#አዲሱ_የካሳ_ህግ_ማብራሪያ
አዲሱ የካሳ አዋጅ ቁጥር 1161/2012 አንቀጽ 2(2) የንብረት ካሳ ማለት የመሬት ይዞታውን እንዲለቅ ለሚወሰንበት ባለይዞታ በመሬቱ ላይ ለሰፈረው ንብረት ወይም ላደረገው ቋሚ ማሻሻያ በዓይነት ወይም በገንዘብ ወይም በሁለቱም የሚከፈል ክፍያ ነው በማለት ይደነግጋል።
#ቋሚ ማሻሻያ ማለት በይዞታው ላይ የሚሰራ የምንጣሮ፣ ድልደላ እርከን ስራ፣ ውሃ የመከተር ስራ እና የግቢ ንጣፍና ማስዋብ የመሳሰሉት ስራዎች ይጠቃለላል በማለት ይደነግጋል ፡፡ በመሆኑም አዲሱ አዋጅ የተሻለ ነገር ይዞ የመጣው ካሳ የሚከፈለው ለሰፈረ ንብረት እና ለተደረገ ቋሚ ማሻሻል እንደሆነ ይደነግጋል፡፡
#ቋሚ ማሻሻል የሚለው አሁንም ሌላ ውዝግብ የሚያስነሳ ነው ምክንያቱም ከተዘረዘሩት ድርጊቶች ውጪ ያደረገው ለምሳሌ መሬት በተለያየ መንገድ ለም እንዲሆን፣ ምርታማ እንዲሆን የሰራው ስራ በየትኛው ነው ሚካተተው? ምንጣሮ ነው?
#አዲሱ_ አዋጅ_የያዛቸው_ትሩፋቶች
(1) #የቀዳሚነት መብት፡-
ቀድሞ በነበረው አዋጅ 455/97 ያልነበረ ነገር ግን አዲሱ አዋጅ ቁጥር 1161/11 አካቶ ያወጣው ሰዎች ቀድሞ ለፍተው ባለሙት የመሬት ይዞታቸው አቅም ያላቸው በሆኑ ጊዜ በከተማ ፕላን መሰረት ለብቻቸው ወይም በጣምራ ማልማት የሚችሉበት የቀዳሚነት መብት በአንቀጽ 7 ስር ማጎናፀፋ በጣም ጥሩ የሚባል ነው፡፡
(2) #ካሳ የማግኘት መብት:-
በአዲሱ አዋጅ ቁጥር 1161/11 አንቀፅ 8(1)(ሰ) ስር የልማት ተነሺውን ማስነሳት የሚቻለው ለተነሺው ካሳ ከተፈለ እና ምትክ ቦታ ወይም ቤት ከሰጠ በኋላ መሆን እንዳለበት አዋጁ ይደነግጋል፡፡በመሆኑም ሰዎች በይዞታቸው ካሳም ሳይከፈላቸው ምትክ ቦታም ሳይሰጣቸው እንዲነሱ ተደርጎ የመብት ጥሰት እየደረሰባቸው የነበሩ ባለይዞታዎች በጣም ብዙ የነበሩ በመሆኑ ይህ አዋጅ ህዝቡ ውስጥ የነበረው ችግር ለመፍታት ተነሺዎች ከመነሳታቸው በፊት አስቀድመው ካሳ እና ምትክ ቦታ ማግኘት እንዳለባቸው መደንገጉ በሕግ ደረጃም ቢሆን ጥሩ የሚባል ነው፡፡
(3) #ካሳ በወቅቱ ካልተከፈላቸው መልሶ የመያዝ መብት
ተነሺዎች የካሳ ግምት በጹሑፍ እንዲያውቁ ከተደረገ ቀን ጀምሮ በሶስት ወር ውስጥ ካሳ ካልተከፈላቸው በመሬት ይዞታቸው ከቋሚ ተክልና ግንባታ በስተቀር ሌሎች ስራዎች መስራት ይችላሉ በማለት ይደነግጋል፡፡ በተጨማሪ በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ተገቢው ካሳ ካልተከፈው በፕላን የሚፈቀድ እና ቀጣይ የቦታውን የልማት ወጪ በመንግስት ላይ የማያበዛ በመሬቱ ላይ ማንኛውም ስራ መስራት ይችላል በማለት ይደነግጋል።
ቢሆንም ግን ይህ ድንጋጌ እጅግ አሻሚ ነው ምክንያቱም መንግስት ካሳ ካልከፈለ በፕላን መሰረት ባለይዞታ ማንኛውንም ዓይነት ስራ መስራት እንደሚችል ከተደነገገ በኋላ በመንግስት የልማት ወጪ የማያበዛ ስራ ማለቱ ምን ማለት ነው? እጅግ በጣም ግልጽ ነት የጎደለው ነው፡፡
