አደገኛ ወንጀል ነው!
አለም አቀፉ የጉምሩክ ድርጅት /WCO/ ኮንትሮባንድን እንደሚከተለው ይተረጉመዋል፡፡ ኮንትሮባንድ ማለት ማንኛውም በህግ የተከለከለ አሰራር ሲሆን እነርሱም፡- ከማምረት /production/፣ ከማጓጓዝ /shipment/፣ ከመቀበል /receipt/፣ ባለቤት ከመሆን /possession/፣ ከማከፋፈል /distribution/፣ ከመግዛትና መሸጥ እንዲሁም ማንኛውም ለዚህ አሰራር ሁኔታዎችን ማመቻቸትን /facilitation/ ያካትታል፡፡
የኢትዮጵያ ጉምሩክ አዋጅ ኮንትሮባንድን <<ህጎችንና በህግ መሰረት የወጡ መመሪያዎችን በመተላለፍ ወደ ጉምሩክ ክልል ዕቃዎችን ማስገባት፣ በህጋዊ መንገድ የወጡትን በህገ ወጥ መንገድ መልሶ ማስገባት፣ መያዝ፣ ማከማቸት፣ ማዘዋወር፣ ማስተላለፍ፣ እንዲገቡ ወይም እንዲወጡ ለማድረግ መሞከር፣ እንዲሁም እነዚህ ዕቃዎችን መግዛትን፣ መሸጥንና ለዚህ ድርጊት ተባባሪ መሆንን ያጠቃልላል፡፡; በማለት ተርጉሞታል።
1. የኮንትሮባንድ ወንጀል በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ብቻ ሳይሆን የህዝብን ጤንነት፣ የሀገርን ሰላምና ፀጥታ የሚያውኩ ዕቃዎችን በማስገባት አገራዊ ደህንነትን አደጋ ላይ የሚጥል አደገኛ ወንጀል ነው፡፡
2. ከኢኮኖሚ አንፃር የኮንትሮባንድ ወንጀል ህጋዊ ነጋዴውንና አምራቹን አዳክሞ ከገበያ በማስወጣት ምርታመነትንና ህጋዊ ንግድን ያቀጭጫል፤ ህጋዊ የንግድ ውድድርን ያዳክማል፤ የመንግስትን የገቢ ምንጭ ያደርቃል፡፡
አማራጭ የሕግ እውቀት
👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/
👉 LinkedIn 👈
https://www.linkedin.com/company/lawsocieties/
👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Ale_Hig
አለም አቀፉ የጉምሩክ ድርጅት /WCO/ ኮንትሮባንድን እንደሚከተለው ይተረጉመዋል፡፡ ኮንትሮባንድ ማለት ማንኛውም በህግ የተከለከለ አሰራር ሲሆን እነርሱም፡- ከማምረት /production/፣ ከማጓጓዝ /shipment/፣ ከመቀበል /receipt/፣ ባለቤት ከመሆን /possession/፣ ከማከፋፈል /distribution/፣ ከመግዛትና መሸጥ እንዲሁም ማንኛውም ለዚህ አሰራር ሁኔታዎችን ማመቻቸትን /facilitation/ ያካትታል፡፡
የኢትዮጵያ ጉምሩክ አዋጅ ኮንትሮባንድን <<ህጎችንና በህግ መሰረት የወጡ መመሪያዎችን በመተላለፍ ወደ ጉምሩክ ክልል ዕቃዎችን ማስገባት፣ በህጋዊ መንገድ የወጡትን በህገ ወጥ መንገድ መልሶ ማስገባት፣ መያዝ፣ ማከማቸት፣ ማዘዋወር፣ ማስተላለፍ፣ እንዲገቡ ወይም እንዲወጡ ለማድረግ መሞከር፣ እንዲሁም እነዚህ ዕቃዎችን መግዛትን፣ መሸጥንና ለዚህ ድርጊት ተባባሪ መሆንን ያጠቃልላል፡፡; በማለት ተርጉሞታል።
1. የኮንትሮባንድ ወንጀል በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ብቻ ሳይሆን የህዝብን ጤንነት፣ የሀገርን ሰላምና ፀጥታ የሚያውኩ ዕቃዎችን በማስገባት አገራዊ ደህንነትን አደጋ ላይ የሚጥል አደገኛ ወንጀል ነው፡፡
2. ከኢኮኖሚ አንፃር የኮንትሮባንድ ወንጀል ህጋዊ ነጋዴውንና አምራቹን አዳክሞ ከገበያ በማስወጣት ምርታመነትንና ህጋዊ ንግድን ያቀጭጫል፤ ህጋዊ የንግድ ውድድርን ያዳክማል፤ የመንግስትን የገቢ ምንጭ ያደርቃል፡፡
አማራጭ የሕግ እውቀት
👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/
👉 LinkedIn 👈
https://www.linkedin.com/company/lawsocieties/
👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Ale_Hig
#ሪልስቴት
ያልተገነባ ቤት / ግንባታ ከማከናወናቸው በፊት ቤት የሚሸጡ ሪል ስቴት አልሚዎች የሚሰበስቡትን ገንዘብ በዝግ አካውንት እንዲያስቀምጡ ሊገደዱ ነው ፤ በተጨማሪ ግንባታው 80 በመቶ ላይ ያልደረሰን ቤት ለደንበኞች እንዳያስተላልፉ ሊከለከሉ ነው።
ይህንም የሚመለከት ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ ቀርቧል።
አዲሱ ረቂቅ አዋጅ ምን ይላል ?
ቤት ለመገንባት የመሬት የይዞታ ማረጋገጫ እና የግንባታ ፈቃድ ያላገኙ የሪል ስቴት አልሚዎች ደንበኞችን #እንዳይመዘግቡ እና #ቅድመ_ክፍያ እንዳይሰበስቡ ይከለክላል።
በአሁኑ ጊዜ ባለው አሠራር መሠረት የንግድ ፈቃድ በማውጣት ብቻ ወደ ሪል ስቴት ገበያው ሲቀላቀሉ የነበሩት አልሚዎች፤ በአዲሱ ረቂቅ አዋጅ " የብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ " የማውጣት ግዴታ ተጥሎባቸዋል። የአገር ውስጥም ሆነ የውጭ ባለሀብት ሪል ስቴት አልሚዎች ይህንን ፈቃድ ለማግኘት ቢያንስ 50 ቤቶችን ገንብተው የሚያስከረክቡ መሆን አለባቸው።
የአገር ውስጥ እና የውጭ አልሚዎች ግንባታውን ለማከናወን የሚያስፈልገውን " የፋይናንስ አቅርቦት ምንጭ " የማቅረብ ቅድመ ሁኔታ ተቀምጦባቸዋል። ይሁንና ረቂቁ፤ " የቅድሚያ ቤት ሽያጭ ተጠቃሚነት " መብትን ከቅድመ ሁኔታ ጋር ለአገር ውስጥ ባለሀብቶች ሰጥቷል።
ይህ አሠራር የሪል ስቴት አልሚዎች የቤት ግንባታውን ሳያከናውኑ ወይም በሂደት ላይ እያለ ለግንባታው የሚውልን ፋይናንስ የሚያሰባስቡበት እና ገንዘቡብ ለግንባታው የሚያውሉበት መንገድ ነው።
የቤት ግንባታው ሳይከናወን በፊት ከገዢዎች ጋር ውል ማሰር እና ክፍያ መፈጸም ኢትዮጵያ ውስጥ በሪል ስቴት ልማት ላይ በተሰማሩ አልሚዎች በኩል የተለመደ አሰራር ነው።
አዲሱ ረቂቅ አዋጅ፤ በዚህ ዓይነት መልኩ ለግንባታ የሚውለውን ሀብት ማሰባሰብ የሚፈልጉ አልሚዎች " አግባብ ካለዉ አካል ፈቃድ ማቅረብ " ይጠበቅባቸዋል። ይህም ግዴታ ነው።
የቅድመ ሽያጭ ዘዴን መጠቀም የሚፈልጉት ሪል ስቴት አልሚዎች፤ ከቤት ገዢዎች የሚሰበስቡት ገንዘብ የሚቀመጥበት የባንክ ሂሳብ እና የገንዘብ አወጣጥ ላይም አስገዳጅ አሠራር በረቂቅ አዋጁ ተጥሎባቸዋል።
አልሚዎቹ ከቤት ገዢዎች የሚሰበስቡትን ገንዘብ " የዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ ማደረግ ወይም ማስያዝ " እንዳለባቸው ረቂቅ ሕጉ ላይ ሰፍሯል።
አዲሱ ሕግ፤ ገንዘቡ የሚቀመጥበት ዝግ የባንክ አካውንት የሚከፈተው " አግባብ ባለው አካል ፈቃድ መሠረት " እንደሆነም ያስረዳል።
በዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ የተደረገው ገንዘብ የሚለቀቅበት ሁኔታ ከረቂቅ አዋጁ መፅደቅ በኋላ በሚወጣ ደንብ ይወሠናል።
ከዚህም ባሻገር በቅድሚያ የተሸጠው ቤት ተገንብቶ ለተጠቃሚዎች እስከሚተላለፍ ድረስ የቤት የመሥሪያ ቦታው የይዞታ ማስረጃ " በሚመለከተው አካል እንዳይሸጥ፣ እንዳይለወጥ " እንደሚታገድ ረቂቁ ይገልጻል።
ቤት ቀድመው በሚሸጡ ሪል ስቴት አልሚዎች ላይ እነዚህ አስገዳጅ አሠራሮች የተቀመጡት " ደንበኞች የሚደርስባቸውን እንግልት እና ኪሳራ ለመቀነስ በማሰብ " እንደሆነ የአዋጁ ማብራሪያ ያስረዳል።
ረቂቅ አዋጁ በሪል ስቴት አልሚዎች ላይ ሌሎችንም ግዴታዎች ጥሏል።
በረቂቁ መሠረት፤ የሪል ስቴት አልሚዎች ግንባታው 80 በመቶ ላይ ያልደረሰን ቤት ለደንበኞች እንዳያስተላልፉ ተከልክለዋል።
" ያለደንበኛው ፍላጎት እና ፈቃድ አጠቃላይ ግንባታው ቢያንስ 80 በመቶ ያልተጠናቀቀ ቤት ለደንበኞች ሊያስተላልፍ አይችልም " ይህንን ለማድረግ በቅድሚያ ደንበኛው መስማማት እንዳለበት ያመለክታል።
ሪል ስቴት አልሚዎች ቤት ገዢዎችን መመመዝገብ እና ቅድመ ክፍያ መሰብሰብ የሚችሉበት ጊዜም ቅድመ ሁኔታ ተቀምጦበታል።
አልሚዎች ምዝገባ ማድረግ እና ክፍያ መሰብሰብ የሚችሉት " የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ እና የግንባታ ፈቃድ ከሚመለከተው አካል ከተረከቡ " በኋላ ነው።
" በሕጋዊ መንገድ የተረከበው መሬት ሊያስተናግድ ከሚችለዉ የቤት ደንበኛ በላይ መመዝገብ አይችልም " የሚለውም ሪል ስቴት አልሚዎች ላይ ከተቀመጡት ግዴታዎች መካከል ነው።
ለሪል ስቴት ልማት አሠራር የሚዘረጋው አዲሱ አዋጅ፤ ከግዴታዎች ባሻገር አልሚዎች ከመንግሥት " መሬት በስፋት " ማግኘት የሚችሉበትን ሂደትም ያስቀመጠ ነው።
ከመንግሥት መሬት " በስፋት " የሚቀርብላቸው አልሚዎች ረቂቁ ላይ ከተጠቀሱ ሦስት ቅድመ ሁኔታዎች ውስጥ ቢያንስ አንዱን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
ከእነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች መካከል በብዛት ቤቶችን መገንባት እና ከእነዚህ ቤቶች ውስጥ " 40 በመቶውን ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ላላቸው የማኅበረሰብ ክፍል ተደራሽ " ማድረግ የሚለው አንዱ ነው።
ይህንን ቅድመ ሁኔታ የሚከተሉ አልሚዎች የሚገነቡበት ቤት ብዛት " እንደ ከተሞች ደረጃ በአንድ ጊዜ ከ500 እስከ 5 ሺህ " ሊሆን እንደሚችል በረቂቁ ላይ ተጠቅሷል።
መንግሥት በአዲስ አበባ ከተማ መሬት " በስፋት " የሚያቀርበው " በአዲስ አበባ ከ5 ሺ በላይ ቤት ለሚገነባ እና ለሚያስተላልፍ " አልሚ እንደሆነ ረቂቁ ላይ ሰፍሯል።
በሌሎች ከተሞች መሬት " በስፋት " የሚቀርበው እደሚኖራቸው " ተጨባጭ የቤት ፍላጎት " ሲሆን፣ " ኢንዱስትሪ ፓርክ ያለበት አካባቢ ባሉ ከተሞች " ደግሞ ከአንድ ሺህ በላይ ቤቶችን ለሚገነቡ አልሚዎች እንደሚቀርብላቸው ረቂቁ ያስረዳል።
ከመንግሥት መሬት " በስፋት " ማግኘት የሚፈልጉ አልሚዎች የተቀመጠባቸው ሌሎች ቅድመ ሁኔታዎች ከውጭ ምንዛሬ ጋር የተገናኙ ናቸው።
በአገር ውስጥ " በጥራት እና በብዛት የማይገኙ " ግብአቶችን በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ (ፍራንኮ ቫሉታ) የሚያስገቡ እንዲሁም የሚያገኙትን ትርፍ እስከ አስር ዓመት ከአገር ሳያወጡ አገር ውስጥ መልሰው የሚጠቀሙ አልሚዎች የዚህ አሠራር ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ረቂቁ ላይ ሰፍሯል።
" የሪል ስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይት እና ግመታ " የተሰኘው ይህ ረቂቅ አዋጅ የቀረበለት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለተጨማሪ ዕይታ ወደ ከተማ፣ መሠረተ ልማት እና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምፅ መርቶታል።
መረጃው ከቢቢሲ አማርኛ የተወሰደ ነው።
@tikvahethiopia
ያልተገነባ ቤት / ግንባታ ከማከናወናቸው በፊት ቤት የሚሸጡ ሪል ስቴት አልሚዎች የሚሰበስቡትን ገንዘብ በዝግ አካውንት እንዲያስቀምጡ ሊገደዱ ነው ፤ በተጨማሪ ግንባታው 80 በመቶ ላይ ያልደረሰን ቤት ለደንበኞች እንዳያስተላልፉ ሊከለከሉ ነው።
ይህንም የሚመለከት ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ ቀርቧል።
አዲሱ ረቂቅ አዋጅ ምን ይላል ?
