አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.83K photos
25 videos
1.86K files
3.55K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1234/13
አዋጁ የፍርድ ቤት ውሣኔዎችንና ትዕዛዞችን ስለ መፈጸም እና ይህንኑ ትእዛዝ አለመፈጸም የሚያስከትለውን የወንጀል ቅጣት ያስቀመጠ ሲሆን ይህም በአዋጁ አንቀጸ 51 ላይ የፍርድ ቤት ውሣኔዎችንና ትዕዛዞችን በተመለከተ፤በማንኛውም የፌዴራል ፍርድ ቤት የተሰጠ ውሳኔ እና ትዕዛዝ በህግ እስካልተለወጠ ድረስ የፀና ሆኖ ተፈፃሚ መሆን እንደለበት፤የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የሚሰጧቸዉን ዉሳኔዎች ወይም ትዕዛዞች በሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች ዉስጥ ተፈጸጻሚ እንደሚሆኑ፤በማንኛዉም ክልል ዉስጥ የሚገኝ የመንግስት አካል፣ ተቋም ወይም መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ወይም ማንኛዉም ሰው ውሳኔዎቹን ወይም ትዕዛዞቹን የመፈጸም እና የማስፈጸም ግዴታ እንዳለበት እና ማንኛዉም ሰዉ የፍርድ ቤት ውሣኔዎችንና ትዕዛዞችን የማይወጣ ከሆነ የወንጀል ተጠያቂነት እንዳለበት ይደነግጋል፡፡ አዋጁ በአንቀጽ 52 ስር የወንጀል ተጠያቂነት ያስቀመጠ ሲሆን ይህም፤-
 የፍርድ ቤት ወይም የዳኞችን በነጻነት መስራት የሚጋፋ ወይም በዳኞች ላይ ተጽእኖ የሚያደርግ ወይም ለማድረግ የሞከረ ማንኛውም ሰዉ በሌላ ህግ ከፍ ያለ ቅጣት ከሌለ በቀር ከሦስት ወር እሥራት ባላነሰ ከሁለት ዓመት ባልበለጠ ጽኑ እስራት እንደሚቀጠ እንዲሁም፤
 የፍርድ ቤትን ትዕዛዝ ወይም ዉሳኔ የማይፈጽም ወይም ለመፈፀም መሰናክል የሚፈጥር ወይም ሲጠየቅ ለመፈፀም ተባባሪ የማይሆን ማንኛዉም ሰዉ በሌላ ህግ ከፍ ያለ ቅጣት ከሌለ በቀር ከሁለት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት ወይም ከአምስት ሺህ ብር በማይበልጥ ገንዘብ እንደሚቀጣ ይደነግጋል፡፡

ፍርድ ቤት ሰዎች ሕግን መከታ አድርገው መብታቸውን የሚያስከብሩበት እንደመሆኑ የፍርድ ቤቱን ክብር መጠበቅ የፍትሕ ሥርዓቱን ሕልውና ለመጠበቅ ፤እንዲሁም ኅብረተሰቡ በዳኝነት አካሉ ላይ ያለውን መተማመን ለመጠበቅ ፍርድ ቤትን ማክበር ወሳኝ ነው፡፡
በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና የተዘጋጀ
ፍትህ ሚኒስቴር
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የጋራ ንብረት ምንነትና አስተዳደር
የጋራ ንብረትን በተመለከተ የጋራ ንብረት የሚባለው ባልና ሚስት ከተጋቡ በኋላ በግብይት የሚያገኟቸው ንብረቶች፣ ባልና ሚስት በግል ጥረታቸው የሚገኝ ገቢ፣ ከግል እና ከጋራ ንብረታቸው የሚገኟቸው ገቢዎች ሁሉ ናቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በስጦታ ወይም በኑዛዜ በጋራ የተሰጧቸው ንብረቶች የጋራ ንብረቶች ናቸው፡፡ እዚህ ላይ መታወቅ ያለበት አንደኛው ተጋቢ የግል ሀብቱ መሆኑን ካላስረዳ በስተቀር በአንደኛው ተጋቢ ስም የተመዘገበ ሀብትም ቢሆን እንኳን የተጋቢዎች የጋራ ሀብት እንደሆነ የህግ ግምት የሚወሰድበት መሆኑ ነው፡፡
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ማስጠንቀቂያ :- 1ሚሊየን ብር ሊቀጡ ይችላሉ

አለማወቅ ከቅጣት አያድንም

👉 በባህሪው አደገኛ የሆነ ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ በወንዝ ዳርቻ ያሰወገደ ድርጅት አንድ ሚሊዮን ብር ይቀጣል፣

👉 ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ ወንዝ ላይ የጣለ ግለሰብ 500 ሺህ ብር ይቀጣል