(4) #ተመጣጣኝ ካሳ ክፍያና ምትክ ቦታ
አዲሱ አዋጅ በመሬቱ ላይ ለተፈራ ንብረት፣ ቋሚ ማሻሻያ ባለይዞታው ንብረቱን ማዘዋወር የሚችል ከሆነ የማዘዋወሪያ ወጪ ወይም የትራንስፖርት/የማጓጓዣ ወጪ ከመክፈሉ በተጨማሪ ከገጠር መሬት ይዞታ ለሚነሳ የመሬት በላይዞታ ተነሺ ከተወሰደበት መሬት ተመጣጣኝ የሆነ ምትክ መሬት እና መሬት ይዞታው ከመልቀቅ በፊት ባሉ ሶስት ተከታታይ ዓመታት ውስጥ ከፍተኛ ምርት ያመረተበትን ምርት በወቅታዊ ዋጋ ተሰልቶ በ15 ተባዝቶ ይከፈላል በማለት ይደነግጋል፡፡
(5) #በአዋጅ አንቀጽ 2(4) የልማት ተነሽ ድጋፍ የመሬት ባለይዞታ ከመሬቱ በጊዜያዊም ሆነ በቋሚነት ሲነሳ ከአዲሱ አከባቢ ጋር መላመድ እንዲችል ከንብረት እና ከልማት ተነሽ ካሳ በተጨማሪ በዓይነት ወይም በገንዘብ የሚሰጥ ድጋፍ ነው፡፡ it is promising move አዲስ እና በጣም ጥሩ የሚባል ነው ነገር ግን ይህ ነገር የሚወሰነው በክልሎች መመሪያ ነው፣ መች ይሁን የሚወጣው? ባይወጣስ?
(6) #የወል ይዞታዎች ላይ ካሳ የሚከፈል መሆኑ
በእርግጥ ወል ይዞታና የመንግስት የወል የተቀላቀለ በመሆኑ በወል ይዞታዎች ላይ ካሳ ሲከፈል አይታይም፣ በዚህ አዋጅ የወል ይዞታ ማለት ከመንግስት ወይም ከግል ይዞታነት ውጭ የሚገኝና የአከባቢው ማህበረሰብ ለግጦሽ፣ ለደንና ለማህበራዊ አገልግሎት በጋራ የሚጠቀሙበት የመሬት ይዞታ ነው በማለት አንቀፅ 2(11) ይደነግጋል።
በመሆኑ የወል ይዞታዎች አገኘን ተብሎ በየ ደረጃው የሚገኙ የመንግስት አካል መሸንሸን አይችሉም ማለት ነው፡፡ የወል መሬቱ የካሳ ስሌት የወል መሬቱ ይሰጥ የነበረው ጥቅም ወይም ጥቅሙ የቀረባቸውን የአኗኗር ዘይቤ ወይም መተዳደሪያ መሰረት ያደረገ ሊሆን ይገባል፡፡ይሰጥ የነበረው ጥቅም ወቅታዊ የገበያ ዋጋ መሰረት ያደረገ ማለት ነው? አሁንም ግልፅነት ይጎድለዋል፡፡የወል መሬቱ የተወሰደባቸው የወል መሬቱ ተጠቃሚ አካል የተገኘው ገንዘብ ለማህበረሰቡ አባላት እኩል ሊካፈል ወይም በዓይነት ሊጠቀሙበት የሚችሉበትን መንገድ መቅረጽ አለበት በማለት አንቀፅ 13(3) ይደነግጋል፡፡ በመሆኑም የወል መሬት ያለካሳ የሚወስድ የመንግስት አካል ከድርጊቱ መቆጠብ አለበት፡፡
(7) #የልማት ተነሺ ካሳ የሚከፈል መሆኑ
የከተማ መሬት ባለይዞታ ከይዞታው በቋሚነት ተነሽ በሚሆንበት ጊዜ የሚከፈለው የልማት ተነሺ ካሳ እና የሚሰጠው ምትክ ቦታ ነው በማለት ይደነግጋል፡፡
የልማት ተነሺ ካሳ ማለት ባለይዞታው የመሬት ይዞታውን ሲለቅ በመሬቱ ላይ የመጠቀም መብቱ በመቋረጡ ምክንያት የሚደርስ ጉዳት ለማካካስ የሚከፈል ክፍያ ነው፡፡ይህ አይነቱ ካሳ የመጠቀም መብት በመኖሩ ብቻ የሚገኝ የካሳ ዓይነት ነው፡፡ ለከተማ ተነሺ በአከባቢ ለነበረው የማህበራዊ ትስስር መቋረጥና ለሚደርሰው የስነ-ልቦና ጉዳት ማካካሻ ይከፈለዋል መጠኑ በደንብ ይወሰናል 13(4)(ሠ) በማለት ይደነግጋል፡፡