ቤት ለመገንባት የመሬት የይዞታ ማረጋገጫ እና የግንባታ ፈቃድ ያላገኙ የሪል ስቴት አልሚዎች ደንበኞችን #እንዳይመዘግቡ እና #ቅድመ_ክፍያ እንዳይሰበስቡ ይከለክላል።
በአሁኑ ጊዜ ባለው አሠራር መሠረት የንግድ ፈቃድ በማውጣት ብቻ ወደ ሪል ስቴት ገበያው ሲቀላቀሉ የነበሩት አልሚዎች፤ በአዲሱ ረቂቅ አዋጅ " የብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ " የማውጣት ግዴታ ተጥሎባቸዋል። የአገር ውስጥም ሆነ የውጭ ባለሀብት ሪል ስቴት አልሚዎች ይህንን ፈቃድ ለማግኘት ቢያንስ 50 ቤቶችን ገንብተው የሚያስከረክቡ መሆን አለባቸው።
የአገር ውስጥ እና የውጭ አልሚዎች ግንባታውን ለማከናወን የሚያስፈልገውን " የፋይናንስ አቅርቦት ምንጭ " የማቅረብ ቅድመ ሁኔታ ተቀምጦባቸዋል። ይሁንና ረቂቁ፤ " የቅድሚያ ቤት ሽያጭ ተጠቃሚነት " መብትን ከቅድመ ሁኔታ ጋር ለአገር ውስጥ ባለሀብቶች ሰጥቷል።
ይህ አሠራር የሪል ስቴት አልሚዎች የቤት ግንባታውን ሳያከናውኑ ወይም በሂደት ላይ እያለ ለግንባታው የሚውልን ፋይናንስ የሚያሰባስቡበት እና ገንዘቡብ ለግንባታው የሚያውሉበት መንገድ ነው።
የቤት ግንባታው ሳይከናወን በፊት ከገዢዎች ጋር ውል ማሰር እና ክፍያ መፈጸም ኢትዮጵያ ውስጥ በሪል ስቴት ልማት ላይ በተሰማሩ አልሚዎች በኩል የተለመደ አሰራር ነው።
አዲሱ ረቂቅ አዋጅ፤ በዚህ ዓይነት መልኩ ለግንባታ የሚውለውን ሀብት ማሰባሰብ የሚፈልጉ አልሚዎች " አግባብ ካለዉ አካል ፈቃድ ማቅረብ " ይጠበቅባቸዋል። ይህም ግዴታ ነው።
የቅድመ ሽያጭ ዘዴን መጠቀም የሚፈልጉት ሪል ስቴት አልሚዎች፤ ከቤት ገዢዎች የሚሰበስቡት ገንዘብ የሚቀመጥበት የባንክ ሂሳብ እና የገንዘብ አወጣጥ ላይም አስገዳጅ አሠራር በረቂቅ አዋጁ ተጥሎባቸዋል።
አልሚዎቹ ከቤት ገዢዎች የሚሰበስቡትን ገንዘብ " የዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ ማደረግ ወይም ማስያዝ " እንዳለባቸው ረቂቅ ሕጉ ላይ ሰፍሯል።
አዲሱ ሕግ፤ ገንዘቡ የሚቀመጥበት ዝግ የባንክ አካውንት የሚከፈተው " አግባብ ባለው አካል ፈቃድ መሠረት " እንደሆነም ያስረዳል።
በዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ የተደረገው ገንዘብ የሚለቀቅበት ሁኔታ ከረቂቅ አዋጁ መፅደቅ በኋላ በሚወጣ ደንብ ይወሠናል።
ከዚህም ባሻገር በቅድሚያ የተሸጠው ቤት ተገንብቶ ለተጠቃሚዎች እስከሚተላለፍ ድረስ የቤት የመሥሪያ ቦታው የይዞታ ማስረጃ " በሚመለከተው አካል እንዳይሸጥ፣ እንዳይለወጥ " እንደሚታገድ ረቂቁ ይገልጻል።
ቤት ቀድመው በሚሸጡ ሪል ስቴት አልሚዎች ላይ እነዚህ አስገዳጅ አሠራሮች የተቀመጡት " ደንበኞች የሚደርስባቸውን እንግልት እና ኪሳራ ለመቀነስ በማሰብ " እንደሆነ የአዋጁ ማብራሪያ ያስረዳል።
ረቂቅ አዋጁ በሪል ስቴት አልሚዎች ላይ ሌሎችንም ግዴታዎች ጥሏል።
በረቂቁ መሠረት፤ የሪል ስቴት አልሚዎች ግንባታው 80 በመቶ ላይ ያልደረሰን ቤት ለደንበኞች እንዳያስተላልፉ ተከልክለዋል።
" ያለደንበኛው ፍላጎት እና ፈቃድ አጠቃላይ ግንባታው ቢያንስ 80 በመቶ ያልተጠናቀቀ ቤት ለደንበኞች ሊያስተላልፍ አይችልም " ይህንን ለማድረግ በቅድሚያ ደንበኛው መስማማት እንዳለበት ያመለክታል።
ሪል ስቴት አልሚዎች ቤት ገዢዎችን መመመዝገብ እና ቅድመ ክፍያ መሰብሰብ የሚችሉበት ጊዜም ቅድመ ሁኔታ ተቀምጦበታል።
አልሚዎች ምዝገባ ማድረግ እና ክፍያ መሰብሰብ የሚችሉት " የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ እና የግንባታ ፈቃድ ከሚመለከተው አካል ከተረከቡ " በኋላ ነው።
" በሕጋዊ መንገድ የተረከበው መሬት ሊያስተናግድ ከሚችለዉ የቤት ደንበኛ በላይ መመዝገብ አይችልም " የሚለውም ሪል ስቴት አልሚዎች ላይ ከተቀመጡት ግዴታዎች መካከል ነው።
ለሪል ስቴት ልማት አሠራር የሚዘረጋው አዲሱ አዋጅ፤ ከግዴታዎች ባሻገር አልሚዎች ከመንግሥት " መሬት በስፋት " ማግኘት የሚችሉበትን ሂደትም ያስቀመጠ ነው።
ከመንግሥት መሬት " በስፋት " የሚቀርብላቸው አልሚዎች ረቂቁ ላይ ከተጠቀሱ ሦስት ቅድመ ሁኔታዎች ውስጥ ቢያንስ አንዱን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
ከእነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች መካከል በብዛት ቤቶችን መገንባት እና ከእነዚህ ቤቶች ውስጥ " 40 በመቶውን ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ላላቸው የማኅበረሰብ ክፍል ተደራሽ " ማድረግ የሚለው አንዱ ነው።
ይህንን ቅድመ ሁኔታ የሚከተሉ አልሚዎች የሚገነቡበት ቤት ብዛት " እንደ ከተሞች ደረጃ በአንድ ጊዜ ከ500 እስከ 5 ሺህ " ሊሆን እንደሚችል በረቂቁ ላይ ተጠቅሷል።
መንግሥት በአዲስ አበባ ከተማ መሬት " በስፋት " የሚያቀርበው " በአዲስ አበባ ከ5 ሺ በላይ ቤት ለሚገነባ እና ለሚያስተላልፍ " አልሚ እንደሆነ ረቂቁ ላይ ሰፍሯል።
በሌሎች ከተሞች መሬት " በስፋት " የሚቀርበው እደሚኖራቸው " ተጨባጭ የቤት ፍላጎት " ሲሆን፣ " ኢንዱስትሪ ፓርክ ያለበት አካባቢ ባሉ ከተሞች " ደግሞ ከአንድ ሺህ በላይ ቤቶችን ለሚገነቡ አልሚዎች እንደሚቀርብላቸው ረቂቁ ያስረዳል።
ከመንግሥት መሬት " በስፋት " ማግኘት የሚፈልጉ አልሚዎች የተቀመጠባቸው ሌሎች ቅድመ ሁኔታዎች ከውጭ ምንዛሬ ጋር የተገናኙ ናቸው።
በአገር ውስጥ " በጥራት እና በብዛት የማይገኙ " ግብአቶችን በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ (ፍራንኮ ቫሉታ) የሚያስገቡ እንዲሁም የሚያገኙትን ትርፍ እስከ አስር ዓመት ከአገር ሳያወጡ አገር ውስጥ መልሰው የሚጠቀሙ አልሚዎች የዚህ አሠራር ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ረቂቁ ላይ ሰፍሯል።
" የሪል ስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይት እና ግመታ " የተሰኘው ይህ ረቂቅ አዋጅ የቀረበለት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለተጨማሪ ዕይታ ወደ ከተማ፣ መሠረተ ልማት እና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምፅ መርቶታል።
መረጃው ከቢቢሲ አማርኛ የተወሰደ ነው።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ልማት ባንክን ጨምሮ ስምንት የመንግስት ልማት ድርጅቶች በኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ስር እንዲተዳደሩ ተወሰነ
ለመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታ እና አስተዳደር ተጠሪ የነበሩ የልማት ድርጅቶች ከአሁን ጀምሮ በባለቤትነት የሚተዳደሩትና የሚመሩት በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ስር መሆናቸው ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፣ ኢትዮ ፖስት ኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ፣ የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት፣ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ኮርፖሬሽን እና ለኢትዯ ፋርማ ግሩፐ ተጠሪ የሆኑት ብሔራዊ የእንስሳት ጤና ጥበቃ ተቋምና ሺልድ ቫክስ በኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ስር እንዲሆኑ የተደረጉት መንግስታዊ ተቋማት ናቸዉ።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ ( ዶ/ር) እንደተናገሩት እነዚህ የልማት ድርጅቶች ለኢትዮጵያ ኢንደስትሪላይዜሽን እና የዕድገት ምኞቶችን ለማሳካት ወሳኝ ናቸው ብለዋል፤ "እኛም ባለን ትኩረት፣ ሙያዊ አስተዳደር እና ንቁ ባለቤትነት እነዚህን ድርጅቶች ወደ አዲስ የስራ አፈጻጸም እና ፈጠራ እንደምናመጣ እርግጠኞች ነን" ሲሉም እርምጃውን አድንቀዉታል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (ኢኢሆ) በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 487/2022 የተቋቋመ ድርጅት ሲሆን አሁን ላይ አዳዲሶችን ጨምሮ በአጠቃላይ ከ 25 በላይ የመንግስት የልማት ድርጅቶችን በባለቤትን እያስተዳደረ እንደሚገኝ ተገልጿል ።
Source: capitalethiopia
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ አማራጭ የሕግ እውቀት እና አገልገሎት
Alternative legal enlightenment and Service
https://linktr.ee/alehig
alehig.com
ለመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታ እና አስተዳደር ተጠሪ የነበሩ የልማት ድርጅቶች ከአሁን ጀምሮ በባለቤትነት የሚተዳደሩትና የሚመሩት በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ስር መሆናቸው ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፣ ኢትዮ ፖስት ኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ፣ የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት፣ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ኮርፖሬሽን እና ለኢትዯ ፋርማ ግሩፐ ተጠሪ የሆኑት ብሔራዊ የእንስሳት ጤና ጥበቃ ተቋምና ሺልድ ቫክስ በኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ስር እንዲሆኑ የተደረጉት መንግስታዊ ተቋማት ናቸዉ።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ ( ዶ/ር) እንደተናገሩት እነዚህ የልማት ድርጅቶች ለኢትዮጵያ ኢንደስትሪላይዜሽን እና የዕድገት ምኞቶችን ለማሳካት ወሳኝ ናቸው ብለዋል፤ "እኛም ባለን ትኩረት፣ ሙያዊ አስተዳደር እና ንቁ ባለቤትነት እነዚህን ድርጅቶች ወደ አዲስ የስራ አፈጻጸም እና ፈጠራ እንደምናመጣ እርግጠኞች ነን" ሲሉም እርምጃውን አድንቀዉታል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (ኢኢሆ) በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 487/2022 የተቋቋመ ድርጅት ሲሆን አሁን ላይ አዳዲሶችን ጨምሮ በአጠቃላይ ከ 25 በላይ የመንግስት የልማት ድርጅቶችን በባለቤትን እያስተዳደረ እንደሚገኝ ተገልጿል ።
