አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.87K photos
25 videos
1.87K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የፐርፐዝ ብላክ አክስዮን ማኅበር ዋና ሥራ አስፈጻሚን ጨምሮ 12 የማኅበሩ አመራሮች በከባድ የሙስና ወንጀል ተከሰሱ


የፐርፐዝ ብላክ አክስዮን ማኅበር ዋና ሥራ አስፈጻሚ የነበሩት ፍስሀ እሸቱ (ዶ/ር) ጨምሮ 12 የማኅበሩ አመራሮች በከባድ አታላይነት የሙስና ወንጀል ተከሰሱ፡፡

ከተከሳሾቹ መካካል ፍስሀን እሸቱ (ዶ/ር) ጨምሮ ምክትላቸው ኤርሚያስ ብርሃኑ (ዶ/ር)፣ ወይዘሮ ኤፍራታ (ሶፊያ/)፣ ነጋሽ ደስታ፣ ተፈራ ኃይሉ፣ ሚሊዮን ስዩም፣ ናኦሊ ዳዲ፣ ብርሀኑ ወልዴ እና ዋስይሁን ዋጋው የተባሉት አመራረሮች ይገኙበታል፡፡

ባልተጨበጠ መንገድ መሀል ሜክሲኮ ላይ በ1.5 ሚሊዮን ብር የቤት ባለቤት እናደርጋለን የሚለውን ማስታወቂያ አነበበ የተባለው ታደለ ሠይፉ እንዲሁም ትንሣኤ ተስፋዬ፣ ራሱ ፐርፐዝ ብላክ እና ኖቶር ዲዛይን የተሰኙ ድርጅቶች በክስ መዝገቡ ተካትተዋል፡፡

በፍትህ ሚኒስቴር የሙሰና ወንጀሎች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት የክስ መዝገብ ላይ እንደተጠቀሰው ይህ ፐርፐዝ ብላክ የተሰኘው አክሲዮን ማኅበር አንድ ብሎ ሲቋቋም የግብርና ሥራዎች እና አግሮ ፕሮሰሲንግ አክሲዮን ሽያጭ ለማከናወን ነበር፡፡

በዚህ እንቅስቃሴ ውስጥ እያለ ከ 2013-2015 ዓ.ም ባሉት ጊዜያት 280 ሚሊዮን ብር ገደማ ከስሮ ባልተገባ መንገድ ጎዶሎውን ሞልቶ ለመጠቀም ተከሳሾቹ የተከሰሱበትን ወንጀል መፈጸማቸውን በክስ መዝገቡ ላይ ተጠቅሷል፡፡

በዚህም መሀል ሜክሲኮ ሰንጋተራ በአስራ አምስት ቀን ውስጥ 1.5 ሚሊዮን ብር ለሚከፍሉ ቤት እናስረክባለን በማለት አማላይ ማስታወቂያ በመገናኛ ብዙሀን በማሰራጨት ከ1 ሺህ 245 ግለሰቦች ከ1.5 ቢሊዮን ብር በላይ አታልለው ወስደዋል በሚል ዐቃቤ ሕግ በከባድ አታላይነት የሙስና ወንጀል ከስሷቸዋል፡፡

ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾቹ ላይ በአጠቃላይ ሰባት የሙስና ወንጀል ክስ የመሰረተባቸው ሲሆን፣ ተከሳሾቹ ዛሬ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 3ኛ የሙስና ወንጀል ችሎት ቀርበው ክሱ ተነብቦላቸዋል፡፡

ችሎቱ የክስ መቃወሚያ ካላቸው ለመቀበልና ያልተገኙትን ፖሊስ እንዲያርባቸው ለጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል።
በጥላሁን ካሳ
#EBC

Stay Connected with #AleHig!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

https://linktr.ee/alehig

Telegram
https://t.me/AleHig

Telegram_Group
https://t.me/AleHig_Group

Facebook Page
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

LinkedIn
https://www.linkedin.com/company/alehig/

YouTube
https://www.youtube.com/@Ale_Hig

TikTok
https://www.tiktok.com/@alehigofficial

Instagram https://www.instagram.com/alehigofficial

Twitter /X
https://x.com/AlehigOfficial?t=yFRauAZ7v70Je2MEPIGGsQ&s=09

official website
https://www.alehig.com

#LegalAwareness #AleHig #LegalUpdates #AccessToJustice
👍16
ሐሰተኛ የባንክ ቅርንጫፍ ቢሮ ከፍተው የሚያጭበረብሩት ሌቦች

አጭበርባሪዎቹ ለ10 ቀናት ህጋዊ ተቋም መስለው ቅርንጫፍ ከፍተው ሰዎችን ሲያታልሉ ነበር ተብሏል

ፖሊስ አጭበርባሪዎቹን እያደነ መሆኑን ያሳወቀ ሲሆን እስካሁን ተጠርጣሪዎቹ ስለመያዛቸው አልተገለጸም

ተጨማሪ ያንብቡ https://bit.ly/3NuYCni


Stay Connected with #AleHig!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

https://linktr.ee/alehig

Telegram
https://t.me/AleHig

Telegram_Group
https://t.me/AleHig_Group

Facebook Page
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

LinkedIn
https://www.linkedin.com/company/alehig/

YouTube
https://www.youtube.com/@Ale_Hig

TikTok
https://www.tiktok.com/@alehigofficial

Instagram https://www.instagram.com/alehigofficial

Twitter /X
https://x.com/AlehigOfficial?t=yFRauAZ7v70Je2MEPIGGsQ&s=09

Website
https://www.alehig.com

#LegalAwareness #AleHig #LegalUpdates #AccessToJustice
👍10😁63😱3
የሕጻናት ቀለብ አወሳሰን መርሆች


1. በዋነኝነት የሕጻናት ጥቅም እና ደህንነት ቀዳሚ ማድረግ አለበት፡፡

2. ሕጻናት ወላጆቻቸውን የማወቅ እና ከወላጆቻቸው እንክብካቤ የማግኘት መብት ላይ መመስረት አለበት፡፡

3. ወላጆች አቅማቸው በፈቀደ መጠን ልጆቻቸውን የማሳደግና የመንከባከብ ህጋዊ ኃላፊነት ግንዛቤ ውስጥ መግባት አለበት:: ወላጆች ኢኮኖሚያዊ ኃላፊነታቸውን እንደየገቢያቸው መጠን ሊጋሩ እንደሚገባ ግንዛቤ ውስጥ መግባት አለበት፡፡

4. በሕጻናት ቀለብ አወሳሰን ሂደት ወላጆች ለመኖር የሚያስፈልጓቸውን መሰረታዊ የሆኑ ምግብ፣ መጠለያ እና አልባሳት ታሳቢ ማድረግ አስፈላጊ ቢሆንም በየትኛውም ሁኔታ ግን ለሕጻናት ቀለብ የመስጠት ግዴታን የሚገድብ መሆን የለበትም፡

5. የሕጻናትን መሠረታዊ ፍላጎቶችና ልዩ ወጪዎች ታሳቢ ማድረግ ያለበት ሲሆን ከወላጆቹ አንዱ የተሻለ ገቢ ያለው ከሆነ ሕጻኑ የዚህ ገቢ ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረግ ይገባል፡፡

6. በማስረጃ የተረጋገጠ ከአቅም በላይ በሆነ ሁኔታ ካልሆነ በስተቀር ስራ ባለመስራት ወይም ገቢ ባለማግኘት ቀሪ የሚሆን አይደለም፡፡

7. የሕጻናቱን እድሜ፣ ብዛት፣ የጤና ሁኔታ፣ ልዩ ፍላጎት፣ የሁለቱም ወላጆቹን የገቢ እና ወጪ መጠን እና ተቀባይነት ያላቸው ወይም ህጋዊ ተቀናሾች ያገናዘበ መሆን አለበት፡፡

8. ቀለብ የመስጠት ግዴታ ያለበት ወላጅ በመምሪያው መሰረት ከሚወሰነው የቀለብ መጠን በተጨማሪ ለመክፈል ፍቃደኛ ከሆነ ወይም ይከፍል ከነበረ ይህንኑ ከግምት ማስገባት አለበት፡፡

9. በሕጻኑ ወላጆች የጋብቻ ሁኔታ የሚወሰን ባለመሆኑ የቀለብ ጥያቄ በቀረበ ጊዜ መወሰን አለበት፡፡

10. ፆታዊ መድሎ የሌለበት መሆን አለበት፡፡

11. በወላጆች መሠረታዊ የኑሮ ሁኔታ ላይ የተጋነነ ችግር ማስከተል የለበትም፡፡ በተለይም የመምሪያው አፈፃፀም ወላጆች ሌላ ቤተሰብ እንዳይመሰርቱ፤ ወይም ስራ ሰርተው ገቢ እንዳያገኙ የሚገፋፋቸው መሆን የለበትም፡

