልግሎት ወይም በየጊዜው በሚወጣ የህትመት ውጤት ከሆነ ቅጣቱ እስከ ሶስት አመት የሚደርስ ቀላል እስራት እና ከብር 100,000 ያልበለጠ መቀጮ ይሆናል፡፡
ከጥላቻ ንግግር በተጨማሪ አዋጁ ሃሰተኛ የሆነ መረጃ ማሰራጨትንም በወንጀልንት የከለከለ ሲሆን ሀሰት የሆነና የመረጃውን ሀሰተኝነት በሚያውቅ ወይም መረጃውን የሚያሰራጨው ሰው ካለበት አጠቃላይ ሁኔታ አንጻር የመረጃውን እዉነተኝነት ለማጣራት በቂ ጥረት ሳይደረግ የሚሰራጭ ሁከት ወይም ግጭት የሚያነሳሳ ወይም ጥቃት እንዲደርስ የሚያደርግ እድሉ ከፍ ያለ የሀሰት ንግግር ነው በሚል ትረጉም ተሰጥቶታል፡፡ በአንቀጽ 5 እና 7(3) መሰረት የሐሰት መረጃን በአደባባይ ስብሰባዎች በብሮድካስት፣ በህትመት ወይም በማህበራዊ ሚዲያዎች ወይም በሌላ ተመሳሳይ ዘዴዎች አማካኝነት በጽሁፍ፣ በምስል፣ በድምጽ ወይም በቪዲዮ ማሰራጨት የተከለከለና ይህን ተግባር የፈጸመ ሰዉ እስከ አንድ አመት በሚደርስ በቀላል እስራት ወይም ከብር 50,000 ባልበለጠ መቀጮ ይቀጣል፡፡ ወንጀሉ የተፈጸመው ከአምስት ሺ በላይ ተከታይ ባለው የማህበራዊ ሚዲያ ገጽ ከሆነ ወይም በብሮድካስት አገልግሎት ወይም በየጊዜው በሚወጣ የህትመት ውጤት ከሆነ ቅጣቱ እስከ ሶስት አመት የሚደርስ ቀላል እስራት እና ከብር 100,000 ያልበለጠ መቀጮ ይሆናል፡፡(አንቀጽ 7(4) በሌላ ሁኔታ ሐሰተኛ መረጃ በመሰራጨቱ ምክንያት በግለሰብ ወይም በቡድን ላይ ጥቃት የተፈጸመ ከሆነ፣ ሁከት ወይም ግጭት የተከሰተ እንደሆነ ቅጣቱ ከሁለት እስከ አምስት አመት በሚደርስ ቀላል እስራት የሚሆን ሲሆን ምንም ጉዳት ካልደረሰ ጥፋተኛውን ለማረም የተሻለ ነው ብሎ ሲያምን ፍርድ ቤት በእስራት ምትክ የግዴታ የማህበረሰብ አገልግሎት ስራን በአማራጭ ቅጣትነት ሊወስን ይችላል።(አንቀጽ 7(5)(6))
ከለይ የተቀመጡት ተጠያቂነቶች እንዳለሆነዉ በአዋጁ አንቀጽ 6 ስር ንግግሩ የሌላ ሰዉ ሆኖ ለትምህርታዊ ወይም ሳይንሳዊ ጥናት አካል ለማድረግ፤ንግግሩን በተመለከተ የዜና ዘገባ ወይም ትንታኔ ለመስራት ወይም የፖለቲካ ትችት ለመስጠት፤የኪነጥበብ ፣ ትወና ወይም መሰል የስነጥበብ ውጤት በማድረግ ህብረተሰብን ለማስተማር፤ ወይም የሃይማኖት አስተምህሮት አካል እንደሆነ እንዲሁም ንግግሩን ያሰራጨው ወይም ያደረገው ሰው የመረጃውን እውነተኛነት ለማረጋገጥ በሱ ሁኔታ ካለ ሰው የሚጠበቀውን ምክንያታዊ ጥረት ያደረገ እንደሆነ እንደ ጥላቻ ንግግር ወይም የሃሰት መረጃ ስርጭት የማይወሰድ ስለመሆኑ በልዩ ሁኔታ ተደንግጓል፡፡
3. በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚፈጠሩ ችግሮችን ለመቅረፍ ምን መደረግ አለበት
በመሆኑም ህብረተሰቡ የጥላቻ ንግግርና ሃሰተኛ መረጃን ማሰራጨት በወንጀል የሚያስጠይቅ መሆኑን ከመረዳት ባለፈ ተግባሩ እጅግ በጣም አስነዋሪና ለሀገር መፈራረስ ምክንያት መሆኑን በመገንዘብ ሃሰብን በነጻነት የመግልጽ መብቱን በአግባቡ መጠቀም አለበት፡፡
በመንግስት በኩልም ለነዚህ የጥላቻ ንግግሮች እንዲሁም ሃሰተኛ መረጃ ስርጭቶች ምክንያት የሆኑትን በህብረተሰቡ መካከል ለተፈጠሩት ቁርሾዎች እና አለመግባባቶች ብሄራዊ መግባበቶችንና እርቆች እንዲፈጸሙ ሁኔታዎችን ማመቻቸት እንዲሁም ህጉን በሚጥሱ ግለሰቦች ላይም ተገቢዉን እርምጃ መዉሰድ አስፈላጊ ነዉ፡፡ ከዚህም ባለፈ ለማህበረሰቡ በተለይም ለወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል በጉዳዩ ላይ ሰፊ የሆነ የ
1. የማህበራዊ ሚዲያ ጽንሰ ሃሳብና በአገራችን ስላለዉ የአጠቃቀም ሁኔታ
በኢንተርኔት ላይ ከምንጠቀማቸው እጅግ በጣም ዝነኛ ከሆኑ መካነ ድሮች መካከል የማኀበራዊ ሚዲያዎች ይገኙበታል። ፌስቡክ ከቢሊዮን በላይ፣ ኢንስታግራም እና ትዊተር እያንዳንዳቸው በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተጠቃሚዎች አሏቸው። ማኀበራዊ ሚዲያዎች የተገነቡት የተለያዩ ሃሳቦችን፣ ፎቶግራፎችን እና የግል መረጃን ለማጋራት ነው። ይሁን እንጂ አሁን ላይ አገራችንን ጨምሮ በተለያዩ የአለመ አገራት ዉስጥ ሰዎች እነዚህን ድረገጾች ለታለመላቸዉ በጎ ተግባራት ከማዋል በተቃራኒዉ ለእኩይ ተገባረት ለምሳሌ የጥላቻ ንግግሮችን እና የሃሰት መረጃዎችን ለማሰራጨት ሲጠቀሙት ይሰተዋላል፡፡ በማህበራዊ ሚዲያዎች እየተስፋፉ የመጡት ኃላፊነት የጎደላቸው መልዕክቶችና የሐሰት ወሬዎች በተለይ እንደፌስቡክ ባሉ የማህበራዊ ድረ ገጾች አንድን ቡድን፣ ብሔር የሚያንቆለጳጵሱ፣ የሌላውን ብሔር ዝቅ የሚያደርጉ፣ የሚዘልፉ፣ የሚያዋርዱ ከፋፋይ አጀንዳዎች በሀገሪቱ ለሚከሰቱ ግጭቶች ምክንያት ናቸዉ፡፡
2. የማህበራዊ ሚዲያዎች አጠቃቀም ገደብ በኢትዮጵያ
የጥላቻ ንግግርና የሃሰተኛ መረጃ ስርጭት ለማህበራዊ ስምሪት፣ ለፖለቲካ መረጋጋት፣ ለሀገራዊ አንድነት፣ ለሰብዓዊ ክብር እና ለብዝሃነት ጠንቅ መሆኑን በመገንዘብ በተለይም በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ በህብረተሰቡ መካከል ያሉ መልካም እሴቶች በጥላቻ ንግግሮችና በሀሰተኛ መረጃ ስርጭት ምክንያት በከፍተኛ ደረጃ እየተሸረሸሩና ለሀገርም ስጋት እየደቀኑ በመሆናቸው በቅርቡ የጥላቻ ንግግርና የሃሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር አዋጅ ቁጥር 1185 ጸድቆ ስራ ላይ ዉሏል፡፡
በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት ዕውቅና ከተሰጣቸው መብቶች አንዱ አንቀጽ 29 ላይ የተደነገገው ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት ቢሆንም ይህ መብት በሕገ መንግሥቱ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ስምምነቶችም ጭምር ገደብ የሚጣልበት ነዉ፡፡ በመሆኑም ሰዎች ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብታቸውን ተግባራዊ ሲያደርጉ ሰብዓዊ ክብርን፣ የሌሎችን ደኅንነትና ሰላም አደጋ ላይ ከሚጥል ንግግር መቆጠብ ይኖርባቸዋል፡፡
የጥላቻ ንግግርና የሃሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በወጣዉ አዋጅ ስለ የጥላቻ ንግግርና ሃሰተኛ መረጃ ስርጭት ምንነት እንዲሁም ድረግቶቹን ፈጽሞ የተገኘ ሰዉ ስለሚቀጣዉ የወንጀል ቅጣት እንደሚከተለዉ እናያለን፡፡