ግን ይህ ካሳ በተግባር ተከፍሎ አያውቅም። #የማህበራዊ ትስስር መቋረጥና የስ-ልቦና ጉዳት ካሳ ማለት ለተጎጂ ከነበረበት አከባቢ በመነሳቱ የነበረው ማህበራዊ ትስስር በመቋረጡ የሚከፈል የጉዳት ማካካሻ ክፍያ ነው፡፡
በመሆኑም በከተማ መሬት ይዞታ የሚነሳ ሰው የልማት ተነሺነት ካሳ፣ምትክ ቦታ፣ቤት ፈርሶበት ከሆነ የቤት መስሪያ ዋጋና በቦታው እስኪገባ ባለው 2 ዓመት የሚኖርበት ቤት ወይም የወቅታዊ የኪራይ ገንዘብ ግምት እና የማህበራዊ ትስስር መቋረጥና የስነ-ልቦና ጉዳት ካሳ ይከፍለዋል፡፡በመሆኑም እነዚህ መብቶች በቀድሞ አዋጅ ያልነበሩ በአዲሱ አዋጅ የተካተቱ ጥሩና ተስፋ ሰጪ የመሬት ካሳ መብቶች ናቸው፡፡
#መልሶ ማቋቋም ፡- በአዋጅ አንቀጽ 16 የክልል መንግስት ወይም የአዲስ አበባ እና የድሬደዋ አስተዳደር ለካሳ ክፍያ እና ለመልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ ያቋቁማል በማለት ይደነግጋል፡፡ መልሶ ማቋቋም ማለት በተወሰደው መሬት ምክንያት የሚያገኙት ጥቅም ለሚቋረጥባቸው ተነሺዎች ዘላቂ የገቢ ምንጭ እንዲያገኙ የሚያስችል የሚሰጥ ድጋፍ ነው ። ጥያቄው ግን መልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ ባይቋቋምስ ❓ በየደረጃው የሚገኙ የመንግሰት እርከን ካሳን በሚመለከት አቤቱታ የሚሰማ ኮሚቴ አንኳን አላቋቋሙም መልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ ያቁማሉ ❓
ከ ኢትዮ ህግ ኧረ በህግ ገፅ ተገኘ
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
አዲሱ የካሳ አዋጅ ቁጥር 1161/2012 አንቀጽ 2(2) የንብረት ካሳ ማለት የመሬት ይዞታውን እንዲለቅ ለሚወሰንበት ባለይዞታ በመሬቱ ላይ ለሰፈረው ንብረት ወይም ላደረገው ቋሚ ማሻሻያ በዓይነት ወይም በገንዘብ ወይም በሁለቱም የሚከፈል ክፍያ ነው በማለት ይደነግጋል።
#ቋሚ ማሻሻያ ማለት በይዞታው ላይ የሚሰራ የምንጣሮ፣ ድልደላ እርከን ስራ፣ ውሃ የመከተር ስራ እና የግቢ ንጣፍና ማስዋብ የመሳሰሉት ስራዎች ይጠቃለላል በማለት ይደነግጋል ፡፡ በመሆኑም አዲሱ አዋጅ የተሻለ ነገር ይዞ የመጣው ካሳ የሚከፈለው ለሰፈረ ንብረት እና ለተደረገ ቋሚ ማሻሻል እንደሆነ ይደነግጋል፡፡
#ቋሚ ማሻሻል የሚለው አሁንም ሌላ ውዝግብ የሚያስነሳ ነው ምክንያቱም ከተዘረዘሩት ድርጊቶች ውጪ ያደረገው ለምሳሌ መሬት በተለያየ መንገድ ለም እንዲሆን፣ ምርታማ እንዲሆን የሰራው ስራ በየትኛው ነው ሚካተተው? ምንጣሮ ነው?