12. ወላጆች በልጆቻቸው አስተዳደግ እና እንክብካቤ ላይ በጋራ እንዲሳተፉ የሚያበረታታ በተቻለ መጠን ወላጆች የሞግዚትነት ኃላፊነትታቸውን በጋራ እንዲወጡ የሚያስችል ሊሆን ይገባል፡፡

13.
የዋጋ ግሽበት ወይም የኑሮ ውድነትን ወይም የሕጻኑ ፍላጎት መጨመርን ወይም የቀለብ ሰጪን የመክፈል አቅም መለወጥን መሠረት አድርጎ ማስተካከያ ሊደረግበት ይገባል፡፡

#አለሕግ #AleHig @AleHig
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ አማራጭ የሕግ እውቀት
Alternative legal enlightenment/ALE https://t.me/AleHig
WhatsApp👉 #+251920666595
https://linktr.ee/alehig
Telegram👉 @MikiasMelak የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ መሰረታዊ የሕግ እውቀት alehig.com
👍54😁1
ስግብግብነት አለ ስንል በተገባር ነው!
ትንሿ ውሀ /ግማሽ ሊትር ውሀ 50 ብር የሚሸጥ ነጋዴ ስግብግብ ካልሆ ምን ይባላል?

ትዝብ ብቻ በቂ አይመስልም እንዲህ አይነት ነጋዴን ማውገዝ ያስፈልጋል‼️ #AleHig_አለሕግ #አለሕግ #AleHig @AleHig
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ አማራጭ የሕግ እውቀት
Alternative legal enlightenment/ALE https://t.me/AleHig
WhatsApp👉 #+251920666595
https://linktr.ee/alehig
Telegram👉 @MikiasMelak የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ መሰረታዊ የሕግ እውቀት alehig.com
😢8👍7🙈3🥱2
Andinet Umoja: Connecting African Businesses 🇪🇹🤝🏿🌍
What an incredible experience at Andinet Umoja, a powerful networking platform uniting Africa’s entrepreneurs, business leaders, and innovators! As the name suggests:
"Andinet" (Amharic) & "Umoja" (Swahili) = Unity
A true reflection of the collaboration driving Africa’s growth.
📅 Date: February 16, 2025
📍 Venue: Monarch Parkview Hotel, Addis Ababa
The breathtaking view of Addis from the venue made the experience even more special! More importantly, I achieved my purpose for attending—it was worth every moment.
🔹 Why this event matters:
Connecting with Africa’s top innovators
Building cross-border partnerships
Strengthening African collaboration
I love Africa, and I sincerely appreciate Mr. Thomas for his dedication in making this event a reality.
Now, we are more connected than ever. This is just the beginning of a powerful journey—expanding networks, fostering regional unity, and creating lasting impact for African businesses. Alehig will always be by your side!
#AndinetUmoja #AfricanUnity #AU2025 #AfricanUnion #Africans #BusinessNetworking #Alehig
👍1
#Alehig #አለሕግ AleHig is currently in Nairobi, Kenya💎. Our local phone has not been working for a week, but you can reach us via WhatsApp +251920666595.
#africa #attorney #lawyerlife
East Africa Law Society
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍61
ለኔ ጥብቅና አርት ነው። የምፅፋቸው ክርክሮች የህግ መሰረት፣ ትንተና እና ጥሩ አመክንዮ ያላቸው፣ ግልፅና ቀላል ሆነው ካገኘኋቸው ደስ ይለኛል። አንዳንዴ 'ታክል/ጠረባ መሳይ ጣል ሳደርግም እንደዚያው፣ በተለይ ቃል ክርክር ላይ። ባጭሩ ጥብቅና ያዝናናኛል።

የፍርድ ቤት ውሳኔዎች ያስገርሙኛል እንጂ አያናድዱኝም። የትኛውንም ጉዳይ የግሌ አድርጌ/ፐርሰናሊ አልወስድም፣አልብሰለሰልም። ይልቅ የማተኩረው የቻልኩትን አድርጌያለሁ ወይስ አላደረግሁም የሚለው ላይ ነው። የቻልኩትን ካደረግሁ፣ ቀሪው የተከበረው ፍርድ ቤት ስራ ነው።

ግን ደግሞ የውሳኔዎች ጥራት ማሽቆልቆል ያሳስበኛል፣ ለኔ ሳይሆን፣ ደንበኞቼ በኢትዮጵያ የፍትህ ስርዓት ላይ ያላቸው ዕምነት ስለሚሸረሸር፣ ይህም ኢንቨስትመንት ሰለሚያሸሽ። ግን እሱንም ቢሆን፣ እኔ ላደርግ የምችለው ነገር ውስን ስለሆነ፣ እዚያ ላይ አተኩራለሁ። ቀሪው የመንግስት ኃላፊዎች ጉዳይ ነው፣ እነሱን ደግሞ ተክቼ ልሰራ አልችልም፣ ከማሳሰብ በቀር። ከሰሙ ዲየግ፣ ታልሰሙም ምን ይደረጋል፣ ያገሪቱ ያርባ ቀን ዕድል ነው።

ለምሳሌ የሰበር አጣሪ ችሎቶችን እንውሰድ። በቅርብ ጊዜ በተደጋጋሚ እንዳየሁት፣ ለምሳሌ እኔ የምቀርብበት 2ኛ ሰበር አጣሪ ችሎት፣ ያለማጋነን በየቀኑ ከ35 እስከ 40 የሰበር አቤቱታዎችን ይሰማል፣ ፣ ብይንም በአንድ ወይም ሁለት ቀን ውስጥ ይሰጣል ላብዛኛው። ሲጀመር መዝገቦችን መርምሮ ብይን ለመስጠት በቂ ጊዜ የሚያስፈልግ ይመስለኛል። በዚህ ጫና ውስጥ ሆኖ አንድ ዳኛ ውስብስብ የህግ ክርክሮች ያሉበትን መዝገብ በአግባቡ ለመመርመር የሚያስችል ጊዜ ያገኛል ወይ? በነርሱ ቦታ ሆኜ ባየው፣ ይህ በጣም ጫና ያለው፣ አታካች ስራ ነው። በቂ ረዳቶች አሏቸው ወይ? ተጨማሪ የሰበር አጣሪ ችሎቶች አያስፈልጉም ወይ? የሚለውን ጉዳይ የፍርድ ቤቱ ኃላፊዎች ቢያዩት ጥሩ ነው እላለሁ።

በተጨማሪም፣ በተለይ ለየት ያሉ እንደ ታክስ፣ አዕምሯዊ ንብረት፣ ሰብዓዊ መብት ያሉ ልዩ ዕውቀት የሚጠይቁ ውስብስብ ጉዳዮችን የሚያዩ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች በየዘርፉ ተገቢው የትምህርት ዝግጅት እና ልምድ እንዲኖራቸው (ለምሳሌ በነዚህ ዘርፎች የማስተርስ ዲግሪ ወይም ከዚያ በላይ) ቢደረግ፣ በዘርፉ ለስነሕግ ዕድገትም ይጠቅማል፣ (ለምሳሌ የህጉን ምክንያት፣ዓለም አቀፍ ስታንዳርዶችን እና እና የሌሎች አገሮች ጠቃሚ ልምድ ለማካተት)፣ ፍትሐዊ ውሳኔ ለመስጠትም ያገለግላል። ይህ ሲሆን የውጭ ባለሃብት በሃገሪቱ የፍትህ ስርዓት ላይ ያለው አመኔታም ይጨምራል።
ስለሆነም፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ፣ በየዘርፉ የመደባቸው ዳኞች ያላቸው ልምድ እና የትምህርት ዝግጅት ከተመደቡበት ዘርፍ ጋር አብሮ የሚሄድ ነወይ የሚለውን ቢገመግም ጥሩ ሊሆን ይችላል። በዘርፉ ልምድ ያላቸው ዳኞች ቢያንስ በሰብሳቢነት ቢሾሙ፣ ቀሪዎቹ ዳኞች ልምድ እየቀሰሙ እንዲሄዱ ለማድረግ ይረዳል እላለሁ። ይሔ አሳብ ጥሩ ከመሰላቸው አላፊዎቹ ቢያዩት፣ በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ አማካሪ ምክር ቤትም ውይይት ቢደረግበት ይጠቅም ይሆን?
እኔና ጥብቅና በሚል ወዳጄ Abebe Asamere ጥብቅና ያስጠላል ስለሚሉ ሰዎች የጻፈውን አነበብኩት ብለው የሰጡት አስተያየት ነው።
ከቁምላቸው ዳኘ ፌስቡክ ገጽ ተወሰደ #Kumlachew_Dagne
Thank you all*via #AleHig

Mikias Melak & Associates Law Office

🔴Attorney and Legal Consultant ጠበቃና የሕግ አማካሪ

Website & Social Media
Linktree:📱📱📱📱📱📱📱📱  

https://www.linkedin.com/in/mikias-melak-76499811a?utm_source=share&utm_campaign=share_via&utm_content=profile&utm_medium=android_app

📱Facebook:
https://www.facebook.com/share/1BXx3RSsLZ/

📱Telegram: ✉️ @MikiasMelak⭐️📱

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com

Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595

Our Commitment
alehig.com
📊አለሕግ🔽
🔠🔠🔠    🔠🔠🔠
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት


We provide expert legal advice, support, and resources on various laws, proclamations, regulations, and directives to empower and guide you.