የጥላቻ ንግግር ማለት በአንድ ሰዉ ወይም የተወሰነ ቡድን ማንነት ላይ ያነጣጠረ፣ ብሄርን፡ብሄረሰብንና ህዝብን፣ ሀይማኖትን፣ ዘርን፣ ጾታን ወይም አካል ጉዳተኝነትን መሰረት በማድረግ ሆን ተብሎ ጥላቻን፣ መድሎን ወይም ጥቃትን የሚያነሳሳ ንግግር ሲሆን ንግግሩ በቃል፣ በጽሑፍ፣ በምሥልና ሥዕል፣ በቅርጻ ቅርጽ እና በሌሎች ተመሳሳይ መንገዶች መልእክትን የማሰራጨት ተግባርን በመጠቀም የተደረገ ሊሆን ይችላል፡፡
በመሆኑም በአዋጁ አንቀጽ 4 እና 7(1) መሰረት የጥላቻ ንግግርን በብሮድካስት፣ በህትመት ወይም በማህበራዊ ሚዲያዎች ወይም በሌላ ተመሳሳይ ዘዴዎች አማካኝነት በጽሁፍ፣ በምስል፣ በድምጽ ወይም በቪዲዮ ማሰራጨት የተከለከለና ይህን የተከለከለዉን የጥላቻ ንግግር ማድረግ እስከ ሁለት አመት በሚደርስ ቀላል እስራት ወይም ከብር 100,000 ያልበለጠ መቀጮ ያስቀጣል፡፡ በጥላቻ ንግግሩ ምክንያት በግለሰብ ወይም በቡድን ላይ ጥቃት የተፈጸመ እንደሆነ ቅጣቱ ከአንድ አመት እስከ አምስት አመት የሚደርስ ቀላል እስራት ነዉ፡፡(አንቀጽ 7(2) በሌላ በኩል ደግሞ በአንቀጹ ንሁስ አንቀጽ 4 መሰረት ወንጀሉ የተፈጸመው ከአምስት ሺ በላይ ተከታይ ባለው የማህበራዊ ሚዲያ ገጽ ከሆነ ወይም በብሮድካስት አገልግሎት ወይም በየጊዜው በሚወጣ የህትመት ውጤት ከሆነ ቅጣቱ እስከ ሶስት አመት የሚደርስ ቀላል እስራት እና ከብር 100,000 ያልበለጠ መቀጮ ይሆናል፡፡
ከጥላቻ ንግግር በተጨማሪ አዋጁ ሃሰተኛ የሆነ መረጃ ማሰራጨትንም በወንጀልንት የከለከለ ሲሆን ሀሰት የሆነና የመረጃውን ሀሰተኝነት በሚያውቅ ወይም መረጃውን የሚያሰራጨው ሰው ካለበት አጠቃላይ ሁኔታ አንጻር የመረጃውን እዉነተኝነት ለማጣራት በቂ ጥረት ሳይደረግ የሚሰራጭ ሁከት ወይም ግጭት የሚያነሳሳ ወይም ጥቃት እንዲደርስ የሚያደርግ እድሉ ከፍ ያለ የሀሰት ንግግር ነው በሚል ትረጉም ተሰጥቶታል፡፡ በአንቀጽ 5 እና 7(3) መሰረት የሐሰት መረጃን በአደባባይ ስብሰባዎች በብሮድካስት፣ በህትመት ወይም በማህበራዊ ሚዲያዎች ወይም በሌላ ተመሳሳይ ዘዴዎች አማካኝነት በጽሁፍ፣ በምስል፣ በድምጽ ወይም በቪዲዮ ማሰራጨት የተከለከለና ይህን ተግባር የፈጸመ ሰዉ እስከ አንድ አመት በሚደርስ በቀላል እስራት ወይም ከብር 50,000 ባልበለጠ መቀጮ ይቀጣል፡፡ ወንጀሉ የተፈጸመው ከአምስት ሺ በላይ ተከታይ ባለው የማህበራዊ ሚዲያ ገጽ ከሆነ ወይም በብሮድካስት አገልግሎት ወይም በየጊዜው በሚወጣ የህትመት ውጤት ከሆነ ቅጣቱ እስከ ሶስት አመት የሚደርስ ቀላል እስራት እና ከብር 100,000 ያልበለጠ መቀጮ ይሆናል፡፡(አንቀጽ 7(4) በሌላ ሁኔታ ሐሰተኛ መረጃ በመሰራጨቱ ምክንያት በግለሰብ ወይም በቡድን ላይ ጥቃት የተፈጸመ ከሆነ፣ ሁከት ወይም ግጭት የተከሰተ እንደሆነ ቅጣቱ ከሁለት እስከ አምስት አመት በሚደርስ ቀላል እስራት የሚሆን ሲሆን ምንም ጉዳት ካልደረሰ ጥፋተኛውን ለማረም የተሻለ ነው ብሎ ሲያምን ፍርድ ቤት በእስራት ምትክ የግዴታ የማህበረሰብ አገልግሎት ስራን በአማራጭ ቅጣትነት ሊወስን ይችላል።(አንቀጽ 7(5)(6))
ከለይ የተቀመጡት ተጠያቂነቶች እንዳለሆነዉ በአዋጁ አንቀጽ 6 ስር ንግግሩ የሌላ ሰዉ ሆኖ ለትምህርታዊ ወይም ሳይንሳዊ ጥናት አካል ለማድረግ፤ንግግሩን በተመለከተ የዜና ዘገባ ወይም ትንታኔ ለመስራት ወይም የፖለቲካ ትችት ለመስጠት፤የኪነጥበብ ፣ ትወና ወይም መሰል የስነጥበብ ውጤት በማድረግ ህብረተሰብን ለማስተማር፤ ወይም የሃይማኖት አስተምህሮት አካል እንደሆነ እንዲሁም ንግግሩን ያሰራጨው ወይም ያደረገው ሰው የመረጃውን እውነተኛነት ለማረጋገጥ በሱ ሁኔታ ካለ ሰው የሚጠበቀውን ምክንያታዊ ጥረት ያደረገ እንደሆነ እንደ ጥላቻ ንግግር ወይም የሃሰት መረጃ ስርጭት የማይወሰድ ስለመሆኑ በልዩ ሁኔታ ተደንግጓል፡፡
3. በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚፈጠሩ ችግሮችን ለመቅረፍ ምን መደረግ አለበት
በመሆኑም ህብረተሰቡ የጥላቻ ንግግርና ሃሰተኛ መረጃን ማሰራጨት በወንጀል የሚያስጠይቅ መሆኑን ከመረዳት ባለፈ ተግባሩ እጅግ በጣም አስነዋሪና ለሀገር መፈራረስ ምክንያት መሆኑን በመገንዘብ ሃሰብን በነጻነት የመግልጽ መብቱን በአግባቡ መጠቀም አለበት፡፡
በመንግስት በኩልም ለነዚህ የጥላቻ ንግግሮች እንዲሁም ሃሰተኛ መረጃ ስርጭቶች ምክንያት የሆኑትን በህብረተሰቡ መካከል ለተፈጠሩት ቁርሾዎች እና አለመግባባቶች ብሄራዊ መግባበቶችንና እርቆች እንዲፈጸሙ ሁኔታዎችን ማመቻቸት እንዲሁም ህጉን በሚጥሱ ግለሰቦች ላይም ተገቢዉን እርምጃ መዉሰድ አስፈላጊ ነዉ፡፡ ከዚህም ባለፈ ለማህበረሰቡ በተለይም ለወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል በጉዳዩ ላይ ሰፊ የሆነ የ
ወራሹ ወይም የኑዛዜ ባለስጦታው ለሌላው እንዲያስተላልፍ ስለመታዘዝ
@@@@@@@@@@@@@@@@@@@
https://t.me/lawsocieties
በአንድ ኑዛዜ ላይ ተናዛዡ በውርስ ወይም በስጦታ የተሰጠውን ሐብት ወይም ከዚሁ ወስጥ የተወሰነውን ክፍል ወራሹ ወይም የኑዛዜ ባለስጦታው ለሌለ ሰው እንዲያስተላልፍ ሊያዝ ይችላል፡፡ ይህ ግን መቼና በምን ሁንታ መፈፀም እንዳለበት ተናዛዡ በግልጽ መጥቀስ አለት (ፍ/ብ/ሕ/ቁ 929)፡፡ ሀብቱን በመጀመሪያ የሚቀበል ወራሽ ወይም የኑዛዜ ስጦታ ተቀባይ የሆነ ሰው ባለግዴታ ይባላል፡፡ የምትክነቱ ሥራ በሚፈፀምበት ጊዜ ከወራሽ ወይም ከኑዛዜ ስጦታ ከተደገለት ሰው ላይ ንብረቱን የሚያኘው ሰው ዋና ወራሽ ይባላል፡፡
ዋናው ወራሹ ተናዡ በሞተበት ጊዜ ውርሱን ወይም ስጦታውን የመቀበል ችሎታ ይኑረው አይኑረው አስፈላጊ አይደለም፡፡ ነገር ግን ውርሱን ወይም ስጦታውን ተተክቶ በሚረከብበት ጊዜ የመቀበል ችሎታ ያለው መሆን አለበት፡፡ ባለ ግዴታው በኑዛዜ ቃል እንዲያስተላልፍ የተሰጠው ኃብት ወይም ንብረቱን በኑዛዜው ላይ የተጠቀሰው ሁኔታ ሲያጋጥም፣ የመተላለፊያው ጊዜ ሲደርስ ወይ በኑዛዜው የተጠሰው ሁኔታ ሲፈፀም የሚያስተላልፈው በመሆኑ ሊሸጠው ለሌላ 3ኛወገን ሊያስተላልፈው ወይም በእዳ ሊያስይዘው እንዳማይችል በፍ/ብ/ሐ/ቁ 931 ላይ ተገልጿል፡፡ ዳኞች ፍታሀዊ ሆነው ሲያገኙት አንድን ንብረት እንዲሸጥ፣ እንዲተላለፍ የማዘዝ ሥልጣን አላቸው፡፡ ነግር ግን ወራሹ ወይም የኑዛዜ ባለስጦታው ለሌላ ሰው እንዲያስተላልፍ የታዘዘውን የማይንቀሳቀስ ንብረት ዳኞች ከላይ በተሰጠው ሁኔታ እንዲሸጥ፣ እንዲለወጥ ወይም ለሌላ ሰው እንዳያስተላልፍ ማዘዘ እንደማይችል በፍ/ብ/ሐ/ቁ 932 ላይ ተገልጿል፡፡ ይህ የሆነበት ምክንያቱ ንብረቱ የዋና ወራሹ ስለሆነ ነው፡፡ ይህ ንብረት መብት ተጥሶ ከተገኘ በሕገ ወጥ መንገድ የተወሰደው ንብረት እንዲመለስ ጥያቄ ማቅረብ አለበት፡፡ ዋናው ተጠቃሚ ወይም ወኪሉ ወይም ተናዛዡ የመተካቱን ሥርዓት ለማስፈፀም የመረጠው ሰው በማይገባ የተደረገ መሸጥ፣ መለወጥ ወይም መያዝ እንዲፈርስ በማንኛውም ጊዜ ለመጠየቅ ይችላል፡፡ የመተካቱ ሥርዓት ከተደረገ በኋላ በሚከተለው ሁለት አመት ውስጥ ክሳቸውን ማቅረብ ይችላሉ (በፍ/ብ/ሐ/ቁ 933)፡፡
