#AddisAbaba #ንግድ
የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ማህበረሰብ ያለወከባ በተረጋጋ መንፈስ የንግድ ተግባሩን ለማከናወን እንዲያስችል ዕድል ይፈጥርለታል የተባለ አዲስ መመሪያ ስራ ላይ መዋሉን ለማወቅ ተችሏል።
አዲሱ መመሪያ " በመንደር ንግድ ቁጥጥር አሰራር ስርዓት መመሪያ 159/2016 " እንደሚባል ከአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
መመሪያው በየትኛው አስተዳደር እርከን የትኛው አይነት እርምጃ እንደሚወሰድ በግልጽ ያስቀመጠ ሲሆን ይህም ሲታይ የነበረውን ግልጽ እና ፍትሃዊ ያልሆነ አሰራር ያስቀራል ተብሏል።
በአዲሱ የመንደር ንግድ መመሪያ መሰረት የወረዳ የንግድ ቁጥጥር ባለሙያ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወስድ ህጉ የሚፈቅድለት በተመደበበት መንደር ላይ ፦
➡ ያለ ንግድ ፍቃድ
➡ ባልታደሰ ፍቃድ
➡ በታገደ አልያም በተሰረዘ ንግድ ፈቃድ የሚነግድ የንግድ ድርጅት ላይ #ብቻ_ነው። ይህን ሲያደርግም ለቅርብ ኃላፊ ማሳወቅ አለበት።
ከዚህ ወጪ ያሉት ጥፋቶች #በሙሉ እርምጃ ሳይወስድ ለቅርብ ኃላፊው በፅሁፍ በማሳወቅ ለውሳኔ ወደ ንግድ ቢሮ መላክ ይጠበቅበታል ፤ የተወሰነውን ውሳኔ የማስፈፀም ኃላፊነትም አለበት።
መመሪያው ፦ https://t.me/tikvahethiopia/87886
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#tikvahethiopia
አማራጭ የሕግ እውቀት
👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/
👉 LinkedIn 👈
https://www.linkedin.com/company/lawsocieties/
👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Ale_Hig
የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ማህበረሰብ ያለወከባ በተረጋጋ መንፈስ የንግድ ተግባሩን ለማከናወን እንዲያስችል ዕድል ይፈጥርለታል የተባለ አዲስ መመሪያ ስራ ላይ መዋሉን ለማወቅ ተችሏል።
አዲሱ መመሪያ " በመንደር ንግድ ቁጥጥር አሰራር ስርዓት መመሪያ 159/2016 " እንደሚባል ከአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
መመሪያው በየትኛው አስተዳደር እርከን የትኛው አይነት እርምጃ እንደሚወሰድ በግልጽ ያስቀመጠ ሲሆን ይህም ሲታይ የነበረውን ግልጽ እና ፍትሃዊ ያልሆነ አሰራር ያስቀራል ተብሏል።
በአዲሱ የመንደር ንግድ መመሪያ መሰረት የወረዳ የንግድ ቁጥጥር ባለሙያ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወስድ ህጉ የሚፈቅድለት በተመደበበት መንደር ላይ ፦
➡ ያለ ንግድ ፍቃድ
➡ ባልታደሰ ፍቃድ
➡ በታገደ አልያም በተሰረዘ ንግድ ፈቃድ የሚነግድ የንግድ ድርጅት ላይ #ብቻ_ነው። ይህን ሲያደርግም ለቅርብ ኃላፊ ማሳወቅ አለበት።
ከዚህ ወጪ ያሉት ጥፋቶች #በሙሉ እርምጃ ሳይወስድ ለቅርብ ኃላፊው በፅሁፍ በማሳወቅ ለውሳኔ ወደ ንግድ ቢሮ መላክ ይጠበቅበታል ፤ የተወሰነውን ውሳኔ የማስፈፀም ኃላፊነትም አለበት።
መመሪያው ፦ https://t.me/tikvahethiopia/87886
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#tikvahethiopia
አማራጭ የሕግ እውቀት
👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/
👉 LinkedIn 👈
https://www.linkedin.com/company/lawsocieties/
👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Ale_Hig
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
#ጉምሩክ
🔴 “ በኢንቮይስም ከፍለን እቃው በገባበት ቀን ነው የምንሰራላችሁ አሉን ” - አስመጪዎች
⚫️ “ በሁሉም ጉዳይ አቤቱታ ይቀርባል አቤቱታ የቀረበበት ሁሉ ተቀባይነት የሚያገኝበት ሁኔታ አይኖርም” - ኮሚሽኑ
ጉምሩክ ኮሚሽን ከማክሮ ኢኮኖሚ ፓሊሲ ጋር በተያያዘ ከዚህ ቀደም ባወጣው አዲስ መመሪያ "ከእጥፍ በላይቀረጥ ክፈሉ'' እየተባሉ መሆኑን አስመጪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው የሚታወስ ሲሆን፤ ኮሚሽኑም ከቅሬታው በኋላ ማሻሻያ ማድረጉን መረጃ ነግረናችሁ ነበር።
ሆኖም ከ150 በላይ የሚሆኑ “ በኢነቮይስ ከፍለናል ” የሚሉ አስመጪዎች፣ ኮሚሽኑ ከማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ትግበራወሰ በኋላ ያወረደውና በአስመጪዎች በኩል “ አዋጅን በደብዳቤ ሽሯል ” በሚል ቅሬታ ቀርቦበት ኮሚሽኑ በድጋሚ ማሻሻያ አደረኩበት ያለው ደብዳቤም ቅሬታቸውን እንዳልፈታላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡
በዚህም እንዲያወያያቸው ጭምር ኮሚሽኑን በደብዳቤ እንደጠቁ ሆኖም ምላሽ እንዳልጠሰጣቸው ገልጸው፤ ጉዳዩን በድጋሚ እንዲያጤነው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳስበዋል።
አስመጪዎች በዝርዝር ያቀረቡት ቅሬታ ምንድን ነው ?
“ ደብዳቤው (ማስተካከያ የተደረገበት) መልስ ስላልሰጠን መልሰን ደብዳቤ ፃፍንላቸው፡፡ ምክንያቱም ከማክሮ ኢኮኖሚው ማሻሻያ በፊት የገቡ እቃዎች እንዲስተካከሉ ተብሎ ብዙዎቹም አውጥተዋል፡፡
የእኛ ጥያቄ፤ ቅድሚያ እቃው ዶኩሜንት እንደደረሰን ጂቡቲ ላይ እንዳለ በኢንቮይስ ዲክላራሲዮን ይቆረጣል። ጂቡቲ ጭነት ሊዘገይ ስለሚችል ፤ በየሳምንቱ ደግሞ ሬት ስለሚቀይር ያንን ነገር እንዳይነካው ሁሉም ነጋዴ ከዚህ በፊት ለዓመታት የሰራው በዚህ አይነት አካሄድ ነው፡፡
እቃው ጂቡቲ እያለ ዶኩሜንቱ ከመጣ በኢንቮይስ ይከፈላል። ቀሪ ሂሳብ ደግሞ ከፍተሻ በኋላ 'ይለቀቅ' ሲባል ያኔ ተከፍሎ ይመጣል፡፡ አሁን ግን በኢንቮይስም ከፍለን 'እቃው በገባበት ቀን ነው የምንሰራላችሁ' አሉን፡፡
እኛ ደግሞ አልተስማማንም፡፡ ጉምሩክ በገባበት ሳይሆን ዶኩሜንት ባስገባንበት፤ ዲክራላሲዮን ባስቆረጥንበት ነው መስተናገድ ያለብን፡፡ 5 ሚሊዮን ስንከፍል የነበርነው 10 ሚሊዮን፣ 10 ሚሊዮን ይከፍል የነበረ 20 ሚሊዮን ብር ከፈሉ እየተባልን ነው፡፡
አሁን ጠዋት አንድ ሬት ከሰዓት ሌላ ሬት አለው ጉምሩክ፤ ድሮ ግን በየሳምንቱ አንድ ሬት ነበረው፡፡ ሐሙስ ቀን የሚቀየር ሬት ብቻ ነበር የሚሰጡት፡፡
ይህ ደግሞ ኪሳራና ተጠቃሚውም ላይ ከፍተኛ ጫና እንደሚጣመጣበት ጉምሩክም ይገነዘባል፡፡ ይህን ነገር ቢያስተካካል ባለው ዋጋ መሸጥ ይቻላል ” ነው ያሉት፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለቀረበው ቅሬታ የኮሚሽኑ ምላሽ ምንድን ነው ? ኮሚሽኑ ባለፈው አደረኩት ባለው ማሻሻያ የአሁኖቹ ቅሬታ አቅራቢዎችን ጉዳይ አካቶ ምላሽ ሰጥቷል? ከሆነ እንዴት ? ሲል ጉምሩክ ኮሚሽኑንን ጠይቋል።
የኮሚሽን ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዘሪሁን አሰፋ ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።
“ ኮሚሽኑ የተለዬ ምላሽ የለውም ከዚያ ጉዳይ ጋር በተያያዘ። የተሰጠው ምላሽ ሁሉንም ጉዳዮች ከቨር ያደረገ ስለሆነ ቀደም ሲል በወጣ ደብዳቤ ምላሽ የተሰጠበት ጉዳይ ነው፡፡
የተለዬ ኮሚሽኑ የሚያየው ጉዳይ የሌለ መሆኑን ነው የማውቀው። ሁሉም ጉዳዮች እዛ ላይ ቴኪኒካሊ ከጉምሩክ አዋጅ አንጻር ታይተው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
አጠቃላይ ነው ባለፈውም አቤቱታ የቀረበው፡፡ ስለዚህ ምላሽ የተሰጠበት አግባብ አለ፡፡ በሁሉም ጉዳይ አቤቱታ ይቀርባል አቤቱታ የቀረበበት ሁሉ ተቀባይነት የሚያገኝበት ሁኔታ አይኖርም፤ ይታወቃል።
'መስተናገድ የለብን በዚህ የሚል ጉዳይ' ካለ ኮሚሽኑ የሰጠውን ምላሽ መቃወም መብት ነው። ተራ ቁጥር 1፣ 2፣ 3፣ 4 በሚሉ ተራ ቁጥሮች ላይ ተገልጿል፡፡
የተቀመጡት ኮንዲሽኖች ጂቡቲ ላሉት እቃዎች፣ አገር ውስጥ ላልገባ እቃ በነባሩ የውጭ ምንዛሪ እንስተናገድ ነው ጥያቄያቸው። ያነም ኮሚሽኑ ደብዳቤው ላይ በገለጸው ልክ (ተራቁጥር አራት ይመስለኛል) በግለጽ የተቀመጠ ጉዳይ ነው።
እነርሱ አቤቱታቸውን መቀጠል ይችላሉ፤ ኮሚሽኑ እኮ ከዚህ አንጻር የከለከለው ነገር የለም፡፡ ስለዚህ የተሰተው ምላሽ ይሄው ነው ከዚያ ውጪ የተለየ የሚሰጥ ምላሽ የለንም በዚያ ደብዳቤ ተመልሶ ያለፈ ጉዳይ ስለሆነ” ብለዋል።
#TikvahethiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴 “ በኢንቮይስም ከፍለን እቃው በገባበት ቀን ነው የምንሰራላችሁ አሉን ” - አስመጪዎች
⚫️ “ በሁሉም ጉዳይ አቤቱታ ይቀርባል አቤቱታ የቀረበበት ሁሉ ተቀባይነት የሚያገኝበት ሁኔታ አይኖርም” - ኮሚሽኑ
ጉምሩክ ኮሚሽን ከማክሮ ኢኮኖሚ ፓሊሲ ጋር በተያያዘ ከዚህ ቀደም ባወጣው አዲስ መመሪያ "ከእጥፍ በላይቀረጥ ክፈሉ'' እየተባሉ መሆኑን አስመጪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው የሚታወስ ሲሆን፤ ኮሚሽኑም ከቅሬታው በኋላ ማሻሻያ ማድረጉን መረጃ ነግረናችሁ ነበር።
ሆኖም ከ150 በላይ የሚሆኑ “ በኢነቮይስ ከፍለናል ” የሚሉ አስመጪዎች፣ ኮሚሽኑ ከማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ትግበራወሰ በኋላ ያወረደውና በአስመጪዎች በኩል “ አዋጅን በደብዳቤ ሽሯል ” በሚል ቅሬታ ቀርቦበት ኮሚሽኑ በድጋሚ ማሻሻያ አደረኩበት ያለው ደብዳቤም ቅሬታቸውን እንዳልፈታላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡
በዚህም እንዲያወያያቸው ጭምር ኮሚሽኑን በደብዳቤ እንደጠቁ ሆኖም ምላሽ እንዳልጠሰጣቸው ገልጸው፤ ጉዳዩን በድጋሚ እንዲያጤነው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳስበዋል።
አስመጪዎች በዝርዝር ያቀረቡት ቅሬታ ምንድን ነው ?