Source: capitalethiopia
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ አማራጭ የሕግ እውቀት እና አገልገሎት
Alternative legal enlightenment and Service
https://linktr.ee/alehig
alehig.com
Forwarded from 🇪🇹የሕግ ጉዳይ
ከማይንቀሳቀስ ንብረት ጋር በተያያዘ የመንደር ውል ህጋዊ የሚሆንባቸው 5/አምስት/ ሁኔታዎች 👉(Abraham Yohanes)
✅ የማንይቀሳቀስ ንብረትን ለማስተላለፍ ወይም የማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለ መብትን ለማስተላለፍ የሚደረግ ውል በ ፍርድ ቤት ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ካልተደረገ ተቀባይነት የለውም። ነገር ግን ከተወሰኑ የሰበር ችሎት ውሳኔዎች በመነሳት የመንደር ውል ህጋዊ ተብለው የሚቆጠሩበት ሁኔታዎች አሉ። እነዚህ 5 ሁኔታዎች የሚከተሉት ናቸው።
❶ኛ የሽያጭ ውል መኖሩ ከታመነ ወይም ካልተካደ
✅ ገዢ ውል እንዲፈፀምለት ክስ አቅርቦ ከሳሽ መከላከያ መልሱ ላይ በመካከላቸው ውል መኖሩን ካመነ ወይም ካልካደና በሌሎች ነጥቦች ላይ መልስ ከሰጠ ፍርድ ቤቱ በራሱ አነሳሽነት ውሉ በፍርድ ቤት ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት አልተደረገም ብሎ ውድቅ ሊያደርገው አይችልም።
❷ኛ በማህበር በመደራጀት የተሰራ ቤት በሽያጭ ማስተላለፍ (ሰ/መ/ቁጥር 36294 ቅፅ 8)
✅ በማህበር በመደራጀት እየተሰራ ያለ ቤት ቤቱ ተጠናቆ ካርታ እስኪወጣለት ድረስ የማህበሩ አባል የሆነ ሰው ይህን ቤት ቢያስተላልፍ ቤት የመስራት መብቱን ወይም እጣውን እንዳስተላለፈ እንጂ የማይንቀሳቀስ ንብረትን እንዳስተላለፈ አይቆጠርም። የማህበሩ አባል በስሙ ካርታና የባለቤትነት ማስረጃ እስካልተሰጠው ድረስ ቤቱ ወይም እየተሰራ ያለው ቤት በማህበሩ አጠቃላይ ይዞታ ስር የሚገኝ በመሆኑ የማህበሩ አባል ለ 3ኛ ወገን ሊያስተላልፍ የሚችለው እጣውን ወይም ጥቅሙን እንጂ የማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለውን መብት አይደለም። እንዲህ አይነት ውሎች የግድ ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ሊረጋገጡ አይገባም።
❸ኛ ያልነበረን ቤት ሰርቶ ለማስተላለፍ የሚደረግ ውል (ሰ/መ/ቁጥር 32222 ቅፅ 7)
✅ ብዙን ግዜ እንዲህ አይነት ውል ከ Real Estate ቤቶች ግንባታ ጋር የተያያ ነው። ምንም እንኳን ውላቸው ላይ የማይንቀሳቀስ ንብረት ሽያጭ ውል ቢሉም ዉሉ በሚደረግበት ግዜ ቤቱ ያልነበረ በመሆኑ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብትነት ከአንዱ ወደ ሌላው ተላልፏል ሊባል አይችልም። ያልነበረን ቤት ሰርቶ ለማስተላለፍ የሚደረግ ውል የግንባታ ውል እንጂ የማይንቀሳቀስ ንብረት ሽያጭ ውል ሊባል የሚችል ባለመሆኑ ውሉ በፍርድ ቤት ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት መረጋገጥ አይኖርበትም።
❹ኛ አዋዋይ ፊት ቀርቦ ነገር ግን አስተዳደራዊ ወይም የፕሮቶኮል ጉዳዮች ለተወሰነ ግዜ ሳይፈፀምበት የቆየ የመንደር ውል (የሰ/መ/ቁጥር 36740 ቅጽ 8)
✅ ችሎቱ በዚህ መዝገብ ላይ በሰጠው ውሳኔ መሠረት በግራ ቀኙ መሀከል የተደረገው የመንደር ውል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ቀርቦ ነገር ግን አስተዳደራዊ ወይም የፕሮቶኮል ጉዳዮች የተሟሉት የተወሰነ ግዜ ከቆየ በኋላ ቢሆንም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰው አካል ፊት ያልተደረገ ነው በሚል ውድቅ ሊደረግ አይገባም የሚል ነው።
✅ ችሎቱ በዚህ መዝገብ ላይ እንዳለው ቤቱን የሚመለከቱ እዳና እገዳ ለማጣራትና ክፍያ ለመፈፀም የውልና ማስረጃ ምዝገባ ጽ/ቤት በውል ላይ ማህተም ሣያሣርፍበትና የፕሮቶኮል ቁጥር ሰጥቶ ሣያረጋግጥበት የተወሰነ ጊዜ ያለፈ ቢሆንም እነዚህ አስተዳደራዊ ጉዳዮች እስኪከናወኑ ድረስ በውል ላይ ማህተም ሣያርፍበት መቆየቱ ወይም የፕሮቶኮል ቁጥር ሣይሰጠው መዘግየቱ ውል እንዳልተደረገ የሚያስቆጥረው ነው ለማለት አያስችልም፡፡
❺ኛ የሊዝ መብትን ለማስተላለፍ የሚደረግ ውል (የሰ/መ/ቁጥር 191095 & 225796)
✅ በሊዝ የተገኘ ይዞታ ላይ ግንባታ ከመጀመሩ በፊት ወይም ተጀምሮ በግማሽ ከመጠናቀቁ በፊት የሊዝ መብት ዘመኑ እስከሚጠናቀቅ ድረስ በቦተው የመጠቀም መብትን ማስተላለፍ ይቻላል። ነገር ግን የሚተላለፈው በቦታው ላይ ግማሽ ግንባታ ከተከናወነ በኋላ ከሆነ በቦታው ላይ የመጠቀም መብት ብቻ ሳይሆን በቦታው ላይ ከተሰራው ህንፃ ጭምር በመሆኑ የሊዝ መብት ማስተላለፍ የማይንቀሳቀስ ንብረት እንደ ማስተላለፍ ይቆጠራል። ስለዚህ ሁለት ነገር መታየት ይኖርበታል። የመጀመሪያው አንድ ሰው መሬት በሊዝ ወስዶ ምንም አይነት ግንባታ ካልፈፀመበት ወይም ግንባታ ጀምሮ በግማሽ ከማጠናቀቁ በፊት የሊዝ መብቱን በመንደር ውል ማስተላለፍ ይችላል። ሁለተኛው የግንባታው ደረጃ ግማሽና ከዛ በላይ የደረሰ ከሆነ ግን የሚተላለፈው በቦታው ላይ የመጠቀም መብት ብቻ ሳይሆን በቦታው ላይ የተገነባውን የማይንቀሳቀስ ንብረት ጭምር በመሆኑ ውሉ ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ቀርቦ መረጋገጥ ይኖርበታል።
https://t.me/Law_issue
✅ የማንይቀሳቀስ ንብረትን ለማስተላለፍ ወይም የማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለ መብትን ለማስተላለፍ የሚደረግ ውል በ ፍርድ ቤት ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ካልተደረገ ተቀባይነት የለውም። ነገር ግን ከተወሰኑ የሰበር ችሎት ውሳኔዎች በመነሳት የመንደር ውል ህጋዊ ተብለው የሚቆጠሩበት ሁኔታዎች አሉ። እነዚህ 5 ሁኔታዎች የሚከተሉት ናቸው።
❶ኛ የሽያጭ ውል መኖሩ ከታመነ ወይም ካልተካደ
✅ ገዢ ውል እንዲፈፀምለት ክስ አቅርቦ ከሳሽ መከላከያ መልሱ ላይ በመካከላቸው ውል መኖሩን ካመነ ወይም ካልካደና በሌሎች ነጥቦች ላይ መልስ ከሰጠ ፍርድ ቤቱ በራሱ አነሳሽነት ውሉ በፍርድ ቤት ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት አልተደረገም ብሎ ውድቅ ሊያደርገው አይችልም።
❷ኛ በማህበር በመደራጀት የተሰራ ቤት በሽያጭ ማስተላለፍ (ሰ/መ/ቁጥር 36294 ቅፅ 8)
✅ በማህበር በመደራጀት እየተሰራ ያለ ቤት ቤቱ ተጠናቆ ካርታ እስኪወጣለት ድረስ የማህበሩ አባል የሆነ ሰው ይህን ቤት ቢያስተላልፍ ቤት የመስራት መብቱን ወይም እጣውን እንዳስተላለፈ እንጂ የማይንቀሳቀስ ንብረትን እንዳስተላለፈ አይቆጠርም። የማህበሩ አባል በስሙ ካርታና የባለቤትነት ማስረጃ እስካልተሰጠው ድረስ ቤቱ ወይም እየተሰራ ያለው ቤት በማህበሩ አጠቃላይ ይዞታ ስር የሚገኝ በመሆኑ የማህበሩ አባል ለ 3ኛ ወገን ሊያስተላልፍ የሚችለው እጣውን ወይም ጥቅሙን እንጂ የማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለውን መብት አይደለም። እንዲህ አይነት ውሎች የግድ ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ሊረጋገጡ አይገባም።
❸ኛ ያልነበረን ቤት ሰርቶ ለማስተላለፍ የሚደረግ ውል (ሰ/መ/ቁጥር 32222 ቅፅ 7)
✅ ብዙን ግዜ እንዲህ አይነት ውል ከ Real Estate ቤቶች ግንባታ ጋር የተያያ ነው። ምንም እንኳን ውላቸው ላይ የማይንቀሳቀስ ንብረት ሽያጭ ውል ቢሉም ዉሉ በሚደረግበት ግዜ ቤቱ ያልነበረ በመሆኑ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብትነት ከአንዱ ወደ ሌላው ተላልፏል ሊባል አይችልም። ያልነበረን ቤት ሰርቶ ለማስተላለፍ የሚደረግ ውል የግንባታ ውል እንጂ የማይንቀሳቀስ ንብረት ሽያጭ ውል ሊባል የሚችል ባለመሆኑ ውሉ በፍርድ ቤት ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት መረጋገጥ አይኖርበትም።
❹ኛ አዋዋይ ፊት ቀርቦ ነገር ግን አስተዳደራዊ ወይም የፕሮቶኮል ጉዳዮች ለተወሰነ ግዜ ሳይፈፀምበት የቆየ የመንደር ውል (የሰ/መ/ቁጥር 36740 ቅጽ 8)
✅ ችሎቱ በዚህ መዝገብ ላይ በሰጠው ውሳኔ መሠረት በግራ ቀኙ መሀከል የተደረገው የመንደር ውል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ቀርቦ ነገር ግን አስተዳደራዊ ወይም የፕሮቶኮል ጉዳዮች የተሟሉት የተወሰነ ግዜ ከቆየ በኋላ ቢሆንም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰው አካል ፊት ያልተደረገ ነው በሚል ውድቅ ሊደረግ አይገባም የሚል ነው።
✅ ችሎቱ በዚህ መዝገብ ላይ እንዳለው ቤቱን የሚመለከቱ እዳና እገዳ ለማጣራትና ክፍያ ለመፈፀም የውልና ማስረጃ ምዝገባ ጽ/ቤት በውል ላይ ማህተም ሣያሣርፍበትና የፕሮቶኮል ቁጥር ሰጥቶ ሣያረጋግጥበት የተወሰነ ጊዜ ያለፈ ቢሆንም እነዚህ አስተዳደራዊ ጉዳዮች እስኪከናወኑ ድረስ በውል ላይ ማህተም ሣያርፍበት መቆየቱ ወይም የፕሮቶኮል ቁጥር ሣይሰጠው መዘግየቱ ውል እንዳልተደረገ የሚያስቆጥረው ነው ለማለት አያስችልም፡፡
❺ኛ የሊዝ መብትን ለማስተላለፍ የሚደረግ ውል (የሰ/መ/ቁጥር 191095 & 225796)