#አዲሱ_ አዋጅ_የያዛቸው_ትሩፋቶች
(1) #የቀዳሚነት መብት፡-
ቀድሞ በነበረው አዋጅ 455/97 ያልነበረ ነገር ግን አዲሱ አዋጅ ቁጥር 1161/11 አካቶ ያወጣው ሰዎች ቀድሞ ለፍተው ባለሙት የመሬት ይዞታቸው አቅም ያላቸው በሆኑ ጊዜ በከተማ ፕላን መሰረት ለብቻቸው ወይም በጣምራ ማልማት የሚችሉበት የቀዳሚነት መብት በአንቀጽ 7 ስር ማጎናፀፋ በጣም ጥሩ የሚባል ነው፡፡
(2) #ካሳ የማግኘት መብት:-
በአዲሱ አዋጅ ቁጥር 1161/11 አንቀፅ 8(1)(ሰ) ስር የልማት ተነሺውን ማስነሳት የሚቻለው ለተነሺው ካሳ ከተፈለ እና ምትክ ቦታ ወይም ቤት ከሰጠ በኋላ መሆን እንዳለበት አዋጁ ይደነግጋል፡፡በመሆኑም ሰዎች በይዞታቸው ካሳም ሳይከፈላቸው ምትክ ቦታም ሳይሰጣቸው እንዲነሱ ተደርጎ የመብት ጥሰት እየደረሰባቸው የነበሩ ባለይዞታዎች በጣም ብዙ የነበሩ በመሆኑ ይህ አዋጅ ህዝቡ ውስጥ የነበረው ችግር ለመፍታት ተነሺዎች ከመነሳታቸው በፊት አስቀድመው ካሳ እና ምትክ ቦታ ማግኘት እንዳለባቸው መደንገጉ በሕግ ደረጃም ቢሆን ጥሩ የሚባል ነው፡፡
(3) #ካሳ በወቅቱ ካልተከፈላቸው መልሶ የመያዝ መብት
ተነሺዎች የካሳ ግምት በጹሑፍ እንዲያውቁ ከተደረገ ቀን ጀምሮ በሶስት ወር ውስጥ ካሳ ካልተከፈላቸው በመሬት ይዞታቸው ከቋሚ ተክልና ግንባታ በስተቀር ሌሎች ስራዎች መስራት ይችላሉ በማለት ይደነግጋል፡፡ በተጨማሪ በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ተገቢው ካሳ ካልተከፈው በፕላን የሚፈቀድ እና ቀጣይ የቦታውን የልማት ወጪ በመንግስት ላይ የማያበዛ በመሬቱ ላይ ማንኛውም ስራ መስራት ይችላል በማለት ይደነግጋል።
ቢሆንም ግን ይህ ድንጋጌ እጅግ አሻሚ ነው ምክንያቱም መንግስት ካሳ ካልከፈለ በፕላን መሰረት ባለይዞታ ማንኛውንም ዓይነት ስራ መስራት እንደሚችል ከተደነገገ በኋላ በመንግስት የልማት ወጪ የማያበዛ ስራ ማለቱ ምን ማለት ነው? እጅግ በጣም ግልጽ ነት የጎደለው ነው፡፡
(4) #ተመጣጣኝ ካሳ ክፍያና ምትክ ቦታ
አዲሱ አዋጅ በመሬቱ ላይ ለተፈራ ንብረት፣ ቋሚ ማሻሻያ ባለይዞታው ንብረቱን ማዘዋወር የሚችል ከሆነ የማዘዋወሪያ ወጪ ወይም የትራንስፖርት/የማጓጓዣ ወጪ ከመክፈሉ በተጨማሪ ከገጠር መሬት ይዞታ ለሚነሳ የመሬት በላይዞታ ተነሺ ከተወሰደበት መሬት ተመጣጣኝ የሆነ ምትክ መሬት እና መሬት ይዞታው ከመልቀቅ በፊት ባሉ ሶስት ተከታታይ ዓመታት ውስጥ ከፍተኛ ምርት ያመረተበትን ምርት በወቅታዊ ዋጋ ተሰልቶ በ15 ተባዝቶ ይከፈላል በማለት ይደነግጋል፡፡
(5) #በአዋጅ አንቀጽ 2(4) የልማት ተነሽ ድጋፍ የመሬት ባለይዞታ ከመሬቱ በጊዜያዊም ሆነ በቋሚነት ሲነሳ ከአዲሱ አከባቢ ጋር መላመድ እንዲችል ከንብረት እና ከልማት ተነሽ ካሳ በተጨማሪ በዓይነት ወይም በገንዘብ የሚሰጥ ድጋፍ ነው፡፡ it is promising move አዲስ እና በጣም ጥሩ የሚባል ነው ነገር ግን ይህ ነገር የሚወሰነው በክልሎች መመሪያ ነው፣ መች ይሁን የሚወጣው? ባይወጣስ?