“ ደብዳቤው (ማስተካከያ የተደረገበት) መልስ ስላልሰጠን መልሰን ደብዳቤ ፃፍንላቸው፡፡ ምክንያቱም ከማክሮ ኢኮኖሚው ማሻሻያ በፊት የገቡ እቃዎች እንዲስተካከሉ ተብሎ ብዙዎቹም አውጥተዋል፡፡
የእኛ ጥያቄ፤ ቅድሚያ እቃው ዶኩሜንት እንደደረሰን ጂቡቲ ላይ እንዳለ በኢንቮይስ ዲክላራሲዮን ይቆረጣል። ጂቡቲ ጭነት ሊዘገይ ስለሚችል ፤ በየሳምንቱ ደግሞ ሬት ስለሚቀይር ያንን ነገር እንዳይነካው ሁሉም ነጋዴ ከዚህ በፊት ለዓመታት የሰራው በዚህ አይነት አካሄድ ነው፡፡
እቃው ጂቡቲ እያለ ዶኩሜንቱ ከመጣ በኢንቮይስ ይከፈላል። ቀሪ ሂሳብ ደግሞ ከፍተሻ በኋላ 'ይለቀቅ' ሲባል ያኔ ተከፍሎ ይመጣል፡፡ አሁን ግን በኢንቮይስም ከፍለን 'እቃው በገባበት ቀን ነው የምንሰራላችሁ' አሉን፡፡
እኛ ደግሞ አልተስማማንም፡፡ ጉምሩክ በገባበት ሳይሆን ዶኩሜንት ባስገባንበት፤ ዲክራላሲዮን ባስቆረጥንበት ነው መስተናገድ ያለብን፡፡ 5 ሚሊዮን ስንከፍል የነበርነው 10 ሚሊዮን፣ 10 ሚሊዮን ይከፍል የነበረ 20 ሚሊዮን ብር ከፈሉ እየተባልን ነው፡፡
አሁን ጠዋት አንድ ሬት ከሰዓት ሌላ ሬት አለው ጉምሩክ፤ ድሮ ግን በየሳምንቱ አንድ ሬት ነበረው፡፡ ሐሙስ ቀን የሚቀየር ሬት ብቻ ነበር የሚሰጡት፡፡
ይህ ደግሞ ኪሳራና ተጠቃሚውም ላይ ከፍተኛ ጫና እንደሚጣመጣበት ጉምሩክም ይገነዘባል፡፡ ይህን ነገር ቢያስተካካል ባለው ዋጋ መሸጥ ይቻላል ” ነው ያሉት፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለቀረበው ቅሬታ የኮሚሽኑ ምላሽ ምንድን ነው ? ኮሚሽኑ ባለፈው አደረኩት ባለው ማሻሻያ የአሁኖቹ ቅሬታ አቅራቢዎችን ጉዳይ አካቶ ምላሽ ሰጥቷል? ከሆነ እንዴት ? ሲል ጉምሩክ ኮሚሽኑንን ጠይቋል።
የኮሚሽን ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዘሪሁን አሰፋ ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።
“ ኮሚሽኑ የተለዬ ምላሽ የለውም ከዚያ ጉዳይ ጋር በተያያዘ። የተሰጠው ምላሽ ሁሉንም ጉዳዮች ከቨር ያደረገ ስለሆነ ቀደም ሲል በወጣ ደብዳቤ ምላሽ የተሰጠበት ጉዳይ ነው፡፡
የተለዬ ኮሚሽኑ የሚያየው ጉዳይ የሌለ መሆኑን ነው የማውቀው። ሁሉም ጉዳዮች እዛ ላይ ቴኪኒካሊ ከጉምሩክ አዋጅ አንጻር ታይተው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
አጠቃላይ ነው ባለፈውም አቤቱታ የቀረበው፡፡ ስለዚህ ምላሽ የተሰጠበት አግባብ አለ፡፡ በሁሉም ጉዳይ አቤቱታ ይቀርባል አቤቱታ የቀረበበት ሁሉ ተቀባይነት የሚያገኝበት ሁኔታ አይኖርም፤ ይታወቃል።
'መስተናገድ የለብን በዚህ የሚል ጉዳይ' ካለ ኮሚሽኑ የሰጠውን ምላሽ መቃወም መብት ነው። ተራ ቁጥር 1፣ 2፣ 3፣ 4 በሚሉ ተራ ቁጥሮች ላይ ተገልጿል፡፡
የተቀመጡት ኮንዲሽኖች ጂቡቲ ላሉት እቃዎች፣ አገር ውስጥ ላልገባ እቃ በነባሩ የውጭ ምንዛሪ እንስተናገድ ነው ጥያቄያቸው። ያነም ኮሚሽኑ ደብዳቤው ላይ በገለጸው ልክ (ተራቁጥር አራት ይመስለኛል) በግለጽ የተቀመጠ ጉዳይ ነው።
እነርሱ አቤቱታቸውን መቀጠል ይችላሉ፤ ኮሚሽኑ እኮ ከዚህ አንጻር የከለከለው ነገር የለም፡፡ ስለዚህ የተሰተው ምላሽ ይሄው ነው ከዚያ ውጪ የተለየ የሚሰጥ ምላሽ የለንም በዚያ ደብዳቤ ተመልሶ ያለፈ ጉዳይ ስለሆነ” ብለዋል።
#TikvahethiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔈 #የዜጎችድምጽ
" ወረዳው ከነእቃዬ ሜዳ ላይ ጥሎኝ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ከቤቴ አስገባው " - እንባ የሚተናነቃት ወጣት
በአዲስ አበባ አስተዳደር የካ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ቀበሌ 9/10 የምትገኝ ወጣት ከአሳዳጊ አክስቷ ጋር ትኖርበት ከነበረው የቀበሌ ቤት አሳዳጊዋ ስትሞት ከቤቱ እንድትወጣ ተደርጋ ጎዳና እንደወጣች በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል እሮሮ አሰምታለች።
" ወረዳው ከነእቃዬን ሜዳ ጥሎ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ከቤቴ አስገባው " ብላለች።
ወርቅነሽ አለሙ የምትባለው ይህች ወጣት የአባቷ ታላቅ እህት ከ3 ዓመቷ ጀምሮ ከባህር ዳር ወደ አ/አ አምጥታት ነው ያሳደገቻት።
እዚሁ ቤት እስከ 2016 ዓ/ም ማለቂያ ድረስ ነበሩ።
በ2016 ዓ/ም አሳዳጊ አክስቷ ከሞትች ከ40 ቀናት በኃላ ወረዳው " ወራሽ ልጅ ስላልሆሽ ልቀቂ " ይላታል።
ጉዳዩን ይዛ ፍርድ ቤት ሄደች። ፍርድ ቤትም ሄዳ መፍትሄ አልተሰጣትም።
" ወረዳ እኔን ጠዋት በግብረ ኃይል ከነእቃዬ አውጥቶ ጥሎኝ ከሰዓት በኋላ ራሱ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ቤቴ ውስጥ አስገባው " ስትል ቅሬታ አሰምታለች።
ከዚህ አለፍ ሲል ቤቱ ሁለት ክፍል ሆኖ ሳለ ወደ አራት ክፍል አስፋፍቶ ሰርቶት ዞር ብሎ የጠየቀው አካል የለም ብላለች።
ወረዳው ምን ምላሽ ሰጠ ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታውን ይዞ የወረዳ 6 ጽ/ቤት አስተዳደር ኃላፊ አቶ ምስጋናው ሂጂቱን አነጋግሯል።
ቅሬታዋ አቅራቢዋ ልጅ ከሆነች የመውረስ መብት እንዳላት አምነውበታል።
ኃላፊው ፤ " ባለመብት ናት የቀበሌ ቤት መውረስ የሚችለው ልጅ ነውና ልጅ ከሆነች መውረስ መብቷ ነው " ብለዋል።
" በሕጉ መሠረት የቀበሌ ቤት ፣ ልጅ ከሆነች የመውረስ መብቷ የተጠበቀ ነው ፤ በዚያ ደረጃ ሆኖ ከነበረ እኔ ጋ ይምጡ እናስተካክላለን ይሄ የተነሳው ጉዳይ ትክክል ከሆነ " ሲሉ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ ጉዳይ ተጨማሪ ማብራሪያ እና ግልጽነት ስለሚፈልግ የሕግ ባለሙያ አነጋግሯል።
የሕግ ባለሙያ የሆኑት አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ ምን አሉ ?