✅ በሊዝ የተገኘ ይዞታ ላይ ግንባታ ከመጀመሩ በፊት ወይም ተጀምሮ በግማሽ ከመጠናቀቁ በፊት የሊዝ መብት ዘመኑ እስከሚጠናቀቅ ድረስ በቦተው የመጠቀም መብትን ማስተላለፍ ይቻላል። ነገር ግን የሚተላለፈው በቦታው ላይ ግማሽ ግንባታ ከተከናወነ በኋላ ከሆነ በቦታው ላይ የመጠቀም መብት ብቻ ሳይሆን በቦታው ላይ ከተሰራው ህንፃ ጭምር በመሆኑ የሊዝ መብት ማስተላለፍ የማይንቀሳቀስ ንብረት እንደ ማስተላለፍ ይቆጠራል። ስለዚህ ሁለት ነገር መታየት ይኖርበታል። የመጀመሪያው አንድ ሰው መሬት በሊዝ ወስዶ ምንም አይነት ግንባታ ካልፈፀመበት ወይም ግንባታ ጀምሮ በግማሽ ከማጠናቀቁ በፊት የሊዝ መብቱን በመንደር ውል ማስተላለፍ ይችላል። ሁለተኛው የግንባታው ደረጃ ግማሽና ከዛ በላይ የደረሰ ከሆነ ግን የሚተላለፈው በቦታው ላይ የመጠቀም መብት ብቻ ሳይሆን በቦታው ላይ የተገነባውን የማይንቀሳቀስ ንብረት ጭምር በመሆኑ ውሉ ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ቀርቦ መረጋገጥ ይኖርበታል።
https://t.me/Law_issue
ከማይንቀሳቀስ ንብረት ጋር በተያያዘ የመንደር ውል ህጋዊ የሚሆንባቸው 5/አምስት/ ሁኔታዎች
የማንይቀሳቀስ ንብረትን ለማስተላለፍ ወይም የማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለ መብትን ለማስተላለፍ የሚደረግ ውል በ ፍርድ ቤት ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ካልተደረገ ተቀባይነት የለውም። ነገር ግን ከተወሰኑ የሰበር ችሎት ውሳኔዎች በመነሳት የመንደር ውል ህጋዊ ተብለው የሚቆጠሩበት ሁኔታዎች አሉ። እነዚህ 5 ሁኔታዎች የሚከተሉት ናቸው።
🥇 ኛ የሽያጭ ውል መኖሩ ከታመነ ወይም ካልተካደ
🥈 ገዢ ውል እንዲፈፀምለት ክስ አቅርቦ ከሳሽ መከላከያ መልሱ ላይ በመካከላቸው ውል መኖሩን ካመነ ወይም ካልካደና በሌሎች ነጥቦች ላይ መልስ ከሰጠ ፍርድ ቤቱ በራሱ አነሳሽነት ውሉ በፍርድ ቤት ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት አልተደረገም ብሎ ውድቅ ሊያደርገው አይችልም።
🥉 ኛ በማህበር በመደራጀት የተሰራ ቤት በሽያጭ ማስተላለፍ (ሰ/መ/ቁጥር 36294 ቅፅ 8)
✏️ በማህበር በመደራጀት እየተሰራ ያለ ቤት ቤቱ ተጠናቆ ካርታ እስኪወጣለት ድረስ የማህበሩ አባል የሆነ ሰው ይህን ቤት ቢያስተላልፍ ቤት የመስራት መብቱን ወይም እጣውን እንዳስተላለፈ እንጂ የማይንቀሳቀስ ንብረትን እንዳስተላለፈ አይቆጠርም። የማህበሩ አባል በስሙ ካርታና የባለቤትነት ማስረጃ እስካልተሰጠው ድረስ ቤቱ ወይም እየተሰራ ያለው ቤት በማህበሩ አጠቃላይ ይዞታ ስር የሚገኝ በመሆኑ የማህበሩ አባል ለ 3ኛ ወገን ሊያስተላልፍ የሚችለው እጣውን ወይም ጥቅሙን እንጂ የማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለውን መብት አይደለም። እንዲህ አይነት ውሎች የግድ ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ሊረጋገጡ አይገባም።
🔴 ኛ ያልነበረን ቤት ሰርቶ ለማስተላለፍ የሚደረግ ውል (ሰ/መ/ቁጥር 32222 ቅፅ 7)
✏️ ብዙን ግዜ እንዲህ አይነት ውል ከ Real Estate ቤቶች ግንባታ ጋር የተያያ ነው። ምንም እንኳን ውላቸው ላይ የማይንቀሳቀስ ንብረት ሽያጭ ውል ቢሉም ዉሉ በሚደረግበት ግዜ ቤቱ ያልነበረ በመሆኑ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብትነት ከአንዱ ወደ ሌላው ተላልፏል ሊባል አይችልም። ያልነበረን ቤት ሰርቶ ለማስተላለፍ የሚደረግ ውል የግንባታ ውል እንጂ የማይንቀሳቀስ ንብረት ሽያጭ ውል ሊባል የሚችል ባለመሆኑ ውሉ በፍርድ ቤት ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት መረጋገጥ አይኖርበትም።
4⃣ ኛ አዋዋይ ፊት ቀርቦ ነገር ግን አስተዳደራዊ ወይም የፕሮቶኮል ጉዳዮች ለተወሰነ ግዜ ሳይፈፀምበት የቆየ የመንደር ውል (የሰ/መ/ቁጥር 36740 ቅጽ 8)
✏️ ችሎቱ በዚህ መዝገብ ላይ በሰጠው ውሳኔ መሠረት በግራ ቀኙ መሀከል የተደረገው የመንደር ውል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ቀርቦ ነገር ግን አስተዳደራዊ ወይም የፕሮቶኮል ጉዳዮች የተሟሉት የተወሰነ ግዜ ከቆየ በኋላ ቢሆንም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰው አካል ፊት ያልተደረገ ነው በሚል ውድቅ ሊደረግ አይገባም የሚል ነው።
✏️ ችሎቱ በዚህ መዝገብ ላይ እንዳለው ቤቱን የሚመለከቱ እዳና እገዳ ለማጣራትና ክፍያ ለመፈፀም የውልና ማስረጃ ምዝገባ ጽ/ቤት በውል ላይ ማህተም ሣያሣርፍበትና የፕሮቶኮል ቁጥር ሰጥቶ ሣያረጋግጥበት የተወሰነ ጊዜ ያለፈ ቢሆንም እነዚህ አስተዳደራዊ ጉዳዮች እስኪከናወኑ ድረስ በውል ላይ ማህተም ሣያርፍበት መቆየቱ ወይም የፕሮቶኮል ቁጥር ሣይሰጠው መዘግየቱ ውል እንዳልተደረገ የሚያስቆጥረው ነው ለማለት አያስችልም፡፡
5⃣ ኛ የሊዝ መብትን ለማስተላለፍ የሚደረግ ውል (የሰ/መ/ቁጥር 191095 & 225796)
#በአለሕግ_ጠበቃና_ሕግ_አማካሪ
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
የማንይቀሳቀስ ንብረትን ለማስተላለፍ ወይም የማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለ መብትን ለማስተላለፍ የሚደረግ ውል በ ፍርድ ቤት ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ካልተደረገ ተቀባይነት የለውም። ነገር ግን ከተወሰኑ የሰበር ችሎት ውሳኔዎች በመነሳት የመንደር ውል ህጋዊ ተብለው የሚቆጠሩበት ሁኔታዎች አሉ። እነዚህ 5 ሁኔታዎች የሚከተሉት ናቸው።
#በአለሕግ_ጠበቃና_ሕግ_አማካሪ
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ሊፈጠር የሚችለውን ቅሬታ ስለማንሳት/ ይፋ ስለማድረግ፡ የውጭ አገር ዜጎችን የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት እና ባለይዞታ ሊያደርግ ይችላል በተባለው ረቂቅ አዋጅ ላይ ጥቂት እይታዎች
1. አሁን ያለው የሕግ ሥርዓት (የቀድሞው ሕግ - የፍትሐ ብሔር ሕግ አንቀጾች 390-393)
አጠቃላይ መርህ፡ ገደብ ከሌለ በቀር የውጭ ዜጎች በፍትሃ ብሔር መብቶቸ፣ የመስራትና የመጠቀም መብቶችን በሚመለከት ረገድ እንደ ኢትዮጵያውያን የሚቆጠሩ መሆኑን ተድንግጎ ይገኛል፡፡ (አንቀጽ 389(1)) ።
መሰረታዊ ገደቦች፡- በ‹ንጉሰ ነገስቱ ትእዛዝ› በግልፅ ካልተፈቀደ በስተቀር የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ ውስጥ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሃብት ሊሆን እንደማይችል በአንቀጽ 390 ስር የተቀመጠውን ድንጋግይ በግልፅ ይከለክላል (ይህም ከንጉሠ ነገሥቱ በኋላ በነበረው ዘመን ከመንግሥት ከፍተኛ ባለስልጣን ይሁንታ ወይም ድንጋጌ ጋር ይዛመዳል) ።
ማስፈጸሚያ፡- የውጭ አገር ዜጎች ሰዎች ንብረቱን ያለፍቃድ ካገኙ በኋላ በስድስት ወራት ውስጥ ለኢትዮጵያዊው መሸጥ ይጠበቅባቸው ነበር፣ ምንም እንኳን በቅን ልቦና ቢያደርጉም፣ ለምሳሌ በውርስ (አንቀጽ 391) ። ይህን ያለማድረግ ንብረቱ በመንግስት ባለስልጣኖች ጠያቂነት ተይዞ በግዳጅ ሽያጭ ለኢትዮጵያዊ እንዲተላለፍ የሚደረግ መሆኑ ይህ ተግባር ላስከተለው ወጪና ደንብ መተላለፍ ደግሞ የሽያጩ 20% የገንዘብ ቅጣት የሚጣል ስለመሆኑ ተደንግጎ ይገኛል፡፡(አንቀጽ 392(1) እና (2))።
የተፈፃሚነት ወሰን፡- ከሙሉ የባለቤትነት መብት በተጨማሪ እነዚህ ገደቦች ከባለቤትነት ጋር በተያያዙ መብቶች ላይም ተፈጻሚ ይሆናሉ፡፡ ለምሳሌ የአላባ ጥቅም (ከሌላ ሰው ንብረት የመጠቀም እና ትርፍ የማግኘት መብት) ወይም ምናልባትም የባለቤትነት መብትን በሚመስሉ የረጅም ጊዜ የሊዝ ውል (አንቀጽ 393)።
አመክንዮ (ከህጉ በውስጠ ታዋቃኒት ሊወሰድ የሚችለው ግምት)፡- የዚህ ማዕቀፍ ታሪካዊ ዳራ ሲቃኝ የጠባቂነት አካሄድን(Protectionist stance) የሚያንፀባርቅ ሲሆን ምናልባትም መሬት በዋነኛነት ለኢትዮጵያውያን እንዲቆይ፣ አስፈላጊ በሆነው አገራዊ ሃብት (መሬት) ላይ የውጭ ቁጥጥርን ለመከላከል እና ምናልባትም ከኢኮኖሚ ብዝበዛ ወይም ከልክ ያለፈ የውጭ ተጽእኖ ለመከላከል ታስቦ የተቀረፀ እንደነበር ደርሳናት ይጠቁማሉ።
2. አዲሱ ረቂቅ ህግ፡ ጠቃሚ ነጥቦች እና ግምገማ
ረቂቅ ህጉ ዜና ከ65 አመታት በላይ የቆየውን ገደብ የሚያነሳ በመሆኑ ጠቃሚም አከራካሪም የህግ፣ ህገመንግስታዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች አሉት፡፡
ሀ. ሕገ መንግሥታዊነት እና ሕጋዊነት፡-
ሕገ መንግሥታዊ መሰናክል (የኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 40(3)) ፡ ትልቁ የሕግ እንቅፋት ይህ ነው። “መሬት የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የጋራ ንብረት በመሆኑ ለሽያጭም ሆነ ለሌላ መገበያያ መንገዶች ሊተላለፍ አይችልም” በማለት አንቀጽ 40(3) በማያሻማ ሁኔታ ይናገራል። እንዲሁም መሬት የመንግስት ወይም የህዝብ ንብረት እንደሆነ እና ዜጎች በትክክል መሬቱን የያዙ እንዳልሆኑ ይልቁንም የመጠቀም መብት እንዳላቸው (በአብዛኛው በመንግስት ሊዝ) መሆኑን በግልፅ አስቀምጧል። በግንባታ እና በመሬት ባለቤትነት መካከል ያለው ዋናው የክርክር ነጥብ ማንም ኢትዮጵያዊ እንኳን ሳይቀር ከስር ያለውን መሬት በግሉ መያዝ ካልቻለ የውጭ ዜጋ እንዴት የማይንቀሳቀስ ንብረት ሊኖረው ይችላል? አብዛኛውን ጊዜ መሬቱም ሆነ በላዩ ላይ ያሉት ሕንፃዎች እንደማይንቀሳቀስ ንብረት የሚቆጠሩ መሆኑ ይታመናል፡፡