Feel free to reach out anytime‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍385🔥1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#AleHig

Mikias Melak & Associates Law Office

🔴Attorney and Legal Consultant ጠበቃና የሕግ አማካሪ

📱📱📱📱📱📱📱  

https://www.linkedin.com/in/mikias-melak-76499811a?utm_source=share&utm_campaign=share_via&utm_content=profile&utm_medium=android_app

📱Facebook:
https://www.facebook.com/share/1BXx3RSsLZ/

📱Telegram: ✉️ @MikiasMelak⭐️📱

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com

Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595

Our Commitment
alehig.com
📊አለሕግ🔽
🔠🔠🔠    🔠🔠🔠
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት


Feel free to reach out anytime‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍6
ሰ/መ/ቁ. 136305 
ቀን: 26/03/2010 

ክርክሩ፣
ተጠሪቷ ወ/ሮ ብዙነሽ በየነ፣ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን የሚገኝ ቤት ከአባታቸው የወረሱት ሲሆን፣ አመልካቹ አቶ አየናቸው ካሣ ቤቱን ከሶስተኛ ወገን (ወ/ሮ የሺ አዱኛ) በህጋዊ በገንዘብ መግዛታቸውን በመከራከር ይግባኝ በማቅረባቸውን ነው።

ዋና ጉዳዮች:
1. የልጅ ድርሻ ጥያቄ: ቤቱ በዋናነት የሟቹ አቶ ቢጂጋ የወረሰው ንብረት ሲሆን፣ ልጃቸው ረቂቁ ጌታቸው ድርሻ እንዳለው ተገልጿል። የሽያጭ ውሉ የዚህን ሕፃን ድርሻ ያለተገባው ስልጣን እና እርሱን ሳያካትት ተፈጽሞ ስለነበረ፣ ውሉ በህግ የማያረጋገጥ ነበር። 
2. የህግ ጥበቃ: በኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 36(2) መሠረት፣ የሕፃናት መብት ቅድሚያ ስለሚሰጥ፣ የሽያጭ ውሉ የሕፃኑን ድርሻ እንዳለመጠበቅ ተደርጎ ተገምግሟል። 
3. የተቃውሞ አቤቱታዎች: አመልካቹ በተደረገው ውሳኔ ተቃውመው ወደ ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች አቤቱታ ማቅረባቸው ቢሆንም፣ ሁሉም ደረጃዎች የታችኛው ፍርድ ቤት ውሳኔን አጸድቀዋል። 

የፍርድ ቤቱ ውሳኔ:
- የሽያጭ ውሉ የሕፃኑን ድርሻ ስላላካተተ እና ህጋዊ ስልጣን የለውም፣ ውሉ ፈርሷል**። 
- አመልካቹ ቤቱን ለቀው �ይዘው ለተጠሪቷ እንዲመለስ ተደረገ። 
- ውሳኔው በሁሉም የፍርድ ቤት ደረጃዎች (ከዞን እስከ ሰበር ሰሚ ችሎት) ተረጋግጧል። 

ማጠቃለያ፣
ፍርድ ቤቶቹ የሕፃናትን የውርስ መብት በህገ መንግሥታዊ ጥበቃ በመጠበቅ፣ የተጠሪቷን የቤት ይገባኛል የሚል ጥያቄ አጸድቀዋል። አመልካቹ የቀረበው አቤቱታ ተቀባይነት አላገኘም። 
#AleHig

Mikias Melak & Associates Law Office

🔴Attorney and Legal Consultant ጠበቃና የሕግ አማካሪ

📱📱📱📱📱📱📱  

https://www.linkedin.com/in/mikias-melak-76499811a?utm_source=share&utm_campaign=share_via&utm_content=profile&utm_medium=android_app

📱Facebook:
https://www.facebook.com/share/1BXx3RSsLZ/

📱Telegram: ✉️ @MikiasMelak⭐️📱

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com

Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595

Our Commitment
alehig.com
📊አለሕግ🔽
🔠🔠🔠    🔠🔠🔠
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት


Feel free to reach out anytime‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍251
የውጭ ዜጎች የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት የሚሆኑበትን አግባብ ለመደንገግ የወጣው ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ ተመራ

የሚኒስትሮች ምክር ቤት፤ የውጭ ዜጎች የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ወይም ባለይዞታ የሚሆኑበትን አግባብ ለመደንገግ የወጣው ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ እንዲተላለፍ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ውሳኔው የተላለፈው በዛሬው እለት በተካሄደው የምክር ቤቱ ስብሰባ ነው፡፡

ይህ የተገለጸው ዛሬ ሐሙስ ሚያዝያ 23/2017 ከተካሄደው 44ኛ መደበኛ ስብሰባ በኋላ ነው፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዚህ ስብሰባ ላይ በአራት ረቂቅ አዋጆች ላይ ተወያይቶ ወደ ፓርላማ ሲመራ፤ ሁለት ደንቦች በሥራላይ እንዲውሉ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ የውጭ ዜጎች የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት የሚሆኑበትን አግባብ ለመደንገግ የወጣው ረቂቅ አዋጅ ወደ ፓርላማ እንዲመሩ ከተደረጉት መካከል ሆኗል፡፡

ምክት ቤቱ ሕጉ የዜጎችን የመሬት ይዞታ የማግኘትና የመጠቀም መብት በማያጣብብ መልኩ ለውጭ ዜጎች ህጋዊ አሠራር መዘርጋቱ “የውጭ ካፒታል በሀገሪቱ ሥራ ላይ እንዲያውሉ ለማበረታታት፣ የቤት ልማት እና ተደራሽነትን ይበልጥ ለማነቃቃት፣ የመኖሪያ ቤት ፍላጎት እና አቅርቦት ሚዛን ለማስጠበቅ እና ለዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ትልቅ ጠቀሜታ ይኖረዋል” ብሏል፡፡

በተመሳሳይ ዛሬው ስብሰባ ምክር ቤቱ የተወያየው በአፍሪካ ፋይናንስ ኮርፖሬሽን መቋቋሚያ ስምምነት ማጽደቂያ ረቂቅ አዋጅ ላይ መሆኑን ገልጿል፡፡ ትኩረቱን በመሠረተ ልማት፣ በተፈጥሮ ሀብት እና በኢንዱስትሪ ዘርፍ ልማት ላይ በማድረግ ለግል አልሚዎችና ለመንግሥት አካላት የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፍ ለመስጠት የተቋቋመው ኮርፖሬሽኑ፤ ኢትዮጵያ በአባልነት መቀላቀሏ ለግሉ ዘርፍ ተጨማሪ የፋይናንስ ሀብት በማቅረብና የግል ዘርፉን የማይተካ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽነት ሚና በማሳደግ ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ለማፋጠንና ድህነትን ለመቀነስ ጠቀሜታ ያለው እንደሆነም ገልጿል፡፡