ባለግዴታው ስጦታውን ለመቀበል ካልቻለ ወይም ፈቃደኛ ካልሆነ ምንም መደረግ እንዳለበት ተናዛዡ በኑዛዜው ላይ ካልገለፀ በስተቀር የኑዛዜ ስጦታ የሚደርሰው ሰው ወዲያውኑ እንዲቀበል እንደሚደረግ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 935 ላይ ተገልጿል፡፡ ይህም ማለት ዋና ወራሹ እንዲወስድ ይደረጋል፡፡ በዋና ወራሸነት መብት ያለው ሰው ቢሞትና የሚተኩትም ሰዎች ባይኖሩ ባለግዴታው ባደራ መልክ በያዘው መብትና ንብረት ያለምንም ገደቡ ሊጠቀም ይችላል፡፡ የሚተካው ሰው ባለመቅረብ ወይም እምቢ ማለት ወይም በማንኛውም ሌላ ምክንኛት በተናዛዡ ፈቃድ ካልተፈፀመ የተሰጡትን ንብረቶች ለዋናው ወራሽ ወራሾች ይተላለፋሉ፡፡ ተቃራኒ ቃል ከሌላ በቀር የተናዛዡ ወራሾች ለዋናው ወራሽ የተሰጡ ንብረቶች ላይ አንድም መብት አይኖራቸውም ሲል የፍ/ብ/ለ/ቁ 936 ይገልፃል፡፡
ከፀጋዬ ደመቀ ሎየር ፌስቡክ ገፅ ተገኘ
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
@@@@@@@@@@@@@@@@@@@
https://t.me/lawsocieties
በአንድ ኑዛዜ ላይ ተናዛዡ በውርስ ወይም በስጦታ የተሰጠውን ሐብት ወይም ከዚሁ ወስጥ የተወሰነውን ክፍል ወራሹ ወይም የኑዛዜ ባለስጦታው ለሌለ ሰው እንዲያስተላልፍ ሊያዝ ይችላል፡፡ ይህ ግን መቼና በምን ሁንታ መፈፀም እንዳለበት ተናዛዡ በግልጽ መጥቀስ አለት (ፍ/ብ/ሕ/ቁ 929)፡፡ ሀብቱን በመጀመሪያ የሚቀበል ወራሽ ወይም የኑዛዜ ስጦታ ተቀባይ የሆነ ሰው ባለግዴታ ይባላል፡፡ የምትክነቱ ሥራ በሚፈፀምበት ጊዜ ከወራሽ ወይም ከኑዛዜ ስጦታ ከተደገለት ሰው ላይ ንብረቱን የሚያኘው ሰው ዋና ወራሽ ይባላል፡፡
ዋናው ወራሹ ተናዡ በሞተበት ጊዜ ውርሱን ወይም ስጦታውን የመቀበል ችሎታ ይኑረው አይኑረው አስፈላጊ አይደለም፡፡ ነገር ግን ውርሱን ወይም ስጦታውን ተተክቶ በሚረከብበት ጊዜ የመቀበል ችሎታ ያለው መሆን አለበት፡፡ ባለ ግዴታው በኑዛዜ ቃል እንዲያስተላልፍ የተሰጠው ኃብት ወይም ንብረቱን በኑዛዜው ላይ የተጠቀሰው ሁኔታ ሲያጋጥም፣ የመተላለፊያው ጊዜ ሲደርስ ወይ በኑዛዜው የተጠሰው ሁኔታ ሲፈፀም የሚያስተላልፈው በመሆኑ ሊሸጠው ለሌላ 3ኛወገን ሊያስተላልፈው ወይም በእዳ ሊያስይዘው እንዳማይችል በፍ/ብ/ሐ/ቁ 931 ላይ ተገልጿል፡፡ ዳኞች ፍታሀዊ ሆነው ሲያገኙት አንድን ንብረት እንዲሸጥ፣ እንዲተላለፍ የማዘዝ ሥልጣን አላቸው፡፡ ነግር ግን ወራሹ ወይም የኑዛዜ ባለስጦታው ለሌላ ሰው እንዲያስተላልፍ የታዘዘውን የማይንቀሳቀስ ንብረት ዳኞች ከላይ በተሰጠው ሁኔታ እንዲሸጥ፣ እንዲለወጥ ወይም ለሌላ ሰው እንዳያስተላልፍ ማዘዘ እንደማይችል በፍ/ብ/ሐ/ቁ 932 ላይ ተገልጿል፡፡ ይህ የሆነበት ምክንያቱ ንብረቱ የዋና ወራሹ ስለሆነ ነው፡፡ ይህ ንብረት መብት ተጥሶ ከተገኘ በሕገ ወጥ መንገድ የተወሰደው ንብረት እንዲመለስ ጥያቄ ማቅረብ አለበት፡፡ ዋናው ተጠቃሚ ወይም ወኪሉ ወይም ተናዛዡ የመተካቱን ሥርዓት ለማስፈፀም የመረጠው ሰው በማይገባ የተደረገ መሸጥ፣ መለወጥ ወይም መያዝ እንዲፈርስ በማንኛውም ጊዜ ለመጠየቅ ይችላል፡፡ የመተካቱ ሥርዓት ከተደረገ በኋላ በሚከተለው ሁለት አመት ውስጥ ክሳቸውን ማቅረብ ይችላሉ (በፍ/ብ/ሐ/ቁ 933)፡፡
ባለግዴታው ስጦታውን ለመቀበል ካልቻለ ወይም ፈቃደኛ ካልሆነ ምንም መደረግ እንዳለበት ተናዛዡ በኑዛዜው ላይ ካልገለፀ በስተቀር የኑዛዜ ስጦታ የሚደርሰው ሰው ወዲያውኑ እንዲቀበል እንደሚደረግ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 935 ላይ ተገልጿል፡፡ ይህም ማለት ዋና ወራሹ እንዲወስድ ይደረጋል፡፡ በዋና ወራሸነት መብት ያለው ሰው ቢሞትና የሚተኩትም ሰዎች ባይኖሩ ባለግዴታው ባደራ መልክ በያዘው መብትና ንብረት ያለምንም ገደቡ ሊጠቀም ይችላል፡፡ የሚተካው ሰው ባለመቅረብ ወይም እምቢ ማለት ወይም በማንኛውም ሌላ ምክንኛት በተናዛዡ ፈቃድ ካልተፈፀመ የተሰጡትን ንብረቶች ለዋናው ወራሽ ወራሾች ይተላለፋሉ፡፡ ተቃራኒ ቃል ከሌላ በቀር የተናዛዡ ወራሾች ለዋናው ወራሽ የተሰጡ ንብረቶች ላይ አንድም መብት አይኖራቸውም ሲል የፍ/ብ/ለ/ቁ 936 ይገልፃል፡፡
ከፀጋዬ ደመቀ ሎየር ፌስቡክ ገፅ ተገኘ
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ከ አስር ሺህ አምስት መቶ #(10,500+) በላይ ተከታይ ያለው ፌስቡክ ፔጃችንን ይቀላቀሉን‼️‼️‼️‼️‼️
https://www.facebook.com/lawsocieties/
#join and #share to all #Ethiopian societies‼️‼️‼️‼️
https://www.facebook.com/lawsocieties/
#join and #share to all #Ethiopian societies‼️‼️‼️‼️
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
Forwarded from Entrust Consult 📗ኢንትረስት
የፌስቡክ አካውንትዎን ደህንነት ለመጠበቅ ሊወሰዱ የሚገቡ የጥንቃቄ እርምጃዎች
INSA
1. የይለፍ-ቃልዎን ደህንነት ማረጋገጥ
#_የፌስቡክ አካውንቶን ለሌላ ማንኛውም የኦንላይን አገልግሎት ላይ አይጠቀሙ፤
#_ የይለፍ-ቃልዎን በፍፁም ለሌላ ሰው አያጋሩ፤
#_የሚጠቀሙበት የይለፍ-ቃል ለመገመት አዳጋች የሆነ፣ በፍጹም የእርሶን ስም እና የተለመዱ ቃላትን ያልያዘ ሊሆን ይገባል፤
#_የይለፍ-ቃልዎ ፣ኢ-ሜይልዎን፣ የስልክ ቁጥሮን ወይም የልደት ቀንዎን በፍፁም የሚጠቀም መሆን የለበትም፤
2. የሚያስሱትን ድረ-ገጽ መረጃ በፍጹም አያጋሩ
#_አጥቂዎች ፌስቡክ የሚመስል የሐሰት ገጽ ፈጥረው በኢ-ሜይል አድራሻዎና በይለፍ ቃልዎ እንዲገቡ ሊጠይቁዎ ይችላሉ፤
#_ሁልጊዜም መረጃ የሚያስሱበትን ድረ-ገጽ URL ትክክለኝነት ያረጋግጡ፤
አጠራጣሪ ነገር ሲያጋጥሞ www.facebook.com በማፈላለጊያው ላይ በመጻፍ ወደ ትክክለኛው የፌስቡክ ገጽ ለመመለስ ይሞክሩ፤
#_ ከሜታ /Meta/ ወይም ፌስቡክ የሚላክሎትን ኢ-ሜይል በፍጹም ለሌላ ሰው አያጋሩ፣ በተለይም ስለ አካውንቶ ምስጢራዊ መረጃዎችን የያዙ ከሆነ፤