ተገቢነት ያለው ወይም እምቅ ትርጓሜ/ሰርከምቬንሽን፡- ወደፊት ተገቢውን ሂደት ጨርሶ ተግባር ላይ እንዲውል የታቀደው ህግ የመሬቱን እና የህንፃውን ባለቤትነት (ለምሳሌ የፋብሪካ መዋቅር ወይም በጋራ መኖሪያ ቤት ውስጥ ያለ አፓርትመንት) መካከል ያለውን ልዩነት ለመለየት ሊሞክር ይችላል። ምናልባት ልክ እንደ ኢትዮጵያውያን ዜጎች፣ በመንግስት የተሰጠ የመሬት ሊዝ ውል እያለ የውጭ አገር ዜጎች የሕንፃው ባለቤት ሊሆኑ እንደሚችሉ ሊጠቁም ይችል ይሆናል፡፡
የሕገ መንግሥት ጥናት፡- ይህ አተረጓጎም እንኳን በጥንቃቄ ሊጤን ይገባዋል። በመዋቅሮች ላይ የባለቤትነት እና የሊዝ መብት ለውጭ ዜጎች መስጠት የአንቀጽ 40(3)ን ይዘትና እና መንፈስ ያከብራልን? ዜጎች በሊዝ የመሸጥ መብት ቢኖራቸውም ሕገ መንግሥቱ “ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች” የመጨረሻውን የመሬት ባለቤትነት የተጎናፀፉ መሆናቸውን በግልፅ አስቀምጧል። ለውጭ አገር ዜጎች የባለቤትነት መሰል መብቶችን መስጠት - ሕንፃዎችን እና የሊዝ ኮንትራቶችን ብቻ ያካተተ ቢሆንም - ይህንን አስፈላጊ ሀሳብ ያጠፋል ተብሎ ክርክር ሊቀርብበት ይችላል፡፡ በዚህ ሁኔታ "ባለቤትነት" የሚለው ቃል እራሱ እጅግ በጣም ረቂቅ ነው፡፡
የይዞታ መብት፡- ምንም እንኳን ለውጭ አገር ዜጎች የተሻሻሉ የይዞታ መብቶችን መስጠት (እንደ ረጅም ጊዜ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ የሊዝ ውል) “የባለቤትነት መብት” የመስጠት ያህል ሕገ መንግሥታዊ ባይሆንም እነዚህ መብቶች በረቂቅ ሕጉ እንዴት እንደሚገለጹ ልብ ማለት ያስፈልጋል።
ህጋዊነት ማጠቃለያ፡- ረቂቅ ህጉ “ባለቤትነት” የሕንፃ ባለቤትነት ብቻ እንደሆነ በጥንቃቄ እስካልተደነገገ ድረስ፣ ለዜጎች ካለው የመሬት ሊዝ ሥርዓት ጋር ተዳምሮ፣ የመሬት ባለቤትነትን ከማስተላለፍ ጋር የተያያዘ ማንኛውንም አንድምታ እስካልቀረበ ድረስ፣ ተከራካሪ ከሆነ ሕገ መንግሥቱን የሚጻረር ከፍተኛ አደጋ አለው። ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌዎችን ስንመለከት ያለዚህ ዓይነት ጥንቃቄ የተሞላበት መመዘኛ “ባለቤትነት” የሚለውን ቃል መጠቀም በሕግ አነጋገር እጅግ በጣም አጠራጣሪ መሆኑ አይቀሬ ነው።
ለ. ማህበረ-ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች፡ መፈናቀል እና የመሬት ዘረፋ/ ነጠቃ፡
ይህ በተለይ እንደ አዲስ አበባ ባሉ ትላልቅ የአገሪቱ ከተሞች ውስጥ ትልቅ የህዝብ ጉዳይ ነው።
ወቅታዊ ጫና፡- ለረዥም ጊዜ ነዋሪዎች ቀደም ሲል በፈጣን የከተሞች መስፋፋት እና የልማት ፕሮጀክቶች (እንደ "ኮሪደር ልማት" ያሉ) ፣ በተደጋጋሚ በቂ የካሳ ክፍያ ላለመከፈልና ለማህበራዊ ትሥስር መበጠስ ተዳርገናል የሚል ስሞታዎችን አልፎ አልፎ በማሰማት ላይ እንደሚገኙም ይሰማል፡፡
የአለምአቀፍ ፍላጎት ተጽእኖ፡- የውጭ ባለቤትነትን መፍቀድ—ምናልባትም በሀብታሞች ወይም በቢዝነስ ሰዎች—በሚፈለጉ ሰፈሮች የሪል እስቴትን ዋጋ በሚያስደንቅ ሁኔታ ሊጨምር ይችላል። በዝቅተኛ እና መካከለኛ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን የመኖሪያ ቤት መግዛት ወይም የቀደመ ትሥ ስራቸውን በከተማ ማዕከላዊ ቦታዎች ላይ ማቆየት የማይቻልበት ሁኔታ በዚህ ምክንያት ፍጥነቱን ሊጨምር የሚችልበት አጋጣሚ ሰፊ ሊሆን ይችላል፡፡ በሌላ አገላለፅ እጅግ ጠቃሚ የሆኑ የከተማ ቦታዎች/አከባቢዎች በአገር ውስጥ ባለሃብቶች እና የውጭ ዜጎች እጅ ሊያከማቹ የሚችሉበት ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል።
የመኖሪያ ቤት የማቅረብ አቅም፡- በኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ የከተማ አካባቢዎች የመኖሪያ ቤት እጥረት ከፍተኛ መሆኑ ይታወቃል፡፡ አሁን ለሚታየው ከፍተኛ የመኖሪያ ቤት እጥረት ለነዋሪዎች አቅርቦትን ለማሳደግ የተሰሩ በርካታ ስራዎች ቢኖሩም ችግሩ በተለያዩ ምክን ያቶች እየጨመረ ከመሔዱ ወጪ ስለመቀነሱ ይፋዊ ሪፖርት ወይም ሳይንሳዊ ጥናት የለም፡፡ ስለሆነም ለዚህ ግዙፍ ችግር ትርጉም ያለውን እርምጃ ሳይወስዱ የውጭ ፍላጎትን ማምጣት ችግሩን የባሰ ሊያባብስ ይችላል፡፡ ይህም የመኖሪያ ቤት ዋጋን
1. አሁን ያለው የሕግ ሥርዓት (የቀድሞው ሕግ - የፍትሐ ብሔር ሕግ አንቀጾች 390-393)
አጠቃላይ መርህ፡ ገደብ ከሌለ በቀር የውጭ ዜጎች በፍትሃ ብሔር መብቶቸ፣ የመስራትና የመጠቀም መብቶችን በሚመለከት ረገድ እንደ ኢትዮጵያውያን የሚቆጠሩ መሆኑን ተድንግጎ ይገኛል፡፡ (አንቀጽ 389(1)) ።
መሰረታዊ ገደቦች፡- በ‹ንጉሰ ነገስቱ ትእዛዝ› በግልፅ ካልተፈቀደ በስተቀር የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ ውስጥ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሃብት ሊሆን እንደማይችል በአንቀጽ 390 ስር የተቀመጠውን ድንጋግይ በግልፅ ይከለክላል (ይህም ከንጉሠ ነገሥቱ በኋላ በነበረው ዘመን ከመንግሥት ከፍተኛ ባለስልጣን ይሁንታ ወይም ድንጋጌ ጋር ይዛመዳል) ።
ማስፈጸሚያ፡- የውጭ አገር ዜጎች ሰዎች ንብረቱን ያለፍቃድ ካገኙ በኋላ በስድስት ወራት ውስጥ ለኢትዮጵያዊው መሸጥ ይጠበቅባቸው ነበር፣ ምንም እንኳን በቅን ልቦና ቢያደርጉም፣ ለምሳሌ በውርስ (አንቀጽ 391) ። ይህን ያለማድረግ ንብረቱ በመንግስት ባለስልጣኖች ጠያቂነት ተይዞ በግዳጅ ሽያጭ ለኢትዮጵያዊ እንዲተላለፍ የሚደረግ መሆኑ ይህ ተግባር ላስከተለው ወጪና ደንብ መተላለፍ ደግሞ የሽያጩ 20% የገንዘብ ቅጣት የሚጣል ስለመሆኑ ተደንግጎ ይገኛል፡፡(አንቀጽ 392(1) እና (2))።
የተፈፃሚነት ወሰን፡- ከሙሉ የባለቤትነት መብት በተጨማሪ እነዚህ ገደቦች ከባለቤትነት ጋር በተያያዙ መብቶች ላይም ተፈጻሚ ይሆናሉ፡፡ ለምሳሌ የአላባ ጥቅም (ከሌላ ሰው ንብረት የመጠቀም እና ትርፍ የማግኘት መብት) ወይም ምናልባትም የባለቤትነት መብትን በሚመስሉ የረጅም ጊዜ የሊዝ ውል (አንቀጽ 393)።
አመክንዮ (ከህጉ በውስጠ ታዋቃኒት ሊወሰድ የሚችለው ግምት)፡- የዚህ ማዕቀፍ ታሪካዊ ዳራ ሲቃኝ የጠባቂነት አካሄድን(Protectionist stance) የሚያንፀባርቅ ሲሆን ምናልባትም መሬት በዋነኛነት ለኢትዮጵያውያን እንዲቆይ፣ አስፈላጊ በሆነው አገራዊ ሃብት (መሬት) ላይ የውጭ ቁጥጥርን ለመከላከል እና ምናልባትም ከኢኮኖሚ ብዝበዛ ወይም ከልክ ያለፈ የውጭ ተጽእኖ ለመከላከል ታስቦ የተቀረፀ እንደነበር ደርሳናት ይጠቁማሉ።
2. አዲሱ ረቂቅ ህግ፡ ጠቃሚ ነጥቦች እና ግምገማ
ረቂቅ ህጉ ዜና ከ65 አመታት በላይ የቆየውን ገደብ የሚያነሳ በመሆኑ ጠቃሚም አከራካሪም የህግ፣ ህገመንግስታዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች አሉት፡፡
ሀ. ሕገ መንግሥታዊነት እና ሕጋዊነት፡-
ሕገ መንግሥታዊ መሰናክል (የኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 40(3)) ፡ ትልቁ የሕግ እንቅፋት ይህ ነው። “መሬት የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የጋራ ንብረት በመሆኑ ለሽያጭም ሆነ ለሌላ መገበያያ መንገዶች ሊተላለፍ አይችልም” በማለት አንቀጽ 40(3) በማያሻማ ሁኔታ ይናገራል። እንዲሁም መሬት የመንግስት ወይም የህዝብ ንብረት እንደሆነ እና ዜጎች በትክክል መሬቱን የያዙ እንዳልሆኑ ይልቁንም የመጠቀም መብት እንዳላቸው (በአብዛኛው በመንግስት ሊዝ) መሆኑን በግልፅ አስቀምጧል። በግንባታ እና በመሬት ባለቤትነት መካከል ያለው ዋናው የክርክር ነጥብ ማንም ኢትዮጵያዊ እንኳን ሳይቀር ከስር ያለውን መሬት በግሉ መያዝ ካልቻለ የውጭ ዜጋ እንዴት የማይንቀሳቀስ ንብረት ሊኖረው ይችላል? አብዛኛውን ጊዜ መሬቱም ሆነ በላዩ ላይ ያሉት ሕንፃዎች እንደማይንቀሳቀስ ንብረት የሚቆጠሩ መሆኑ ይታመናል፡፡
ተገቢነት ያለው ወይም እምቅ ትርጓሜ/ሰርከምቬንሽን፡- ወደፊት ተገቢውን ሂደት ጨርሶ ተግባር ላይ እንዲውል የታቀደው ህግ የመሬቱን እና የህንፃውን ባለቤትነት (ለምሳሌ የፋብሪካ መዋቅር ወይም በጋራ መኖሪያ ቤት ውስጥ ያለ አፓርትመንት) መካከል ያለውን ልዩነት ለመለየት ሊሞክር ይችላል። ምናልባት ልክ እንደ ኢትዮጵያውያን ዜጎች፣ በመንግስት የተሰጠ የመሬት ሊዝ ውል እያለ የውጭ አገር ዜጎች የሕንፃው ባለቤት ሊሆኑ እንደሚችሉ ሊጠቁም ይችል ይሆናል፡፡
የሕገ መንግሥት ጥናት፡- ይህ አተረጓጎም እንኳን በጥንቃቄ ሊጤን ይገባዋል። በመዋቅሮች ላይ የባለቤትነት እና የሊዝ መብት ለውጭ ዜጎች መስጠት የአንቀጽ 40(3)ን ይዘትና እና መንፈስ ያከብራልን? ዜጎች በሊዝ የመሸጥ መብት ቢኖራቸውም ሕገ መንግሥቱ “ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች” የመጨረሻውን የመሬት ባለቤትነት የተጎናፀፉ መሆናቸውን በግልፅ አስቀምጧል። ለውጭ አገር ዜጎች የባለቤትነት መሰል መብቶችን መስጠት - ሕንፃዎችን እና የሊዝ ኮንትራቶችን ብቻ ያካተተ ቢሆንም - ይህንን አስፈላጊ ሀሳብ ያጠፋል ተብሎ ክርክር ሊቀርብበት ይችላል፡፡ በዚህ ሁኔታ "ባለቤትነት" የሚለው ቃል እራሱ እጅግ በጣም ረቂቅ ነው፡፡
የይዞታ መብት፡- ምንም እንኳን ለውጭ አገር ዜጎች የተሻሻሉ የይዞታ መብቶችን መስጠት (እንደ ረጅም ጊዜ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ የሊዝ ውል) “የባለቤትነት መብት” የመስጠት ያህል ሕገ መንግሥታዊ ባይሆንም እነዚህ መብቶች በረቂቅ ሕጉ እንዴት እንደሚገለጹ ልብ ማለት ያስፈልጋል።
ህጋዊነት ማጠቃለያ፡- ረቂቅ ህጉ “ባለቤትነት” የሕንፃ ባለቤትነት ብቻ እንደሆነ በጥንቃቄ እስካልተደነገገ ድረስ፣ ለዜጎች ካለው የመሬት ሊዝ ሥርዓት ጋር ተዳምሮ፣ የመሬት ባለቤትነትን ከማስተላለፍ ጋር የተያያዘ ማንኛውንም አንድምታ እስካልቀረበ ድረስ፣ ተከራካሪ ከሆነ ሕገ መንግሥቱን የሚጻረር ከፍተኛ አደጋ አለው። ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌዎችን ስንመለከት ያለዚህ ዓይነት ጥንቃቄ የተሞላበት መመዘኛ “ባለቤትነት” የሚለውን ቃል መጠቀም በሕግ አነጋገር እጅግ በጣም አጠራጣሪ መሆኑ አይቀሬ ነው።