(6) #የወል ይዞታዎች ላይ ካሳ የሚከፈል መሆኑ
በእርግጥ ወል ይዞታና የመንግስት የወል የተቀላቀለ በመሆኑ በወል ይዞታዎች ላይ ካሳ ሲከፈል አይታይም፣ በዚህ አዋጅ የወል ይዞታ ማለት ከመንግስት ወይም ከግል ይዞታነት ውጭ የሚገኝና የአከባቢው ማህበረሰብ ለግጦሽ፣ ለደንና ለማህበራዊ አገልግሎት በጋራ የሚጠቀሙበት የመሬት ይዞታ ነው በማለት አንቀፅ 2(11) ይደነግጋል።
በመሆኑ የወል ይዞታዎች አገኘን ተብሎ በየ ደረጃው የሚገኙ የመንግስት አካል መሸንሸን አይችሉም ማለት ነው፡፡ የወል መሬቱ የካሳ ስሌት የወል መሬቱ ይሰጥ የነበረው ጥቅም ወይም ጥቅሙ የቀረባቸውን የአኗኗር ዘይቤ ወይም መተዳደሪያ መሰረት ያደረገ ሊሆን ይገባል፡፡ይሰጥ የነበረው ጥቅም ወቅታዊ የገበያ ዋጋ መሰረት ያደረገ ማለት ነው? አሁንም ግልፅነት ይጎድለዋል፡፡የወል መሬቱ የተወሰደባቸው የወል መሬቱ ተጠቃሚ አካል የተገኘው ገንዘብ ለማህበረሰቡ አባላት እኩል ሊካፈል ወይም በዓይነት ሊጠቀሙበት የሚችሉበትን መንገድ መቅረጽ አለበት በማለት አንቀፅ 13(3) ይደነግጋል፡፡ በመሆኑም የወል መሬት ያለካሳ የሚወስድ የመንግስት አካል ከድርጊቱ መቆጠብ አለበት፡፡
(7) #የልማት ተነሺ ካሳ የሚከፈል መሆኑ
የከተማ መሬት ባለይዞታ ከይዞታው በቋሚነት ተነሽ በሚሆንበት ጊዜ የሚከፈለው የልማት ተነሺ ካሳ እና የሚሰጠው ምትክ ቦታ ነው በማለት ይደነግጋል፡፡
የልማት ተነሺ ካሳ ማለት ባለይዞታው የመሬት ይዞታውን ሲለቅ በመሬቱ ላይ የመጠቀም መብቱ በመቋረጡ ምክንያት የሚደርስ ጉዳት ለማካካስ የሚከፈል ክፍያ ነው፡፡ይህ አይነቱ ካሳ የመጠቀም መብት በመኖሩ ብቻ የሚገኝ የካሳ ዓይነት ነው፡፡ ለከተማ ተነሺ በአከባቢ ለነበረው የማህበራዊ ትስስር መቋረጥና ለሚደርሰው የስነ-ልቦና ጉዳት ማካካሻ ይከፈለዋል መጠኑ በደንብ ይወሰናል 13(4)(ሠ) በማለት ይደነግጋል፡፡
ግን ይህ ካሳ በተግባር ተከፍሎ አያውቅም። #የማህበራዊ ትስስር መቋረጥና የስ-ልቦና ጉዳት ካሳ ማለት ለተጎጂ ከነበረበት አከባቢ በመነሳቱ የነበረው ማህበራዊ ትስስር በመቋረጡ የሚከፈል የጉዳት ማካካሻ ክፍያ ነው፡፡