#_ስለፊሺንግ ጥቃት እና ጠንካራ የይለፍ-ቃል አጠባበቅ ላይ ያለዎትን እውቀትና ግንዛቤ በየጊዜው ያሳድጉ፤
3. ኮምፒውተርዎን ለሌላ ሰው የሚያጋሩ ከሆነ የፌስቡክ አካውንቶን ዘግተው መውጣትዎን /Log Out/ ማድረግዎን አይዘንጉ፤
#_ኮምፒውተርዎን ዘግተው ሳይወጡ ወይም መሣሪያዎን ያዋሱ ከሆነም ከርቀት እንዴት መውጣት /Log Out Remotely/ እንደሚችሉ ይወቁ፤
#_ከርቀት ሆነው ለሌላ አካል ካዋሱት ኮምፒውተር ላይ ለመውጣት(log out) ለማድረግ ወደ ፌስቡክ "Security and Login Setting" ሲገቡ ከዚህ በፊት ይገቡባቸው የነበሩ መሣሪያዎችን ዝርዝር የሚያቀርብልዎ ሲሆን ከዚህ ውስጥ የሚፈልጉት መሣሪያ ላይ "Logout" የሚለውን ትዕዛዝ በመጫን መውጣት ይችላሉ፤
4. ከማያውቋቸው ሰዎች የጓደኝነት ጥያቄ ሲላክልዎ አይቀበሉ
#_ጠላፊዎች ሰዎችን ለማጥመድ ሲፈልጉ ሀሰተኛ አካውንት ሊፈጥሩ ይችላሉ፤
#_የጠላፊዎች ጓደኛ መሆን ምን አልባት የእርሶን የፌስቡክ የፊት ገጽን /Timeline/ ሊበክሉ፣ የተለያዩ ጉዳዮችን በገጾ ላይ ሊያጋሩ ወይም በካይ መልዕክቶችን በመልዕክት መቀበያዎ ሊልኩብዎ ይችላሉ፤
5. ከበካይ ሶፍትዌሮች እራሶን ይጠብቁ
#_አጥፊ ሶፍትዌሮች ኮምፒውተሮች፣ ሰርቨሮች /Server/ ወይም የኮምፒውተር ኔትወርክ ላይ ጉዳት ሊጥሉ ይችላሉ፤
#_የተበከለ ኮምፒውተር ወይም መሣሪያ ምን ዓይነት ባህሪያት እንደሚያሳዩ እና እነዚህን በካይ ሶፍትዌሮችን እንዴት ማስወገድ እንደሚችሉ በሚመለከት ያለዎትን እውቀት ያዳብሩ፤
#_ማፈላለጊያዎትን በየጊዜው ያዘምኑ፣ አጠራጣሪ መተግበሪያዎችን እና የማፈላለጊያ ማስታወቂያዎችን ያስወግዱ፤
6. አጠራጣሪ ማስፈንጠሪያዎችን /Links/ ከሚያውቁት ጓደኛ ወይም ድርጅት እንኳ ቢላክልዎ ከመክፈት ይቆጠቡ
#_እነዚህ በፌስቡክ ወይም በኢ-ሜይል የሚላኩ ማስፈንጠሪያዎች /Links/ ሊሆኑ ይችላሉ፤
#_ፌስቡክ ወይም Meta የይለፍ-ቃሎን በኢ-ሜይል እንዲያስገቡ በፍጹም እንደማይጠይቅዎ ይወቁ፤
#_አጠራጣሪ ማስፈንጠሪያ ሲያጋጥሞ ለፌስቡክ ሪፖርት /report it/ ያድረጉ፤
7. ተጨማሪ የደህንነት መጠበቂያ መንገዶችን ይተግብሩ
#_ከማይታወቁ አድራሻዎችና መሣሪያዎች ወደ አካውንትዎ የመግባት ሙከራ ሲደረግ የጥቆማ መረጃ እንዲደርሶ /get alerts about unrecognized logins/ ያድረጉ፤
#_ባለሁለት ደረጃ የማንነት ማረጋገጫ ዘዴ /Set up two-factor authentication/ ይጠቀሙ፤
#_ሌሎች የደህንነት ጉዳዮችን በተመለከተ የፌስቡክ Help & Support ላይ በመግባት ያለዎትን ግንዛቤ በየጊዜው ያሳድጉ፤
https://t.me/GudayAsfetsami
#Share
Muktarovich O.
1. የይለፍ-ቃልዎን ደህንነት ማረጋገጥ
#_የፌስቡክ አካውንቶን ለሌላ ማንኛውም የኦንላይን አገልግሎት ላይ አይጠቀሙ፤
#_ የይለፍ-ቃልዎን በፍፁም ለሌላ ሰው አያጋሩ፤
#_የሚጠቀሙበት የይለፍ-ቃል ለመገመት አዳጋች የሆነ፣ በፍጹም የእርሶን ስም እና የተለመዱ ቃላትን ያልያዘ ሊሆን ይገባል፤
#_የይለፍ-ቃልዎ ፣ኢ-ሜይልዎን፣ የስልክ ቁጥሮን ወይም የልደት ቀንዎን በፍፁም የሚጠቀም መሆን የለበትም፤
2. የሚያስሱትን ድረ-ገጽ መረጃ በፍጹም አያጋሩ
#_አጥቂዎች ፌስቡክ የሚመስል የሐሰት ገጽ ፈጥረው በኢ-ሜይል አድራሻዎና በይለፍ ቃልዎ እንዲገቡ ሊጠይቁዎ ይችላሉ፤
#_ሁልጊዜም መረጃ የሚያስሱበትን ድረ-ገጽ URL ትክክለኝነት ያረጋግጡ፤
አጠራጣሪ ነገር ሲያጋጥሞ www.facebook.com በማፈላለጊያው ላይ በመጻፍ ወደ ትክክለኛው የፌስቡክ ገጽ ለመመለስ ይሞክሩ፤
#_ ከሜታ /Meta/ ወይም ፌስቡክ የሚላክሎትን ኢ-ሜይል በፍጹም ለሌላ ሰው አያጋሩ፣ በተለይም ስለ አካውንቶ ምስጢራዊ መረጃዎችን የያዙ ከሆነ፤
#_ስለፊሺንግ ጥቃት እና ጠንካራ የይለፍ-ቃል አጠባበቅ ላይ ያለዎትን እውቀትና ግንዛቤ በየጊዜው ያሳድጉ፤
3. ኮምፒውተርዎን ለሌላ ሰው የሚያጋሩ ከሆነ የፌስቡክ አካውንቶን ዘግተው መውጣትዎን /Log Out/ ማድረግዎን አይዘንጉ፤
#_ኮምፒውተርዎን ዘግተው ሳይወጡ ወይም መሣሪያዎን ያዋሱ ከሆነም ከርቀት እንዴት መውጣት /Log Out Remotely/ እንደሚችሉ ይወቁ፤
#_ከርቀት ሆነው ለሌላ አካል ካዋሱት ኮምፒውተር ላይ ለመውጣት(log out) ለማድረግ ወደ ፌስቡክ "Security and Login Setting" ሲገቡ ከዚህ በፊት ይገቡባቸው የነበሩ መሣሪያዎችን ዝርዝር የሚያቀርብልዎ ሲሆን ከዚህ ውስጥ የሚፈልጉት መሣሪያ ላይ "Logout" የሚለውን ትዕዛዝ በመጫን መውጣት ይችላሉ፤
4. ከማያውቋቸው ሰዎች የጓደኝነት ጥያቄ ሲላክልዎ አይቀበሉ
#_ጠላፊዎች ሰዎችን ለማጥመድ ሲፈልጉ ሀሰተኛ አካውንት ሊፈጥሩ ይችላሉ፤
#_የጠላፊዎች ጓደኛ መሆን ምን አልባት የእርሶን የፌስቡክ የፊት ገጽን /Timeline/ ሊበክሉ፣ የተለያዩ ጉዳዮችን በገጾ ላይ ሊያጋሩ ወይም በካይ መልዕክቶችን በመልዕክት መቀበያዎ ሊልኩብዎ ይችላሉ፤
5. ከበካይ ሶፍትዌሮች እራሶን ይጠብቁ
#_አጥፊ ሶፍትዌሮች ኮምፒውተሮች፣ ሰርቨሮች /Server/ ወይም የኮምፒውተር ኔትወርክ ላይ ጉዳት ሊጥሉ ይችላሉ፤
#_የተበከለ ኮምፒውተር ወይም መሣሪያ ምን ዓይነት ባህሪያት እንደሚያሳዩ እና እነዚህን በካይ ሶፍትዌሮችን እንዴት ማስወገድ እንደሚችሉ በሚመለከት ያለዎትን እውቀት ያዳብሩ፤
#_ማፈላለጊያዎትን በየጊዜው ያዘምኑ፣ አጠራጣሪ መተግበሪያዎችን እና የማፈላለጊያ ማስታወቂያዎችን ያስወግዱ፤
6. አጠራጣሪ ማስፈንጠሪያዎችን /Links/ ከሚያውቁት ጓደኛ ወይም ድርጅት እንኳ ቢላክልዎ ከመክፈት ይቆጠቡ
#_እነዚህ በፌስቡክ ወይም በኢ-ሜይል የሚላኩ ማስፈንጠሪያዎች /Links/ ሊሆኑ ይችላሉ፤
#_ፌስቡክ ወይም Meta የይለፍ-ቃሎን በኢ-ሜይል እንዲያስገቡ በፍጹም እንደማይጠይቅዎ ይወቁ፤
#_አጠራጣሪ ማስፈንጠሪያ ሲያጋጥሞ ለፌስቡክ ሪፖርት /report it/ ያድረጉ፤
7. ተጨማሪ የደህንነት መጠበቂያ መንገዶችን ይተግብሩ
#_ከማይታወቁ አድራሻዎችና መሣሪያዎች ወደ አካውንትዎ የመግባት ሙከራ ሲደረግ የጥቆማ መረጃ እንዲደርሶ /get alerts about unrecognized logins/ ያድረጉ፤
#_ባለሁለት ደረጃ የማንነት ማረጋገጫ ዘዴ /Set up two-factor authentication/ ይጠቀሙ፤
#_ሌሎች የደህንነት ጉዳዮችን በተመለከተ የፌስቡክ Help & Support ላይ በመግባት ያለዎትን ግንዛቤ በየጊዜው ያሳድጉ፤
https://t.me/GudayAsfetsami
#
Muktarovich O.