- ኑዛዜውን ማጽደቅ ትችላለች። ግን የቀበሌ ቤት ላይ ተወላጆች ካልሆኑ በስተቀር ከሕግ አንጻር በባዮሎጂካል ተወላጅ ያልሆነ ልጅ የጉጂፈቻ ማስረጃ ቀደም ሲል ሊኖር ይገባል።
- ለቀበሌ ቤት የጉዲፈቻ ማስረጃ ስሌላት ውርስ ተቀባዩዋን ከሞራልና ከአስተዳደራዊ አንጻር ካልሆነ በስተቀር ከሕግ አንጻር የወረዳው አስተደዳደር ሊያስተናግዳት አይችልም።
- ከሞራል አንጻር አሳዳጊዋ ስላረፉ፣ ልጅቷ ደግሞ ተተኪ ልጅ ናት፤ በሥነ ልቦና እናትና ልጅ ሆነው አብረው ኖረዋል። የቀበሌ ቤት የሚባለው ደግሞ አነስተኛ ገቢ ያላቸው ሰዎች የሚኖበት ነው። ስለዚህ ከሕግ አንጻር የኑዛዜ ተቀባይ መሆን ባትችልም አንዱ ወጥቶ ሌላው የሚገባበት፣ ለዜጎች የተሰራ ቤት በመሆኑ ልትኖርበት ይገባ ነበር ከሞራል አንጻር።
- ከሕግ አንጻር በቀበሌ ቤት ላይ ኑዛዜ ማድረግ አይቻልም።
- ለምሳሌ የፌደራል ኪራይ ቤቶችን አንድ ሰው ተከራይቶ ቢኖር ሲሞት ሊናዘዝበት አይችልም። ምክንያቱም የንብረቱ ባለቤት መንግስት ነው። በመሳሳይ ሁኔታ የቀበሌ ቤቶች ውስጥ የሚኖር ሰው ሲሞት ኑዛዜ ሊያደርግ አይችልም። ኑዛዜ ማድረጉ በሕግ ውጤት አያመጣም።
- በዜጎች ንብረትና ሕይወት ላይ ውሳኔ የሚሰጡ ሰዎች (ዳኞች) ከወረዳ ጋር በመመሳጠር ክርክር በተነሳበት የመንግስት ቤት ውስጥ መግባት የሕግ ጥሰት ነው። ሕግን ያልተከተለ አካሄድ ነው። በተወሰነ ደረጃ ሙስና ተብሎ ጉዳዩን ወደ ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ብታመለክትበት ዳኛው ከኃላፊነቱ የሚነሳበት ቀጥተኛ ማስረጃ ነው የሚሆነው።
- ክርክር በተነሳበት ጉዳይ ላይ የጥቅም ግንኙነት በመፍጠር እንዲህ ማድረግ ትልቅ የዲሲፒሊን ጥፋት ነው።
- ልጅቷ ቅጹ ላይ አለች፣ ደባል ናት፣ የቤተሰብ አባል ናት ቀጥተኛ ልጅ ባትሆንም፣ የቀበሌ ቤቶች ደግሞ አነስተኛ ገቢ ላላቸው ሰዎቸ ነው የተዘጋጁት፣ ሜዳ ላይ መጣል የለባትም ብሎ የወረዳው አስተዳደር ወስኖ ወይ በዚያው ቤት ሊያስቀጥላት ይገባል የቀበሌ ቤቱ የሚፈርስ ከሆነም ምትክ የመንግስት ቤት እንድታገኝ ሁኔታዎችን ማመቻቸት አለበት።
- በህሊና ፍርድ ወይ አስተዳደራዊ በሆነ መንገድ የወረዳው አስተዳደር መፍትሄ ሊሰጣት ይገባል።
ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-08
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ወረዳው ከነእቃዬ ሜዳ ላይ ጥሎኝ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ከቤቴ አስገባው " - እንባ የሚተናነቃት ወጣት
በአዲስ አበባ አስተዳደር የካ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ቀበሌ 9/10 የምትገኝ ወጣት ከአሳዳጊ አክስቷ ጋር ትኖርበት ከነበረው የቀበሌ ቤት አሳዳጊዋ ስትሞት ከቤቱ እንድትወጣ ተደርጋ ጎዳና እንደወጣች በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል እሮሮ አሰምታለች።
" ወረዳው ከነእቃዬን ሜዳ ጥሎ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ከቤቴ አስገባው " ብላለች።
ወርቅነሽ አለሙ የምትባለው ይህች ወጣት የአባቷ ታላቅ እህት ከ3 ዓመቷ ጀምሮ ከባህር ዳር ወደ አ/አ አምጥታት ነው ያሳደገቻት።
እዚሁ ቤት እስከ 2016 ዓ/ም ማለቂያ ድረስ ነበሩ።
በ2016 ዓ/ም አሳዳጊ አክስቷ ከሞትች ከ40 ቀናት በኃላ ወረዳው " ወራሽ ልጅ ስላልሆሽ ልቀቂ " ይላታል።
ጉዳዩን ይዛ ፍርድ ቤት ሄደች። ፍርድ ቤትም ሄዳ መፍትሄ አልተሰጣትም።
" ወረዳ እኔን ጠዋት በግብረ ኃይል ከነእቃዬ አውጥቶ ጥሎኝ ከሰዓት በኋላ ራሱ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ቤቴ ውስጥ አስገባው " ስትል ቅሬታ አሰምታለች።
ከዚህ አለፍ ሲል ቤቱ ሁለት ክፍል ሆኖ ሳለ ወደ አራት ክፍል አስፋፍቶ ሰርቶት ዞር ብሎ የጠየቀው አካል የለም ብላለች።
ወረዳው ምን ምላሽ ሰጠ ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታውን ይዞ የወረዳ 6 ጽ/ቤት አስተዳደር ኃላፊ አቶ ምስጋናው ሂጂቱን አነጋግሯል።
ቅሬታዋ አቅራቢዋ ልጅ ከሆነች የመውረስ መብት እንዳላት አምነውበታል።
ኃላፊው ፤ " ባለመብት ናት የቀበሌ ቤት መውረስ የሚችለው ልጅ ነውና ልጅ ከሆነች መውረስ መብቷ ነው " ብለዋል።
" በሕጉ መሠረት የቀበሌ ቤት ፣ ልጅ ከሆነች የመውረስ መብቷ የተጠበቀ ነው ፤ በዚያ ደረጃ ሆኖ ከነበረ እኔ ጋ ይምጡ እናስተካክላለን ይሄ የተነሳው ጉዳይ ትክክል ከሆነ " ሲሉ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ ጉዳይ ተጨማሪ ማብራሪያ እና ግልጽነት ስለሚፈልግ የሕግ ባለሙያ አነጋግሯል።
የሕግ ባለሙያ የሆኑት አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ ምን አሉ ?
- ኑዛዜውን ማጽደቅ ትችላለች። ግን የቀበሌ ቤት ላይ ተወላጆች ካልሆኑ በስተቀር ከሕግ አንጻር በባዮሎጂካል ተወላጅ ያልሆነ ልጅ የጉጂፈቻ ማስረጃ ቀደም ሲል ሊኖር ይገባል።
- ለቀበሌ ቤት የጉዲፈቻ ማስረጃ ስሌላት ውርስ ተቀባዩዋን ከሞራልና ከአስተዳደራዊ አንጻር ካልሆነ በስተቀር ከሕግ አንጻር የወረዳው አስተደዳደር ሊያስተናግዳት አይችልም።
- ከሞራል አንጻር አሳዳጊዋ ስላረፉ፣ ልጅቷ ደግሞ ተተኪ ልጅ ናት፤ በሥነ ልቦና እናትና ልጅ ሆነው አብረው ኖረዋል። የቀበሌ ቤት የሚባለው ደግሞ አነስተኛ ገቢ ያላቸው ሰዎች የሚኖበት ነው። ስለዚህ ከሕግ አንጻር የኑዛዜ ተቀባይ መሆን ባትችልም አንዱ ወጥቶ ሌላው የሚገባበት፣ ለዜጎች የተሰራ ቤት በመሆኑ ልትኖርበት ይገባ ነበር ከሞራል አንጻር።
- ከሕግ አንጻር በቀበሌ ቤት ላይ ኑዛዜ ማድረግ አይቻልም።
- ለምሳሌ የፌደራል ኪራይ ቤቶችን አንድ ሰው ተከራይቶ ቢኖር ሲሞት ሊናዘዝበት አይችልም። ምክንያቱም የንብረቱ ባለቤት መንግስት ነው። በመሳሳይ ሁኔታ የቀበሌ ቤቶች ውስጥ የሚኖር ሰው ሲሞት ኑዛዜ ሊያደርግ አይችልም። ኑዛዜ ማድረጉ በሕግ ውጤት አያመጣም።
- በዜጎች ንብረትና ሕይወት ላይ ውሳኔ የሚሰጡ ሰዎች (ዳኞች) ከወረዳ ጋር በመመሳጠር ክርክር በተነሳበት የመንግስት ቤት ውስጥ መግባት የሕግ ጥሰት ነው። ሕግን ያልተከተለ አካሄድ ነው። በተወሰነ ደረጃ ሙስና ተብሎ ጉዳዩን ወደ ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ብታመለክትበት ዳኛው ከኃላፊነቱ የሚነሳበት ቀጥተኛ ማስረጃ ነው የሚሆነው።
- ክርክር በተነሳበት ጉዳይ ላይ የጥቅም ግንኙነት በመፍጠር እንዲህ ማድረግ ትልቅ የዲሲፒሊን ጥፋት ነው።
- ልጅቷ ቅጹ ላይ አለች፣ ደባል ናት፣ የቤተሰብ አባል ናት ቀጥተኛ ልጅ ባትሆንም፣ የቀበሌ ቤቶች ደግሞ አነስተኛ ገቢ ላላቸው ሰዎቸ ነው የተዘጋጁት፣ ሜዳ ላይ መጣል የለባትም ብሎ የወረዳው አስተዳደር ወስኖ ወይ በዚያው ቤት ሊያስቀጥላት ይገባል የቀበሌ ቤቱ የሚፈርስ ከሆነም ምትክ የመንግስት ቤት እንድታገኝ ሁኔታዎችን ማመቻቸት አለበት።
- በህሊና ፍርድ ወይ አስተዳደራዊ በሆነ መንገድ የወረዳው አስተዳደር መፍትሄ ሊሰጣት ይገባል።
ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-08
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" በስም ከተለዩት ግለሰቦች መካከል ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ዜጎችም ይገኙበታል " -የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ከ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ ዕዳ ያለባቸው 62 ግብር ከፋዮች ከሀገር እንዳይወጡ የእግድ ትዕዛዝ ማስተላለፉን ገልጿል፡፡
እግድ የተጣለባቸው 62 ግለሰቦች በተደጋጋሚ ጥሪ ቢደረግላቸውም ዕዳቸውን ለመክፈል ፈቃደኛ ያልሆኑ ናቸው ተብሏል።
" በስም ከተለዩት ግለሰቦች መካከል ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ዜጎችም ይገኙበታል ዕዳቸውን የማይከፍሉ ከሆነም አዋጁ በሰጠን ሥልጣን መሰረትም በቀጣይ የንብረት እግድ እና ንብረታቸውን በሃራጅ የመሸጥ እርምጃዎች ይወሰዳሉ " ሲሉ የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቢሮው በታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008 አንቀፅ 44 ንዑስ አንቀፅ ከ1-3 ለተቋሙ በተሰጠ ስልጣን መሰረት ከሀገር እንዳይወጡ እግድ የተጣለባቸው ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለፌዴራል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ማስተላለፉን አሳውቋል፡፡
የ62ቱ ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለፌዴራል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የተላከው በትላንትናው ዕለት ነው።
አቶ ሰውነት " በህጉ መሰረት የተቀመጠ ቀነ ገደብ አለ በአዋጁ በተቀመጠው ቀነ ገደብ መሰረት መጥተው እስካልከፈሉ ድረስ ለእዳው ማካካሻ በሚሆን መሰረት ንብረታቸው በሃራጅ ተሽጦ እዳው ይሸፈናል " ብለዋል።
ቢሮው የግብር ዕዳቸውን ሳይወጡ የሚሰወሩ ግብር ከፋዮችን በመከታተል ግዴታቸውን እንዲወጡ ለማስቻል የዕዳ ክትትልና አስተዳደር የስራ ክፍልን በ2017 በጀት ዓመት እንደ አዲስ አዋቅሯል።
በዚህም መሰረት ባለፉት 6 ወራት ከ 6.4 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ እዳ መሰብሰቡን አቶ ሰውነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#tikvahethiopia
Welcome to Mikias Melak & Associates Law Office!