በምክር ቤቱ ውይይት ተደርጎበታል የተባለው ሌላው ጉዳይ ለአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና ስምምነት የዕቃዎች ቀረጥ ምጣኔ ቅነሳን ለማስፈፀም በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ ስምምነቱ በአባል ሀገራት መካከል ንግድ እንዲስፋፋ፣ የገበያ ትስስሩ እንዲጠናከር፣ የእሴት ሠንሰለቱ እንዲጎለብት እና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን ማበረታታት የሚያስችል እንደሆነም ነው የተገለጸው፡፡ በአባል ሀገሮች መካከል የሚደረጉ ግብይቶች በታሪፍ ምክንያት ሳይደናቀፉ የእቃዎች ፍሰት የተሳለጠ እንዲሆን ከአባል አገራት በሚመጡ እቃዎች ላይ የጉምሩክ ታሪፍ ምጣኔ ለይቶ መወሰን አስፈላጊ መሆኑን ውይይት ተደርጎበት፤ ምክር ቤቱ ደንቡ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተፈፃሚ እንዲሆን በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

ምክር ቤቱ እንዳወጣው መረጃ ከሆነ፤ ቀጥሎ የተወያየው በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ለሚሰጡ አገልግሎቶች እና በኢ.ፌዲ.ሪ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን ለሚሰጡ አገልግሎቶች የሚከፈሉ የአገልግሎት ክፍያዎችን ለመወሰን በቀረቡ ሁለት ረቂቅ ደንቦች ላይ ነው፡፡ ተቋማቱ አገልግሎት ለመስጠት የሚያወጡትን ወጪ በመሸፈን፣ ገቢያቸውን አሳድገው ጥራት ያለው አገልግሎት በመስጠት የተገልጋይ እርካታ ማሳደግ የሚያስችል የደንበኞችን አቅም ባገናዘበ መልኩ የአገልግሎት ክፍያ መወሰን አስፈላጊ መሆኑን በመጥቀስ፤ በረቂቅ ደንቦቹ ላይ በስፋት ከተወያየ በኋላ በነጋሪት ጋዜጣ ታትመው ከወጡበት ቀን ጀምሮ በሥራ ላይ እንዲውሉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ (ሚንበር ቲቪ)

★ ★ ★ Minber TV | EthioSat | 11545 | H | 45000
#ሚንበር_ቲቪ #ሁለንተናዊ_ከፍታ! #Minber_TV
#AleHig
Mikias Melak & Associates Law Office

🔴Attorney and Legal Consultant ጠበቃና የሕግ አማካሪ

Website & Social Media
Linktree:📱📱📱📱📱📱📱📱  

https://www.linkedin.com/in/mikias-melak-76499811a?utm_source=share&utm_campaign=share_via&utm_content=profile&utm_medium=android_app

📱Facebook:
https://www.facebook.com/share/1BXx3RSsLZ/

📱Telegram: ✉️ @MikiasMelak⭐️📱

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com

Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595

Our Commitment
alehig.com
📊አለሕግ🔽
🔠🔠🔠    🔠🔠🔠
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት


We provide expert legal advice, support, and resources on various laws, proclamations, regulations, and directives to empower and guide you.

Feel free to reach out anytime‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍6😁1
ፍትህ ለድሬድዋ ሴት የህግ ተማሪዎች
👇👇👇 #ፍትህ #justice #Alehig #ጾታ_እኩልነት #Ethiopia #አለሕግ
#AffirmativeAction #ladiesfirst
👍22🤔31
በወንጀል የተገኘ ንብረት ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር አዋጅ ላይ የተደቀኑ ስጋቶች፣

ዓለም አቀፍና የሕገ-መንግስት ብርሃን ውስጥ ሲፈተሽ በኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቆ ሥራ ላይ የዋለው በወንጀል የተገኘ ንብረትን ሕጋዊ ማስመሰልን እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከል የወጣው አዋጅ፣ ከአገራዊ የሕገ-መንግስት ድንጋጌዎችና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ሕጎች አኳያ ሲታይ በርካታ ጥያቄዎችን የሚያስነሳ ሆኖ አግኝተነዋል። በተለይም "በሽፋን ስር ምርመራ የሚያደርጉ መርማሪዎች ከግድያ ውጪ በሆነ በማንኛውም ወንጀል ተጠያቂ እንደማይሆኑ" የሚያዘው ድንጋጌ፣ የሕግ የበላይነትን እና የሰብዓዊ መብቶችን መርሆዎች አደጋ ላይ የሚጥል ነው የሚሉ አስተያየቶች በስፋት እየተሰሙ ነው።

#የኢትዮጵያ_ሕገ-መንግስት እና #የአዋጁ_ተግዳሮቶች
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግስት፣ በመሰረታዊ መብቶችና ነጻነቶች ዙሪያ ሰፊ ድንጋጌዎችን አስቀምጧል። በተለይም አንቀጽ 13 የመንግስት አካላት ሁሉ በሕገ-መንግስቱ የተደነገጉትን የሰብዓዊ መብቶችና ነጻነቶች የማክበርና የማስከበር ግዴታ እንዳለባቸው ይደነግጋል። አንቀጽ 14 የሰብዓዊ ክብርን፣ አንቀጽ 15 የሕይወት መብትን፣ አንቀጽ 16 የአካል ደህንነት መብትን፣ አንቀጽ 17 የነጻነት መብትን፣ አንቀጽ 18 ደግሞ ጭካኔ የተሞላበት፣ ኢ-ሰብዓዊ ወይም አዋራጅ ቅጣት ወይም አያያዝን ይከለክላል።
አዲሱ አዋጅ "መርማሪዎች ከግድያ ውጪ በማንኛውም ወንጀል አይጠየቁም" በሚለው ድንጋጌው፣ እነዚህን የሕገ-መንግስት መርሆዎች የሚጻረር ነው የሚል ጠንካራ መከራከሪያ ይቀርባል። አንድ መርማሪ ገንዘብ በመቀበል፣ ንጹሃንን በማሰቃየት ወይም ሌላ የመብት ጥሰት በመፈጸም ተጠያቂነትን የሚያመልጥ ከሆነ፣ የሕገ-መንግስቱ የመብቶች ጥበቃ ዋጋ የለውም የሚል ስጋት ይፈጠራል። ይህ ድንጋጌ ለሙስና፣ ለሥልጣን አላግባብ መጠቀም እና ለሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ክፍት በር ሊከፍት ይችላል።

#ዓለም_አቀፍ_ሕጎችና_ስምምነቶች
ኢትዮጵያ በርካታ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ስምምነቶችንና ኮንቬንሽኖችን አጽድቃለች።

ከእነዚህም መካከል፡-
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቻርተር (UN Charter): ይህ ቻርተር የሰብዓዊ መብቶችን ማክበር እና ማስከበር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መሰረታዊ ዓላማዎች አንዱ እንደሆነ ይገልጻል።

ዓለም አቀፍ የሲቪል እና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን (International Covenant on Civil and Political Rights - ICCPR): ኢትዮጵያ ይህን ቃል ኪዳን አጽድቃለች። ቃል ኪዳኑ በግልጽ የሕይወትን፣ የነጻነትን፣ ከማሰቃየት የመጠበቅን እና የሕግ ፊት እኩልነትን መብቶች ያስቀምጣል። የትኛውም አገር ሽብርተኝነትን ለመዋጋት በሚል ሰበብ እነዚህን መሰረታዊ መብቶች መርገጥ እንደሌለበት ዓለም አቀፍ ሕግ ያዛል።

የማሰቃየትን እና ሌሎች ጭካኔ የተሞላባቸው፣ ኢ-ሰብዓዊ ወይም አዋራጅ ቅጣቶችን ወይም አያያዞችን የሚከለክል ኮንቬንሽን (Convention Against Torture and Other Cruel, Inhuman or Degrading Treatment or Punishment - CAT): ኢትዮጵያ የዚህ ኮንቬንሽን አባል ስትሆን፣ ማሰቃየትን በማንኛውም ሁኔታ ለመከልከል እና ወንጀለኞችን ተጠያቂ ለማድረግ ግዴታ አለባት። አዲሱ አዋጅ "መርማሪው ማሰቃየት ቢፈጽም አይጠየቅም ማለት ነው?" የሚለው ስጋት፣ የዚህን ኮንቬንሽን መርሆዎች የሚጻረር ነው።
በተጨማሪም፣ ገንዘብ ሕገወጥ የማድረግ (Money Laundering) እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት (Terrorist Financing) ወንጀሎችን ለመዋጋት የወጡ ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ቢኖሩም፣ እነዚህ ስምምነቶች ወንጀልን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት የሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩ አበክረው ያሳስባሉ። የፋይናንስ ተግባር ግብረ ኃይል (Financial Action Task Force - FATF) ያሉ ድርጅቶችም ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመዋጋት የሚረዱ ደረጃዎችን ሲያወጡ፣ የሕግ የበላይነትን እና የመብቶችን ጥበቃ ግምት ውስጥ ያስገባሉ።