የፊልም ቲያትሮች ፊልም ከመጀመሩ በፊት ማስታወቂያዎችን ይሰራሉ ። አስተዋዋቂዎች በፍላጎት እና በእድሜ መሰረት ተመልካቾችን በማነጣጠር ገበያውን መመርመር እና ማስታወቂያዎችን መጫወት ይችላሉ ። የፊልም ማስታወቂያዎች ዝቅተኛ ድግግሞሽ ሊኖራቸው ይችላል ። ነገር ግን ቲያትሮች ውድ በመሆናቸው ሰዎች ወደ ቲያትር ቤት ለመሄድ ብዙ ፍላጎት የላቸውም ።
የበይነመረብ ሚዲያ
የበይነመረብ ሚዲያ የዲጂታል ሚዲያ ወይም አዲስ ሚዲያ በመባልም ይታወቃል ።
ተጠቃሚዎቹ ንቁ ሆነው እንዲቆዩ እና መረጃን የሚያመርቱበት ማራኪ የሁለት መንገድ ግንኙነት ነው ። በመስመር ላይ የሚቀርበው እና የሚተላለፈው የቪዲዮ ወይም የድምጽ ይዘት በኢንተርኔት ሚዲያ ይመጣል ። ግራፊክስ፣ ቃላት እና ምስሎች የበይነመረብ ሚዲያ ውስጥ ሊካተቱ ይችላሉ።
በይነመረቡ የምንፈልገውን የዜና አይነቶች እንድናይ ያስችለናል ። ይህም ከባህላዊ ሚዲያ የበለጠ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል ። ከኤሌክትሮኒካዊ መልእክቶች እስከ የሞባይል መልእክት እንዲሀም የመስመር ላይ ጆርናሎች ሁሉም የበይነመረብ ሚዲያ ቻናሎች ወሳኝ ናቸው።
የኢንተርኔት ሚዲያ ዓይነቶች ኢሜይሎች ፣ ሶሻል ሚዲያ፣ ፖድካስቶች/Multimedia files /፣ የመስመር ላይ መድረኮች ፣ የብሎግ ድር ጣቢያዎች የተከፋፈሉ ማስታወቂያዎች ወዘተ ናቸው ።
ኢሜይሎች እንደ ኢንተርኔት ሚዲያ
ኢሜይሎች ኩባንያዎች በፍጥነት እና በቀላሉ ደንበኞቻቸውን እንዲያገኙ ያግዛሉ ። አንድ ሰው የደንበኛን ኢሜይል አድራሻ በተደጋጋሚ በሽያጭ ስለሚያቀርቡት መፈለግ ስለማያስፈልገው ትንሽ ጥናት ብቻ ይጠይቃሉ ።
በሌላ በኩል ሰዎች ፖስታዎችን ለመክፈት ወይም ላለመክፈት እድሉ አላቸው ። ስለዚህ ጥቂቶቹ የማስታወቂያ ጣቢያውን ከፍተው ሊጎበኙ ይችላሉ ። ብዙዎቹ ጣቢያውን ማየት ይቅርና ደብዳቤ መክፈት እንኳን ላይመርጡ ይችላሉ።
ማህበራዊ ሚዲያ እንደ ኢንተርኔት ሚዲያ
ማህበራዊ ሚዲያ ወይም የማህበራዊ ትስስር ገፆች የሚባሉት ኢንስታግራም፣ ፌስቡክ፣ ትዊተር፣ ዩቲዩብ ፣ ወዘተ ናቸው ። በአለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች ይህን አይነት ሚዲያ በብዛት ይጠቀማሉ።
ስለዚህ የማህበራዊ ሚዲያ ለኩባንያዎች ምርቶቻቸው ታዋቂ እና ረጅም ዕድሜ ስላለው ምርቶቻቸውን ለገበያ ለማቅረብ አስፈላጊው የትስስር መስመር ይሆናል ። የማህበራዊ ሚዲያ ዓላማ መስተጋብርን እና ግንኙነትን መፍጠር ነው ። ስለዚህ ማስታወቂያዎቹ በጣም በይነተገናኝ ሊሆኑ ስለሚችሉ የተጠቃሚዎችን ተሳትፎ እድል ይጨምራሉ ።
ኩባንያዎች ከደንበኞች ጋር በቀጥታ መገናኘት ይችላሉ ። ከፍተኛ መጠን ያለው መረጃ አለው ። ይህም ደንበኞችን የማወቅ ግምገማ እና አፈፃፀም ይጨምራላቸዋል ።
አስተዋዋቂዎች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ያለውን አፈጻጸም ለመከታተል፣ ለመዘገብ ወይም ለመቆጣጠር በቀላሉ የተለያዩ ፕሮግራሞችን መጠቀም ይችላሉ ። ቢሆንም ጥልቅ የተጠቃሚ ጥናት ከተካሄደ ይህ ሚዲያ ውድ ሊሆን ይችላል።
ማህበራዊ ሚዲያ ክፍት በሆነ ክፍል ውስጥ አስተያየቶችን የመፃፍ ባህሪ አለው ። ይህም አሉታዊ ልጥፎችን እና አስተያየቶችን የመፍጠር እድልን ይጨምራል ።
4. ከቤት ውጭ ሚዲያ
ከቤት ውጭ ሚዲያ የውጭ ሚዲያ በመባልም ይታወቃል ። በጣም ታዋቂ ከሆኑ የመገናኛ ብዙሃን ዓይነቶች መካከል አንዱ ነው ። የቤት ውስጥ ሚዲያ ከቤት ውጭ በሚሆኑበት ጊዜ ዜናውን ወይም መረጃን ለህዝብ በማድረስ ላይ ያተኩራል ።
ከቤት ውጭ ሚዲያ በተሽከርካሪዎች ላይ ፣ በጎዳናዎች እና በመሳሰሉት ማስታወቂያዎች በኩል የሚስተዋውቁ ሲሆን ይህም ደንበኞቹን አዲስ የምርት አይነት መምጣት ጋር ያስተዋውቃል ። ከቤት ውጭ ሚዲያ ብዙሃኑ ለማህበራዊ ጉዳይ ወይም ለህብረተሰቡ እድገት አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ለማበረታታት ይረዳሉ ። ይህ ሚዲያ ከሕዝብ ደኅንነት እና በአጠቃላይ የንግድ ማስታወቂያዎች ጋር ለተያያዙ ማስታወቂያዎች በጣም ጥቅም ላይ ይውላል።
ከቤት ውጭ ሚዲያ እንደ ፖስተሮች፣ ቢልቦርዶች፣ የብሮሹሮች ስርጭት፣ ወዘተ የመሳሰሉ ዓይነቶች አሉት ።
በተመሳሳይ መንገድ የሚሄዱ ሰዎች ማስታወቂያዎቹን በመደበኛነት ስለሚያዩ ከፍተኛ ድግግሞሽ ይሰጣል ። ነገር ግን መልዕክቱን ወይም መረጃውን በየቀኑ ካጋጠማቸው ገለልተኞች ስለሚሆኑ የህዝቡን ስሜት ማጣትንም ያስከትላል።
ቢልቦርዶች እንደ ከቤት ዉጭ ሚዲያ
ቢልቦርዶች በአጠገባቸው የሚያልፉትን ሰዎች ስለሚስቡ ለአንድ ምርት ወይም ዓላማ ማስታወቂያ ቀላል ያደርጉታል።
ቢልቦርዶች በኮምፒውተሮች እገዛ የተፈጠሩ ትልልቅ ማስታወቂያዎች ናቸው ። በጎዳናዎች ፣በከተማ የእግረኛ መንገዶች ፣በመዝናኛ ማእከሎችወዘተ ላይ ሊተከሉ ይችላሉ ።
የመጓጓዣ ጣቢያ ማስታወቂያዎች እንደ ከከቤት ውጭ ሚዲያ
የትራንዚት ሚዲያ በህዝብ ቦታዎች ሲጓዙ ወይም በመጓጓዣ ላይ ሲሆኑ መረጃን ለሰዎች በማስተዋወቅ እና በማድረስ ላይ ያተኩራሉ ። በተሽከርካሪዎች እና በሌሎች የመጓጓዣ መንገዶች ላይ ማስታወቂያዎችን ያሳያል።
የትራንዚት ሚዲያ ዓላማው “ወደ ቤት መልእክት የመንዳት” ዓላማ አለው ። በዚህም በሚሊዮን የሚቆጠሩ በጎዳናዎች ላይ የሚንከራተቱ ወይም በዓለም ዙሪያ የሚጓዙ ሰዎችን ይስባል። ባህላዊ የማስታወቂያ ዘዴ ሊመስል ይችላል፣ ግን እስከ ዛሬ ድረስ ውጤታማ የማስታወቂያ ዘዴ ነው።
ማስታወቂያዎች በዋናነት በአውቶብሶች ወይም የምድር ውስጥ ባቡር መኪኖች እና ሰዎች ከህዝብ የመጓጓዣ መንገዶች በሚገቡበት ወይም በሚወጡባቸው ጣቢያዎች ላይ ይታያሉ ።
እንደ ትራንዚት መጠለያ ማስታወቂያ ፣ የታክሲ ማስታወቂያ ፣ የአውቶቡስ ማስታወቂያ እና የባቡር ማስታወቂያ አራት አይነት የመሸጋገሪያ ማስታወቂያዎች አሉ ።
@ የፌዴራል የፍትሕና ሕግ ኢንስቲትዩት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር
#Share
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
የበይነመረብ ሚዲያ