🔹 Facebook: AlehigOfficial
🔹 Telegram Channel: AleHig
🔹 Website: alehig.com
📧 Email: mikiasmelak.mm@gmail.com
📞 Direct Contact:
✅ WhatsApp: +251920666595
✅ Telegram: @MikiasMelak
For legal consultations and inquiries, feel free to reach out. We’ll get back to you as soon as possible!
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ከ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ ዕዳ ያለባቸው 62 ግብር ከፋዮች ከሀገር እንዳይወጡ የእግድ ትዕዛዝ ማስተላለፉን ገልጿል፡፡
እግድ የተጣለባቸው 62 ግለሰቦች በተደጋጋሚ ጥሪ ቢደረግላቸውም ዕዳቸውን ለመክፈል ፈቃደኛ ያልሆኑ ናቸው ተብሏል።
" በስም ከተለዩት ግለሰቦች መካከል ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ዜጎችም ይገኙበታል ዕዳቸውን የማይከፍሉ ከሆነም አዋጁ በሰጠን ሥልጣን መሰረትም በቀጣይ የንብረት እግድ እና ንብረታቸውን በሃራጅ የመሸጥ እርምጃዎች ይወሰዳሉ " ሲሉ የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቢሮው በታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008 አንቀፅ 44 ንዑስ አንቀፅ ከ1-3 ለተቋሙ በተሰጠ ስልጣን መሰረት ከሀገር እንዳይወጡ እግድ የተጣለባቸው ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለፌዴራል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ማስተላለፉን አሳውቋል፡፡
የ62ቱ ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለፌዴራል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የተላከው በትላንትናው ዕለት ነው።
አቶ ሰውነት " በህጉ መሰረት የተቀመጠ ቀነ ገደብ አለ በአዋጁ በተቀመጠው ቀነ ገደብ መሰረት መጥተው እስካልከፈሉ ድረስ ለእዳው ማካካሻ በሚሆን መሰረት ንብረታቸው በሃራጅ ተሽጦ እዳው ይሸፈናል " ብለዋል።
ቢሮው የግብር ዕዳቸውን ሳይወጡ የሚሰወሩ ግብር ከፋዮችን በመከታተል ግዴታቸውን እንዲወጡ ለማስቻል የዕዳ ክትትልና አስተዳደር የስራ ክፍልን በ2017 በጀት ዓመት እንደ አዲስ አዋቅሯል።
በዚህም መሰረት ባለፉት 6 ወራት ከ 6.4 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ እዳ መሰብሰቡን አቶ ሰውነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#tikvahethiopia
Welcome to Mikias Melak & Associates Law Office!
🔹 Facebook: AlehigOfficial
🔹 Telegram Channel: AleHig
🔹 Website: alehig.com
📧 Email: mikiasmelak.mm@gmail.com
📞 Direct Contact:
✅ WhatsApp: +251920666595
✅ Telegram: @MikiasMelak
For legal consultations and inquiries, feel free to reach out. We’ll get back to you as soon as possible!
" አስተማሪ ተማሪውን የመምታት መብት የለውም በተማሪዋ ላይ ያደረሰችው ቅጣት ቀላልም ቢሆን እንኳ የአካል ጉዳት በማድረስ በህግ ያስጠይቃታል " - የህግ ባለሙያ
" የቤት ስራ አልሰራሽም " በማለት የሁለተኛ ክፍል ተማሪዋን ተገቢ ያልሆነና አጸያፊ የሆነ ቅጣት የቀጣችው መምህርት ከስራ ታግዳ በህግ ቁጥጥር ስር መደረጓ መገለፁ ይታወሳል።
በመሆኑም መምህርቷ በተማሪዋ ላይ የወሰደችው እርምጃ በህገመንግስቱ አንደት ይታያል ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ጠይቋል።
የህግ አማካሪና ጠበቃ ሳሙኤል ግርማ መምህርቷ የወሰደችው እርምጃ " ቀላል የአካል ጉዳት በማድረስ በወንጀል ህጉ 5/ 35 እስከ 3 አመት ፅኑ እስራት ቅጣት " ሊጠብቃት አንደሚችል ተናግረዋል።
የህግ ባለሙያው ምን አሉ ?
" አስተማሪ ተማሪውን የመምታት መብት የለውም በተማሪዋ ላይ ያደረሰችው ቅጣት ቀላልም ቢሆን እንኳ የአካል ጉዳት በማድረስ በህግ ያስጠይቃታል፣ በወንጀል ህጉ ደግሞ 5/ 35 እስከ 3 አመት ያሳስራል፣ ይህ ድርጊት ግን ከዚህም ባለፈ ነው የሚታየው " ብለዋል።
አክለውም " በአስተማሪ የዲስፕሊን መመሪያ በአስተዳደራዊ እርምጃ ከስራዋ ልትሰናበት የሚያስችል ወንጀል ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
የህግ ባለሙያው " መምህሯ ቅጣት ያደረሰችባት ተማሪ ከ13 አመት በታች ታዳጊ ከሆነች ይሄ ተገቢ ያልሆነ እና በወንጀል የሚያስጠይቅ ግልፅ የሆነ ጉዳይ ነው " ሲሉ አስረድተዋል።
" መምህሯ ተማሪዋን የመታችበት መሳሪያ ወይም ቁስ የቅጣቱን መጠን ይወስነዋል " ያሉ ሲሆን በእንጨት፣ በድንጋይ እና በመሳሰሉት ሆኖ በልጅቷ አካል ላይ መፋፋቅ፣ መድማት የአጥንት መሰበር አይነት ጉዳት ከሆነ ያደረሰችባት ከዚህም ከፍ ያለ ቅጣት ሊጠብቃት እንደሚችል ጠቁመዋል።
በተለይም መምህር፣ ሹፌር እና ሀኪሞች በስራ ያገኟቸውን ሰዎች የበለጠ የመጠበቅ ሃላፊነት አለባቸው። ይሄም እንደ ወንጀል ማክበጃ ይታያል ብለዋል።
የህግ ባለሙያው ሳሙኤል ይሄ ጉዳይ ይፋ መደረጉ እና በመምህርቷ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ለሌሎች አስተማሪዎች መማሪያ የሚሆን ነው ሲሉ ገልጸዋል።
" በመጨረሻም አሁን ላይ ተማሪዎችን አንደድሮው አይነት ቅጣቶች መቅጣት አይቻልም፣ ምክንያቱም ከህፃናት መብት ጋር የሚጣረስ ነው " ሲሉ አመላክተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" የቤት ስራ አልሰራሽም " በማለት የሁለተኛ ክፍል ተማሪዋን ተገቢ ያልሆነና አጸያፊ የሆነ ቅጣት የቀጣችው መምህርት ከስራ ታግዳ በህግ ቁጥጥር ስር መደረጓ መገለፁ ይታወሳል።
በመሆኑም መምህርቷ በተማሪዋ ላይ የወሰደችው እርምጃ በህገመንግስቱ አንደት ይታያል ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ጠይቋል።
የህግ አማካሪና ጠበቃ ሳሙኤል ግርማ መምህርቷ የወሰደችው እርምጃ " ቀላል የአካል ጉዳት በማድረስ በወንጀል ህጉ 5/ 35 እስከ 3 አመት ፅኑ እስራት ቅጣት " ሊጠብቃት አንደሚችል ተናግረዋል።
የህግ ባለሙያው ምን አሉ ?
" አስተማሪ ተማሪውን የመምታት መብት የለውም በተማሪዋ ላይ ያደረሰችው ቅጣት ቀላልም ቢሆን እንኳ የአካል ጉዳት በማድረስ በህግ ያስጠይቃታል፣ በወንጀል ህጉ ደግሞ 5/ 35 እስከ 3 አመት ያሳስራል፣ ይህ ድርጊት ግን ከዚህም ባለፈ ነው የሚታየው " ብለዋል።
አክለውም " በአስተማሪ የዲስፕሊን መመሪያ በአስተዳደራዊ እርምጃ ከስራዋ ልትሰናበት የሚያስችል ወንጀል ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
የህግ ባለሙያው " መምህሯ ቅጣት ያደረሰችባት ተማሪ ከ13 አመት በታች ታዳጊ ከሆነች ይሄ ተገቢ ያልሆነ እና በወንጀል የሚያስጠይቅ ግልፅ የሆነ ጉዳይ ነው " ሲሉ አስረድተዋል።
" መምህሯ ተማሪዋን የመታችበት መሳሪያ ወይም ቁስ የቅጣቱን መጠን ይወስነዋል " ያሉ ሲሆን በእንጨት፣ በድንጋይ እና በመሳሰሉት ሆኖ በልጅቷ አካል ላይ መፋፋቅ፣ መድማት የአጥንት መሰበር አይነት ጉዳት ከሆነ ያደረሰችባት ከዚህም ከፍ ያለ ቅጣት ሊጠብቃት እንደሚችል ጠቁመዋል።
በተለይም መምህር፣ ሹፌር እና ሀኪሞች በስራ ያገኟቸውን ሰዎች የበለጠ የመጠበቅ ሃላፊነት አለባቸው። ይሄም እንደ ወንጀል ማክበጃ ይታያል ብለዋል።
የህግ ባለሙያው ሳሙኤል ይሄ ጉዳይ ይፋ መደረጉ እና በመምህርቷ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ለሌሎች አስተማሪዎች መማሪያ የሚሆን ነው ሲሉ ገልጸዋል።
" በመጨረሻም አሁን ላይ ተማሪዎችን አንደድሮው አይነት ቅጣቶች መቅጣት አይቻልም፣ ምክንያቱም ከህፃናት መብት ጋር የሚጣረስ ነው " ሲሉ አመላክተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ በህግ የሚገደዱ ግብር ከፋዮች ከመጪው ሀምሌ የግብር ማሳወቂያ ወር ጀምሮ የተሟላ የሂሳብ መዝገብ በመያዝ ካልመጡ በስተቀር አይስተናገዱም "- የገቢዎች ቢሮ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ከመጪው ዓመታዊ የግብር ማሳወቂያ ወር ጀምሮ የደረጃ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋይ ሆነው በህግ የሚገደዱ ግብር ከፋዮች ያለ ሂሳብ መዝገብ የማይስተናገዱ መሆኑን አሳውቋል።
አይስተናገዱም የተባሉት በደረጃ "ሀ" እና "ለ" የግብር ከፋይነት የተመዝገቡ እና በህጉ መሰረት የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ የሚገደዱትን ብቻ ነው።
የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደተናገሩት በህጉ መሰረት የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ የሚገደዱ ነጋዴዎች ከሚቀጥለው በጀት አመት በኋላ ግብር ለመክፈል ያላቸውን አጠቃላይ ወጪ እና ገቢያቸውን በዝርዝር የሚያሳይ መዝገብ መያዝ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
አቶ ሰውነት አየለ በዝርዝር ምን አሉ ?