ለ. ማህበረ-ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች፡ መፈናቀል እና የመሬት ዘረፋ/ ነጠቃ፡
ይህ በተለይ እንደ አዲስ አበባ ባሉ ትላልቅ የአገሪቱ ከተሞች ውስጥ ትልቅ የህዝብ ጉዳይ ነው።
ወቅታዊ ጫና፡- ለረዥም ጊዜ ነዋሪዎች ቀደም ሲል በፈጣን የከተሞች መስፋፋት እና የልማት ፕሮጀክቶች (እንደ "ኮሪደር ልማት" ያሉ) ፣ በተደጋጋሚ በቂ የካሳ ክፍያ ላለመከፈልና ለማህበራዊ ትሥስር መበጠስ ተዳርገናል የሚል ስሞታዎችን አልፎ አልፎ በማሰማት ላይ እንደሚገኙም ይሰማል፡፡
የአለምአቀፍ ፍላጎት ተጽእኖ፡- የውጭ ባለቤትነትን መፍቀድ—ምናልባትም በሀብታሞች ወይም በቢዝነስ ሰዎች—በሚፈለጉ ሰፈሮች የሪል እስቴትን ዋጋ በሚያስደንቅ ሁኔታ ሊጨምር ይችላል። በዝቅተኛ እና መካከለኛ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን የመኖሪያ ቤት መግዛት ወይም የቀደመ ትሥ ስራቸውን በከተማ ማዕከላዊ ቦታዎች ላይ ማቆየት የማይቻልበት ሁኔታ በዚህ ምክንያት ፍጥነቱን ሊጨምር የሚችልበት አጋጣሚ ሰፊ ሊሆን ይችላል፡፡ በሌላ አገላለፅ እጅግ ጠቃሚ የሆኑ የከተማ ቦታዎች/አከባቢዎች በአገር ውስጥ ባለሃብቶች እና የውጭ ዜጎች እጅ ሊያከማቹ የሚችሉበት ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል።
የመኖሪያ ቤት የማቅረብ አቅም፡- በኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ የከተማ አካባቢዎች የመኖሪያ ቤት እጥረት ከፍተኛ መሆኑ ይታወቃል፡፡ አሁን ለሚታየው ከፍተኛ የመኖሪያ ቤት እጥረት ለነዋሪዎች አቅርቦትን ለማሳደግ የተሰሩ በርካታ ስራዎች ቢኖሩም ችግሩ በተለያዩ ምክን ያቶች እየጨመረ ከመሔዱ ወጪ ስለመቀነሱ ይፋዊ ሪፖርት ወይም ሳይንሳዊ ጥናት የለም፡፡ ስለሆነም ለዚህ ግዙፍ ችግር ትርጉም ያለውን እርምጃ ሳይወስዱ የውጭ ፍላጎትን ማምጣት ችግሩን የባሰ ሊያባብስ ይችላል፡፡ ይህም የመኖሪያ ቤት ዋጋን
በጅቡቲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ህጋዊ መኖሪያ ማግኘት ያልቻሉበት ምክንያት ምንድነው ?
የጅቡቲ መንግስት ሰነድ አልባ ስደተኞች በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በፈቃዳቸው ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ካወጀ ሰነባብቷል፡፡ የተሰጠው ቀነገደብ በመጠናቀቁም መጠነ ሰፊ አፈሳ እንደሚጀምር አውጇል፡፡
በዚያች ሀገር የሚኖሩ ሰነድ አልባ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በበኩላቸው፣ ሀብት ንብረታችንን ሸጠን የምንወጣበት ጊዜ ይስጠን እያሉ ይማፀናሉ፡፡ ለዚህም ቀነገደቡ እንዲራመዝላቸው ይፈልጋሉ፡፡
ለመሆኑ እነዚህ ሰነድ አልባ ኢትዮጵያውያን (ቁጥራቸው በትንሹ ከ200 ሺህ በላይ ይገመታል) ለምን እስካሁን ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ መያዝ አልቻሉም፡፡
ይህን ጥያቄ ያነሳንላቸው ስማችን አይጠቀስ ያሉ ሶስት ስደተኞች፣ ሕጋዊ ለመሆን ስላለው ሁኔታ የሚከተለውን ሀሳብ ሰጥተዋል፡፡
ሕጋዊ ለመሆን ያለው ችግር ምንድነው ?
" ሁሉም ሰው ህጋዊ መሆን ይፈልጋል፡፡ ችግሩ የገንዘቡ መብዛት ነው፡፡ ሒደቱም ረጅም የድለላ ሰንሰለትን የሚያልፍ እና በእጅጉ ረዥም፣ አድካሚና ውስብስብ ነው፡፡ የአንድ ሰው የአመት ገቢ እንኳ አይበቃም፡፡
ህጋዊ ለመሆን ለጅቡቲ መንግስት የሚከፈለው ገንዘብ አንድ አመት ሙሉ ሰርቶ ማጠራቀም አይቻልም፡፡ የዚህ ሀገር ህጋዊ መሆኛ አሰራር ለድሀና ለስደተኛ የሚመጥን አይደለም፡፡ እንኳን ግለሰብ ቀርቶ፣ ድርጅቶችም አይችሉትም፡፡
የንግድ ድርጅቶች ለሰራተኞቻቸው ህጋዊ የስራ ፈቃድ ለማውጣት፣ እስከ 200 ሺህ ፍራንክ (160 ሺህ ብር ገደማ) ይጠየቃሉ፤ ለአንድ ሰራተኛ፡፡ ለግለሰብ ደግሞ እስከ 70 ሺህ ፍራንክ ይደርሳል በህጋዊው መንገድ፡፡ ግን አብዛኛውን ጊዜ ህጋዊው አካሔድ ስለማይገኝ በደላሎች በኩል እስከ 120 ሺህ ፍራንክ ትጠየቃለህ፡፡ አሁን በቅርቡ 120 ሺህ ፍራንክ ከፍለው ያወጡ ሰዎች አሉ፡፡ አንዳንዴም ከ150 ሺህ እስከ 200 ሺህ ብር ያስወጣሀል፡፡ ይህን ያህል ከፍለህ የምታገኘው የመኖሪያ ፈቃድ፣ ተሰጠህ ሳይሆን ገዛህ ነው ሊባል የሚችለው፡፡ አንዴ ከፍለህ የሚያበቃ ነገር ደግሞ አይደለም፡፡ በየአመቱ ከ 20 ሺህ እስከ 30 ሺህ ፍራንክ እየከፈልክ ታሳድሳለህ ፈቃድህን፡፡
እንደ ሌሎች ሀገራት ብዙ አመት ከቆየህ በኋላ ህጋዊ ነዋሪ አትሆንም፡፡ ሁሌም ጊዜያዊ ነዋሪ እየተባልክ በየአመቱ ፈቃድህን እያደስክ ትኖራለህ፡፡ የቋሚ ነዋሪነት መታወቂያ አይሰጡህም፡፡ ይህ ችግር አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ስደተኛ፣ ሰነድ አልባ ሆኖ በስጋት ውስጥ እንዲኖር አስገድዶታል፡፡
ህጋዊ ሰነድ ለማግኘት ደግሞ ፓስፖርትህ ላይ ቪዛ መመታት አለበት ይሉሀል፡፡ ይህን ቪዛ ለማስመታት ከጅቡቲ ትወጣና እንደገና መግባት አለብህ፣ ቪዛ ለማግኘት የግድ ከጅቡቲ መውጣት አለብህ በየአመቱ፡፡ ተመልሰህ ስትገባ ኤርፖርት ቪዛ ይሰጠሀል፡፡ አዲስ አበባ እና ድሬዳዋም ይመታልሀል፡፡ ግን ቅድመ ሁኔታው በጣም ብዙ ነው፣ አሰልቺም ጭምር፡፡ በዚህ መልኩ፣ ህጋዊ የመሆኛው ሒደት ውድና አድካሚ ነው፡፡ ምንም አይነት ግልፅ የሆነ ህጋዊ አሰራር የላቸውም፡፡
ይህን የምታደርገው ደግሞ ፓስፖርት ካለህ ነው፡፡ ፓስፖርት ይዘን ነው፣ ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የምትጠይቀው፡፡ የእኛ ኤምባሲ ፓስፖርት ለመስጠት 200 ዶላር ይጠይቃል፡፡ በጅቡቲ ፍራንክ ሳይሆን፣ በዶላር ክፈል ነው የምትባለው፡፡ ይህ ራሱ በጣም ብዙ ነው፡፡
ከአንድ አመት በፊት የኢትዮጵያ ፓስፖርት ለመውሰድ ክፍያው ዝቅተኛ ነበር፡፡ 100 ዶላር፣ 150 ዶላር የነበረበት ወቅት ነበር፡፡ አሁን በጣም ነው የጨመረው፡፡ አዲስ ፓስፖርት ተቀይሯል ተብሎ ነው የጨመረው፡፡ አንድ የጥበቃ ሰራተኛና አንዲት የቤት ሰራተኛ የሆኑ ስደተኞች የአንድ ወር ሙሉ ደመወዛቸው ለፓስፖርት ማውጫ አይበቃቸውም፡፡ ሙሉ ደመወዝ ለዚህ ብቻ ልታውለው አትችልም፡፡ መብላት መጠጣት መልበስ የሚባሉ ነገሮች አሉ፡፡ 200 ዶላር ለመቆጠብ ጊዜ ይፈጃል፡፡ ሰዉ ደግሞ የተወሰነ አመት ሰርቶ፣ ገንዘብ አጠራቅሞ ወደ ሀገሩ መመለስ ነው እንጂ፣ ያገኛትን ገንዘብ ለመኖሪያ ፈቃድና ለፓስፖርት መጨረስ አይፈልግም፡፡
ስለዚህ በኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል ያለው የፓስፖርት ክፍያ ቢቀንስ ጥሩ ነበር፡፡ እንደው 100 ዶላር እንኳን ቢያደርግልን፡፡ በሁሉም አቅጣጫ፣ ህጋዊ ሰነድ ማግኘት የምትችልበት ሁኔታ ነው መፈጠር ያለበት፡፡ ኤምባሲያችን ይህ ጉዳይ እንዲቀረፍ መስራት አለበት፡፡
የጅቡቲ መንግስት የመኖሪያ ፈቃዱ ቀለል ባለ መንገድ እንዲገኝ ማድረግ አለበት፡፡ የኢትዮጵያ ኤምባሲም ለዚህ ጫና ማድረግና የመኖሪያ ፈቃድ ለማግኘት በደላሎች እየተበዘበዘ ያለውን ህዝብ ችግር ከግምት አስገብቶ መስራት አለበት፡፡ ሁሉም ሰው ህጋዊ መሆን ይፈልጋል፡፡ ስርዓቱ ለዚህ መመቸት አለበት ነው የምንለው፡፡ "
ስደተኞቹ ህጋዊ ሰነድ ለመያዝ ይገጥሙናል ስላሉዋቸው ችግሮች እንዲሁም የኢትዮጵያን ፓስፖርት ለማውጣት እስከ 200 ዶላር መክፈል አግባብ አይደለም በማለት ላቀረቡት ቅሬታ፣ በጅቡቲ ካለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ማብራሪያ ካገኘን እናቀርባለን፡፡ ሆኖም የፓስፖርት የአገልግሎት ክፍያን በተመለከተ በህገደንብ የተወሰነ መሆኑን ማረጋገጥ ችለናል፡፡
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለሚሰጣቸው አገልግሎቶች የሚከፈል የአገልግሎት ክፍያን ለመወሰን የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 520/2016 ላይ እንደተገለፀው፣ በውጭ ሀገራት በኤምባሲ በኩል የሚሰጥ ባለ 32 ገፅ መደበኛ ፓስፖርት የአገልግሎት ክፍያው 200 ዶላር መሆኑን ተመልክተናል፡፡ በኦንላይንና በእድሳት ደግሞ 250 ዶላር እንደሚያስከፍል ይጠቅሳል ደንቡ፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
143_2011_143_2011ለውጦችን_ስለማሳውቅ.pdf
1.2 MB
ውድ ግብር ከፋዮቻችን የታክስ እንቅስቃሴ ለውጥ ላይ ከሆነ በመመሪያ 143 /2011 መሰረት ለውጥ የተካሄደባቸውን እንቅስቃሴዎች ያሳውቁ
ማንኛውም ድርጅት ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ የመመስረቻ ጽሑፍ፣ የመተዳደሪያ ደንብ፣ የሽርክና ማህበር ስምምነት ወይም ሌላ የመመስረቻ ወይም የምዝገባ ሰነድ ቅጂ ለባለሥልጣኑ መቅረብ አለበት፡፡ እነዚህ ሰነዶች ላይ ማንኛውም ለውጥ ሲደረግ ድርጅቱ ለውጡ በተደረገ በ30 ቀናት ውስጥ ለውጡን በጽሑፍ ለባለሥልጣኑ ማሳወቅ አለበት፡፡
ሀ. በንግድ ድርጅቱ ስያሜ ላይ የተደረገ ለውጥ፤
ለ. በድርጅቱ ስም የተመዘገበ፡-
i. ቋሚ የንግድ ሥራ፣ የቢሮ እና የመኖሪያ አድራሻ ለውጥ፣
ii. በማምረቻ ቦታ ወይም ታክስ ከፋዩ በሚጠቀምበት መጋዘን ላይ የተደረገ የአድራሻ ለውጥ፤
iii. በፖስታ ወይም በመደበኛ እና በተንቀሳቃሽ ሰልክ፣ ፋክስ ወይም ኢ-ሜል አድራሻ ላይ የተደረገ ለውጥ፤
ሐ. በዋነኛ የሥራ እንቅስቃሴው ወይም በቅርንጫፍ ወይም በንግድ ሥራው ዘርፍ ወይም መስክ ላይ የተደረገ ለውጥ፤
መ. በድርጅቱ መተዳደሪያ ደንብ ወይም የመመስረቻ ጽሑፍ ወይም የሽርክና ስምምነት ላይ የተደረገ ለውጥ፤
ሠ. በአክሲዮን ባለድርሻ አባላት ላይ የተደረገ ለውጥ፤
ረ. በድርጅቱ ወይም በታክስ እንደራሴው የባንክ ሂሳብ ወይም የባንክ ቅርንጫፍ አድራሻ ላይ የተደረገ ለውጥ፤
ሰ.በታክስ እንደራሴው እና ከሚኒስቴሩ ጋር ግንኙነት በሚያደርግበት የኤሌክትሮኒክስ አድራሻ ላይ የተደረገ ለውጥ፤
ሸ. በተመዘገበና በተከፈለ ካፒታል ላይ የተደረገ ለውጥ፤……………..