#የሞራል_ሕግ_እና_የሕግ_የበላይነት
ከሕግ በላይ የሆነ የሞራል ሕግ አለ የሚለው መርህ በበርካታ ፍልስፍናዎች እና የሕግ አስተምህሮዎች ዘንድ ተቀባይነት አለው። ይህ ማለት አንድ ሕግ በጽሑፍ ቢቀመጥም፣ ዓለም አቀፍ የሞራል እና የፍትህ መርሆዎችን የሚጻረር ከሆነ ተቀባይነት የለውም። "ከግድያ ውጪ በሌላ ወንጀል አይጠየቅም" የሚለው ድንጋጌ፣ የሕግ የበላይነትን እና የፍትህን መሰረታዊ መርሆዎች የሚዳፈር በመሆኑ፣ በብዙዎች ዘንድ የሞራል ብቁነት የለውም የሚል ትችት ይቀርብበታል። የሕግ የበላይነት ሁሉም ሰው ከሕግ በታች እኩል ነው የሚለውን መርህ ያመለክታል፤ የመርማሪዎችን ተጠያቂነት ማስቀረት ይህን መርህ ይጥሳል።

#የመናገር_እና_የመሰብሰብ_ነጻነት
አዋጁ በተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በጋዜጠኞች እና በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ላይ ጫና ይፈጥራል የሚለው ስጋትም ትልቅ ቦታ አለው። የኢትዮጵያ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 29 የመናገር እና የመግለጽ ነጻነትን፣ አንቀጽ 30 የመሰብሰብ፣ የመመደብ እና ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትን ያረጋግጣል። አዋጁ ከእነዚህ መብቶች ጋር እንዴት እንደሚጣጣም ግልጽ የሆነ ማብራሪያ ያስፈልገዋል። የመንግስት ተቃዋሚዎችን ወይም ሕጋዊ በሆነ መንገድ የፖሊሲ ትችት የሚያቀርቡ አካላትን "ሽብርተኝነትን መርዳት" በሚል ሰበብ ኢላማ ለማድረግ የሚያስችል ክፍተት እንዳለው የሚሰጋ ከሆነ፣ ለዴሞክራሲያዊ ምህዳር መስፋፋት እንቅፋት ይሆናል።
መደምደሚያ
ሽብርተኝነትን እና ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውርን መዋጋት የማንኛውም ሉዓላዊ መንግስት ሕጋዊ ግዴታ እና የዜጎች ደህንነት ጉዳይ ነው። ይሁን እንጂ፣ ይህ ትግል የዜጎችን መሰረታዊ መብቶች እና የሕግ የበላይነት መርሆዎችን ሳያጓድል መከናወን ይኖርበታል። አዲሱ አዋጅ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ሕጎችን እና የኢትዮጵያን ሕገ-መንግስት መሰረታዊ ድንጋጌዎችን የሚያከብር መሆኑን ለማረጋገጥ፣ ሰፊ ውይይት እና ምናልባትም ክለሳ ሊደረግበት ይገባል። አለበለዚያ፣ ሕግን ለማስከበር በሚል የሚወጡ ሕጎች ራሳቸው ለሕገ-ወጥነት በር ከፍተው የሞራል እና የሕግ ቀውስ ሊፈጥሩ ይችላሉ።

እናንተስ፣ አዲሱ አዋጅ የሀገራችንን ሕገ-መንግስት እና ዓለም አቀፍ ሕጎችን ያከብራል ብላችሁ ታስባላችሁ?

የህዝብ ጤና የሀገር ጤና ነው!

በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
ሚኪያስ መላክ ተዘጋጅቶ በአለሕግ አማራጭ የሕግ እውቀት እና አገልግሎት ቀረበ ነው።
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
10
#የአዋጁ_አስፈላጊነትና_የሕግ_ከለላ_ስጋቶች
የፍትህ ሚኒስቴር የአዋጅ ቁጥር 1387/2017ን በተመለከተ ማብራሪያ ቢሰጥም፣ የሕጉ አተገባበር በዜጎች መሠረታዊ ሰብዓዊ መብቶች እና የሕግ የበላይነት ላይ ሊያስከትል የሚችለው ተጽእኖ አሁንም አሳሳቢ ሆኖ ቀጥሏል። "አላምንም" የሚለው ምላሽዎም፣ በዚህ አዋጅ ዙሪያ ያለውን ሰፊ አለመተማመን የሚያንፀባርቅ ነው።

#እስቲ_ይህንን_ስጋት በዝርዝር እንመልከት።

#የአዋጁ_አስፈላጊነትና_የሕግ_ከለላ_ስጋቶች
አዋጅ ቁጥር 1387/2017 የወንጀል ድርጊት ማትረፍ እንደማይቻል ለማረጋገጥ፣ የገንዘብ ሕገወጥነትንና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከል ያለመ መሆኑን የፍትህ ሚኒስቴር ያብራራል። አዋጁ ከቀድሞው አዋጅ ቁጥር 780/2005 በተሻለ መልኩ 21 አመንጪ ወንጀሎችን በዝርዝር ማካተቱ፣ ጠንካራ የአሰራር ስርዓት ማበጀቱ እና የዋና ተጠቃሚዎችን ማንነት የመለየት ሥርዓት መዘርጋቱ፣ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመከላከል ከዓለም አቀፍ መስፈርቶች ጋር ለመጣጣም ጠቃሚ እርምጃዎች ናቸው።
ሆኖም፣ የአዋጁ ዋነኛ አወዛጋቢ ነጥብ "በሽፋን ስር ምርመራ" ለሚያካሂዱ መርማሪዎች የሚሰጠው የሕግ ከለላ (Immunity) ነው። ሚኒስቴሩ ይህ ከለላ የሚሰጠው መርማሪው "በራሱ ፈቃድ አስቦና ፈቅዶ ሳይሆን ያለፈቃዱ፣ ተገዶ፣ በተጽእኖ፣ ወይም ከአቅሙ በላይ በሆነ ማንኛውንም ምክንያት ሌላ ከባድ ጉዳትን ለማስቀረት ወይም የተሰጠውን ሕጋዊ ተልእኮ ለማሳካት ሲል" ለሚፈጽመው ወንጀል መሆኑን ቢያብራራም፣ ይህ ትርጓሜ በተግባር አደገኛ ስጋቶችን ይዞ ይመጣል።

#የግዳጅ" ትርጓሜ ብዥታ እና የተጠያቂነት ክፍተቶች
የ"ግዳጅ" የሚለው ቃል አተረጓጎም እና አተገባበር አሁንም ግልጽ አይደለም። መርማሪው በእርግጥ ተገዶ ነው ወይስ በፈቃደኝነት ወንጀል የፈጸመው? ይህንን ለመወሰን የሚያስችል ግልጽ፣ ተጨባጭ እና ገለልተኛ የክትትልና የቁጥጥር ሥርዓት ከሌለ፣ የሕግ ከለላው ለሥልጣን አላግባብ መጠቀም ምቹ ሽፋን ሊሆን ይችላል። ሕግን አስከባሪ አካላት ራሳቸው ለሕግ ተገዢ መሆናቸውን ማረጋገጥ እጅግ አስፈላጊ ነው።

በተጨማሪም፣ አዋጁ "ከግድያ ውጪ" የሚል ገደብ ቢያስቀምጥም፣ እንደ ማሰቃየት፣ ሕገወጥ እስር፣ ከሕግ ውጪ የሆነ የገንዘብ ዝውውር እና ሌሎች የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በመርማሪዎች ቢፈጸሙ፣ ተጠያቂነትን የሚያረጋግጥበት መንገድ ምን ያህል ጠንካራ ነው የሚለው ጥያቄ መልስ አላገኘም። የኢትዮጵያ ሕገ-መንግስት (አንቀጽ 18) ከጭካኔ የተሞላበት፣ ኢ-ሰብዓዊ ወይም አዋራጅ ቅጣት የመጠበቅ መብትን ይደነግጋል። ኢትዮጵያ የፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ሕጎች፣ በተለይም የማሰቃየትን የሚከለክል ኮንቬንሽን (CAT)፣ ማሰቃየትን ጨምሮ ማንኛውንም ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት ይከለክላሉ።
"በግዳጅ ተደረገ" በሚል ሽፋን እነዚህ ወንጀሎች ያለ ቅጣት እንዲያልፉ ከተደረገ፣ የአገር ውስጥም ሆነ ዓለም አቀፍ የሕግ ግዴታዎች ይጣሳሉ። ይህ ደግሞ እርስዎ የገለጹትን "ሕጋዊ ህገወጥ" ተግባራት መራባት ያስከትላል።