በመሆኑም በከተማ መሬት ይዞታ የሚነሳ ሰው የልማት ተነሺነት ካሳ፣ምትክ ቦታ፣ቤት ፈርሶበት ከሆነ የቤት መስሪያ ዋጋና በቦታው እስኪገባ ባለው 2 ዓመት የሚኖርበት ቤት ወይም የወቅታዊ የኪራይ ገንዘብ ግምት እና የማህበራዊ ትስስር መቋረጥና የስነ-ልቦና ጉዳት ካሳ ይከፍለዋል፡፡በመሆኑም እነዚህ መብቶች በቀድሞ አዋጅ ያልነበሩ በአዲሱ አዋጅ የተካተቱ ጥሩና ተስፋ ሰጪ የመሬት ካሳ መብቶች ናቸው፡፡
#መልሶ ማቋቋም ፡- በአዋጅ አንቀጽ 16 የክልል መንግስት ወይም የአዲስ አበባ እና የድሬደዋ አስተዳደር ለካሳ ክፍያ እና ለመልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ ያቋቁማል በማለት ይደነግጋል፡፡ መልሶ ማቋቋም ማለት በተወሰደው መሬት ምክንያት የሚያገኙት ጥቅም ለሚቋረጥባቸው ተነሺዎች ዘላቂ የገቢ ምንጭ እንዲያገኙ የሚያስችል የሚሰጥ ድጋፍ ነው ። ጥያቄው ግን መልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ ባይቋቋምስ ❓ በየደረጃው የሚገኙ የመንግሰት እርከን ካሳን በሚመለከት አቤቱታ የሚሰማ ኮሚቴ አንኳን አላቋቋሙም መልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ ያቁማሉ ❓
ከ ኢትዮ ህግ ኧረ በህግ ገፅ ተገኘ
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
👍2
ከውል ውጪ ስለሚደርስ ጉዳት ካሳ ማወቅ ያለብዎት ነገር
ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ጉዳት ሊደርስባቸው ይችላል።
እነዚህ ጉዳቶች ከወንጀል ድርጊት፣ ከውል ጥሰት ወይም ከውል ውጪ ከሚመጣ ኃላፊነት ሊነሱ ይችላሉ። የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የህግ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ከፍተኛ የህግ ባለሙያ የሆኑት አቶ ደመቀ ይብሬ እንደሚሉት፣ ከውል ውጪ በሚደርስ ጉዳት ህግ ዋነኛ ዓላማ ጉዳት ያደረሰውን አካል በመለየት ተጎጂው ተገቢውን ካሳ እንዲያገኝ ማስቻልና ሌሎችም ከዚህ እንዲማሩ ማድረግ ነው።
#ጉዳት ምንድን ነው?