👉 ፍቃድ የወሰዱም ሆነ ሳይወስዱ ፍሳሽን ቀጥታ በወንዞች ዳርቻ ሲያስወግዱ ቢገኙ 100 ሺህ ብር ይቀጣሉ፣

👉 በወንዝ ዳርቻና አካባቢ መጸዳዳት ሁለት ሺህ፤

👉 የፈሳሽ ማጣሪያ ሳይኖር በወንዝ ዳርቻና አካባቢ ተሽከርካሪ ማጠብ 400ሺህ ብር፤

👉 እንስሳትን ማሰማራት፣ ማስገባት ከተፈቀደው ውጪ ተሽከርካሪ ማሽከርከር 30 ሺህ ብር

👉 ለመዝናኛ፣ ለመናፈሻና ለፖርክ ከተፈቀደ ውጪ ግንባታ መገንባት 200 ሺህ ብር፤

👉 ከአምራችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ማንኛውም ያልታከመ ቆሻሻ መልቀቅ 300 ሺህ ብር ያስቀጣል፣

👉 ኬሚካል ነክ ቆሻሻዎችን የማከሚያ ዘዴ ሳይጠቀም የለቀቀ ግለሰብ 50 ሺህ፤ ድርጅት 300 ሺህ ብር ይቀጣሉ፣

👉 ማንኛውም በካይ ቆሻሻ ከተፈቀደ የፈሳሽ ማጠራቀሚያ ውጪ ያፈሰስ ግለስብ 50 ሺህ ድረጅት 400 ሺህ ብር፤

👉 የአትክልትና ፍራፍሬ ተረፈ ምርቶችን በወንዝ ዳርቻ ማስወገድ ግለሰብ 20 ሺህ፣ ድርጅት 100 ሺህ፤

👉 ዘይት፣ ጨዋማ ፈሳሽ፣የሞተር ዘይት፣ ነዳጅ ሳሙና ነክ ነገሮችን በወንዝ ዳርቻ ያስወገደ 400 ሺህ ብር ይቀጣል፣

👉 ማንኛውም ያልተጣራ ቆሻሻ ወደ ወንዝ መልቀቅ ግለሰብ 150 ሺህ ድርጀት 300 ሺህ ይቀጣል፣

👉 ፍቃድ ሳይሰጠው ያልታከመ ቆሻሻን ወደ ወንዝ ያስወገደ ግለሰብ 15 ሺህ ብር ድርጅት 40 ሺህ ብር ይቀጣል፣
የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ጋብቻ ከፈረሰ በኃላ (የንብረት ክፍፍል ከመደረጉ በፊት) የጋራ ንብረት የሆነን የማይንቀሳቀስ ንብረት (ቤት) አንደኛው ወገን ያለሌላኛው ፈቃድ በሽያጭ ያስተላለፉት ከሆነ የቤተሰብ ሕጉ አንቀጽ 69 (1) “ም” ሆነ (2) ድንጋጌዎች ለክርክሩ ተፈጻሚነት ሊኖራቸው የሚችልበት አግባብ አይኖርም፡፡ አግባብነት ያለው የጋራ ንብረትን ለማስተላለፍ የጋራ ባለሀብትን ፈቃድ የሚያስፈልግ ስለመሆኑ በፍ/ሕ/ቁ.1266 የተመለከተው ድንጋጌ ነው።

የቤተሰብ ሕጉ አንቀጽ 69 የሚገኘው በቤተሰብ ሕጉ የጋብቻ ውጤትን በሚመለከተው ምዕራፍ ሦስት ክፍል ሦስት ስር ሲሆን ይህ ክፍልም ጋብቻው ጸንቶ በሚገኝበት ጊዜ በንብረት በኩል የሚያስከትለውን ሕጋዊ ውጤት የሚገዛ ነው፡፡

ዳሩ ግን፣ አንደኛው ወገን ቤቱን በሽያጭ ያስተላለፉት ጋብቻው ከፈረሰ በኃላ (የንብረት ክፍፍል ክፍፍል ከመደረጉ በፊት) ከሆነ ለጉዳዩ ተፈጻሚነት የሚኖረው የጋራ ባለሀብትነትን የሚመለከተው የፍ/ብ/ሕጉ ድንጋጌ ነው።