#ዲሞክራሲያዊ ምህዳር እና #የሕግ_የበላይነት_ስጋት
አዋጁ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት ያለመ ቢሆንም፣ የፖለቲካ ተቃዋሚዎችን፣ ጋዜጠኞችን እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን ኢላማ ለማድረግ የሚያስችል ክፍተት እንዳለው የሚሰነዘረው ስጋት ተገቢ ነው። የኢትዮጵያ ሕገ-መንግስት (አንቀጽ 29 እና 30) የመናገር፣ የመሰብሰብና የመደራጀት መብቶችን በግልጽ ያረጋግጣል። ማንኛውም ሕግ እነዚህን መብቶች ምክንያታዊ በሆነ መልኩ ብቻ ሊገድብ ይገባል እንጂ ሊያጠፋ አይገባም። የመንግስት ተቃዋሚዎችን ወይም ሕጋዊ በሆነ መንገድ የፖሊሲ ትችት የሚያቀርቡ አካላትን "ሽብርተኝነትን መርዳት" በሚል ሰበብ ኢላማ ለማድረግ የሚያስችል ክፍተት እንዳለው የሚሰጋ ከሆነ፣ የሀገሪቱ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት በእጅጉ ይጎዳል።

#የሕግ_የበላይነት ማለት ሁሉም ሰው፣ መንግስትንና ባለሥልጣናትን ጨምሮ፣ ለሕግ ተገዢ ነው ማለት ነው።

አዋጁ ለመርማሪዎች የሚሰጠው ልዩ የሕግ ከለላ፣ ይህንን መርህ የሚሸረሽር እና ከመደበኛ የፍትህ ሥርዓት በላይ የሆነ "ልዩ ሥርዓት" የሚፈጥር ሆኖ ከታየ፣ አለመተማመን መፈጠሩ አይቀሬ ነው። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ የመብቶች ጥሰት እና ተጠያቂነት አለመኖር ሲነሱ የቆዩ ስጋቶች እንደነበሩ ግምት ውስጥ ሲገባ፣ አዲሱ አዋጅ እነዚህን ስጋቶች ይበልጥ የሚያባብስ ነው የሚል ስሜት መፍጠሩ ተፈጥሯዊ ነው።

#የሕግ_ማዕቀፎች የሀገርን ደህንነት ማስጠበቅ ሲገባቸው፣ በተመሳሳይ መልኩ የዜጎችን መብት ዋስትና መስጠት እና የሕግ የበላይነትን ማክበር አለባቸው። አንዱን ለማስጠበቅ ሌላውን መስዋዕት ማድረግ ዘላቂ ሰላምንና መረጋጋትን አያመጣም። የአዋጅ ቁጥር 1387/2017 ተግባራዊነት፣ የመሠረታዊ መብቶችን እና የሕግ የበላይነትን ዋጋ እንዳይቀንስ ከፍተኛ ጥንቃቄ እና ቁርጠኝነት ይጠይቃል። ያለበለዚያ፣ አደገኛ ሁኔታዎችን በመፍጠር ወደ #"ሕጋዊ_ህገወጥ" ድርጊቶች ሊያመራ የሚችልበት ስጋት #አለ
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
ሚኪያስ መላክ ተዘጋጅቶ በአለሕግ አማራጭ የሕግ እውቀት እና አገልግሎት ቀረበ ነው።
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
13🔥1
በድብቅ የሚደረግ ምርመራ በአዲሱ አዋጅ መሰረት
የፍትሕ ሚኒስቴር በቅርቡ የጸደቀው፣ የወንጀል ንብረትን ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ፣ ከፍርድ ቤት ፈቃድ ውጪ የሚደረግ ምርመራን እንደማይፈቅድ አስታውቋል።
ይህ ማብራሪያ አዋጁን በተመለከተ በሕዝብ ዘንድ ያለውን የተሳሳተ ግንዛቤ ለመፍታት ያለመ ነው።
የፍትሕ ሚኒስቴር ማብራሪያ፦
ሚኒስቴሩ አዲሱ አዋጅ ከመደበኛው የወንጀል ምርመራ ሂደት የተለየ መንገድ እንደሚከተል አጽንኦት ሰጥቷል። እንዲህም ሲል አብራርቷል፦

ከተለመደው ምርመራ የተለየ ነው፡ እንደ ተለመደው ምርመራ፣ ተጠርጣሪዎችን በፍርድ ቤት ትእዛዝ መያዝ፣ ሰነዶችን መሰብሰብ እና ምስክሮችን መስማት የመሳሰሉትን ሂደቶች አይከተልም።

ውስብስብ ወንጀሎች ላይ ያተኩራል፡ አዋጁ ውስብስብ ወንጀሎችን ከመሰረቱ ለመለየት የሚያስችል የምርመራ ሂደትን የሚከተል ነው። ለምሳሌ፣ መርማሪ አካል፡-

እንደ ወንጀለኛ መስሎ ከወንጀለኞች ጋር ሊቀላቀል ወይም አብሮ ሊሰራ ይችላል።

እንደ ተባባሪ መስሎ አብሮ ውሎ ሊያድር ይችላል።

ወንጀለኞች ሲሸጡ ገዢ መስሎ፣ ሲገዙ ደግሞ ሻጭ መስሎ ሊሆን ይችላል።
የፍርድ ቤት ትእዛዝ ሚና፦
የፍርድ ቤት ትእዛዝ ግዴታ ነው፡ መርማሪው አካል ምርመራ ማድረግ የሚችለው የፍርድ ቤት ትእዛዝ ሲያገኝ ብቻ ነው።

የፍርድ ቤት ግልጽ መመሪያዎች፡ ፍርድ ቤት በአሳማኝ ምክንያት በሽፋን የሚደረግ ምርመራ እንዲደረግ ሲፈቅድ፣ አዋጁ በትእዛዙ ላይ የሚከተሉትን በግልጽ ማስቀመጥ እንዳለበት ደንግጓል፦
የምርመራው ዘዴ።
የአተገባበር ሁኔታ።
ምርመራው የሚከናወንበት ጊዜ።
የተሳሳቱ ግንዛቤዎች ማስተባበያ፦
ሚኒስቴሩ ስለ አዲሱ አዋጅ ያሉትን በርካታ የተሳሳቱ ግንዛቤዎችን አስተባብሏል፦

ማሰቃየት ወይም ማስገደድ የለም፡ አዋጁ ተጠርጣሪን አስሮ በማሰቃየት እንዲመረመር አይፈቅድም፣ እንዲሁም ማስረጃዎችን በማስገደድ እንዲሰበሰቡ አያደርግም።
ይህ ፈጽሞ ስህተት ነው።

ለወንጀል ድርጊት ተጠያቂነት፡ አዋጁ ወንጀል ለፈጸሙ መርማሪዎች ያለመከሰስ መብት አይሰጥም። ፍርድ ቤት በአሳማኝ ምክንያት በሽፋን ስር የሚደረግ ልዩ የምርመራ ዘዴ እንዲተገበር ሲፈቅድ፣ መርማሪው በተጠርጣሪዎች ወይም በሌላ ሦስተኛ ወገኖች ላይ ወንጀል ቢፈጽም፣ በወንጀል ይጠየቃል።
መርማሪ ከክስ ነጻ የሚሆንባቸው ሁኔታዎች፦
ሚኒስቴሩ፣ መርማሪ ከወንጀል ክስ ነጻ የሚሆንበትን ልዩ ድንጋጌ አስረድቷል፤ ይህ ግን ወንጀል ለመፈጸም አጠቃላይ ያለመከሰስ መብት አይደለም፦

ይህ ነጻ መሆን የሚመለከተው መርማሪው ከተጠርጣሪዎች ጋር የወንጀል ተካፋይ ወይም ግብረ-አበር ሲሆን፣ ይህን ያደረገው በራሱ ፈቃድ አስቦና ፈቅዶ ሳይሆን፦
ያለፈቃዱ፣
ተገዶ፣
በተጽእኖ፣
በተጠርጣሪዎች ሕገ ወጥ ትዕዛዝ፣ ወይም