" የሂሳብ መዝገብ ማለት ያላቸውን አጠቃላይ ሽያጭ እና ወጪ በዝርዝር የሚያሳይ ሰነድ/መዝገብ ነው።
ህጋዊ የሆነ ግብይት የሚፈጸም ከሆነ እና በደረሰኝ ላይ የተመሰረተ ግብይት ካለ ከዚህ መዝገብ ጋር ተያይዞ ነው የሚቀርበው።
ይህ ህግ ከወጣ ረጅም ጊዜ ነው ነገር ግን አፈጻጸም ላይ የተለያዩ ክፍተቶች በመኖራቸው በቁርጥ ግብር የሚስተናገዱ ነበሩ።
ለእነዚህ ግብር ከፋዮች በተለያየ መንገድ መረጃዎችን እያደረስን ነው ያለነው ከሚቀጥለው በጀት አመት በኋላ ከዚህ ሂሳብ መዝገብ ውጪ እንደማናስተናግዳቸው እንዲያውቁ እያደረግን ነው።
ግብይቶቻቸውን በደረሰኝ ላይ ተመስርተው ፈጽመው በሂሳብ ባለሙያ አልያም የድርጅታቸው ተቀጣሪ በሆነ የሂሳብ ባለሙያ የተዘጋጀ የሂሳብ መዝገብ ማቅረብ አለባቸው።
ግብር ከፋዮች ከግምት የጸዳ የግብር አሰባሰብ ስርዓት የራሳቸውን ሚና እንዲጫወቱ ለማስቻል ይህንን የማሳወቅ ስራ እየሰራን ነው።
በደረጃ "ሀ" እና "ለ" ከ120 ሺ በላይ ግብር ከፋዮች አሉ ከእነዚህ ውስጥ ገቢ እና ወጪያቸውን በአግባቡ እየመዘገቡ ፣ደረሰኝ እየቆረጡ አመታዊ ግብራቸውን የሚያሳውቁ አሉ ነገር ግን ከዚህ ውጪ ሲስተናገዱ የቆዩ ግብር ከፋዮቾም ነበሩ።
ይህ አሰራር ተለምዶ ከአመት አመት ዝም ብሎ በቁርጥ ግብር ለመስተናገድ የመፈለግ አዝማሚያ ይታያል ህጉ ግን ይህንን አሰራር የማይፈቅድ በመሆኑ ከመጪው ሐምሌ ወር ጀምሮ ሲመጡ በተሟላ መንገድ ሂሳብ መዝገባቸውን ይዘው ካልመጡ በስተቀር አይስተናገዱም።
መያዝ አለባቸው እያልን ያለነው በደረጃ "ሀ" እና "ለ" የግብር ከፋይ ተመዝግበው በህጉ መሰረት የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ የሚገደዱትን ብቻ ነው።
ሁሉንም ማለት አይደለም በተሰማሩበት የንግድ ዘርፋቸው ምክንያት እዚህ ውስጥ የማይካተቱ ይኖራሉ የሚመለከተው የተሰማሩበት የስራ ዘርፍ የሂሳብ መዝገብ መያዝ እያስገደዳቸው በተለያየ ምክንያት የማይዙትን እና በቁርጥ ግብር ሲስተናገዱ የነበሩ የንግዱን ማህበረሰብ ነው።
ይህ አይነቱ አሰራር ግብር በዛብኝ በማለት ለሚቀርቡ ቅሬታዎች መፍትሄ የሚሆን ነው " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ከመጪው ዓመታዊ የግብር ማሳወቂያ ወር ጀምሮ የደረጃ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋይ ሆነው በህግ የሚገደዱ ግብር ከፋዮች ያለ ሂሳብ መዝገብ የማይስተናገዱ መሆኑን አሳውቋል።
አይስተናገዱም የተባሉት በደረጃ "ሀ" እና "ለ" የግብር ከፋይነት የተመዝገቡ እና በህጉ መሰረት የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ የሚገደዱትን ብቻ ነው።
የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደተናገሩት በህጉ መሰረት የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ የሚገደዱ ነጋዴዎች ከሚቀጥለው በጀት አመት በኋላ ግብር ለመክፈል ያላቸውን አጠቃላይ ወጪ እና ገቢያቸውን በዝርዝር የሚያሳይ መዝገብ መያዝ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
አቶ ሰውነት አየለ በዝርዝር ምን አሉ ?
" የሂሳብ መዝገብ ማለት ያላቸውን አጠቃላይ ሽያጭ እና ወጪ በዝርዝር የሚያሳይ ሰነድ/መዝገብ ነው።
ህጋዊ የሆነ ግብይት የሚፈጸም ከሆነ እና በደረሰኝ ላይ የተመሰረተ ግብይት ካለ ከዚህ መዝገብ ጋር ተያይዞ ነው የሚቀርበው።
ይህ ህግ ከወጣ ረጅም ጊዜ ነው ነገር ግን አፈጻጸም ላይ የተለያዩ ክፍተቶች በመኖራቸው በቁርጥ ግብር የሚስተናገዱ ነበሩ።
ለእነዚህ ግብር ከፋዮች በተለያየ መንገድ መረጃዎችን እያደረስን ነው ያለነው ከሚቀጥለው በጀት አመት በኋላ ከዚህ ሂሳብ መዝገብ ውጪ እንደማናስተናግዳቸው እንዲያውቁ እያደረግን ነው።
ግብይቶቻቸውን በደረሰኝ ላይ ተመስርተው ፈጽመው በሂሳብ ባለሙያ አልያም የድርጅታቸው ተቀጣሪ በሆነ የሂሳብ ባለሙያ የተዘጋጀ የሂሳብ መዝገብ ማቅረብ አለባቸው።
ግብር ከፋዮች ከግምት የጸዳ የግብር አሰባሰብ ስርዓት የራሳቸውን ሚና እንዲጫወቱ ለማስቻል ይህንን የማሳወቅ ስራ እየሰራን ነው።
በደረጃ "ሀ" እና "ለ" ከ120 ሺ በላይ ግብር ከፋዮች አሉ ከእነዚህ ውስጥ ገቢ እና ወጪያቸውን በአግባቡ እየመዘገቡ ፣ደረሰኝ እየቆረጡ አመታዊ ግብራቸውን የሚያሳውቁ አሉ ነገር ግን ከዚህ ውጪ ሲስተናገዱ የቆዩ ግብር ከፋዮቾም ነበሩ።
ይህ አሰራር ተለምዶ ከአመት አመት ዝም ብሎ በቁርጥ ግብር ለመስተናገድ የመፈለግ አዝማሚያ ይታያል ህጉ ግን ይህንን አሰራር የማይፈቅድ በመሆኑ ከመጪው ሐምሌ ወር ጀምሮ ሲመጡ በተሟላ መንገድ ሂሳብ መዝገባቸውን ይዘው ካልመጡ በስተቀር አይስተናገዱም።
መያዝ አለባቸው እያልን ያለነው በደረጃ "ሀ" እና "ለ" የግብር ከፋይ ተመዝግበው በህጉ መሰረት የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ የሚገደዱትን ብቻ ነው።
ሁሉንም ማለት አይደለም በተሰማሩበት የንግድ ዘርፋቸው ምክንያት እዚህ ውስጥ የማይካተቱ ይኖራሉ የሚመለከተው የተሰማሩበት የስራ ዘርፍ የሂሳብ መዝገብ መያዝ እያስገደዳቸው በተለያየ ምክንያት የማይዙትን እና በቁርጥ ግብር ሲስተናገዱ የነበሩ የንግዱን ማህበረሰብ ነው።
ይህ አይነቱ አሰራር ግብር በዛብኝ በማለት ለሚቀርቡ ቅሬታዎች መፍትሄ የሚሆን ነው " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በጅቡቲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ህጋዊ መኖሪያ ማግኘት ያልቻሉበት ምክንያት ምንድነው ?
የጅቡቲ መንግስት ሰነድ አልባ ስደተኞች በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በፈቃዳቸው ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ካወጀ ሰነባብቷል፡፡ የተሰጠው ቀነገደብ በመጠናቀቁም መጠነ ሰፊ አፈሳ እንደሚጀምር አውጇል፡፡
በዚያች ሀገር የሚኖሩ ሰነድ አልባ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በበኩላቸው፣ ሀብት ንብረታችንን ሸጠን የምንወጣበት ጊዜ ይስጠን እያሉ ይማፀናሉ፡፡ ለዚህም ቀነገደቡ እንዲራመዝላቸው ይፈልጋሉ፡፡
ለመሆኑ እነዚህ ሰነድ አልባ ኢትዮጵያውያን (ቁጥራቸው በትንሹ ከ200 ሺህ በላይ ይገመታል) ለምን እስካሁን ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ መያዝ አልቻሉም፡፡
ይህን ጥያቄ ያነሳንላቸው ስማችን አይጠቀስ ያሉ ሶስት ስደተኞች፣ ሕጋዊ ለመሆን ስላለው ሁኔታ የሚከተለውን ሀሳብ ሰጥተዋል፡፡
ሕጋዊ ለመሆን ያለው ችግር ምንድነው ?