ሙሉን ለማግኘት ከላይ የተቀመጠውን መመሪያ ያንብቡ
እናመሰግናለን !!
ማንኛውም ድርጅት ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ የመመስረቻ ጽሑፍ፣ የመተዳደሪያ ደንብ፣ የሽርክና ማህበር ስምምነት ወይም ሌላ የመመስረቻ ወይም የምዝገባ ሰነድ ቅጂ ለባለሥልጣኑ መቅረብ አለበት፡፡ እነዚህ ሰነዶች ላይ ማንኛውም ለውጥ ሲደረግ ድርጅቱ ለውጡ በተደረገ በ30 ቀናት ውስጥ ለውጡን በጽሑፍ ለባለሥልጣኑ ማሳወቅ አለበት፡፡
ሀ. በንግድ ድርጅቱ ስያሜ ላይ የተደረገ ለውጥ፤
ለ. በድርጅቱ ስም የተመዘገበ፡-
i. ቋሚ የንግድ ሥራ፣ የቢሮ እና የመኖሪያ አድራሻ ለውጥ፣
ii. በማምረቻ ቦታ ወይም ታክስ ከፋዩ በሚጠቀምበት መጋዘን ላይ የተደረገ የአድራሻ ለውጥ፤
iii. በፖስታ ወይም በመደበኛ እና በተንቀሳቃሽ ሰልክ፣ ፋክስ ወይም ኢ-ሜል አድራሻ ላይ የተደረገ ለውጥ፤
ሐ. በዋነኛ የሥራ እንቅስቃሴው ወይም በቅርንጫፍ ወይም በንግድ ሥራው ዘርፍ ወይም መስክ ላይ የተደረገ ለውጥ፤
መ. በድርጅቱ መተዳደሪያ ደንብ ወይም የመመስረቻ ጽሑፍ ወይም የሽርክና ስምምነት ላይ የተደረገ ለውጥ፤
ሠ. በአክሲዮን ባለድርሻ አባላት ላይ የተደረገ ለውጥ፤
ረ. በድርጅቱ ወይም በታክስ እንደራሴው የባንክ ሂሳብ ወይም የባንክ ቅርንጫፍ አድራሻ ላይ የተደረገ ለውጥ፤
ሰ.በታክስ እንደራሴው እና ከሚኒስቴሩ ጋር ግንኙነት በሚያደርግበት የኤሌክትሮኒክስ አድራሻ ላይ የተደረገ ለውጥ፤
ሸ. በተመዘገበና በተከፈለ ካፒታል ላይ የተደረገ ለውጥ፤……………..
ሙሉን ለማግኘት ከላይ የተቀመጠውን መመሪያ ያንብቡ
እናመሰግናለን !!
#ለቲክቶከሮች እና #የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች #አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ!
ጤና ይስጥልኝ! ሚኪያስ መላክ ነኝ፣ ጠበቃ እና የህግ አማካሪ።
በማህበራዊ ሚዲያ በተለይም በቲክቶክ ላይ ንቁ ተሳትፎ ለምታደርጉ ሁሉ፣ አሁን የምሰጣችሁን ማስጠንቀቂያ በደንብ እንድትገነዘቡት እጠይቃለሁ። የቅርብ ጊዜዎቹ #ቲክቶከሮች #ጃኒ በትክክለኛው ስሟ ስመኝ ገብሩ እና የሌሎችን ቲክቶከር ጉዳዮችን ስንታዘብ ያየነው እና የተመለከትናቸው ዋነኛ ምሳሌዎች ናቸው። ሁሉም በፖሊስ ተይዘው ወደ ጣቢያ መወሰዳቸው፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች የሕግ ተጠያቂነትን በሚመለከት ሊገነዘቡት የሚገባ ትልቅ ትምህርት ነው። የእናንተ ተፅዕኖ ፈጣሪነት የራሱ የሆነ ኃላፊነት አለበት።
ጥንቃቄ አይለያችሁ!
አንድ ስኬታማ ሰው በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚኖረው እንቅስቃሴ የሚያስከትለው ጉዳት የጎላ ነው። አንድ ተራ ሰው በሰራው ስህተት ጉዳዩ ተራ ሆኖ ሊቀር ቢችልም፣ እንደ ጃኒ ያሉ ብዙ ተከታይ እና አድማጭ ያላችሁ ሰዎች ግን የሚፈጠረው መዘዝ እጅግ ትልቅ ነው። ተጠንቀቁ!
በተለይ "የአፍ ወለምታ" እና መሰል ንግግሮች የሚያስከትሉትን የህግ ተጠያቂነት አቅልላችሁ እንዳትመለከቱ። ያላሰባችሁት ንግግር ከባድ የህግ መዘዝ ሊያስከትል ይችላል።
የሕግ አማካሪ ወይም ቋሚ ጠበቃ ይኑራችሁ!
ይህ በጣም አስፈላጊ ነገር ነው። ስራችሁን እና ንግግራችሁን ከህግ አንፃር ሳንሱር የሚያደርግ እና ከህዝብ ጋር ከመድረሱ በፊት አስፈላጊውን እርምጃ የሚወስድ የህግ አማካሪ ያስፈልጋችኋል። ይህ ከብዙ ችግሮች ሊታደጋችሁ ይችላል። የጃኒ እና በእስር ላይ የሚገኙ ቲክቶከሮች እና ጉዳዮች ይህንን ፍላጎት በግልጽ ያሳያሉ።
#አላውቅም"፣ #ቀልድ ነው"፣ "#እድሜዬ አልደረሰም" - እነዚህ የህግ መከላከያ ሊሆኑ አይችሉም!
ምንም እንኳን ታሳቢ የሚደረጉ ሁኔታዎች ቢኖሩም በወንጀል ሕጉ መሰረት ጉዳዩ የሚታየው በህጉ ላይ በተመለከቱት መደበኛ ድንጋጌዎች መሰረት ነው። ስለዚህ፣ እድሜም ሆነ የትምህርት ደረጃ ለፈጸሙት ወንጀል መከለያ ሊሆን እንደማይችል ልብ ይበሉ።
ማህበረሰብን/ህዝብን/ብሄርን ማጥላላት ወንጀል ነው፣ ያስጠይቃልም!
በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ስትለጥፉ ወይም ስትናገሩ ዘርን፣ ሀይማኖትን፣ ብሄርን ወይም ማንኛውንም የማህበረሰብ ክፍል የሚያንቋሽሽ ወይም ጥላቻን የሚያነሳሳ ነገር ከመናገር ተቆጠቡ። ይህ በህግ የሚያስቀጣ ወንጀል መሆኑን አትርሱ።
በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የምታደርጉትን እንቅስቃሴ በጥንቃቄ እንድታደርጉት አሳስባለሁ። ህጉን ማወቅ ከችግር ያድናል!
Mikias Melak AleHig
ጠበቃ እና የህግ አማካሪ
ጤና ይስጥልኝ! ሚኪያስ መላክ ነኝ፣ ጠበቃ እና የህግ አማካሪ።
በማህበራዊ ሚዲያ በተለይም በቲክቶክ ላይ ንቁ ተሳትፎ ለምታደርጉ ሁሉ፣ አሁን የምሰጣችሁን ማስጠንቀቂያ በደንብ እንድትገነዘቡት እጠይቃለሁ። የቅርብ ጊዜዎቹ #ቲክቶከሮች #ጃኒ በትክክለኛው ስሟ ስመኝ ገብሩ እና የሌሎችን ቲክቶከር ጉዳዮችን ስንታዘብ ያየነው እና የተመለከትናቸው ዋነኛ ምሳሌዎች ናቸው። ሁሉም በፖሊስ ተይዘው ወደ ጣቢያ መወሰዳቸው፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች የሕግ ተጠያቂነትን በሚመለከት ሊገነዘቡት የሚገባ ትልቅ ትምህርት ነው። የእናንተ ተፅዕኖ ፈጣሪነት የራሱ የሆነ ኃላፊነት አለበት።
ጥንቃቄ አይለያችሁ!
አንድ ስኬታማ ሰው በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚኖረው እንቅስቃሴ የሚያስከትለው ጉዳት የጎላ ነው። አንድ ተራ ሰው በሰራው ስህተት ጉዳዩ ተራ ሆኖ ሊቀር ቢችልም፣ እንደ ጃኒ ያሉ ብዙ ተከታይ እና አድማጭ ያላችሁ ሰዎች ግን የሚፈጠረው መዘዝ እጅግ ትልቅ ነው። ተጠንቀቁ!
በተለይ "የአፍ ወለምታ" እና መሰል ንግግሮች የሚያስከትሉትን የህግ ተጠያቂነት አቅልላችሁ እንዳትመለከቱ። ያላሰባችሁት ንግግር ከባድ የህግ መዘዝ ሊያስከትል ይችላል።
የሕግ አማካሪ ወይም ቋሚ ጠበቃ ይኑራችሁ!
ይህ በጣም አስፈላጊ ነገር ነው። ስራችሁን እና ንግግራችሁን ከህግ አንፃር ሳንሱር የሚያደርግ እና ከህዝብ ጋር ከመድረሱ በፊት አስፈላጊውን እርምጃ የሚወስድ የህግ አማካሪ ያስፈልጋችኋል። ይህ ከብዙ ችግሮች ሊታደጋችሁ ይችላል። የጃኒ እና በእስር ላይ የሚገኙ ቲክቶከሮች እና ጉዳዮች ይህንን ፍላጎት በግልጽ ያሳያሉ።
#አላውቅም"፣ #ቀልድ ነው"፣ "#እድሜዬ አልደረሰም" - እነዚህ የህግ መከላከያ ሊሆኑ አይችሉም!
ምንም እንኳን ታሳቢ የሚደረጉ ሁኔታዎች ቢኖሩም በወንጀል ሕጉ መሰረት ጉዳዩ የሚታየው በህጉ ላይ በተመለከቱት መደበኛ ድንጋጌዎች መሰረት ነው። ስለዚህ፣ እድሜም ሆነ የትምህርት ደረጃ ለፈጸሙት ወንጀል መከለያ ሊሆን እንደማይችል ልብ ይበሉ።
ማህበረሰብን/ህዝብን/ብሄርን ማጥላላት ወንጀል ነው፣ ያስጠይቃልም!
በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ስትለጥፉ ወይም ስትናገሩ ዘርን፣ ሀይማኖትን፣ ብሄርን ወይም ማንኛውንም የማህበረሰብ ክፍል የሚያንቋሽሽ ወይም ጥላቻን የሚያነሳሳ ነገር ከመናገር ተቆጠቡ። ይህ በህግ የሚያስቀጣ ወንጀል መሆኑን አትርሱ።
በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የምታደርጉትን እንቅስቃሴ በጥንቃቄ እንድታደርጉት አሳስባለሁ። ህጉን ማወቅ ከችግር ያድናል!