ይህ ከሆነ ደግሞ፣ አንደኛው ወገን በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ነው የሚለው ንብረት ላይ የተፈጸመው የሽያጭ ውል እንዲፈርስ ክስ ለማቅረብ የሚችለው በምን ያህል ጊዜ ውስጥ እንደሆነ በቤተሰብ ሕጉ ውስጥ በተለይ የተመለከተ ድንጋጌ ባለመኖሩ በዚህ ዓይነት ጉዳዮች ላይ ተፈጸሚነት ሊኖረው የሚገባው በፍ/ብ/ሕ/ቁ.1677(1) ድንጋጌ መሰረት በፍ/ብ/ሕ/ቁ.1845 ድንጋጌ የተመለከተው አጠቃላይ የአስር ዓመት የይርጋ ጊዜ ነው፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ሚያዝያ 12 ቀን 2007 ዓ.ም በሰ/መ/ቁጥር 95338 የሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጉም
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ከጋብቻ በፊት የነበረ የግል ቤት በትዳር ዉስጥ ከፍተኛ ወጪ ወጥቶ ማሻሻያ እና ማስፋፊያ ቢደረግለትም የጋራ ንብረት ሊሆን አይገባም። ቤቱን ለማሻሻል እና ለማስፋፋት የወጣ ወጪ ተጣርቶ ወጪዉ በድርሻ እንዲወስዱ ከሚደረግ በስተቀር ቤቱ የጋራ አይሆንም፡፡

የፌዴሬሽን ምክር ቤት መስከረም 28 ቀን 2017 ዓ.ም በመ/ቁጥር 130/16 የሰጠው ውሳኔ ነው።
#በአለሕግ_ጠበቃና_ሕግ_አማካሪ
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
የፌዴራል ህጎች በክልል ደረጃ የተቀራረበ አተረጓጎም እንዲኖራቸው በትኩረት መስራት ይገባል’’ ሲሉ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ተናገሩ።

አቶ ቴዎድሮስ እንዳሉት ህጎቹ በክልል ደረጃ በተቀራረበ ደረጃ እየተተረጎሙ ስለመሆናቸው ለማረጋገጥ በየጊዜው መረጃዎችን የመሰብሰብ፣ የመተንተን እና ውጤቱን መሰረት በማድረግ እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል ።

አተረጓገሞቹ ላይ የሚታዩ ችግሮችን በዚህ መንገድ ማረም ችግሮችን ከምንጫቸው ለመፍታት ያስችላል ነው ያሉት።

ሀገር አቀፍ የህግ ተርጓሚዎች የግንኙነት መድረክ በቢሾፍቱ እየተካሄደ ይገኛል።

መድረኩ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት፣ የሁሉም ክልሎች ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ፕሬዝዳንቶች እንዲሁም የአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተሞች የይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤቶች ፕሬዝዳንቶች ያሉበት ነው።

በዓመት ሁለት ጊዜ እየተገናኘ በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚመክርም አቶ ቴዎድሮስ በመድረኩ ላይ ሲናገሩ ሠምተናል።
ንጋቱ ረጋሣ ፣ የሸገርን ወሬዎች፣ መጋቢት 27 2017
#በአለሕግ_ጠበቃና_ሕግ_አማካሪ
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
👉National champion Team/የውድድሩ አሸናፊ ቡድን ባህርዳር ዩኒቨርስቲ ሁኖል

የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ህግ ትምህርት ቤት ከፌደራል ፍትህ እና ህግ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ከአርብ ግንቦት 8 ቀን 2017 ጀምሮ እስከ ዛሬ እሁድ ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ ሲካሄድ የቆየው 9ኛው ዙር ሀገር አቀፍ የህግ ትም/ት ቤቶች የምስለ ችሎት ውድድር ፍጻሜውን አግኝቶል ።

በውድድሩ ላይ 12 ዪኒቨርሲቲይዎች የተሳተፉ ሲሆን።የውድድሩ የመጨረሻ ውጤትም የሚከተለው ነው።

👉National champion Team/የውድድሩ አሸናፊ ቡድን ባህርዳር ዩኒቨርስቲ ሁኖል

1.ቤተልሔም ገበየሁ ጸጋነህ
2.ዮናስ ሙጨ ዳኘ
3.እዮብ ይመች

👉Best Runner Up Team (2ኛ ደረጃን) የያዙት ሰላሌ ዩኒቨረሲቲ ናቸው

1.ሄርሜላ መስፍን
2 ሀዴሳ መረከቡ
3.አብዲ ረታ

👉Second runner up team(3ኛ ደረጃን የያዙት) ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ሰሆን
1.ፋሲል ዘለቀ ዘውደ
2.ወርቁ ማስሬ አበበ
3. ፈቲያ ኑረድን መሃመድ

👉Best Memorial Applicant

ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ

👉Best Memorial Respondet winner

ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ
👉Best orator of the preliminary round competition
እዮብ ይመች ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ

👉Best Femal orator of the preliminary round Competition
ቤተልሔም ገበየሁ ጸጋነህ ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ

👉Best orator of the final round competition competition

እዮብ ይመች ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ

via:- Law Students Union
ጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#የዳኞችስነምግባር #አለሕግ #ህግ