" ሁሉም ሰው ህጋዊ መሆን ይፈልጋል፡፡ ችግሩ የገንዘቡ መብዛት ነው፡፡ ሒደቱም ረጅም የድለላ ሰንሰለትን የሚያልፍ እና በእጅጉ ረዥም፣ አድካሚና ውስብስብ ነው፡፡ የአንድ ሰው የአመት ገቢ እንኳ አይበቃም፡፡
ህጋዊ ለመሆን ለጅቡቲ መንግስት የሚከፈለው ገንዘብ አንድ አመት ሙሉ ሰርቶ ማጠራቀም አይቻልም፡፡ የዚህ ሀገር ህጋዊ መሆኛ አሰራር ለድሀና ለስደተኛ የሚመጥን አይደለም፡፡ እንኳን ግለሰብ ቀርቶ፣ ድርጅቶችም አይችሉትም፡፡
የንግድ ድርጅቶች ለሰራተኞቻቸው ህጋዊ የስራ ፈቃድ ለማውጣት፣ እስከ 200 ሺህ ፍራንክ (160 ሺህ ብር ገደማ) ይጠየቃሉ፤ ለአንድ ሰራተኛ፡፡ ለግለሰብ ደግሞ እስከ 70 ሺህ ፍራንክ ይደርሳል በህጋዊው መንገድ፡፡ ግን አብዛኛውን ጊዜ ህጋዊው አካሔድ ስለማይገኝ በደላሎች በኩል እስከ 120 ሺህ ፍራንክ ትጠየቃለህ፡፡ አሁን በቅርቡ 120 ሺህ ፍራንክ ከፍለው ያወጡ ሰዎች አሉ፡፡ አንዳንዴም ከ150 ሺህ እስከ 200 ሺህ ብር ያስወጣሀል፡፡ ይህን ያህል ከፍለህ የምታገኘው የመኖሪያ ፈቃድ፣ ተሰጠህ ሳይሆን ገዛህ ነው ሊባል የሚችለው፡፡ አንዴ ከፍለህ የሚያበቃ ነገር ደግሞ አይደለም፡፡ በየአመቱ ከ 20 ሺህ እስከ 30 ሺህ ፍራንክ እየከፈልክ ታሳድሳለህ ፈቃድህን፡፡
እንደ ሌሎች ሀገራት ብዙ አመት ከቆየህ በኋላ ህጋዊ ነዋሪ አትሆንም፡፡ ሁሌም ጊዜያዊ ነዋሪ እየተባልክ በየአመቱ ፈቃድህን እያደስክ ትኖራለህ፡፡ የቋሚ ነዋሪነት መታወቂያ አይሰጡህም፡፡ ይህ ችግር አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ስደተኛ፣ ሰነድ አልባ ሆኖ በስጋት ውስጥ እንዲኖር አስገድዶታል፡፡
ህጋዊ ሰነድ ለማግኘት ደግሞ ፓስፖርትህ ላይ ቪዛ መመታት አለበት ይሉሀል፡፡ ይህን ቪዛ ለማስመታት ከጅቡቲ ትወጣና እንደገና መግባት አለብህ፣ ቪዛ ለማግኘት የግድ ከጅቡቲ መውጣት አለብህ በየአመቱ፡፡ ተመልሰህ ስትገባ ኤርፖርት ቪዛ ይሰጠሀል፡፡ አዲስ አበባ እና ድሬዳዋም ይመታልሀል፡፡ ግን ቅድመ ሁኔታው በጣም ብዙ ነው፣ አሰልቺም ጭምር፡፡ በዚህ መልኩ፣ ህጋዊ የመሆኛው ሒደት ውድና አድካሚ ነው፡፡ ምንም አይነት ግልፅ የሆነ ህጋዊ አሰራር የላቸውም፡፡
ይህን የምታደርገው ደግሞ ፓስፖርት ካለህ ነው፡፡ ፓስፖርት ይዘን ነው፣ ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የምትጠይቀው፡፡ የእኛ ኤምባሲ ፓስፖርት ለመስጠት 200 ዶላር ይጠይቃል፡፡ በጅቡቲ ፍራንክ ሳይሆን፣ በዶላር ክፈል ነው የምትባለው፡፡ ይህ ራሱ በጣም ብዙ ነው፡፡
ከአንድ አመት በፊት የኢትዮጵያ ፓስፖርት ለመውሰድ ክፍያው ዝቅተኛ ነበር፡፡ 100 ዶላር፣ 150 ዶላር የነበረበት ወቅት ነበር፡፡ አሁን በጣም ነው የጨመረው፡፡ አዲስ ፓስፖርት ተቀይሯል ተብሎ ነው የጨመረው፡፡ አንድ የጥበቃ ሰራተኛና አንዲት የቤት ሰራተኛ የሆኑ ስደተኞች የአንድ ወር ሙሉ ደመወዛቸው ለፓስፖርት ማውጫ አይበቃቸውም፡፡ ሙሉ ደመወዝ ለዚህ ብቻ ልታውለው አትችልም፡፡ መብላት መጠጣት መልበስ የሚባሉ ነገሮች አሉ፡፡ 200 ዶላር ለመቆጠብ ጊዜ ይፈጃል፡፡ ሰዉ ደግሞ የተወሰነ አመት ሰርቶ፣ ገንዘብ አጠራቅሞ ወደ ሀገሩ መመለስ ነው እንጂ፣ ያገኛትን ገንዘብ ለመኖሪያ ፈቃድና ለፓስፖርት መጨረስ አይፈልግም፡፡
ስለዚህ በኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል ያለው የፓስፖርት ክፍያ ቢቀንስ ጥሩ ነበር፡፡ እንደው 100 ዶላር እንኳን ቢያደርግልን፡፡ በሁሉም አቅጣጫ፣ ህጋዊ ሰነድ ማግኘት የምትችልበት ሁኔታ ነው መፈጠር ያለበት፡፡ ኤምባሲያችን ይህ ጉዳይ እንዲቀረፍ መስራት አለበት፡፡
የጅቡቲ መንግስት የመኖሪያ ፈቃዱ ቀለል ባለ መንገድ እንዲገኝ ማድረግ አለበት፡፡ የኢትዮጵያ ኤምባሲም ለዚህ ጫና ማድረግና የመኖሪያ ፈቃድ ለማግኘት በደላሎች እየተበዘበዘ ያለውን ህዝብ ችግር ከግምት አስገብቶ መስራት አለበት፡፡ ሁሉም ሰው ህጋዊ መሆን ይፈልጋል፡፡ ስርዓቱ ለዚህ መመቸት አለበት ነው የምንለው፡፡ "
ስደተኞቹ ህጋዊ ሰነድ ለመያዝ ይገጥሙናል ስላሉዋቸው ችግሮች እንዲሁም የኢትዮጵያን ፓስፖርት ለማውጣት እስከ 200 ዶላር መክፈል አግባብ አይደለም በማለት ላቀረቡት ቅሬታ፣ በጅቡቲ ካለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ማብራሪያ ካገኘን እናቀርባለን፡፡ ሆኖም የፓስፖርት የአገልግሎት ክፍያን በተመለከተ በህገደንብ የተወሰነ መሆኑን ማረጋገጥ ችለናል፡፡
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለሚሰጣቸው አገልግሎቶች የሚከፈል የአገልግሎት ክፍያን ለመወሰን የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 520/2016 ላይ እንደተገለፀው፣ በውጭ ሀገራት በኤምባሲ በኩል የሚሰጥ ባለ 32 ገፅ መደበኛ ፓስፖርት የአገልግሎት ክፍያው 200 ዶላር መሆኑን ተመልክተናል፡፡ በኦንላይንና በእድሳት ደግሞ 250 ዶላር እንደሚያስከፍል ይጠቅሳል ደንቡ፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
" የተሽከርካሪ ታርጋ አይፈታም ክልክል ነው ፤ ደንቡም ላይ ተቀምጧል " - የመንገድ ደኅንነት እና መድን ፈንድ
➡️ " ተሳፋሪን ለማውረድ ክልክል የነበሩ ቦታዎች እየተፈቀዱ ነው ተጨማሪ ቦታዎችም እየታዩ ቅሬታ የሚነሳባቸው ቦታዎች ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተነጋገርን ነው ! "
ከነሐሴ 13 ቀን 2016 ዓም ጀምሮ በስራ ላይ የዋለው " የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ ቁጥር 557/2016 " ተግባራዊ ከሆነ ስምንት ወራት ተሻግሯል።
ነባሩ ደንብን በመተካት ተሻሽሎ የወጣው ደንብ የጥፋት እርከንን በሦስት በመክፈል የትራፊክ ቅጣቱንም ከ500 ብር እስከ 1,500 ብር ከፍ አድርጓል።
ደንቡ የከተማ የፍጥነት ወሰንን በ 50 ኪሜ በሰዓት ከመወሰኑ በተጨማሪ ፣ የራዳር መቆጣጠሪያ የሚያውኩ መሳሪያዎችን ይዞ መንቀሳቀስን ይከለክላል።
በተጨማሪም አደጋ አድርሰው በአደጋው ህይወታቸው ያለፈ አሽከርካሪዎች የአደጋውን ምክንያት ለመመርመር ህይወታቸው ካለፈ በኋላም የደም ናሙና እንዲወሰድ የሚፈቅዱ አዳዲስ ጉዳዮችን አካቷል።
ደንቡ ተግባራዊ ከሆነ ጀምሮ " የቅጣት ገንዘቡ የተጋነነ ነው " የሚሉ ቅሬታዎችን ጨምሮ " ያለ አግባብ እየተቀጣን ነው " የሚሉ ቅሬታዎች በአሽከርካሪዎች ዘንድ ይሰማል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ደንቡ ተግባራዊ ከሆነ ጀምሮ ውጤታማነቱ ተገምግሟል ወይ ? ስለሚነሱት ቅሬታዎችን ምን ምላሽ አላቹ ? ሲል የሚመለከተውን አካል ጠይቋል።
የመንገድ ደኅንነት እና መድን ፈንድ ህግ ትግበራ ዴስክ ሃላፊ ወ/ሮ ብርክቲ ባህሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
" ደንቡ ከወጣ ጊዜ ጀምሮ ሁሉም ክልሎች እንዲደርሳቸው ተደርጓል ከደረሳቸውም በኋላ የማስተዋወቅ እና ምን ምን ተሻሻለ የሚለውን ነገር የማሳወቅ ስራ ሰርተናል።
ጀምረዋል አልጀመሩም የሚለውን አንድ ዙር ተገምግሟል አብዛኛው ክልል ጀምሯል ማለት ይቻላል አጀማመራቸው እኩል ባይሆንም።
' ቅጣቱ ተጋኗል ' የሚል ቅሬታ በሚመለከት ከዚህ በፊት የነበረው ቅጣት አስተማሪ አልነበረም በጣም አነስተኛ ነበር።
ዋናው አላማችን አደጋን መቀነስ ነው ቅጣቶቹ የተቀመጡት ከአደጋ አንጻር ነው።
ቢያንስ ግንዛቤ እየኖረው ነው ' ቅጣቱ ይሄን ያህል ነው ' የማለት የመጠንቀቅ ነገር አለ ለውጥ አለ።
ደረጃ አንድ፣ ሁለት ፣ ሦስት እና ልዩ ጥፋት እርከን ተብሎ ነው የተቀመጠው።
አሽከርካሪዎች ደጋግመው ሊያጠፏቸው ይችላሉ የተባሉትን ጥፋቶች ከመጠናቸውም አንጻር ታይቶ በአንደኛ ደረጃ የጥፋት እርከን ነው የተቀመጡት።
ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡት ከበድ ያለ አደጋ ሊያደርሱ ይችላሉ ተብለው የተለዩ ጥፋቶች ናቸው ቅጣታቸውም 1,500 ብር ነው።
' ተጋኗል ' የሚል ካለ የማያጠፋን አይመለከትውም ቅጣት የሚመለከተው አጥፊውን ብቻ ነው።
ስፒድ ሊሚተር የሚገጠምላቸው አሽከርካሪዎች አሉ ይህንን ሲፒድ ሊሚተር በትክክል እንዳያሳይ የሚያበላሽ አለ እንደዚህ አይነት ቴክኖሎጂዎችን የሚያሰናክሉ ካሉ የገጠሙት ነገር ይወረሳል ፣በወንጀልም ይጠየቃሉ ቅጣትም አለው።
ይህን አይነቱን ጥፋት የሚያጠፉ አሽከርካሪዎች እንዳሉ ከዚህ ቀደም በተሰሩ ጥናቶች በመታወቁ በደንቡ ላይ እንዲካተቱ ሆኗል።
ከዚህ ቀደም በነበረው ድንብ ላይ ጠጥቶ ወይም አደንዛዥ እጽ ተጠቅሞ አደጋ ያደረሰ እና ህይወቱ ያለፈ አሽከርካሪ ላይ ጠጥቶ ይሁን አይሁን ለማረጋገጥ የሚቻልበት መንገድ አያስቀምጥም ነበር።
በአሁኑ ደንብ አሽከርካሪው በህይወት ባይኖርም የደም ናሙና እንዲወሰድ ይፈቅዳል አተገባበሩ ላይ መመሪያ እየተዘጋጀ ነው።
ተሳፋሪን ለማውረድ ክልክል የነበሩ ቦታዎች እየተፈቀዱ ነው ተጨማሪ ቦታዎችም እየታዩ ቅሬታ የሚነሳባቸው ቦታዎች ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተነጋገርን ነው።
ህጉ ገና መውጣቱ ነው ረዥም ጊዜው አይደለም መሬት ላይ ያለው ሁኔታ ምን ላይ ነው ያለው ? የሚለውን ከሁሉም ክፍል የተወጣጣ ቡድን በስራ ላይ ነው።
ከዚህ ቀደም አሽከርካሪዎች ተደጋጋሚ ጥፋት ስለሚያጠፉ የትራፊክ ፖሊሶች ታርጋ ይፈቱ ነበር መንጃ ፈቃድም ይወስዱ ነበር።