Mikias Melak AleHig
ጠበቃ እና የህግ አማካሪ
#የፍርድ_ቤቱን_ውሳኔ_አጥብቄ_የምቃወም_ቢሆንም_እቀበላለሁ ፣ የዚህን ውጤት የመጨረሻነት ተቀብያለሁ ፤ እንደ ህዝብ ለአንድነታችን እና ለዲሞክራሲያችን ጥንካሬ ስል እሺ እላለሁ።"
ይህን ታሪካዊ ንግግር ያደረገው ለ43ኛ የአሜሪካን ሀገር ፕሬዚዳንትነት ከ ጆርጅ ደብልዩ ቡሽ ጋር የተወዳደረው እና በጠቅላይ ፍርድ ቤት ብይን 5 -4 በሆነ ድምጽ የተወሰነበት #አል_ጎር ነበር!
ጉዳዩን እንበልጥጠው!
ፍሎሪዳ በአሜሪካ ካሉ ግዛቶች ውሰጥ የምትገኝ እና በፕሬዝዳንትነት ምርጫ ላይ ሁነኛ ሚና ከሚጫወቱ እና ወሳኝ ከሚባሉ ግዛቶች አንዷ ናት ።
ግዛቷ ውስጥ አንድ ሕግ አለ በከባድ ወንጀል የተፈረደበት እና መሰየም ያልተደረገለት ሰው የመምረጥ መብት ይነፈጋል ።
በምርጫው ጊዜ ከዚህ በፊት ወንጀል ሰርተዋል ተብሎ በ Database ተመዝግቦ የሚገኙ ሰዎች ስም ከሌሎች ወንጀል ካልሰሩ ሰዎች ፤ እንዲሁም ወንጀል ቢሰሩም የመምረጥ መብትን ከማያስከለክሉ ቀላል የወንጀል ዓይነት ከሰሩ ሰዎች ጋር የስም መመሳሰል በመፈጠሩ በግዛቲቱ ወደ 91,000 ሰዎች እንዳይመርጡ ተደርገዋል ።
እነዚህ የስም መመሳሰሎች ደግሞ ጥቁር አሜሪካዊያን እና አል ጎርን ይመርጣሉ ተብሎ የሚጠበቁ ሰዎች እንደሆኑም ይገለጻል ፤ ይህ ውጤት አጠቃላይ የምርጫ ውጤትም ላይ ጥላ አጥልቶ ነበር ፤ ከጠቅላይ ፍርድ ቤት ውሳኔ በኋላ በመካከላቸው የነበረውን ልዩነት እንመልከት
ጆርጅ ደብልዩ ቡሽ 2,912,790
አል ጎር 2,912,253
ልዩነት 537 ድምጽ ብቻ
91,000 ሰው በስም መመሳሰል ባይወገድ እና አል ጎርን ቢመርጥ ወይም አብዛኛው አል ጎርን ቢመርጥ በአሜሪካን ታሪክ አል ጎር 43ኛ ፕሬዚዳንት ይሆን ነበር ።
የስም መመሳሰልን ጉዳይ እናፍታታው ።
በፍሎሪዳ ግዛት ውስጥ ወንጀል ከሰራህ ስምህ ዳታቤዝ ላይ ይመዘገባል ፤ በተለይም ከባድ የሚባሉ ወንጀሎቹን ከሰራህ የመምረጥ መብትህ ይነፈጋል ዳታ ቤዝ ላይ Flagged 🛑 ይደረጋል ።
ለምሳሌ 1.Alex L.Smith (ከባድ ወንጀል የሰራ)
2.Allex A.Smith (ወንጀል ያልሰራ) ግን በስም መመሳሰል ከምርጫ የተወገደ
እንግዲህ በዚህ መልክ ሀቁን ያጣው አል ጎር ፤ ከጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ በኋላ "ምንም ጥርጥር አይኑር፣ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ አጥብቄ ባልስማማም እቀበላለሁ" በማለቱ ይህ ንግግሩ ለፍርድ ቤቱ የሰጠው ቦታን በማመልከት ታሪካዊ ንግግር ሊባል ችሏል ፤ ከግል ምኞቱ በላይ የሀገሪቱን መረጋጋት በማስቀደም ሕገ መንግሥታዊ ቀውስ እንዳይፈጠር ረድቷል ተብሎም ተንቆለጳጵሷል ።
#ወደ_መልዕክቴ_ልምጣ👇
የኢፌዴሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 79 ንዑስ አንቀጽ 2 እና 3 እንደሚከተለው ይነበባል ።
2. በየትኛውም ደረጃ የሚገኝ የዳኝነት አካል ከማንኛውም የመንግሥት አካል፣ከማንኛውም ባለሥልጣን ሆነ ከማንኛውም ሌላ ተጽዕኖ ነጻ ነው፡፡
3. ዳኞች የዳኝነት ተግባራቸውን በሙሉ ነጻነት ያከናውናሉ፡፡ ከሕግ በስተቀር በሌላ ሁኔታ አይመሩም፡፡
ፍርድ ቤቶቻችን ላይ ችግር የለውም ካላችሁ 10 ገጽ የሚሆኑ ችግሮችን ልጽፍላችሁ እችላለሁ የ አስፈጻሚው አካል ጣልቃ ገበነት ፣ ሙስና ፣ የዳኞች ብቃት ማነስ ፣ የዳኞች ክፍያ ማነስ ለስራው ተነሳሽነት እንዲያጡ ማድረግ ፤ በቴክኖሎጂዎች አለመታገዝ..........
ግን ከእነዚህ ሁሉ ችግሮችም ጋር በቻልነው አቅም የፍርድ ቤቱን ገለልተኝነት እናክብር ፤ ፍርድ ቤቶችን ከአስፈጻሚው አካል ከጫና ነጻ እንዲሆኑ እንስራ ፤ በሕግ እና በሕግ ብቻ እንዲመሩ እናበረታታ ፤ ስነ ምግባር የጎደላቸውን ዳኞችን በሕጉ መሰረት እንቅጣ ፤ ፍርድ ቤት የሕዝብ አመኔታ የሚጣልበት ተቋም ስህተት ቢሰራም እንኳን ሕጉ ባስቀመጠው በራሱ ሰንሰለት የሚስተካከልበት ተቋም እንጂ የሕዝብ የጩኸት ምንጭ እንዳይሆን እንተባበር እንጂ የማንም አካል ጣልቃ ገብነትን አንሻት አንመኝ! ምክንያቱም ውጤቱ ከዚህም እጅግ የከፋ ነውና! አበቃሁ!
#ሰላም ✌️
Abebayehu Geta Enaro
መምህር ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
Alternative legal enlightenment & Service
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
https://t.me/AleHig
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#አለሕግ #ህግ #ሰበርመዝገብ #ሕግ_መረጃ #እግድ
ይህን ታሪካዊ ንግግር ያደረገው ለ43ኛ የአሜሪካን ሀገር ፕሬዚዳንትነት ከ ጆርጅ ደብልዩ ቡሽ ጋር የተወዳደረው እና በጠቅላይ ፍርድ ቤት ብይን 5 -4 በሆነ ድምጽ የተወሰነበት #አል_ጎር ነበር!
ጉዳዩን እንበልጥጠው!
ፍሎሪዳ በአሜሪካ ካሉ ግዛቶች ውሰጥ የምትገኝ እና በፕሬዝዳንትነት ምርጫ ላይ ሁነኛ ሚና ከሚጫወቱ እና ወሳኝ ከሚባሉ ግዛቶች አንዷ ናት ።
ግዛቷ ውስጥ አንድ ሕግ አለ በከባድ ወንጀል የተፈረደበት እና መሰየም ያልተደረገለት ሰው የመምረጥ መብት ይነፈጋል ።
በምርጫው ጊዜ ከዚህ በፊት ወንጀል ሰርተዋል ተብሎ በ Database ተመዝግቦ የሚገኙ ሰዎች ስም ከሌሎች ወንጀል ካልሰሩ ሰዎች ፤ እንዲሁም ወንጀል ቢሰሩም የመምረጥ መብትን ከማያስከለክሉ ቀላል የወንጀል ዓይነት ከሰሩ ሰዎች ጋር የስም መመሳሰል በመፈጠሩ በግዛቲቱ ወደ 91,000 ሰዎች እንዳይመርጡ ተደርገዋል ።
እነዚህ የስም መመሳሰሎች ደግሞ ጥቁር አሜሪካዊያን እና አል ጎርን ይመርጣሉ ተብሎ የሚጠበቁ ሰዎች እንደሆኑም ይገለጻል ፤ ይህ ውጤት አጠቃላይ የምርጫ ውጤትም ላይ ጥላ አጥልቶ ነበር ፤ ከጠቅላይ ፍርድ ቤት ውሳኔ በኋላ በመካከላቸው የነበረውን ልዩነት እንመልከት
ጆርጅ ደብልዩ ቡሽ 2,912,790
አል ጎር 2,912,253
ልዩነት 537 ድምጽ ብቻ
91,000 ሰው በስም መመሳሰል ባይወገድ እና አል ጎርን ቢመርጥ ወይም አብዛኛው አል ጎርን ቢመርጥ በአሜሪካን ታሪክ አል ጎር 43ኛ ፕሬዚዳንት ይሆን ነበር ።
የስም መመሳሰልን ጉዳይ እናፍታታው ።
በፍሎሪዳ ግዛት ውስጥ ወንጀል ከሰራህ ስምህ ዳታቤዝ ላይ ይመዘገባል ፤ በተለይም ከባድ የሚባሉ ወንጀሎቹን ከሰራህ የመምረጥ መብትህ ይነፈጋል ዳታ ቤዝ ላይ Flagged 🛑 ይደረጋል ።
ለምሳሌ 1.Alex L.Smith (ከባድ ወንጀል የሰራ)
2.Allex A.Smith (ወንጀል ያልሰራ) ግን በስም መመሳሰል ከምርጫ የተወገደ
እንግዲህ በዚህ መልክ ሀቁን ያጣው አል ጎር ፤ ከጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ በኋላ "ምንም ጥርጥር አይኑር፣ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ አጥብቄ ባልስማማም እቀበላለሁ" በማለቱ ይህ ንግግሩ ለፍርድ ቤቱ የሰጠው ቦታን በማመልከት ታሪካዊ ንግግር ሊባል ችሏል ፤ ከግል ምኞቱ በላይ የሀገሪቱን መረጋጋት በማስቀደም ሕገ መንግሥታዊ ቀውስ እንዳይፈጠር ረድቷል ተብሎም ተንቆለጳጵሷል ።
#ወደ_መልዕክቴ_ልምጣ👇
የኢፌዴሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 79 ንዑስ አንቀጽ 2 እና 3 እንደሚከተለው ይነበባል ።
2. በየትኛውም ደረጃ የሚገኝ የዳኝነት አካል ከማንኛውም የመንግሥት አካል፣ከማንኛውም ባለሥልጣን ሆነ ከማንኛውም ሌላ ተጽዕኖ ነጻ ነው፡፡
3. ዳኞች የዳኝነት ተግባራቸውን በሙሉ ነጻነት ያከናውናሉ፡፡ ከሕግ በስተቀር በሌላ ሁኔታ አይመሩም፡፡
ፍርድ ቤቶቻችን ላይ ችግር የለውም ካላችሁ 10 ገጽ የሚሆኑ ችግሮችን ልጽፍላችሁ እችላለሁ የ አስፈጻሚው አካል ጣልቃ ገበነት ፣ ሙስና ፣ የዳኞች ብቃት ማነስ ፣ የዳኞች ክፍያ ማነስ ለስራው ተነሳሽነት እንዲያጡ ማድረግ ፤ በቴክኖሎጂዎች አለመታገዝ..........
ግን ከእነዚህ ሁሉ ችግሮችም ጋር በቻልነው አቅም የፍርድ ቤቱን ገለልተኝነት እናክብር ፤ ፍርድ ቤቶችን ከአስፈጻሚው አካል ከጫና ነጻ እንዲሆኑ እንስራ ፤ በሕግ እና በሕግ ብቻ እንዲመሩ እናበረታታ ፤ ስነ ምግባር የጎደላቸውን ዳኞችን በሕጉ መሰረት እንቅጣ ፤ ፍርድ ቤት የሕዝብ አመኔታ የሚጣልበት ተቋም ስህተት ቢሰራም እንኳን ሕጉ ባስቀመጠው በራሱ ሰንሰለት የሚስተካከልበት ተቋም እንጂ የሕዝብ የጩኸት ምንጭ እንዳይሆን እንተባበር እንጂ የማንም አካል ጣልቃ ገብነትን አንሻት አንመኝ! ምክንያቱም ውጤቱ ከዚህም እጅግ የከፋ ነውና! አበቃሁ!
#ሰላም ✌️
Abebayehu Geta Enaro
መምህር ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
Alternative legal enlightenment & Service
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
https://t.me/AleHig
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#አለሕግ #ህግ #ሰበርመዝገብ #ሕግ_መረጃ #እግድ