የፍትሐ ብሔር ህጉ ለ"ጉዳት" የሚለው ቃል ቀጥተኛ ትርጉም ባይሰጥም፣ ከህጉ አጠቃላይ ይዘት በመነሳት በሰው ጥቅም፣ አካል ወይም ህይወት ላይ የሚደርስ ጉድለት መሆኑን መረዳት ይቻላል።
#ለካሳ ክፍያ መሟላት ያለባቸው ነገሮች
ከውል ውጪ ባለው የኃላፊነት ህግ መሰረት ካሳ ለማስከፈል፣ ተጎጂው ጉዳት እንደደረሰበት እና ጉዳቱም የደረሰው ኃላፊነት አለበት በተባለው ሰው ድርጊት ወይም እሱ ኃላፊነት በሚወስድባቸው ድርጊቶች መሆኑን ማረጋገጥ አለበት።
የኃላፊነት ምንጮች
ከፍተኛ የህግ ባለሙያው አቶ ደመቀ እንደሚጠቅሱት፣ ከውል ውጪ የሚደርስ ኃላፊነት ህግ መሰረት (የፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2027) ሶስት አይነት የኃላፊነት ምንጮች አሉ፦
#በጥፋት ላይ የተመሰረተ ኃላፊነት
#ጥፋት ሳይኖር የሚመጣ ኃላፊነት
#ሌላ ሰው ለሚያደርሰው ጉዳት የሚኖር ኃላፊነት
የጉዳት ዓይነቶች
የህግ ባለሙያው እንዳብራሩት፣ የተለያዩ የጉዳት ዓይነቶች አሉ።
1. ግልጽ የሆኑ ጉዳቶች
እነዚህ ጉዳቶች የተጎጂውን ንብረት ወይም ገንዘብ ነክ ጥቅም በቀጥታ የሚነኩ ናቸው። ይህ የጉዳት አይነት ቀጥታ ንብረት ላይ የሚደርስ ጉዳትን ወይም በአካልና በህይወት ላይ የሚደርስ ጉዳትን ያጠቃልላል።
ግልጽ የሆኑ ጉዳቶች አሁን የደረሱ ወይም ወደፊት የሚደርሱ ሊሆኑ ይችላሉ።
#አሁን የደረሱ ጉዳቶች: የፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2090 እንደሚያመለክተው፣ እነዚህ በአሁኑ ጊዜ በእርግጠኝነት የደረሱና በግልጽ የሚታወቁ ጉዳቶች ሲሆኑ፣ ከደረሱበት ጊዜ ጀምሮ የጉዳትና የካሳ መጠኑ በፍርድ ቤት እስከሚወሰንበት ጊዜ ድረስ ያለውን ይመለከታል።
#ወደፊት የሚደርሱ ጉዳቶች: የፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2092 እንደሚያስረዳው፣ በደረሰው ጉዳትና በካሳ ተመኑ ላይ ፍርድ ከተሰጠ በኋላ የማይቆሙና የሚቀጥሉ የጉዳት ዓይነቶች ናቸው።
2. የህሊና ጉዳት
ይህ የጉዳት አይነት የተጎጂውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማይጎዳ ሆኖም በስሜት፣ በሀዘን ወይም በሀፍረት መልክ የሚገለጽ ሞራላዊ ጉዳት ነው።
የጉዳት ካሳ ስሌት
ጉዳትን ተከትሎ የሚመጣው ካሳ፣ ለጉዳት ለደረሰበት ሰው የጉዳት መጠኑ ተሰልቶ በዛ ልክ የሚሰጠው ጥቅም ነው። የፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2090(1) እና 2091 ይህንን ያብራራል።
ለተጎጂው የሚገባውን ካሳ ለማስላት፣ የተጎጂውን የስራ ሁኔታ ማወቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አለው። ጉዳት የደረሰበት ሰው ተቀጥሮ የሚሰራ፣ የራሱን ስራ እየሰራ የሚኖር ወይም ስራ በመስራት ላይ ያልነበረ ሊሆን ይችላል።
1. ተቀጥሮ ለሚሰራ ሰው የሚሰጥ ካሳ
ጉዳቱ ከስራው ጋር የተገናኘ ከሆነ፣ የክርክሩ ሂደትና የካሳ አሰላል ስርዓቱ በአሰሪና ሰራተኛ ህግ (ቁጥር 1064/2010 እና 1156/2011) መሰረት ይመራል። ከስራው ጋር የማይገናኝ ከሆነ ግን በከውል ውጪ ኃላፊነት የህግ ድንጋጌዎች ይመራል።
#ጊዜያዊ ጉዳት: ጉዳቱ ጊዜያዊ ከሆነ፣ ስራ እስከሚጀምር ድረስ ሊያገኝ ይችል የነበረውን ያክል ካሳ ያገኛል።
#ከፊል ቋሚ ጉዳት: መስራት ባላስቻለው መጠን ልክ ይሰላል።
#ቋሚ ጉዳት: እስከ ጡረታ ጊዜው ድረስ ተሰልቶ ይሰጠዋል።