የበይነመረብ ሚዲያ የዲጂታል ሚዲያ ወይም አዲስ ሚዲያ በመባልም ይታወቃል ።
ተጠቃሚዎቹ ንቁ ሆነው እንዲቆዩ እና መረጃን የሚያመርቱበት ማራኪ የሁለት መንገድ ግንኙነት ነው ። በመስመር ላይ የሚቀርበው እና የሚተላለፈው የቪዲዮ ወይም የድምጽ ይዘት በኢንተርኔት ሚዲያ ይመጣል ። ግራፊክስ፣ ቃላት እና ምስሎች የበይነመረብ ሚዲያ ውስጥ ሊካተቱ ይችላሉ።
በይነመረቡ የምንፈልገውን የዜና አይነቶች እንድናይ ያስችለናል ። ይህም ከባህላዊ ሚዲያ የበለጠ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል ። ከኤሌክትሮኒካዊ መልእክቶች እስከ የሞባይል መልእክት እንዲሀም የመስመር ላይ ጆርናሎች ሁሉም የበይነመረብ ሚዲያ ቻናሎች ወሳኝ ናቸው።
የኢንተርኔት ሚዲያ ዓይነቶች ኢሜይሎች ፣ ሶሻል ሚዲያ፣ ፖድካስቶች/Multimedia files /፣ የመስመር ላይ መድረኮች ፣ የብሎግ ድር ጣቢያዎች የተከፋፈሉ ማስታወቂያዎች ወዘተ ናቸው ።
ኢሜይሎች እንደ ኢንተርኔት ሚዲያ
ኢሜይሎች ኩባንያዎች በፍጥነት እና በቀላሉ ደንበኞቻቸውን እንዲያገኙ ያግዛሉ ። አንድ ሰው የደንበኛን ኢሜይል አድራሻ በተደጋጋሚ በሽያጭ ስለሚያቀርቡት መፈለግ ስለማያስፈልገው ትንሽ ጥናት ብቻ ይጠይቃሉ ።
በሌላ በኩል ሰዎች ፖስታዎችን ለመክፈት ወይም ላለመክፈት እድሉ አላቸው ። ስለዚህ ጥቂቶቹ የማስታወቂያ ጣቢያውን ከፍተው ሊጎበኙ ይችላሉ ። ብዙዎቹ ጣቢያውን ማየት ይቅርና ደብዳቤ መክፈት እንኳን ላይመርጡ ይችላሉ።
ማህበራዊ ሚዲያ እንደ ኢንተርኔት ሚዲያ
ማህበራዊ ሚዲያ ወይም የማህበራዊ ትስስር ገፆች የሚባሉት ኢንስታግራም፣ ፌስቡክ፣ ትዊተር፣ ዩቲዩብ ፣ ወዘተ ናቸው ። በአለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች ይህን አይነት ሚዲያ በብዛት ይጠቀማሉ።
ስለዚህ የማህበራዊ ሚዲያ ለኩባንያዎች ምርቶቻቸው ታዋቂ እና ረጅም ዕድሜ ስላለው ምርቶቻቸውን ለገበያ ለማቅረብ አስፈላጊው የትስስር መስመር ይሆናል ። የማህበራዊ ሚዲያ ዓላማ መስተጋብርን እና ግንኙነትን መፍጠር ነው ። ስለዚህ ማስታወቂያዎቹ በጣም በይነተገናኝ ሊሆኑ ስለሚችሉ የተጠቃሚዎችን ተሳትፎ እድል ይጨምራሉ ።
ኩባንያዎች ከደንበኞች ጋር በቀጥታ መገናኘት ይችላሉ ። ከፍተኛ መጠን ያለው መረጃ አለው ። ይህም ደንበኞችን የማወቅ ግምገማ እና አፈፃፀም ይጨምራላቸዋል ።
አስተዋዋቂዎች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ያለውን አፈጻጸም ለመከታተል፣ ለመዘገብ ወይም ለመቆጣጠር በቀላሉ የተለያዩ ፕሮግራሞችን መጠቀም ይችላሉ ። ቢሆንም ጥልቅ የተጠቃሚ ጥናት ከተካሄደ ይህ ሚዲያ ውድ ሊሆን ይችላል።
ማህበራዊ ሚዲያ ክፍት በሆነ ክፍል ውስጥ አስተያየቶችን የመፃፍ ባህሪ አለው ። ይህም አሉታዊ ልጥፎችን እና አስተያየቶችን የመፍጠር እድልን ይጨምራል ።
4. ከቤት ውጭ ሚዲያ
ከቤት ውጭ ሚዲያ የውጭ ሚዲያ በመባልም ይታወቃል ። በጣም ታዋቂ ከሆኑ የመገናኛ ብዙሃን ዓይነቶች መካከል አንዱ ነው ። የቤት ውስጥ ሚዲያ ከቤት ውጭ በሚሆኑበት ጊዜ ዜናውን ወይም መረጃን ለህዝብ በማድረስ ላይ ያተኩራል ።
ከቤት ውጭ ሚዲያ በተሽከርካሪዎች ላይ ፣ በጎዳናዎች እና በመሳሰሉት ማስታወቂያዎች በኩል የሚስተዋውቁ ሲሆን ይህም ደንበኞቹን አዲስ የምርት አይነት መምጣት ጋር ያስተዋውቃል ። ከቤት ውጭ ሚዲያ ብዙሃኑ ለማህበራዊ ጉዳይ ወይም ለህብረተሰቡ እድገት አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ለማበረታታት ይረዳሉ ። ይህ ሚዲያ ከሕዝብ ደኅንነት እና በአጠቃላይ የንግድ ማስታወቂያዎች ጋር ለተያያዙ ማስታወቂያዎች በጣም ጥቅም ላይ ይውላል።
ከቤት ውጭ ሚዲያ እንደ ፖስተሮች፣ ቢልቦርዶች፣ የብሮሹሮች ስርጭት፣ ወዘተ የመሳሰሉ ዓይነቶች አሉት ።
በተመሳሳይ መንገድ የሚሄዱ ሰዎች ማስታወቂያዎቹን በመደበኛነት ስለሚያዩ ከፍተኛ ድግግሞሽ ይሰጣል ። ነገር ግን መልዕክቱን ወይም መረጃውን በየቀኑ ካጋጠማቸው ገለልተኞች ስለሚሆኑ የህዝቡን ስሜት ማጣትንም ያስከትላል።
ቢልቦርዶች እንደ ከቤት ዉጭ ሚዲያ
ቢልቦርዶች በአጠገባቸው የሚያልፉትን ሰዎች ስለሚስቡ ለአንድ ምርት ወይም ዓላማ ማስታወቂያ ቀላል ያደርጉታል።
ቢልቦርዶች በኮምፒውተሮች እገዛ የተፈጠሩ ትልልቅ ማስታወቂያዎች ናቸው ። በጎዳናዎች ፣በከተማ የእግረኛ መንገዶች ፣በመዝናኛ ማእከሎችወዘተ ላይ ሊተከሉ ይችላሉ ።
የመጓጓዣ ጣቢያ ማስታወቂያዎች እንደ ከከቤት ውጭ ሚዲያ
የትራንዚት ሚዲያ በህዝብ ቦታዎች ሲጓዙ ወይም በመጓጓዣ ላይ ሲሆኑ መረጃን ለሰዎች በማስተዋወቅ እና በማድረስ ላይ ያተኩራሉ ። በተሽከርካሪዎች እና በሌሎች የመጓጓዣ መንገዶች ላይ ማስታወቂያዎችን ያሳያል።
የትራንዚት ሚዲያ ዓላማው “ወደ ቤት መልእክት የመንዳት” ዓላማ አለው ። በዚህም በሚሊዮን የሚቆጠሩ በጎዳናዎች ላይ የሚንከራተቱ ወይም በዓለም ዙሪያ የሚጓዙ ሰዎችን ይስባል። ባህላዊ የማስታወቂያ ዘዴ ሊመስል ይችላል፣ ግን እስከ ዛሬ ድረስ ውጤታማ የማስታወቂያ ዘዴ ነው።
ማስታወቂያዎች በዋናነት በአውቶብሶች ወይም የምድር ውስጥ ባቡር መኪኖች እና ሰዎች ከህዝብ የመጓጓዣ መንገዶች በሚገቡበት ወይም በሚወጡባቸው ጣቢያዎች ላይ ይታያሉ ።
እንደ ትራንዚት መጠለያ ማስታወቂያ ፣ የታክሲ ማስታወቂያ ፣ የአውቶቡስ ማስታወቂያ እና የባቡር ማስታወቂያ አራት አይነት የመሸጋገሪያ ማስታወቂያዎች አሉ ።
@ የፌዴራል የፍትሕና ሕግ ኢንስቲትዩት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር
#Share
https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
የፌደራል ፍርድ ቤቶች ድጋፍ ፍጪ ሰራተኞች የምሳ እቃ❓
በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ የሚሰራ አንድ ድጋፍ ሰጪ ሰራተኛ በየጊዜው የምሳ ሰዓት ሲደርስ ስራውን አጠናቆ ለምሳ ሲወጣ እጁን በኪሱ ውስጥ ከቶ ከጊቢው ወጥቶ ሲሄድ እመለከታለው።
አንድ ቀን በተመሳሳይ ከጊቢ ወጥቶ የስራ ሰዓት ሲደርስ ሲመለስ አገኘሁትና ጠጋ ብዬ ጠየኩት።