አሁን ላይ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ይህንን የሚያስቀር መተግበሪያ አበልጽጓል።
ከዚህ በኋላ ሰሌዳ መፍታትም ሆነ መንጃ ፈቃድ መውሰድ ሳያስፈልግ አሽከርካሪን የሚቀጣበት አሰራር ነው።
ከዚህ በኋላ ታርጋ አይፈታም ክልክል ነው ደንቡም ላይ ተቀምጧል።
ሲስተሙ ይፋ ተደርጓል ወደ ተግባር እየገቡበት ነው ተሞክሮው ተወስዶ ወደ ክልሎችም የማስተዋወቅ ስራ ይሰራል።
በህጉ መሰረት እንደማይፈቀድ ሁሉም ግንዛቤ እስከሚኖረው ድረስ ጊዜ ይጠይቃል ነገር ግን ታርጋ መፍታት አይፈቀድም " ብለዋል።
ከዚህ ቀደም " የተሽከርካሪን ሰሌዳን መፍታት ክልክል ነው " የሚለው ህግ በተጨባጭ ለምን ተግባራዊ አልሆነም ? የሚል ጥያቄ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን አቶ ክበበው ሚደቅሳ አቀርቦላቸው ነበር።
አቶ ክበበው " ሰሌዳ ቁጥሩ የሚፈታበት አጋጣሚ ይኖራል፣ እሱም የሚሆነው የቅጣት እግድ የደረሱ ከሆነ፣ መንጃ ፍቃዳቸው ላይ ያለው ስልክ ቁጥራቸው የማይሰራ ወይም የክፍለ ሀገር ከሆነ ይፈታል፣ ምክንያቱም አስገዳጅ ምክንያቶች ስለሆኑ በሂደት ግን የሁሉም ሰው አንዳይፈታ እናደርጋለን " ሲሉ መልሰው ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
➡️ " ተሳፋሪን ለማውረድ ክልክል የነበሩ ቦታዎች እየተፈቀዱ ነው ተጨማሪ ቦታዎችም እየታዩ ቅሬታ የሚነሳባቸው ቦታዎች ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተነጋገርን ነው ! "
ከነሐሴ 13 ቀን 2016 ዓም ጀምሮ በስራ ላይ የዋለው " የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ ቁጥር 557/2016 " ተግባራዊ ከሆነ ስምንት ወራት ተሻግሯል።
ነባሩ ደንብን በመተካት ተሻሽሎ የወጣው ደንብ የጥፋት እርከንን በሦስት በመክፈል የትራፊክ ቅጣቱንም ከ500 ብር እስከ 1,500 ብር ከፍ አድርጓል።
ደንቡ የከተማ የፍጥነት ወሰንን በ 50 ኪሜ በሰዓት ከመወሰኑ በተጨማሪ ፣ የራዳር መቆጣጠሪያ የሚያውኩ መሳሪያዎችን ይዞ መንቀሳቀስን ይከለክላል።
በተጨማሪም አደጋ አድርሰው በአደጋው ህይወታቸው ያለፈ አሽከርካሪዎች የአደጋውን ምክንያት ለመመርመር ህይወታቸው ካለፈ በኋላም የደም ናሙና እንዲወሰድ የሚፈቅዱ አዳዲስ ጉዳዮችን አካቷል።
ደንቡ ተግባራዊ ከሆነ ጀምሮ " የቅጣት ገንዘቡ የተጋነነ ነው " የሚሉ ቅሬታዎችን ጨምሮ " ያለ አግባብ እየተቀጣን ነው " የሚሉ ቅሬታዎች በአሽከርካሪዎች ዘንድ ይሰማል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ደንቡ ተግባራዊ ከሆነ ጀምሮ ውጤታማነቱ ተገምግሟል ወይ ? ስለሚነሱት ቅሬታዎችን ምን ምላሽ አላቹ ? ሲል የሚመለከተውን አካል ጠይቋል።
የመንገድ ደኅንነት እና መድን ፈንድ ህግ ትግበራ ዴስክ ሃላፊ ወ/ሮ ብርክቲ ባህሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
" ደንቡ ከወጣ ጊዜ ጀምሮ ሁሉም ክልሎች እንዲደርሳቸው ተደርጓል ከደረሳቸውም በኋላ የማስተዋወቅ እና ምን ምን ተሻሻለ የሚለውን ነገር የማሳወቅ ስራ ሰርተናል።
ጀምረዋል አልጀመሩም የሚለውን አንድ ዙር ተገምግሟል አብዛኛው ክልል ጀምሯል ማለት ይቻላል አጀማመራቸው እኩል ባይሆንም።
' ቅጣቱ ተጋኗል ' የሚል ቅሬታ በሚመለከት ከዚህ በፊት የነበረው ቅጣት አስተማሪ አልነበረም በጣም አነስተኛ ነበር።
ዋናው አላማችን አደጋን መቀነስ ነው ቅጣቶቹ የተቀመጡት ከአደጋ አንጻር ነው።
ቢያንስ ግንዛቤ እየኖረው ነው ' ቅጣቱ ይሄን ያህል ነው ' የማለት የመጠንቀቅ ነገር አለ ለውጥ አለ።
ደረጃ አንድ፣ ሁለት ፣ ሦስት እና ልዩ ጥፋት እርከን ተብሎ ነው የተቀመጠው።
አሽከርካሪዎች ደጋግመው ሊያጠፏቸው ይችላሉ የተባሉትን ጥፋቶች ከመጠናቸውም አንጻር ታይቶ በአንደኛ ደረጃ የጥፋት እርከን ነው የተቀመጡት።
ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡት ከበድ ያለ አደጋ ሊያደርሱ ይችላሉ ተብለው የተለዩ ጥፋቶች ናቸው ቅጣታቸውም 1,500 ብር ነው።
' ተጋኗል ' የሚል ካለ የማያጠፋን አይመለከትውም ቅጣት የሚመለከተው አጥፊውን ብቻ ነው።
ስፒድ ሊሚተር የሚገጠምላቸው አሽከርካሪዎች አሉ ይህንን ሲፒድ ሊሚተር በትክክል እንዳያሳይ የሚያበላሽ አለ እንደዚህ አይነት ቴክኖሎጂዎችን የሚያሰናክሉ ካሉ የገጠሙት ነገር ይወረሳል ፣በወንጀልም ይጠየቃሉ ቅጣትም አለው።
ይህን አይነቱን ጥፋት የሚያጠፉ አሽከርካሪዎች እንዳሉ ከዚህ ቀደም በተሰሩ ጥናቶች በመታወቁ በደንቡ ላይ እንዲካተቱ ሆኗል።
ከዚህ ቀደም በነበረው ድንብ ላይ ጠጥቶ ወይም አደንዛዥ እጽ ተጠቅሞ አደጋ ያደረሰ እና ህይወቱ ያለፈ አሽከርካሪ ላይ ጠጥቶ ይሁን አይሁን ለማረጋገጥ የሚቻልበት መንገድ አያስቀምጥም ነበር።
በአሁኑ ደንብ አሽከርካሪው በህይወት ባይኖርም የደም ናሙና እንዲወሰድ ይፈቅዳል አተገባበሩ ላይ መመሪያ እየተዘጋጀ ነው።
ተሳፋሪን ለማውረድ ክልክል የነበሩ ቦታዎች እየተፈቀዱ ነው ተጨማሪ ቦታዎችም እየታዩ ቅሬታ የሚነሳባቸው ቦታዎች ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተነጋገርን ነው።
ህጉ ገና መውጣቱ ነው ረዥም ጊዜው አይደለም መሬት ላይ ያለው ሁኔታ ምን ላይ ነው ያለው ? የሚለውን ከሁሉም ክፍል የተወጣጣ ቡድን በስራ ላይ ነው።
ከዚህ ቀደም አሽከርካሪዎች ተደጋጋሚ ጥፋት ስለሚያጠፉ የትራፊክ ፖሊሶች ታርጋ ይፈቱ ነበር መንጃ ፈቃድም ይወስዱ ነበር።
አሁን ላይ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ይህንን የሚያስቀር መተግበሪያ አበልጽጓል።
ከዚህ በኋላ ሰሌዳ መፍታትም ሆነ መንጃ ፈቃድ መውሰድ ሳያስፈልግ አሽከርካሪን የሚቀጣበት አሰራር ነው።
ከዚህ በኋላ ታርጋ አይፈታም ክልክል ነው ደንቡም ላይ ተቀምጧል።
ሲስተሙ ይፋ ተደርጓል ወደ ተግባር እየገቡበት ነው ተሞክሮው ተወስዶ ወደ ክልሎችም የማስተዋወቅ ስራ ይሰራል።
በህጉ መሰረት እንደማይፈቀድ ሁሉም ግንዛቤ እስከሚኖረው ድረስ ጊዜ ይጠይቃል ነገር ግን ታርጋ መፍታት አይፈቀድም " ብለዋል።
ከዚህ ቀደም " የተሽከርካሪን ሰሌዳን መፍታት ክልክል ነው " የሚለው ህግ በተጨባጭ ለምን ተግባራዊ አልሆነም ? የሚል ጥያቄ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን አቶ ክበበው ሚደቅሳ አቀርቦላቸው ነበር።
አቶ ክበበው " ሰሌዳ ቁጥሩ የሚፈታበት አጋጣሚ ይኖራል፣ እሱም የሚሆነው የቅጣት እግድ የደረሱ ከሆነ፣ መንጃ ፍቃዳቸው ላይ ያለው ስልክ ቁጥራቸው የማይሰራ ወይም የክፍለ ሀገር ከሆነ ይፈታል፣ ምክንያቱም አስገዳጅ ምክንያቶች ስለሆኑ በሂደት ግን የሁሉም ሰው አንዳይፈታ እናደርጋለን " ሲሉ መልሰው ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#Tigray
ዛሬ በመቐለ ማእከላይ ፍርድ ቤት ምንድን ነው የተከሰተው ?
እንስት ዘውዱ ሃፍቱ ከሁለት ዓመት በፊት በግፍ ከተገደሉት ሴቶች አንድዋ ናት።
የሟችዋ ጉዳይ በፓሊስ ተጣርቶ መዝገቡ ወደ ፍርድ ደርሶ ለሁለት ዓመት ያህል ውሳኔ ሳያገኝ በይዋል ይደር ረጅም ጊዜ መውሰዱ የተበዳይዋ ቤተሰብና የፍትህ ፈላጊዎች ሁሉ መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል።
ይህ በእንዲህ አንዳለ የመቐለ ማእከላይ ፍርድ ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ/ም ከሰዓት በፊት የመጨረሻው ውሳኔ ለመስጠት ችሎት ይቀመጣል።
ፍርድ ቤቱ በግድያ ወንጀሉ በተጠረጠሩት ላይ የመጨረሻ ያለውን የጥፋተኝነት የቅጣት ውሳኔ ይሰጣል።
ይህንን ተከትሎ ችሎቱ በሚከናወንበት አዳራሽ የነበሩት ብዛት ያላቸው የተጠርጣሪ ወገኖች ጠረጴዛ በመደብደብና የተለያዩ ድምፆች በማሰማት ረብሻ ይጀምራሉ።
ከረብሻ በዘለለ ዳኞቹን " እናንተም እንደመስሳቹሃለን ፤ ቀናችሁን ጠብቁ " የሚሉ የስድብ ናዳና ዛቻ ያወርዳሉ።
በችሎት አዳራሹ በቂ የሆነ ስርዓት አስከባሪ ባለመኖሩና ዳኞቹ ሁኔታው ከአቅማቸው በላይ እና አስፈሪ በመሆኑ ምክንያት ውሳኔውን ሳይቋጩ ለግንቦት 18/2017 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ስጥተዋል።
የችሎት መድፈር ተግባሩ የማህበራዊ የትስስር ገፅ ሰፊ መነጋገሪ ሆኖዋል።
ጠበቃ ሚኪኤለ ፍስሃ የተባሉ የሟች ጠበቃ " በፍርሃት ስራዬን አላቋርጥም፤ የተበዳይን እንባ ለማበስ ነገም ዛሬም እሰራለሁ " ሲሉ በማህበራዊ ሚድያ የትሰስር ገጻቸው ላይ ሀሳባቸውን አስፍረዋል።
በርካቶች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የህግ ልዕልና እንዲከበር አገልግሎት በሚሰጠው ፍርድ ቤትና ዳኞች ላይ የተፈፀመ ድፍረት በምሬትና በቁጣ ሲያወግዙት ተስተውለዋል።
የመቐለ ማእከላይ ፍ/ቤት በያዝነው ሳምንት ብቻ የእንስት ዘውዱን ጨምሮ 4 በግፍ የተበደሉ ሴቶችን ጉዳይ መመልከቱን የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ከቦታው መረጃውን አድርሷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ዛሬ በመቐለ ማእከላይ ፍርድ ቤት ምንድን ነው የተከሰተው ?