የአካል ጉዳት ሲደርስ፣ የወደፊት ጉዳት ካሳ ስሌት ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን፣ የሰራተኛውን የገቢ መጠን እና ተጎጂው ጡረታ ለመውጣት የቀረውን ጊዜ በደንብ ማጤን ያስፈልጋል።
2. የራሱን ስራ ለሚሰራ ሰው የሚሰጥ ካሳ
የራሱን ስራ እየሰራ ለሚተዳደር ሰው ካሳውን ለማስላት ገቢውን ለማወቅ አስቸጋሪ ሊሆን ቢችልም፣ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ወርሃዊ ወይም አመታዊ አማካይ ገቢውን በመመልከት ያጣውን ወይም ሊያጣ የሚችለውን ጥቅም በማስላት ካሳውን መተመን ይቻላል።
3. ስራ አጥ ለነበረ ሰው የሚሰጥ ካሳ
በህመም፣ ለመስራት ባለመፈለግ፣ የሚመጥነውን ስራ በማጣት ወይም በጠቅላላው ስራ አጥ በመሆን ስራ እየሰሩ ያልነበሩ ሰዎች ላይ ጉዳት ቢደርስባቸው የገቢውን መጠን ማወቅ ስለሚያስቸግር ካሳውን ማስላት ይከብዳል። በዚህ ጊዜ ዳኞች በፍትሃዊነት (በርትዕ) ካሳውን ለማስላት ይገደዳሉ።
4. በሞት ምክንያት የሚሰጥ ካሳ
በአደጋ ምክንያት ሞት ሲያጋጥም፣ ካሳ የመጠየቅ መብት ያለው ማነው የሚለው ወሳኝ ነው። የፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2095 መሰረት የሟች ባል/ሚስት፣ ወላጆች እና ተወላጆች ካሳ መጠየቅ ይችላሉ። ለእነዚህ ሰዎች የሚከፈለው ካሳ ቀለብ ስለሆነ፣ በቤተሰብ ህጉ መሰረት ቀለብ ጠያቂ ሊያሟላቸው የሚገቡ መስፈርቶችን ማሟላትና ማስረዳት ይጠበቅባቸዋል።
5. ለህሊና ጉዳት የሚሰጥ ካሳ
የህሊና ጉዳት የሰው ልጅ የውስጥ ስሜት ጉዳት በመሆኑ ካሳውን በገንዘብ መለካት አስቸጋሪ ነው። ሆኖም የህሊና ጉዳት ሲያጋጥም የገንዘብ ካሳ እንደሚከፈል በፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2105(1) ተቀምጧል።
የህሊና ጉዳት ካሳ የሚከፈለው በልዩ ሁኔታ በህግ ለተመለከቱ ጉዳቶች ብቻ እንጂ ሁልጊዜም ካሳ እንደማያስከፍል የፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2105(2) ይደነግጋል። የህሊና ጉዳት ካሳ የሚወሰነው ርትዕን መሰረት አድርጎ ሲሆን፣ የፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2106-2115 ይህንን ያብራራል። የህሊና ጉዳት ካሳ 1,000 ብር መብለጥ እንደሌለበት የፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2116(3) ያስቀምጣል።
የካሳ አከፋፈል ስርዓት
ጉዳት መድረሱ፣ ለጉዳቱ ማን ኃላፊነት እንደሚወስድና የካሳ ክፍያው መጠን ከተለየ በኋላ መወሰን ያለበት ሌላ ወሳኝ ጉዳይ የካሳ አከፋፈል ስርዓቱ ነው። የህግ ባለሙያው እንዳሉት፣ ሁለት አይነት የካሳ አከፋፈል ስርዓቶች አሉ፦
1. የቁርጥ ክፍያ
ይህ የካሳ ክፍያ የተወሰነበትን መጠን በአንድ ጊዜ ለባለመብቱ በመክፈል የሚፈጸም ነው። ይህ ዘዴ በብዙ ሀገራት የሚተገበርና መርህም ነው።
2. በየጊዜው የሚደረግ ክፍያ
መርሁ የጉዳት ካሳን በቁርጥ መክፈል ቢሆንም፣ በልዩ ሁኔታ ግን በየጊዜው እንዲከፈል ተደርጎ መወሰን እንደሚቻል በህጉ ተቀምጧል። ካሳን በየጊዜው እንዲከፈል ለመወሰን፣ የካሳው ባህሪ፣ የአካባቢ ሁኔታዎች እና የካሳ ከፋዩ ማረጋገጫ መስጠት ያለባቸው ነጥቦች ናቸው።
#Mikias_Melak
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
Linktree
AleHig | Instagram, Facebook, TikTok | Linktree
AleHig attorney & Legal consult present across multiple social media platforms..
❤13