ሁል ጊዜ ስመለከትህ ምሳ ሰዓት ከጊቢ ትወጣለህ ውጪ ነው ወይስ ቤትህ ሄደህ ነው ምሳ የምትበላው? በማለት ጠየኩት
''አይ አንቺ ''ብሎ ፈገግ አለ
የምሬን እኮ ነው አልኩት መልስ እየጠበኩ
''ዝም ብዬ ዞር ዞር ብዬ ነው የምመለሰው ያው ለሰዓት ማዳረሻ '' አለኝ
አልገባኝም አልኩት በድጋሚ
''አይ ታሪክዬ'' አለ በሀዘን ስሜት እየተዋጠ
ቀጠል አደረገና ''1700 ብር ነው የወር ደሞዜ ከዝች ደሞዜ ላይ የቆርቆሮ ቤት 1400 ብር ተከራይቼ ነው የምኖረው ታድያ በምሳ እቃ ምኑን ልቋጥር ፣ ከየትስ አምጥቼ ምግብ ቤት እገባለሁ ብለሽ ነው ያው ሰዓት እስኪደርስ ልደታ ቤተክርስቲያንን ተሳልሜ ትንሽ ቁጭ ብዬ ምሳ ተመግቦ እንደመጣ ሰው ዞር ዞር ብዬ ነው የምመለሰው'' አለኝ
'',በቀን አንዴ ማታ ላይ ትንሽ ከተመገብን አይበዛብንም ብለሽ ነው ''
አለ በቀልድ መልክ እንዳልከፋው ለማስመሰል ፈገግ እያለ
ወዲያው ውስጤ በሀዘን ተሞላ ምነው ባልጠየኩት ብዬ እራሴን ወቀስኩኝ
በዚህ መልኩ በተመሳሳይ ህይወት ውስጥ በፍርድ ቤቱ በድጋፍ ሰጪ ዘርፍ ላይ በሚከፈላቸው አነስተኛ ደሞዝ ህይወታቸውን እየገፉ ያሉ በርካቶች ናቸው።
በዚህ ኑሮና በዚህ ደሞዝ ቤተሰብ የሚመሩ ህጻናት ልጆች ያሏቸውም ይገኛሉ።
የጠ /ሚ አብይ አህመድ ወደ ስልጣን መምጣትን ተከትሎ ለፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት በኃላፊነት ተሹመው የነበሩት የቀድሞ የጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊና ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ሰለሞን አረዳ የድጋፍ ሰጪ ሰራተኞችን ችግር ተረድተው '' የደሞዛችንን ያስተካክሉልን ይሆናል ''ብለው ተስፋ ያደረጉ ሰራተኞች በርካቶች ነበር።
ይሁንና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞችን ደሞዝ በሚመለከት ምንም ማስተካከያ ሳይደረግ ሁለቱም ፕሬዝዳንቶች በገዛ ፍቃዳቸው ስራቸውን መልቀቃቸው ተሰማ።
ከዛ በኋላ ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የህግ ትምህርት ረዳት ፕሮፌሰር ነበሩ የተባሉት የቀድሞ ጠበቃ አቶ ቴዎድሮስ ምህረት እና ፣በዳኝነት ዘርፍ ላይ ለበርካታ ጊዜያት አገልግለዋል የተባሉት ወይዘሮ አበባ እምቢ አለ እንደ ቅደም ተከተላቸው ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙ።
በጥር 15 ቀን 2015 ከቀድሞዎቹ ፕሬዝዳንቶች የስራ ኃላፊነት ርክክብ አድርገው ስራቸውን ጀመሩ ከዚህ በኋላ ደግሞ በድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች ዘንድ ሌላ ተስፋ ተጫረ
ሰኔ 15 ቀን 2015 ዓ/ ም ደግሞ ሌላኛው የፍርድቤቶች ሰራተኞችን ተስፋ የሰነቀ ፌሽታን የፈጠረ
የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 25ኛ መደበኛ ጉባዔው ላይ የፌደራል ፍርድ ቤቶች የሰራተኞች አስተዳደር ደንብ መፅደቁ ተሰማ ፣
ይህ ከተሰማ አሁን አምስት ወራት ተቆጠረ
ይሁንና ደንቡ ተግባራዊ ሆኖ ጠብ የሚል ነገር ይኖራል በሚል ተስፋ በተለመደው በኑሮ ጫና ውስጥ ሆነው የህይወታቸውን ውጣ ውረድ የሚገፉት ሰራተኞች ተግባራዊነቱን በተመናመነ ተስፋ እየተጠባበቁ ይገኛሉ።
ተስፋ የቆረጡት ደግሞ ስራቸውን እየለቀቁ የተሻለ እንጀራ ፍለጋ ላይ ተሰማርተዋል።
''ያም መጣ ይህ ለራሱ እንጂ ለኔ የሚያስብ የሚጠቅም የለም '' በማለት ፊታቸውን ወደ ፈጣሪ ያዞሩና ከነገ ዛሬ ይሻል ይሆን ብለው ፈጣሪያቸውን ተስፋ ያደረጉም አሉ።
ለማንኛውም የተቋማት መሪዎች በቤታችሁ ወይም በሆቴል ስትመገቡ፣ስትዝናኑ፣ውስኪም ስታፈሱ ፣በዝቅተኛ ደሞዝ የሚሰቃዩ ሰራተኞችን አስታውሱ እላለሁ።
በኔ በኩል አበቃሁ
Via #TarikAdugna
Tarik Adugna
በታረክ አዱኛ ፌስቡክ ገፅ ላይ ተገኘ
ሰላም ለሀገራችን ህዝብ ይሁን
ይድረስ #አለ_ህግ #Ale_Hig አባላት እና ደጋፊዎች ፣
ሼር በማድረግ ድጋፋችሁን አሳዩ።
ሼር ለወዳጅ ዘመድ ጓደኛ።
👆👆👆👆🙏🙏🙏🙏🙏
@Lawsocieties #አለ_ህግ
#Lawsocieties @Alehig
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
Facebook Page
https://www.facebook.com/lawsocieties/
Telegram Channel
https://t.me/lawsocieties
👇👇👇👇👇👇👇
👉Facebook Page 👈
👆👆👆👆👆👆👆
👇👇👇👇👇👇👇👇
👉Telegram Channel 👈
👆👆👆👆👆👆👆👆
በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ የሚሰራ አንድ ድጋፍ ሰጪ ሰራተኛ በየጊዜው የምሳ ሰዓት ሲደርስ ስራውን አጠናቆ ለምሳ ሲወጣ እጁን በኪሱ ውስጥ ከቶ ከጊቢው ወጥቶ ሲሄድ እመለከታለው።
አንድ ቀን በተመሳሳይ ከጊቢ ወጥቶ የስራ ሰዓት ሲደርስ ሲመለስ አገኘሁትና ጠጋ ብዬ ጠየኩት።
ሁል ጊዜ ስመለከትህ ምሳ ሰዓት ከጊቢ ትወጣለህ ውጪ ነው ወይስ ቤትህ ሄደህ ነው ምሳ የምትበላው? በማለት ጠየኩት
''አይ አንቺ ''ብሎ ፈገግ አለ
የምሬን እኮ ነው አልኩት መልስ እየጠበኩ
''ዝም ብዬ ዞር ዞር ብዬ ነው የምመለሰው ያው ለሰዓት ማዳረሻ '' አለኝ
አልገባኝም አልኩት በድጋሚ
''አይ ታሪክዬ'' አለ በሀዘን ስሜት እየተዋጠ
ቀጠል አደረገና ''1700 ብር ነው የወር ደሞዜ ከዝች ደሞዜ ላይ የቆርቆሮ ቤት 1400 ብር ተከራይቼ ነው የምኖረው ታድያ በምሳ እቃ ምኑን ልቋጥር ፣ ከየትስ አምጥቼ ምግብ ቤት እገባለሁ ብለሽ ነው ያው ሰዓት እስኪደርስ ልደታ ቤተክርስቲያንን ተሳልሜ ትንሽ ቁጭ ብዬ ምሳ ተመግቦ እንደመጣ ሰው ዞር ዞር ብዬ ነው የምመለሰው'' አለኝ
'',በቀን አንዴ ማታ ላይ ትንሽ ከተመገብን አይበዛብንም ብለሽ ነው ''
አለ በቀልድ መልክ እንዳልከፋው ለማስመሰል ፈገግ እያለ
ወዲያው ውስጤ በሀዘን ተሞላ ምነው ባልጠየኩት ብዬ እራሴን ወቀስኩኝ
በዚህ መልኩ በተመሳሳይ ህይወት ውስጥ በፍርድ ቤቱ በድጋፍ ሰጪ ዘርፍ ላይ በሚከፈላቸው አነስተኛ ደሞዝ ህይወታቸውን እየገፉ ያሉ በርካቶች ናቸው።