ከአቅሙ በላይ በሆነ በማንኛውም ምክንያት ሌላ ከባድ ጉዳትን ለማስቀረት ወይም የተሰጠውን ሕጋዊ ተልእኮ ለማሳካት ሲል ወንጀል የሚፈጽምበት ሁኔታ ሲኖር ነው።
ይህ ድንጋጌ የሚያሳየው መርማሪ በምርመራ ወቅት ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያት (ከግድያ ውጪ) ማንኛውንም ዓይነት ወንጀል ቢፈጽም ከወንጀል ክስ ነጻ የሚደረግበትን ሁኔታ ለማመላከት የተደነገገ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።
የሕዝብ ስጋቶች፦
ይህ አዋጅ፣ መርማሪዎችን በአቅማቸው በላይ በሆነ ምክንያት (ከግድያ በስተቀር) ማንኛውንም ወንጀል ቢፈጽሙ ተጠያቂ የማያደርግ መሆኑ፣ ከምክር ቤት ትችት ሲቀርብበት ቆይቷል። ተቺዎች ይህ ድንጋጌ መርማሪዎችን ወንጀል እንዲፈጽሙ በር ይከፍታል የሚል ስጋት አላቸው።
ይህ የፍትሕ ሚኒስቴር ማብራሪያ፣ በድብቅ የሚደረጉ ምርመራዎች የሚከናወኑበትን ሁኔታዎች እና ገደቦች ግልጽ ለማድረግ ያለመ ሲሆን፣ የፍርድ ቤት ቁጥጥር ወሳኝ መሆኑን በማጉላት፣ ሊኖር በሚችል አላግባብ አጠቃቀም ዙሪያ የሚነሱ ስጋቶችን ለመፍታት ይሞክራል።
ፍትሕ ሚኒስቴር
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
12👏5
ሕግ ማለት ሰውን የሚያንጽ፣ የተሻለ ዜጋ የሚያደርግ፣ የሚያበለጽግ እና ወደተሻለ የኢኮኖሚ ደረጃ ለመድረስ በር የሚከፍት ሥርዓት የሚዘረጋ መሆን አለበት። ሕግ ሰዎች የሚገደቡበት፣ የሚያስጨንቅ፣ የሚያደኸይ፣ የሚጎዳና የሚያንገበግብ መሆን የለበትም። በተሻለ ነፃነት የሚያኖር እና ሕጉን ለሚያከብሩ የሚያበረታታ ሲሆን፣ ለማያከብሩት ግን ደግሞ በተቃራኒው በዋናነት የሚያስተምር ሲሆን ነገር ግን መተላለፉ ሲደጋገም የሚቀጣ መሆን አለበት።
#Mikias_Melak
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
14👍5🤔1
የንግድ ሥራ ፍቃድ ሳይኖራቸው በሞያ ፍቃድ ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ ጠበቆች ፣የኢንሹራንስ ወኪሎች ፣ኢንሹራንስ ጉዳት ገማች ግለሰቦች በሚመለከት:-

➡️ ከግብር አመቱ አጠቃላይ እንደ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።

➡️ የንግድ ሥራ ያልሆነ ገቢ ያላቸው የመኖሪያ ቤት አከራዮች ከግብር አመቱ አጠቃላይ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።

➡️ በግል ኮድ 02 እና በንግድ ኮድ 03 ተሸከርካሪ የኪራይ አገልግሎት የሚሰጡ አጠቃላይ የኪራይ ገቢ ላይ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት በመረጃ የሚወሰን በመሆኑ ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።

➡️ በህግ ደረሰኝ የመጠቀም ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው የከተማ ውስጥ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎች /በቴክኖሎጂ ስምሪት የሚሰጣቸውን የሜትር ታከሲዎች ጨምሮ/ የገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 ሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ መወሰኑን ይገልጻል።

(ተጨማሪውን ከተያያዘው ደብዳቤ ይመልከቱ)

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
Mikias_Melak
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
8👍1
ከውርስ መንቀል (Dishersion)
ከውርስ መንቀል ማለት አንድ ተናዛዥ የውርስ ሕግ በሚደነግገው መሠረት ባደረገው ኑዛዜ ውስጥ፣ ምክንያቱን በግልጽ በመግለጽ ወይም በዝምታ፣ ከወራሾቹ አንዱን ወይም ከአንድ በላይ የሆኑትን ወራሾች በውርሱ እንዳይካፈሉ ያደረገበት ሥርዓት ነው። ይህ በውርስ ሕግ እውቅና እና ውጤት የሚሰጠው የሕግ ሂደት ነው።
* ከወራሽነት ሙሉ በሙሉ ማውጣት: ከውርስ መንቀል ማለት ከውርስ ሀብቱ ምንም ዓይነት ድርሻ አለማግኘት እንጂ አነስተኛ ድርሻ ማግኘት አይደለም።
* የሕግ ድንጋጌዎች:
* የፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 937/1/ ተናዛዡ ከወራሾቹ አንዱን ከወራሽነት የመንቀል መብት እንዳለው ይደነግጋል።
* የፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 938/1/ ደግሞ፣ ተናዛዡ ልጅን ወይም ወደታች የሚቆጠረውን ወራሽ ለመንቀል የደረሰበትን ምክንያት በኑዛዜው ውስጥ ካልገለፀ በቀር፣ ያደረገው ኑዛዜ እንደማይፀና ያስቀምጣል። ይህ የሚያሳየው ህጉ የቅርብ ወራሾችን ከውርስ የመንቀል ጉዳይ ላይ ጥብቅ መስፈርቶችን እንዳስቀመጠ ነው።
* ተፈጻሚነት: ይህ እርምጃ ሊወሰድ የሚችለው ሕጉ ወራሾች በሚያደርጋቸው ግለሰቦች ላይ ብቻ ነው። አንድ ግለሰብ የሚወረሰው በ3ኛ ወይም 4ኛ ደረጃ ወራሾች በሚሆኑ ዘመዶቹ ከሆነ፣ ለሌላ ሰው ሲናዘዝ እነዚህን ዘመዶቹን በዝምታ ከውርሱ መንቀል ይችላል።
* አላማ: ከውርስ መንቀል ወራሾችን ከውርስ ሀብት የሚያስወግድ ጠንካራ ውሳኔ ነው። ይህ ውሳኔ በሰከነ አእምሮ እና በቂ ምክንያት መወሰድ እንዳለበት ታሳቢ መሆን አለበት። ያለ በቂ ምክንያት እና በእልህ ወይም በቁጣ ተነሳስቶ የሚደረግ ውሳኔ በዘላቂነት በሰዎች መካከል የስሜት መሻከርን ሊያስከትል ይችላል።

በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ሚኪያስ መላክ ተዘጋጅቶ በአለሕግ አማራጭ የሕግ እውቀት እና አገልግሎት የቀረበ ነው።
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
12
ከውል ውጪ ስለሚደርስ ጉዳት ካሳ ማወቅ ያለብዎት ነገር
ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ጉዳት ሊደርስባቸው ይችላል።

እነዚህ ጉዳቶች ከወንጀል ድርጊት፣ ከውል ጥሰት ወይም ከውል ውጪ ከሚመጣ ኃላፊነት ሊነሱ ይችላሉ። የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የህግ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ከፍተኛ የህግ ባለሙያ የሆኑት አቶ ደመቀ ይብሬ እንደሚሉት፣ ከውል ውጪ በሚደርስ ጉዳት ህግ ዋነኛ ዓላማ ጉዳት ያደረሰውን አካል በመለየት ተጎጂው ተገቢውን ካሳ እንዲያገኝ ማስቻልና ሌሎችም ከዚህ እንዲማሩ ማድረግ ነው።

#ጉዳት ምንድን ነው?
የፍትሐ ብሔር ህጉ ለ"ጉዳት" የሚለው ቃል ቀጥተኛ ትርጉም ባይሰጥም፣ ከህጉ አጠቃላይ ይዘት በመነሳት በሰው ጥቅም፣ አካል ወይም ህይወት ላይ የሚደርስ ጉድለት መሆኑን መረዳት ይቻላል።

