አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
June 11
1. በቂ የወንጀል ጥርጣሬ መኖሩ ተጣርቶ በፓሊስ የወንጀል ምርመራ ይጀመርበታል ፣
2. የምርመራ መዝገቡ ለአቃቤሕግ ከተላከ በሁላ ፣ ለመክሰስ የሚያስችል ማስረጃና የሕግ መሰረት መኖሩ ሲረጋግጥ ክስ የመስረትበታል ፣ ካልሆነ መዝገቡ ይዘጋል ፣
3. ፍ/ቤት ክሱ እንዲደረሰው ትእዛዝ ከስጠ በሁላ ይሄው ደርሶት እራሱን ለመከላከል እድል ይስጠዋል
4. አቃቤሕግ መጀመሪያ ማስረጃውን ያሰማል ፣
5. ፍ/ቤቱ የአቃቤ ሕግን ማስረጃ ከሰማ በሁዋላ ፣ ተከላከል ይለዋል ፣ ወይም መከላከል ሳያስፈልገው በነጻ ያሰናብተዋል ፣
6. ተከላከል ከተባለ ፣ አለኝ የሚለውን መከላከያ አቅርቦ ያሰማል ፣ ይከራከራል ። መከላከል መስረታዊ መብት ነው ፣
7. ተከላከል ከተባለ በሁዋላ ፍ/ቤቱ ጥፋተኛ ሊለው ወይም በነጻ ሊያሰናብተው ይችላል ፣

አንድ ሰው ወንጀል ፈጽሞ ጥፋተኛ ተባለ የሚባለው በዚህ ሂደት ውስጥ አልፎ ነው ። ክስ ከተመሰረተበት በሁዋላ እንኩዋን በሁለት የስነ ስርአት ደረጃዎች ነጻ የመባል እድል አለው ። ማንኛችንም ነገ በሆነ አጋጣሚ በሰውየው ቦታ ልንሆን እንችላለን ። ሕግ የስጠውን መብት እናክብርለት ፣ ቀድሞ ፈራጅ አንሁን ፣ ውጤቱን እንጠብቅ ።

፣ ከማስታወሻዬ ፣ በአንድ ወቅት ...

እነ እገሌ ፣ በቢሊዮን ብር ዘረፉ ተባለ ። ተራገበ ፣ ተጋነነ ፣ ብዙ ተጮህ ። ተጠርጣሪዋቹ ፣ ቤተሰብ ፣ ወዳጅ ዘመዳቸው አፈረ ፣ አንገቱን ደፋ ። ብዙ ሰው በየቤቱ ሰምቶ አዘነባቸው ፣ እነዚህን መግደል እንጂ የምን ክስ ምናምን ነው ተባለ ፣ እኛ ጠበቆቹም ተሰደብን ፣ ሞራል የሌላችው ፣ እንዴት ለነዚህ ይቆማሉ ተባልን ።

ክስ ተመሰረተ ፣ ወሬውና ክሱ አይገናኝም ፣ ክሱና እውነታው አይገናኝም ። እናም ፣ ቆይቶ ፣ ሰዎቹ እንዲከሱ ይፈለግበት የነበረው ፓለቲካ ሲለወጥ ፣ ክሳቸው ተነሳ ።

ዝርዝሩን ሳናውቅ ለመፍረድ አንቸኩል ። ብዙ በተዋራባቸው የወንጀል ጉዳዮች ላይ በጠበቃነት ተሳትፌአለሁ ። በአብዛኛው ግነቱና እውነቱ አይገናኝም ። ሰከን ማለት ፣ ግራ ቀኙን መስማት ፣ ማገናዘብ ፣ ከስሜታዊ ፈራጅነት መቆጠብ ጥሩ ነው ... የወንጀል ምርመራውን ለፓሊስ ፣ የክሱን ጉዳይ ለአቃቤሕግ ፣ ዳኝነቱን ለፍ/ቤት እንተወው ....

መልካም ቀን ። በአበበ አስማረ
Alternative legal enlightenment & Service
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
https://t.me/AleHig
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#አለሕግ #ህግ #ሰበርመዝገብ  #ሕግ_መረጃ #እግድ
June 11
June 11