በዚህ ኑሮና በዚህ ደሞዝ ቤተሰብ የሚመሩ ህጻናት ልጆች ያሏቸውም ይገኛሉ።
የጠ /ሚ አብይ አህመድ ወደ ስልጣን መምጣትን ተከትሎ ለፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት በኃላፊነት ተሹመው የነበሩት የቀድሞ የጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊና ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ሰለሞን አረዳ የድጋፍ ሰጪ ሰራተኞችን ችግር ተረድተው '' የደሞዛችንን ያስተካክሉልን ይሆናል ''ብለው ተስፋ ያደረጉ ሰራተኞች በርካቶች ነበር።
ይሁንና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞችን ደሞዝ በሚመለከት ምንም ማስተካከያ ሳይደረግ ሁለቱም ፕሬዝዳንቶች በገዛ ፍቃዳቸው ስራቸውን መልቀቃቸው ተሰማ።
ከዛ በኋላ ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የህግ ትምህርት ረዳት ፕሮፌሰር ነበሩ የተባሉት የቀድሞ ጠበቃ አቶ ቴዎድሮስ ምህረት እና ፣በዳኝነት ዘርፍ ላይ ለበርካታ ጊዜያት አገልግለዋል የተባሉት ወይዘሮ አበባ እምቢ አለ እንደ ቅደም ተከተላቸው ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙ።
በጥር 15 ቀን 2015 ከቀድሞዎቹ ፕሬዝዳንቶች የስራ ኃላፊነት ርክክብ አድርገው ስራቸውን ጀመሩ ከዚህ በኋላ ደግሞ በድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች ዘንድ ሌላ ተስፋ ተጫረ
ሰኔ 15 ቀን 2015 ዓ/ ም ደግሞ ሌላኛው የፍርድቤቶች ሰራተኞችን ተስፋ የሰነቀ ፌሽታን የፈጠረ
የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 25ኛ መደበኛ ጉባዔው ላይ የፌደራል ፍርድ ቤቶች የሰራተኞች አስተዳደር ደንብ መፅደቁ ተሰማ ፣
ይህ ከተሰማ አሁን አምስት ወራት ተቆጠረ
ይሁንና ደንቡ ተግባራዊ ሆኖ ጠብ የሚል ነገር ይኖራል በሚል ተስፋ በተለመደው በኑሮ ጫና ውስጥ ሆነው የህይወታቸውን ውጣ ውረድ የሚገፉት ሰራተኞች ተግባራዊነቱን በተመናመነ ተስፋ እየተጠባበቁ ይገኛሉ።
ተስፋ የቆረጡት ደግሞ ስራቸውን እየለቀቁ የተሻለ እንጀራ ፍለጋ ላይ ተሰማርተዋል።
''ያም መጣ ይህ ለራሱ እንጂ ለኔ የሚያስብ የሚጠቅም የለም '' በማለት ፊታቸውን ወደ ፈጣሪ ያዞሩና ከነገ ዛሬ ይሻል ይሆን ብለው ፈጣሪያቸውን ተስፋ ያደረጉም አሉ።
ለማንኛውም የተቋማት መሪዎች በቤታችሁ ወይም በሆቴል ስትመገቡ፣ስትዝናኑ፣ውስኪም ስታፈሱ ፣በዝቅተኛ ደሞዝ የሚሰቃዩ ሰራተኞችን አስታውሱ እላለሁ።
በኔ በኩል አበቃሁ
Via #TarikAdugna
Tarik Adugna
በታረክ አዱኛ ፌስቡክ ገፅ ላይ ተገኘ
ሰላም ለሀገራችን ህዝብ ይሁን
ይድረስ #አለ_ህግ #Ale_Hig አባላት እና ደጋፊዎች ፣
ሼር በማድረግ ድጋፋችሁን አሳዩ።
ሼር ለወዳጅ ዘመድ ጓደኛ።
👆👆👆👆🙏🙏🙏🙏🙏
@Lawsocieties #አለ_ህግ
#Lawsocieties @Alehig
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
Facebook Page
https://www.facebook.com/lawsocieties/
Telegram Channel
https://t.me/lawsocieties
👇👇👇👇👇👇👇
👉Facebook Page 👈
👆👆👆👆👆👆👆
👇👇👇👇👇👇👇👇
👉Telegram Channel 👈
👆👆👆👆👆👆👆👆
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
EFAA BYLAW FINAL PDF.pdf
480.3 KB
ረቂቅ የመተዳደሪያ ደንብ
*******
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር በቅርቡ ለሚያካሂደው ጉባኤ ዝግጅቶችን እያደረገ ያለ መሆኑ ይታወቃል::
በዚሁ ጉባኤ ላይ ከሚቀርቡ ሰነዶች አንዱና ዋነኛው የማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ ነው:: በመሆኑም መላው የማህበሩ አባላት ይህ ሰነድ የማህበሩን ህጋዊ አቋም ፤ የአመራር አደረጃጀት እና አስራር የሚወስን ወሳኝ ሰነድ መሆኑን በመገንዘብ በአግባብ በማንበብ እና ሀሳባቸውን በማደራጀት መስጠት እንደሚገባቸው ታምኖበታል::
በመሆኑም የማህበሩ አባላት መተዳደሪያ ደንቡ የተሻለ እና ማህበሩን የሚያጠናክር ሆኖ እንዲወጣ የበኩላቸውን እንዲወጡ ማህበሩ ጥሪውን ያቀርባል::
መረጃውን #share #like በማድረግ እንድታጋሩልን እንጠይቃለን::
መረጃዎች በፍጥነት እንዲደርሷችሁ ይፋዊ ገፃችንን በሚከተለው መስፈንጠሪያ ይቀላቀሉ::
ፌስቡክ- https://www.facebook.com/ethiopianbarassociation?mibextid=9R9pXO
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
ሚያዝያ 18 ቀን 2016ዓ.ም
አዲስ አበባ፤
*******
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር በቅርቡ ለሚያካሂደው ጉባኤ ዝግጅቶችን እያደረገ ያለ መሆኑ ይታወቃል::
በዚሁ ጉባኤ ላይ ከሚቀርቡ ሰነዶች አንዱና ዋነኛው የማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ ነው:: በመሆኑም መላው የማህበሩ አባላት ይህ ሰነድ የማህበሩን ህጋዊ አቋም ፤ የአመራር አደረጃጀት እና አስራር የሚወስን ወሳኝ ሰነድ መሆኑን በመገንዘብ በአግባብ በማንበብ እና ሀሳባቸውን በማደራጀት መስጠት እንደሚገባቸው ታምኖበታል::
በመሆኑም የማህበሩ አባላት መተዳደሪያ ደንቡ የተሻለ እና ማህበሩን የሚያጠናክር ሆኖ እንዲወጣ የበኩላቸውን እንዲወጡ ማህበሩ ጥሪውን ያቀርባል::
መረጃውን #share #like በማድረግ እንድታጋሩልን እንጠይቃለን::
መረጃዎች በፍጥነት እንዲደርሷችሁ ይፋዊ ገፃችንን በሚከተለው መስፈንጠሪያ ይቀላቀሉ::
ፌስቡክ- https://www.facebook.com/ethiopianbarassociation?mibextid=9R9pXO
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
ሚያዝያ 18 ቀን 2016ዓ.ም
አዲስ አበባ፤