#ለካሳ ክፍያ መሟላት ያለባቸው ነገሮች
ከውል ውጪ ባለው የኃላፊነት ህግ መሰረት ካሳ ለማስከፈል፣ ተጎጂው ጉዳት እንደደረሰበት እና ጉዳቱም የደረሰው ኃላፊነት አለበት በተባለው ሰው ድርጊት ወይም እሱ ኃላፊነት በሚወስድባቸው ድርጊቶች መሆኑን ማረጋገጥ አለበት።
የኃላፊነት ምንጮች
ከፍተኛ የህግ ባለሙያው አቶ ደመቀ እንደሚጠቅሱት፣ ከውል ውጪ የሚደርስ ኃላፊነት ህግ መሰረት (የፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2027) ሶስት አይነት የኃላፊነት ምንጮች አሉ፦
#በጥፋት ላይ የተመሰረተ ኃላፊነት
#ጥፋት ሳይኖር የሚመጣ ኃላፊነት
#ሌላ ሰው ለሚያደርሰው ጉዳት የሚኖር ኃላፊነት
የጉዳት ዓይነቶች
የህግ ባለሙያው እንዳብራሩት፣ የተለያዩ የጉዳት ዓይነቶች አሉ።
1. ግልጽ የሆኑ ጉዳቶች
እነዚህ ጉዳቶች የተጎጂውን ንብረት ወይም ገንዘብ ነክ ጥቅም በቀጥታ የሚነኩ ናቸው። ይህ የጉዳት አይነት ቀጥታ ንብረት ላይ የሚደርስ ጉዳትን ወይም በአካልና በህይወት ላይ የሚደርስ ጉዳትን ያጠቃልላል።
ግልጽ የሆኑ ጉዳቶች አሁን የደረሱ ወይም ወደፊት የሚደርሱ ሊሆኑ ይችላሉ።

#አሁን የደረሱ ጉዳቶች: የፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2090 እንደሚያመለክተው፣ እነዚህ በአሁኑ ጊዜ በእርግጠኝነት የደረሱና በግልጽ የሚታወቁ ጉዳቶች ሲሆኑ፣ ከደረሱበት ጊዜ ጀምሮ የጉዳትና የካሳ መጠኑ በፍርድ ቤት እስከሚወሰንበት ጊዜ ድረስ ያለውን ይመለከታል።

#ወደፊት የሚደርሱ ጉዳቶች: የፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2092 እንደሚያስረዳው፣ በደረሰው ጉዳትና በካሳ ተመኑ ላይ ፍርድ ከተሰጠ በኋላ የማይቆሙና የሚቀጥሉ የጉዳት ዓይነቶች ናቸው።
2. የህሊና ጉዳት
ይህ የጉዳት አይነት የተጎጂውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማይጎዳ ሆኖም በስሜት፣ በሀዘን ወይም በሀፍረት መልክ የሚገለጽ ሞራላዊ ጉዳት ነው።
የጉዳት ካሳ ስሌት
ጉዳትን ተከትሎ የሚመጣው ካሳ፣ ለጉዳት ለደረሰበት ሰው የጉዳት መጠኑ ተሰልቶ በዛ ልክ የሚሰጠው ጥቅም ነው። የፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2090(1) እና 2091 ይህንን ያብራራል።
ለተጎጂው የሚገባውን ካሳ ለማስላት፣ የተጎጂውን የስራ ሁኔታ ማወቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አለው። ጉዳት የደረሰበት ሰው ተቀጥሮ የሚሰራ፣ የራሱን ስራ እየሰራ የሚኖር ወይም ስራ በመስራት ላይ ያልነበረ ሊሆን ይችላል።
1. ተቀጥሮ ለሚሰራ ሰው የሚሰጥ ካሳ
ጉዳቱ ከስራው ጋር የተገናኘ ከሆነ፣ የክርክሩ ሂደትና የካሳ አሰላል ስርዓቱ በአሰሪና ሰራተኛ ህግ (ቁጥር 1064/2010 እና 1156/2011) መሰረት ይመራል። ከስራው ጋር የማይገናኝ ከሆነ ግን በከውል ውጪ ኃላፊነት የህግ ድንጋጌዎች ይመራል።
#ጊዜያዊ ጉዳት: ጉዳቱ ጊዜያዊ ከሆነ፣ ስራ እስከሚጀምር ድረስ ሊያገኝ ይችል የነበረውን ያክል ካሳ ያገኛል።
#ከፊል ቋሚ ጉዳት: መስራት ባላስቻለው መጠን ልክ ይሰላል።
#ቋሚ ጉዳት: እስከ ጡረታ ጊዜው ድረስ ተሰልቶ ይሰጠዋል።
የአካል ጉዳት ሲደርስ፣ የወደፊት ጉዳት ካሳ ስሌት ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን፣ የሰራተኛውን የገቢ መጠን እና ተጎጂው ጡረታ ለመውጣት የቀረውን ጊዜ በደንብ ማጤን ያስፈልጋል።
2. የራሱን ስራ ለሚሰራ ሰው የሚሰጥ ካሳ
የራሱን ስራ እየሰራ ለሚተዳደር ሰው ካሳውን ለማስላት ገቢውን ለማወቅ አስቸጋሪ ሊሆን ቢችልም፣ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ወርሃዊ ወይም አመታዊ አማካይ ገቢውን በመመልከት ያጣውን ወይም ሊያጣ የሚችለውን ጥቅም በማስላት ካሳውን መተመን ይቻላል።
3. ስራ አጥ ለነበረ ሰው የሚሰጥ ካሳ
በህመም፣ ለመስራት ባለመፈለግ፣ የሚመጥነውን ስራ በማጣት ወይም በጠቅላላው ስራ አጥ በመሆን ስራ እየሰሩ ያልነበሩ ሰዎች ላይ ጉዳት ቢደርስባቸው የገቢውን መጠን ማወቅ ስለሚያስቸግር ካሳውን ማስላት ይከብዳል። በዚህ ጊዜ ዳኞች በፍትሃዊነት (በርትዕ) ካሳውን ለማስላት ይገደዳሉ።
4. በሞት ምክንያት የሚሰጥ ካሳ
በአደጋ ምክንያት ሞት ሲያጋጥም፣ ካሳ የመጠየቅ መብት ያለው ማነው የሚለው ወሳኝ ነው። የፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2095 መሰረት የሟች ባል/ሚስት፣ ወላጆች እና ተወላጆች ካሳ መጠየቅ ይችላሉ። ለእነዚህ ሰዎች የሚከፈለው ካሳ ቀለብ ስለሆነ፣ በቤተሰብ ህጉ መሰረት ቀለብ ጠያቂ ሊያሟላቸው የሚገቡ መስፈርቶችን ማሟላትና ማስረዳት ይጠበቅባቸዋል።
5. ለህሊና ጉዳት የሚሰጥ ካሳ
የህሊና ጉዳት የሰው ልጅ የውስጥ ስሜት ጉዳት በመሆኑ ካሳውን በገንዘብ መለካት አስቸጋሪ ነው። ሆኖም የህሊና ጉዳት ሲያጋጥም የገንዘብ ካሳ እንደሚከፈል በፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2105(1) ተቀምጧል።
የህሊና ጉዳት ካሳ የሚከፈለው በልዩ ሁኔታ በህግ ለተመለከቱ ጉዳቶች ብቻ እንጂ ሁልጊዜም ካሳ እንደማያስከፍል የፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2105(2) ይደነግጋል። የህሊና ጉዳት ካሳ የሚወሰነው ርትዕን መሰረት አድርጎ ሲሆን፣ የፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2106-2115 ይህንን ያብራራል። የህሊና ጉዳት ካሳ 1,000 ብር መብለጥ እንደሌለበት የፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2116(3) ያስቀምጣል።
የካሳ አከፋፈል ስርዓት
ጉዳት መድረሱ፣ ለጉዳቱ ማን ኃላፊነት እንደሚወስድና የካሳ ክፍያው መጠን ከተለየ በኋላ መወሰን ያለበት ሌላ ወሳኝ ጉዳይ የካሳ አከፋፈል ስርዓቱ ነው። የህግ ባለሙያው እንዳሉት፣ ሁለት አይነት የካሳ አከፋፈል ስርዓቶች አሉ፦
1. የቁርጥ ክፍያ
ይህ የካሳ ክፍያ የተወሰነበትን መጠን በአንድ ጊዜ ለባለመብቱ በመክፈል የሚፈጸም ነው። ይህ ዘዴ በብዙ ሀገራት የሚተገበርና መርህም ነው።
2. በየጊዜው የሚደረግ ክፍያ
መርሁ የጉዳት ካሳን በቁርጥ መክፈል ቢሆንም፣ በልዩ ሁኔታ ግን በየጊዜው እንዲከፈል ተደርጎ መወሰን እንደሚቻል በህጉ ተቀምጧል። ካሳን በየጊዜው እንዲከፈል ለመወሰን፣ የካሳው ባህሪ፣ የአካባቢ ሁኔታዎች እና የካሳ ከፋዩ ማረጋገጫ መስጠት ያለባቸው ነጥቦች ናቸው።
#Mikias_Melak
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
4