እንስት ዘውዱ ሃፍቱ ከሁለት ዓመት በፊት በግፍ ከተገደሉት ሴቶች አንድዋ ናት።
የሟችዋ ጉዳይ በፓሊስ ተጣርቶ መዝገቡ ወደ ፍርድ ደርሶ ለሁለት ዓመት ያህል ውሳኔ ሳያገኝ በይዋል ይደር ረጅም ጊዜ መውሰዱ የተበዳይዋ ቤተሰብና የፍትህ ፈላጊዎች ሁሉ መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል።
ይህ በእንዲህ አንዳለ የመቐለ ማእከላይ ፍርድ ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ/ም ከሰዓት በፊት የመጨረሻው ውሳኔ ለመስጠት ችሎት ይቀመጣል።
ፍርድ ቤቱ በግድያ ወንጀሉ በተጠረጠሩት ላይ የመጨረሻ ያለውን የጥፋተኝነት የቅጣት ውሳኔ ይሰጣል።
ይህንን ተከትሎ ችሎቱ በሚከናወንበት አዳራሽ የነበሩት ብዛት ያላቸው የተጠርጣሪ ወገኖች ጠረጴዛ በመደብደብና የተለያዩ ድምፆች በማሰማት ረብሻ ይጀምራሉ።
ከረብሻ በዘለለ ዳኞቹን " እናንተም እንደመስሳቹሃለን ፤ ቀናችሁን ጠብቁ " የሚሉ የስድብ ናዳና ዛቻ ያወርዳሉ።
በችሎት አዳራሹ በቂ የሆነ ስርዓት አስከባሪ ባለመኖሩና ዳኞቹ ሁኔታው ከአቅማቸው በላይ እና አስፈሪ በመሆኑ ምክንያት ውሳኔውን ሳይቋጩ ለግንቦት 18/2017 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ስጥተዋል።
የችሎት መድፈር ተግባሩ የማህበራዊ የትስስር ገፅ ሰፊ መነጋገሪ ሆኖዋል።
ጠበቃ ሚኪኤለ ፍስሃ የተባሉ የሟች ጠበቃ " በፍርሃት ስራዬን አላቋርጥም፤ የተበዳይን እንባ ለማበስ ነገም ዛሬም እሰራለሁ " ሲሉ በማህበራዊ ሚድያ የትሰስር ገጻቸው ላይ ሀሳባቸውን አስፍረዋል።
በርካቶች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የህግ ልዕልና እንዲከበር አገልግሎት በሚሰጠው ፍርድ ቤትና ዳኞች ላይ የተፈፀመ ድፍረት በምሬትና በቁጣ ሲያወግዙት ተስተውለዋል።
የመቐለ ማእከላይ ፍ/ቤት በያዝነው ሳምንት ብቻ የእንስት ዘውዱን ጨምሮ 4 በግፍ የተበደሉ ሴቶችን ጉዳይ መመልከቱን የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ከቦታው መረጃውን አድርሷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ከነገ ግንቦት 21 ጀምሮ ወደ ስራ ገበታ ይመለሳሉ " - ፅ/ቤቱ
ላለፉት 12 ቀናት በስራ ማቆም አድማ የቆዩት የመቐለ ዳኞች ስራ ለመጀመር መግባባት ላይ መደረሳቸው ተነግሯል።
ዳኞቹ ያቀረቡት የደህንነት ስጋት ጥያቄ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚከታተለው በተደረሰው ስምምነት ምክንያት ነው ወደ ስራ ገበታቸው ለመመለስ የወሰኑት።
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት " ዳኞቹ ያለባቸው የድህንነት ስጋት በማስመልከት ከፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) እና ከፍትህ አካላት አመራሮች ጋር ተወያይተዋል " ብሏል።
" በውይይቱ በዳኞቹ ላይ ያንዣበበው የደህንነት ስጋት በጥልቀት ተዳሷል ፤ ችግሩን ከስሩ በመረዳት ለመፍትሄው ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል " ሲል ገልጿል።
" የደህንነት ስጋቱ በዘላቂነት ለመፍታት የአጭርና የረጅም ጊዜ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል። በተደረሰው መግባባት መሰረት የመቐለ ሰባቱ ክፍለ ከተማ ፍርድ ቤቶች ከነገ ግንቦት 21/2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ስራ ገበታ ይመለሳሉ " ብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ላለፉት 12 ቀናት በስራ ማቆም አድማ የቆዩት የመቐለ ዳኞች ስራ ለመጀመር መግባባት ላይ መደረሳቸው ተነግሯል።
ዳኞቹ ያቀረቡት የደህንነት ስጋት ጥያቄ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚከታተለው በተደረሰው ስምምነት ምክንያት ነው ወደ ስራ ገበታቸው ለመመለስ የወሰኑት።
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት " ዳኞቹ ያለባቸው የድህንነት ስጋት በማስመልከት ከፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) እና ከፍትህ አካላት አመራሮች ጋር ተወያይተዋል " ብሏል።
" በውይይቱ በዳኞቹ ላይ ያንዣበበው የደህንነት ስጋት በጥልቀት ተዳሷል ፤ ችግሩን ከስሩ በመረዳት ለመፍትሄው ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል " ሲል ገልጿል።
" የደህንነት ስጋቱ በዘላቂነት ለመፍታት የአጭርና የረጅም ጊዜ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል። በተደረሰው መግባባት መሰረት የመቐለ ሰባቱ ክፍለ ከተማ ፍርድ ቤቶች ከነገ ግንቦት 21/2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ስራ ገበታ ይመለሳሉ " ብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" የተርሚናል አገልግሎት ክፍያው የሚፈጸመው ማህበራቱ በስኬት ባንክ በከፈቷቸው አካውንቶች በቴሌብር አማካኝነት ነው " - ማህበራቱ
ነባር ተራ እስከባሪዎችን በመተካት የተርሚናል አስተዳደር እና ቁጥጥር ስልጠና የወሰዱ ከ 80 በላይ በሚሆኑ ማህበራት(ኢንተርፕራይዝ) የተደራጁ ተራ አስከባሪ ወጣቶች ዛሬ ከሰአት ስራ ጀምረዋል።
ዛሬ ጠዋት የአዲስ አበባ ከተማ ስራ እና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ ፣የአዲስ አበባ የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ እና የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ያብባል አዲስ በተገኙበት የተመረቁት 996 የታክሲ ተራ አስከባሪ ወጣቶች ከሰአት በኋላ ስራ መጀመራቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተዘዋውሮ ተመልክቷል።
ነባሮቹን ተራ አስከባሪ ወጣቶች በመተካት ከዛሬ ጀምሮ ወደ ስራ የገቡት ወጣቶች በየወረዳው የተደራጁ ሲሆን በከተማዋ በሚገኙ 87 ተርሚናሎች ወደ ስራ ገብተዋል።
የተርሚናል አገልግሎት ክፍያው የሚፈጸመው ማህበራቱ በስኬት ባንክ በከፈቷቸው አካውንቶች በቴሌብር አማካኝነት መሆኑን ቲክቫህ ያነጋገራቸው የማህበራቱ አባላት ገልጸዋል።
ለትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ግንዛቤ ማስጨበጫ በሚል ከትላንት ጀምሮ የተበተነው እና ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው በራሪ ወረቀት የተቀመጠው የአገልግሎት ክፍያ በየትኛውም መነሻ እና መድረሻ ላይ 10 ብር መሆኑን በመግለጽ ክፍያውንም በዲጂታል መንገድ ብቻ እንዲፈጸም ይጠይቃል።
በተጨማሪም ከተቀመጠው የአገልግሎት ክፍያ በላይ የከፈለ አሽከርካሪም ሆነ ረዳት 4000 ብር እንደሚቀጡ ይገልጻል።
ነባር ተራ አስከባሪዎች በመረጡት የስራ ዘርፍ እንዲሰማሩ አስፈላጊው ድጋፍ ይደረግላቸዋል ተብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ነባር ተራ እስከባሪዎችን በመተካት የተርሚናል አስተዳደር እና ቁጥጥር ስልጠና የወሰዱ ከ 80 በላይ በሚሆኑ ማህበራት(ኢንተርፕራይዝ) የተደራጁ ተራ አስከባሪ ወጣቶች ዛሬ ከሰአት ስራ ጀምረዋል።
ዛሬ ጠዋት የአዲስ አበባ ከተማ ስራ እና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ ፣የአዲስ አበባ የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ እና የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ያብባል አዲስ በተገኙበት የተመረቁት 996 የታክሲ ተራ አስከባሪ ወጣቶች ከሰአት በኋላ ስራ መጀመራቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተዘዋውሮ ተመልክቷል።
ነባሮቹን ተራ አስከባሪ ወጣቶች በመተካት ከዛሬ ጀምሮ ወደ ስራ የገቡት ወጣቶች በየወረዳው የተደራጁ ሲሆን በከተማዋ በሚገኙ 87 ተርሚናሎች ወደ ስራ ገብተዋል።
የተርሚናል አገልግሎት ክፍያው የሚፈጸመው ማህበራቱ በስኬት ባንክ በከፈቷቸው አካውንቶች በቴሌብር አማካኝነት መሆኑን ቲክቫህ ያነጋገራቸው የማህበራቱ አባላት ገልጸዋል።
ለትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ግንዛቤ ማስጨበጫ በሚል ከትላንት ጀምሮ የተበተነው እና ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው በራሪ ወረቀት የተቀመጠው የአገልግሎት ክፍያ በየትኛውም መነሻ እና መድረሻ ላይ 10 ብር መሆኑን በመግለጽ ክፍያውንም በዲጂታል መንገድ ብቻ እንዲፈጸም ይጠይቃል።
በተጨማሪም ከተቀመጠው የአገልግሎት ክፍያ በላይ የከፈለ አሽከርካሪም ሆነ ረዳት 4000 ብር እንደሚቀጡ ይገልጻል።
ነባር ተራ አስከባሪዎች በመረጡት የስራ ዘርፍ እንዲሰማሩ አስፈላጊው ድጋፍ ይደረግላቸዋል ተብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia