አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.83K photos
25 videos
1.86K files
3.55K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ማሳሰቢያ አለ_ህግ #law #societies
ሁሉንም የ #አለ_ህግ አባላት የሚያሳትፍ ቀጠሮ፣ ሁሌም እሁድ እሁድ የቀጥታ (Live stream) የድምፅ ውይይት ይኖረናል።
#የህግ ጉዳይ የመወያያ እርዕስ አስቀድማችሁ እንዳትመርጡ እናሳስባለን።
ምክንያቱም፣ ከወዲሁ ተዘጋጅተው ለውይይቱ እንዲመጡና ፍሬአማ ሀሳቦችን እንድናገኝ ይረዳናል።
1. የመወያያ አጀንዳ ይምረጡ
2. ተዘጋጅተው የውይይቱ ተሳታፊ ይሁኑ
3. Share and add ማድረግን አትርሱ
#Ale_Lawsocieties
#አለ_ህግ
https://t.me/lawsocieties

@lawsocieties
አለሕግAleHig ️
ማሳሰቢያ ከ አለ_ህግ #law #societies ሁሉንም የ #አለ_ህግ አባላት የሚያሳትፍ ቀጠሮ፣ ሁሌም እሁድ እሁድ የቀጥታ (Live stream) የድምፅ ውይይት ይኖረናል። #የህግ ጉዳይ የመወያያ እርዕስ አስቀድማችሁ እንዳትመርጡ እናሳስባለን። ምክንያቱም፣ ከወዲሁ ተዘጋጅተው ለውይይቱ እንዲመጡና ፍሬአማ ሀሳቦችን እንድናገኝ ይረዳናል። 1. የመወያያ አጀንዳ ይምረጡ 2. ተዘጋጅተው የውይይቱ ተሳታፊ ይሁኑ…
ማስታወቂያ ከ አለ_ህግ #law #societies
እሁድ የ #አለ_ህግ አባላት የሚያሳትፍ ቀጠሮ፣ ሁሌም እሁድ እሁድ የቀጥታ (Live stream) የድምፅ ውይይት
...... ከምሽቱ 3:00 ስዓት ጀምሮ ይኖረናል።

#የህግ ጉዳይ የመወያያ አጀንዳ፣

የሰብአዊ መብቶች እና የሕግ ጥሰት ከመከሰቱ በፊት እንዴት መከላከል ይቻላል?
ከማን ምን ይጠበቃል?



ተዘጋጅተው የውይይቱ ተሳታፊ ይሁኑ
Share and add ማድረግን አትርሱ
#Ale_Lawsocieties
#አለ_ህግ
https://t.me/lawsocieties

@lawsocieties
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Lawyer Mike 🔊የህግ ባለሙያ)
ማስታወቂያ ከ አለ_ህግ #law #societies
እሁድ የ #አለ_ህግ አባላት የሚያሳትፍ ቀጠሮ፣ ሁሌም እሁድ እሁድ የቀጥታ (Live stream) የድምፅ ውይይት
...... ከምሽቱ 3:00 ስዓት ጀምሮ ይኖረናል።

#የህግ ጉዳይ የመወያያ አጀንዳ፣

የሰብአዊ መብቶች እና የሕግ ጥሰት ከመከሰቱ በፊት እንዴት መከላከል ይቻላል?
ከማን ምን ይጠበቃል?



ተዘጋጅተው የውይይቱ ተሳታፊ ይሁኑ
Share and add ማድረግን አትርሱ
#Ale_Lawsocieties
#አለ_ህግ
https://t.me/lawsocieties

@lawsocieties
Assistant Professor
#bahir_dar_university
#legal_services
#law
#assistant_professor
Bahir Dar
Master's Degree in Human Rights,
Law, Criminal Justices and Human Rights or related field of study
Quanitity Required: 2
Minimum Years Of Experience:
#0_years
Deadline: November 9, 2022
How To Apply: Submit your official release letter from the previous institution (if you have been employed) and necessary application documents to Bahir Dar University Human Resource Office For more information contact Tel. 0583206002


https://t.me/lawsocieties
220830.pdf
825.3 KB
ከባንክ ሂሳቤ ላይ ገንዘብ አላአግባብ ወጪ በመደረጉ ባንኩ ገንዘቡን እንዲመልስ የሚል ክስ ሲቀርብ የፎረንሲክ ምረመራውን ውጤት ብቻ መሠረት በማድረግ ባንኩን ለክሱ ኃላፊ ማድረግ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ነው።

በወጪ ማዘዣው ላይ የተመለከተዉ ፊርማ በሲስተሙ ላይ ከተመለከተዉ የፊርማ ናሙና ጋር ተመሳሳይ መሆን አለመሆኑን ለማረጋገጥ የወጪ ማዘዣው ላይ የተመለከተዉ ፊርማ ከናሙና ፊርማ ጋር የሚመሳሰል መሆን አለመሆኑ ገለልተኛ በሆነ አካል ታይቶ መረጋገጥ ይኖርበታል።

በመሆኑም ክስ ከቀረበበት ባንክ ዉጪ በሌሎች ባንኮች ከወጪ ማዛዣ ክፍያ ጋር በተያያዘ ልምድ ባላቸዉ የባንክ ባለሙያዎች እንዲታይ በማድረግ ባንኩ ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ ግዴታዉን የተወጣ መሆን አለመሆኑ ማረጋገጥ ይገባል፡፡ የባለሂሳቡ ባንክ ደብተር ቀርቦ ሂሳቡ ተቀንሶ የተጻፈ መሆን አለመሆኑ ሆነ የባለሂሳቡ መታወቂያ በማየት ባንኩ ያረጋገጠ መሆን አለመሆኑ ደግሞ በሰው ማስረጃ ሆኖ የባንክ ሂሳብ ደብተሩ ካለ በማስቀረብ መረጋገጥ ይኖርበታል።

ሰ/መ/ቁ. 220830 ጥቅምት 29 ቀን 2015 ዓ/ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#Bank #law #lawyer
#SAMUELGIRMA
Join 👈
https://t.me/lawsocieties
#ህጉ ምን ይላል?
ድፍንፍን ለማድረግ የተሞከረው ሹም ሽረት #ከህግ አንፃር፣
ስለ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት እና ምክትል ፕሬዚዳንት “ መልቀቂያ እና ሹመት ” ህገ መንግስቱ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንት በፌደራል መንግስት ጠቅላይ ሚኒሰቴር አቅራቢነት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይሾማሉ።
የፌደራል ዳኝነት አስተዳደር አዋጅ
አላማ- በፌደራል ፍርድ ቤቶች የሚሾሙ ዳኞች ግልጽ፣ ገለልተኛና ተአማኒ በሆነ አሰራር የሚሾሙበትን ሥርዓት በመዘርጋት ዳኞች የዳኝነት ተግባራቸውን በብቃት፣ በሙሉ ነጻነት፣ ገለልተኝነትና ተጠያቂነት የሚያከናውኑበትን አሰራር ማረጋገጥ፤
"የፌደራል ዳኞች" ማለት በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሾሙ ዳኞች ሲሆኑ ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንቶችን ይጨምራል ።
የፌደራል ዳኝነት አስተዳደር አዋጅ የዳኞች የሥራ ስንብት/ መልቀቅን በተመለከተ
ከዳኝነት ሥራ ለመልቀቅ ጥያቄ ሲያቀርብ የሁለት ወር / እንጊሊዝኛው 3 ወር ይላል / ቅድሚያ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ በመስጠት፤
በተጨማሪም
የፌደራል ጠቅላይ ፕሬዚዳንት ወይም ምክትል ፕሬዚዳንት ስለቀረበበት ከስራ የሚሰናበቱት ጉዳይ በጉባዔው ታይቶ ውሳኔ ሲያገኝ እና ጥያቄው በጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካኝነት ለህዝብ ተወካዮች ቀርቦ ምክርቤቱ ውሳኔውን በአብላጫ ድምጽ ሲያጸድቀው ነው ፡፡
የፌደራል ጠቅል ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንትና ምከትል የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ አባሎች እንደመሆናቸው ሥራቸውን ስለሚለቁበት ሁኔታ አንቀጽ 19 ላይ ዝርዘር ድንጋጌዎችን ያስቀምጣል
የጉባዔው አባሎች ሥራቸውን ስለሚለቁበት ሁኔታ
፩/ በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፮(፩ ) ሀ፣ ለ፣ሐ፣መ፤ ሠ እና ሰ ከተመለከቱት በስተቀር ማንኛዋም የጉባኤ አባል፤
ሀ) ከደንብ መተላለፍ ውጭ በሆነ ወንጀል ተከሶ ሲፈረድበት፣
ለ)በጤና ችግር ምክንያት ስራውን በአግባቡ ማከናወን ሲሳነው፤
ሐ) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወይም በክልል ምክር ቤት አባልነት ሲመረጥ ወይም በሹመት፤ ወይም በዝውውር በፌደራል ወይም በክልል መንግስት ሥራ አስፈጻሚ ቦታ ሲመደብ፤
መ) ይህን አዋጅ ወይም የጉባዔውን የውስጥ የአሰራር ሥነ ሥርዓት ባለማክበሩ ጉዳዩ ለጉባኤው ቀርቦ ለአባልነት ተገቢ አለመሆኑ ከጉባኤው ጠቅላላ አባላት በሁለት ሶስተኛ ድምጽ ሲወሰን፤
ሠ) በሌላ ማናቸውም ምክንያት በጉባኤው ላለዉ ከፍተኛ ኃላፊነት አባል ሆኖ ለመቀጠል የማይችል ሲሆን እና በጉባኤዉ ሲወሰን፤ ከጉባዔው አባልነት ይሰናበታል ፡፡
፪/ ማንኛውም የጉባኤው አባል ከጉባኤው ጽሕፈት ቤቱ በኩል ከአንድ ወር አስቀድሞ ለጉባዔው በጽሁፍ ማቅረብ አለበት፡፡
ተሿሚዎችን በተመለከተ
በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ ሆኖ ለመሾም - የሚያበቁ ተጨማሪ ሁኔታዎች
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ ሆኖ ለመሾም ከዚህ በላይ በአንቀጽ ፳፪ ከተደነገገው በተጨማሪ የሚከተሉት ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
፩/ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዳኝነት ቢያንስ አስር ዓመት ወይም በክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዳኝነት ቢያንስ አስር ዓመት ያገለገለ እና በሥራዉ ዘመን መልካም ሥነ-ምግባርን ፣ታታሪነትን ፣ ብቃትን እና ቅንነትን ያሳየ፤ ይህም በዳኞች ምልመላ ኮሚቴ ከተረጋገጠ፤ ወይም
፪/ በዚህ አንቀጽ በንዑስ አንቀጽ ፩ የተደነገገው ቢኖርም በዳኝነት ሙያ ከተጠቀሰው የአገልግሎት ጊዜ ሁለት ሶስተኛውን ያገለገለ በዳኝነት ሥራዉ ላይ በቆየችበት ጊዜ መልካም ሥነ-ምግባሩ፣ ታታሪነቱ እና የላቀ ሞያዊ ብቃቱ የተመሰከረለት ሰው የጉባዔውን ሁለት ሦስተኛ የድምፅ ድጋፍ ካገኘ በልዩ ሁኔታ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኝነት ዕጩ ሆኖ ሊቀርብ ልትቀርብ ይችላል፡፡
፫/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ፩ እና ፪ የተደነገገው ቢኖርም በማንኛውም የህግ ሙያ ቢያንስ ፳ ዓመት ያገለገለ በሥራው ላይ በቆየችበት ጊዜ መልካም ሥነ-ምግባሩ፣ ታታሪነቱ እና የላቀ ሞያዊ ብቃቱ የተመሰከረለት ሰው የጉባዔውን ሁለት ሦስተኛ የድምፅ ድጋፍ ካገኘ በልዩ ሁኔታ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኝነት ዕጩ ሆኖ ሊቀርብ ይችላል።

ህገመንግስቱ እና የፌደራል ዳኝነት አስተዳደር አዋጅ ከላይ በተዘረዘረው መልኩ ሰንበትና ሹመቱ ግልጽነትና ተጠያቂነት ባለመት መንገድ መሆን እንዳለበት በግልጽ ቢደነግጉም ፣ ከአንዳንድ የፓርላማ አባላትም የምክር ቤት አባላት አዲስ የተሸሙት ግለሰቦች ማንነት በተገቢው ሁኔታ ለመገምገም ቀድሞ ስለግለሰቦቹ አለመነገሩን እንዲሁም ከዚህ ቀደም የነበሩት ፕሬዚዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንት በምን ምክንያት እንደለቀቁ አለመብራራቱ ጥያቄ አንስተው የነበር ቢሆንም መልቀቂያውና ሹመቱ መጽደቁ አልቀረም፡፡
#Daniel_Fikadu /ዳንኤል ፍቃዱ
(ጠበቃና የህግ አማካሪ)/
#አለ_ህግ #Ale_Hig #Law_Societies
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
ኢትዮጵያ የሚበላ ምግብ ዋጋ ውድ ከሆነባቸው የአፍሪካ ሃገራት ከቀዳሚዎቹ ተርታ ነች ተባለ

ከአለም 8ተኛ ደረጃ ላይ መሆኗን ሰምተናል፡፡

ከዚምባቡዌ ቀጥላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት ያለባት ሃገር እንደሆነች በጥናት ተረጋግጧል፡፡

የኢትዮጵያ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት በዋጋ ግሸበት ምክንያቶችና መፍትሄ ላይ ያደረገውን ጥናት ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል ይፋ አድርጓል፡፡

አጠቃላይ የዋጋ ግሽበቱ 49.1 በመቶ ነው የተባለ ሲሆን የምግብ የዋጋ ንረት ከፍተኛውን ድርሻ ይዟል፡፡

ይህም ከክልል ክልል የተለያየ መሆኑ በጥናቱ ተጠቅሷል፡፡

በአማራና ደቡብ ክልል ያለው የዋጋ ግሽበት ከሃገራዊ ምጣኔው ከፍ ያለ ነው ተብሏል፡፡

በተለይ ለምግብ የዋጋ ንረቱ የምርት መጠን ከፍላጎት ጋር አለመመጣጠን አንዱ ምክንያት ነው ብለዋል ጥናቱን ያቀረቡት ዶ/ር ታደሰ ኩማ፡፡

ገበሬው ከሚያመርተው ምርት ከራሱ ፍጆታ ተርፎት ለገበያ የሚያቀርበው በአማካይ ከ20 በመቶ አይበልጥም ተብሏል፡፡

ከሚመረተው በቆሎ 85 በመቶው ገበሬው ለእለት ፍጆታው ያውለዋል ተብሏል፡፡

በሌላ በኩል ከሚመረተው ጤፍ ለገበያ ቀርቦ ከተማው የሚሸምተው 30 በመቶውን ብቻ ነው ተብሏል፡፡

ይህም ምርታማነት ጨምሯል ቢባልም አብዛኛው አነስተኛ አምራች ገበሬ በመሆኑ የሚያመርተው እህል እምብዛም ከራሱ የሚያልፍ በመሆኑ ዋጋ እንዲንር ምክንያት መሆኑን ሰምተናል፡፡

ማምረት እንደተቻለ ከውጭ ማስመጣት ደግሞ ሌላው ምክንያት ሆኖ ቀርቧል፡፡

ኢትዮጵያ ከ97 በመቶ በላይ የዘይት ፍላጎቷን ከውጭ ገዝታ እንደምታመጣም በጥናቱ ተጠቅሷል፡፡

ከፍላጎትና አቅርቦት አለመመጣጠን ባሻገር እሴት የማይጨምሩ ደላሎች በገበያ ሰንሰለቱ በብዛት መሳተፍ ፣ መንግስትም ተገቢውን ቁጥጥርና የእርምት እርምጃ አለመውሰድ የዋጋ ንረቱን አባብሶታል ይላል ጥናቱ፡፡

በዚህም ምክንያት ምርት አምራቹ ከሚሸጥበት 58 በመቶ ዋጋው ከፍ ብሎ ሸማቹ ጋር እንዲደርስ አድርጓል ተብሏል፡፡

ይህን ሁኔታ ለመቀየር መንግስት የፖሊሲ ለውጥ እንዲያደርግ ጥናቱ መክሯል፡፡

ገበያውን ማዘመን፣ የገበያውን ምርታማነት ለመጨመር ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል ተብሏል፡፡

በተጨማሪም የተቋማት አደረጃጀትና አሰራርን በመፈተሽ ተገቢውን እና መልክ ያጣውን የገበያ ሥርዓት ማስተካልም የመንግስት የቤት ስራ ነው ተብሏል፡፡

ትዕግስት ዘሪሁን
#Ethiopia #ShegerWerewoch
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law
https://t.me/lawsocieties
#ሰበር_ዜና #Breaking_News

ከ2014 የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የማለፊያ ውጤት ያመጡት ሦስት በመቶ ብቻ ናቸው ተባለ 😳

ኩረጃን ለማስቀረትና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚል፣ በልዩ ሁኔታ ከተሰጠው የ2014 የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ የመልቀቂያ ፈተና ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት (የማለፊያ ነጥብ) ያገኙ ተማሪዎች 28 ሺሕ ብቻ መሆናቸውን አዲስ ማለዳ ከአስተማማኝ ምንጮቿ መስማቷን ዘግባለች።
#atc_newsbot
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law
https://t.me/lawsocieties
መሰረታዊ የሕግ ስህተት በአዲሱ የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
አንድ ጉዳይ የመጨረሻ ፍርድ ከተሰጠው በኋላ መሰረታዊ የህግ ስህተት ተፈፅሞበታል የሚባል ከሆነ መሰረታዊ የህግ ስህተቱ ሳይታረም እንዳይቀር በሰበር ለመታየት ዕድል ይሰጠዋል፡፡ ቀደም ሲል መሰረታዊ የህግ ስህተት ምንነት የህግ ትርጉም ያልተሰጠው የነበረ በመሆኑ ጉዳዮች መሰረታዊ የህግ ስህተት አለባቸው በሚል በብዛት ሲቀርቡ ይስተዋል ነበር፡፡ ይህን ለማስቀረት አዲሱ የፍርድ ቤቶች አዋጅ መሰረታዊ የህግ ስህተትን ምንነት ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ የመሠረታዊ የሕግ ስህተት ምንነትን እና ተያያዥ ጉዳዮችን እንመለከታለን፡፡

የመሠረታዊ የሕግ ስህተት ምንነት

በአዲሱ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀፅ 2(4) መሠረት “መሠረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት” ማለት

. የሕገ-መንግሥቱን ድንጋጌዎች የሚቃረን

ለ. ሕግን አላግባብ የሚተረጉም ወይም ለጉዳዩ አግባብነት የሌለውን ሕግ የሚጠቅስ

ሐ. ለክርክሩ አግባብነት ያለው ጭብጥ ያልተያዘበት ወይም ከክርክሩ ጋር የማይዛመድ አግባብነት የሌለው ጭብጥ የተያዘበት

መ. በዳኝነት ታይቶ ሊወሰን የሚገባውን ጉዳይ ውድቅ የተደረገበት

ሠ. በፍርድ አፈፃፀም ሂደት ከዋናው ፍርድ ጋር የማይገናኝ ትእዛዝ የተሰጠበት

ረ. ጉዳዩን አይቶ የመወሰን የዳኝነት ሥልጣን ሳይኖር ውሳኔ የተሰጠበት

ሰ. የአስተዳደር አካል ወይም ተቋም ከሕግ ውጭ ውሳኔ የሰጠበት

ሸ. የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎትን አስገዳጅ ውሳኔ በመቃረን የተወሰነ
እና ፍትህን የሚያዛባ ጉልህ የሕግ ስህተት ያለበት የመጨረሻ ውሳኔ፣ ፍርድ፣ ብይን፣ ትዕዛዝ ሲሆን መሰል ስህተት ያለባቸው ጉዳዮች በዚህ አዋጅ አንቀፅ 10 መሠረት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሚታረሙ ይሆናል፡፡ የመጨረሻ ውሳኔ ማለት በፍርድ ቤት፣ በህግ የመዳኘት ስልጣን በተሰጠው አካል፣ በተቋማት ወይም በአማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች የተሰጠ እና ለጉዳዩ እልባት የሚሰጥ ፍርድ፣ ብይን፣ ትዕዛዝ ውሳኔ ሲሆን የይግባኝ ሂደቶችን የጨረሰ ፍርድ፣ ብይን፣ ትዕዛዝ ወይም ውሳኔን እንደሚጨምር በአዋጁ አንቀፅ 2(5) ትርጓሜ ተሰጥቶታል፡፡

የጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ስልጣን

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ስልጣን የመነጨው ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 80(3)(ሀ) ሲሆን መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበትን ማናቸውንም የመጨረሻ ውሳኔ ለማረም በሰበር ችሎት የማየት ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡ በዚህም በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/13 አንቀፅ 10 መሰረት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለባቸውን የፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት በይግባኝ አይቶ የመጨረሻ ውሳኔ የሰጠባቸውን ጉዳዮች የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት የመጨረሻ ውሳኔ የሰጠባቸውን ጉዳዮች የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወይም የክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በህገ መንግስቱ በተሰጣቸው የውክልና ስልጣን ፌደራል ጉዳይን አይተው መጨረሻ ውሳኔ የሰጡበት ጉዳይ
የአዲስ አበባ ወይም የድሬደዋ ከተማ ፍርድ ቤት የመጨረሻ ውሳኔ የተሰጠባቸው የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የህገ መንግስቱ ድንጋጌዎች እና የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎቶች አስገዳጅ ውሳኔ ጋር በተያያዘ የመጨረሻ ውሳኔ የተሰጠባቸው ጉዳዮች የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ህግን አለአግባብ ከመተርጎም እና ለጉዳዩ አግባብነት የሌለውን ህግ ከመጥቀስ ጋር በተያያዘ የመጨረሻ ውሳኔ የተሰጠባቸው እና ጉዳዮቹ ለህዝብ ጥቅም ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው ውሳኔዎች በህግ የመዳኘት ስልጣን ተሰጠው አካል ወይም በሌሎች አካላት የተሰጠ የመጨረሻ ውሳኔ አግባብነት ያላቸው የህግ ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆነው በፌደራል ፍርድ ቤት ሊታይ ይችል በነበረ ጉዳይ ላይ በአማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች መሰረት የተሰጡ የመጨረሻ ውሳኔዎች እንዲሁም በሌሎች ህጎች የተጠቀሱ ጉዳዮች በሰበር አይቶ የማረም ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡

አንድ ጉዳይ በሰበር ሲታይ ከአምስት ያላነሱ ዳኞች ሊሰየሙ እንደሚገባ በአዋጁ አንቀፅ 25(2) ተደንግጓል፡፡ ከአምስት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት የሚሰጠው የሕግ ትርጉም በየትኛውም ደረጃ ላይ በሚገኝ የፌዴራል ወይም የክልል ፍርድ ቤት ላይ አስገዳጅነት እንደሚኖረው ከአንቀፅ 10(2) መረዳት ይቻላል፡፡

ይህን አምስት ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት የተሰጠው አስገዳጅ ውሳኔ ሰባት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት በድጋሚ ሊታይ ይችላል፡፡ ይህ የሚሆነው በባለጉዳዮች አመልካችነት ወይም በችሎቱ በራሱ አነሳሽነት ቀድሞ የሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም በተለያዩ ምክንያቶች ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው በሰባት ዳኞች ችሎት እንዲታ በቂ እና አሳማኝ ምክንያቶችን ተንትኖ በመግለፅ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሲያቀርብ እንደሆነ ከአንቀፅ 26(1) መረዳት ይቻላል፡፡ በዚህ መልኩ ጥያቄ ሲቀርብ ፕሬዝዳንቱ ጉዳዩ ሰባት ዳኞች በሚሰየሙበት ችሎት እንዲታይ የሚያደርግ ሲሆን በችሎቱ የሚሰጠው ውሳኔ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በማንኛውም ደረጃ ፍርድ ቤት አስገጃጅ ይሆናል፡፡

በተጨማሪም ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት ቀድሞ የሰጠውን የህግ ትርጉም ከሰባት ባላነሱ ዳኞች በተመሳሳይ ጭብጥ በሌላ ጊዜ ሊሻሻል ይችላል፡፡

ማጠቃለያ

በአጠቃላይ የሰበር ሥርዓት መሰረታዊ ህግ ስህተት ያለበት የመጨረሻ ውሳኔ የተሰጠበት ጉዳይ ለመጨረሻ ጊዜ የሚታይበትና እና የሚታረምበት የዳኝነት ሂደት ነው፡፡ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት ምንነት ደግሞ በአዋጁ የተገለፀ በመሆኑ ለሰበር የሚቀርቡ ጉዳዮች ይህንን ተከትለው መቅረብ አለባቸው፡፡

በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law https://t.me/lawsocieties
ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ
ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ማለት
ሠራተኛው ካለፈው፣ አሁን ካለው ወይም ወደፊት ከሚመጣው የቅጥር ውል ጋር በተያያዘ የሚያገኘው ደመወዝ/ምንዳ፣ አበል፣ ጉርሻ፣ ኮሚሽን፣ የመልካም ሥራ አፈፃፀም ማበረታቻ ስጦታ ወይም ሌላ የአገልግሎት ዋጋ ክፍያ፣ ተቀጣሪው ከስራ ሲቀነስ ወይም ከስራ ሲለቅ ወይም ስራን እንዲለቅ ለማግባባት የሚከፈል ገንዘብ ወይም የስራ ውል በመቋረጡ ምክንያት በፈቃደኝነት፣ በስምምነት፣ በዳኝነት ውሳኔ መሠረት በጥሬ ገንዘብ (በዓይነት) የተቀበለው ማንኛውም የገንዘብ መጠን ከታክስ ነጻ ከተደረገው ውጪ እንደ ገቢ ተቆጥሮ ታክስ የሚሰላበት ይሆናል፡፡
* አንድ ተቀጣሪ ከመቀጠር የሚያገኘው ገቢ በኢትዮጵያ የመነጨ ነው የሚባለው፡-
1. ክፍያው የሚፈፀመው ስፍራ ግምት ውስጥ ሳይገባ ኢትዮጵያ ውሰጥ ከሚከናወነው የቅጥር አገልግሎት የተገኘ ገቢ ከሆነ ወይም
2. የቅጥር አገልግሎቱ የትም ቢከናወን በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት ስም ክፍያው ለተቀጣሪው ከተፈፀመ ነው፡፡
* ተቀጣሪው ከመቀጠር በሚያገኘው ገቢ የሚያወጣው ማንኛውም ወጪ በተቀናሽ ሊያዝለት አይችልም፡፡
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law https://t.me/lawsocieties
Federal_Supreme_Court_Cassation_Decisions_Table_of_content_Volume.pdf
6.6 MB
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሕግ ትርጉም የሰጠባቸው ውሣኔዎች ዝርዝር ማውጫ ሰንጠረዥ ከቅጽ 1 እስከ 25

በ፦ ዋስይሁን ኃይለማርያም እና የኋላሸት ታምሩ

አዘጋጆቹ በዚህ ጊዜ በመስፍን ታፈሰ እና ጓዶቹ (MTA) የሕግ ቢሮ በአሶሲየትነት በመስራት ላይ የሚገኙ ሲሆኑ ይህን ስራ አዘጋጆቹ በግላቸው የሰሩት እና የሚሰሩበትን ተቋም ያካተተ ወይም የሚወክል አይደለም። ይህ ማውጫ የሚያገለግለው ለትምህርት እና ለመረጃ ምንጭነት ብቻ ነው። በዚህ ማውጫ ዝግጅት ላይ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያዘጋጀው ከ ቅጽ 1 እስከ 16 ማውጫን በመጠቀም የቀሩትን ቅጾች አጠቃለን አዘጋጅተናል።

አዘጋጆቹ ይህን ማውጫ በሚያዘጋጁበት ጊዜ በውስጡ ያሉትን መረጃዎች እውነታነት ለማረጋገጥ አስፈላጊውን ጥረት አድርገዋል፡፡ ይህ ማውጫ ሲዘጋጅም ትክክለኛ መረጃ እንዲይዝ በማሰብ ነው፡፡ ሆኖም ግን በዚህ ማውጫ ላይ ሊኖሩ በሚችሉ ስህተቶች፣ ግድፈቶች፣ ጉድለቶች እንዲሁም አለመስማማቶች ሊከሰቱ ለሚችሉ ጉዳቶችም ሆነ ኪሳራ አዘጋጆቹ ምንም አይነት ኃላፊነት እንደማይወስዱ ያሳውቃሉ።

ይህ ማውጫ በዋነኛነት የመረጃ ምንጭ እንዲሆን እና ለሕግ ማህበረሰቡ ቀላል እና ፈጣን ማጣቀሻ እንዲሆን የተዘጋጀ ቢሆንም ቀጥታ የባለሞያ ምክር ወይም ድጋፍ አይተካም። ይህን አይነት አገልግሎት ከተፈለገ ከባለሞያ መጠየቅ አለበት፡፡

አዘጋጆቹን አቢሲኒያሎውን ከልብ ያመሰግናል!
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law https://t.me/lawsocieties
የዘንድሮ 12ኛ ክፍል የተማሪዎች አማካይ ውጤት በየትምህርት አይነቱ፤

አጠቃላይ መረጃ፡-  ፈተና የተፈተኑ ብዛት-----908,256 ናቸው፡፡

  አማራ………..30.37%
  ኦሮሚያ…..…27.96%
  ደቡብ………..28.17%
  ሀረሪ…………32.88%
  አዲስ አበባ----38.46%
  ደሬደዋ--------31.42%
  ሲዳማ---------28.34%

2. ከ50% እና በላይ ያስመዘገቡ ተማሪዎች ብዛት ከተፈተኑ መካከል

(እንደ ሀገር ያለፉ 29909 (3.3%) ናቸው

  አማራ………ከ246,675 መካከል 8,810 ((3.6%)
  ኦሮሚያ…..…327,737 መካከል 6,407 (2.0%)
  ደቡብ………..ከ127,345 መካል 2,533 (2.0%)
  ሀረሪ…………ከ1,849 መካከል 194 (10.5%)
  አዲስ አበባ----ከ47,980 መካከል 9,491 (19.8%)
  ደሬደዋ-------- ከ3,726 መካከል 250 (6.7%)
  ሲዳማ---------ከ53,478 መካከል 1247 (2.3%)

3. ተፈጥሮ ሳይንስ  ከ600 እና በላይ እንደ ሀገር 263 ተማሪዎች ያስመዘገቡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ

  አማራ………70 ተማሪዎች
  ኦሮሚያ…..…51 ተማሪዎች
  ደቡብ………..10 ተማሪዎች
  ሀረሪ…………1 ተማሪዎች
  አዲስ አበባ----117 ተማሪዎች
  ደሬደዋ-------- 2 ተማሪዎች
  ሲዳማ---------8 ተማሪዎች

4. ማህበራዊ ሳይንስ  ከ500 እና በላይ እንደሀገር 10 ተማሪዎች ያስመዘገቡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ

  አማራ………1ተማሪ
  አዲስ አበባ----8 ተማሪዎች
  ደሬደዋ-------- 1 ተማሪ

5. ሁሉንም ተማሪዎች 100% ያሳለፉ ት/ቤቶች 7 ትምህርት ቤቶች ሲሆኑ ከነዚህ ውስጥ

  ደሴ ልዩ አዳሪ ት/ቤት
  ባሕር ዳር ስቲም ት/ቤት
  ጎንደር ኮሙኒቲ ስኩል
  ወላይታ ሶዶ ሊቃ ት/ ቤት
  አዳማ ኦዳ አዳሪ ት/ ቤት
ናቸው።

6. ከፍተኛ ውጤት (የዓመቱ ሰቃይ)

👉ከአማራ ክልል ደሴ ልዩ አዳሪ ት/ቤት ተማሪ ሚኪያስ አዳነ 666 አስመዝግቧል።

https://t.me/lawsocieties
#housinginaddisababa
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law https://t.me/lawsocieties
Ministry of Revenues of Ethiopia/የገቢዎች ሚኒስቴር:
ሀብትን በማስተላለፍ የሚገኝ ገቢ
1. አንድ ሰው አንድን ሀብት ሲያስተላልፍ ከዚህ ሀብት የተገኘ ገቢ ሆኖ የሚወሰደው ሀብቱን ሲያስተላልፍ የተቀበለው ወይም የሚቀበለው ጠቅላላ የገንዘብ መጠን ሲሆን፣ ሀብቱ በተላለፈበት ጊዜ በዓይነት የተገኘውን ማንኛውንም ጥቅም ትክክለኛ የገበያ ዋጋ ይጨምራል፡፡
2. ለኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ደርጅት ወይም የኢትዮጵያ ማህበር የሚሰጥን እርዳታ ሳይጨምር ሀብት በስጦታ የተላለፈ እንደሆነ በተላለፈበት ጊዜ ያለው ትክክለኛ የገበያ ዋጋ ከሀብቱ የተገኘ ገቢ እንደሆነ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
3. አንድ ሰው ሀብቱን በማስተላለፍ ያገኘው ገቢ ሀብቱን ከማስተላለፍ ጋር በተያያዘ ከቀረበለት ምርጫ ያገኘውን ጥቅም ይጨምራል፡፡ ሆኖም ይህ ጥቅም እንደገቢ ተደርጐ የሚወሰደው ከቀረበለት ምርጫ ጋር በተያያዘ ባገኘው ጥቅም ላይ ግብር ያልከፈለ ሲሆን ብቻ ነው፡፡
4. አንድ ሀብት የጠፋ ወይም የወደመ እንደሆነ፣ የዚህ ሀብት ዋጋ ነው የሚባለው ባለሀብቱ ሀብቱ በመጥፋቱ ወይም በመውደሙ ምክንያት የተቀበለው ወይም የሚቀበለው የካሳ መጠን ሲሆን የሚከተሉትን ይጨምራል፡-
   ሀ) በመድን ፖሊሲ መሠረት፣ በካሳ ወይም በሌላ ስምምነት ምክንያት የተቀበለውን ወይም የሚቀበለውን የገንዘብ መጠን፤
   ለ) በድርድር ምክንያት የሚቀበለውን የገንዘብ መጠን፤ ወይም
   ሐ) የፍርድ ቤት ውሳኔን ተከትሎ የተቀበለውን ወይም የሚቀበለውን የገንዘብ መጠን፤
5. አንድ ሰው በአንድ ግብይት ሁለትና ከዚያ በላይ የሆኑ ሀብቶችን ያስተላለፈ እንደሆነና የእያንዳንዱ ሀብት ዋጋ ተለይቶ ያልታወቀ እንደሆነ፣ ሀብቶቹ በተላለፉበት ጊዜ ባለው ትክክለኛ የገበያ ዋጋ መሠረት በማስተላለፉ ምክንያት የተቀበለው የገንዘብ መጠን ለተላለፉት ሀብቶች እንደየድርሻቸው ይደለደላል፡፡
6. አንድ ግብር ከፋይ የተላለፈውን ሀብት ዋጋ የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ ያልቻለ እንደሆነ ሀብቱ በተላለፈበት ጊዜ የነበረው ትክክለኛ የገበያ ዋጋ የሀብቱ ዋጋ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
https://t.me/lawsocieties
#housinginaddisababa
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law https://t.me/lawsocieties
Ministry of Revenues of Ethiopia/የገቢዎች ሚኒስቴር:
ሀብትን በማስተላለፍ የሚገኝ ገቢ
https://t.me/lawsocieties
#housinginaddisababa
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law https://t.me/lawsocieties
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (TransparencyE TE)
"መኖር ማለት አለመሞት ከሆነ እስትንፋስ ያለው ሁሉ እየኖረ ነው።
ግን መኖር ማለት እራስን መሆን፣
ለዓላማ መቆም፣
ህሊናን አለመዘንጋት፣
ፍርድን አለማጓደል፣
ለራስ ብቻ ሳይሆን ለሌላው እራስን መስዋዕት ማድረግ ብሎም አርአያ የሚሆን ነገር ጥሎ ማለፍ ከሆነ ስንቶቻችን ነን በህይወት ያለነው?" ዶክተር #ምህረት_ደበበ
⁉️⁉️⁉️⁉️⁉️⁉️⁉️⁉️
#law #societies @lawsocieties
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Lawyer Mike 🔊የህግ ባለሙያ)
መሰረታዊ የሕግ ስህተት በአዲሱ የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
አንድ ጉዳይ የመጨረሻ ፍርድ ከተሰጠው በኋላ መሰረታዊ የህግ ስህተት ተፈፅሞበታል የሚባል ከሆነ መሰረታዊ የህግ ስህተቱ ሳይታረም እንዳይቀር በሰበር ለመታየት ዕድል ይሰጠዋል፡፡ ቀደም ሲል መሰረታዊ የህግ ስህተት ምንነት የህግ ትርጉም ያልተሰጠው የነበረ በመሆኑ ጉዳዮች መሰረታዊ የህግ ስህተት አለባቸው በሚል በብዛት ሲቀርቡ ይስተዋል ነበር፡፡ ይህን ለማስቀረት አዲሱ የፍርድ ቤቶች አዋጅ መሰረታዊ የህግ ስህተትን ምንነት ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ የመሠረታዊ የሕግ ስህተት ምንነትን እና ተያያዥ ጉዳዮችን እንመለከታለን፡፡

የመሠረታዊ የሕግ ስህተት ምንነት

በአዲሱ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀፅ 2(4) መሠረት “መሠረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት” ማለት

. የሕገ-መንግሥቱን ድንጋጌዎች የሚቃረን

ለ. ሕግን አላግባብ የሚተረጉም ወይም ለጉዳዩ አግባብነት የሌለውን ሕግ የሚጠቅስ

ሐ. ለክርክሩ አግባብነት ያለው ጭብጥ ያልተያዘበት ወይም ከክርክሩ ጋር የማይዛመድ አግባብነት የሌለው ጭብጥ የተያዘበት

መ. በዳኝነት ታይቶ ሊወሰን የሚገባውን ጉዳይ ውድቅ የተደረገበት

ሠ. በፍርድ አፈፃፀም ሂደት ከዋናው ፍርድ ጋር የማይገናኝ ትእዛዝ የተሰጠበት

ረ. ጉዳዩን አይቶ የመወሰን የዳኝነት ሥልጣን ሳይኖር ውሳኔ የተሰጠበት

ሰ. የአስተዳደር አካል ወይም ተቋም ከሕግ ውጭ ውሳኔ የሰጠበት

ሸ. የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎትን አስገዳጅ ውሳኔ በመቃረን የተወሰነ
እና ፍትህን የሚያዛባ ጉልህ የሕግ ስህተት ያለበት የመጨረሻ ውሳኔ፣ ፍርድ፣ ብይን፣ ትዕዛዝ ሲሆን መሰል ስህተት ያለባቸው ጉዳዮች በዚህ አዋጅ አንቀፅ 10 መሠረት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሚታረሙ ይሆናል፡፡ የመጨረሻ ውሳኔ ማለት በፍርድ ቤት፣ በህግ የመዳኘት ስልጣን በተሰጠው አካል፣ በተቋማት ወይም በአማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች የተሰጠ እና ለጉዳዩ እልባት የሚሰጥ ፍርድ፣ ብይን፣ ትዕዛዝ ውሳኔ ሲሆን የይግባኝ ሂደቶችን የጨረሰ ፍርድ፣ ብይን፣ ትዕዛዝ ወይም ውሳኔን እንደሚጨምር በአዋጁ አንቀፅ 2(5) ትርጓሜ ተሰጥቶታል፡፡

የጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ስልጣን

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ስልጣን የመነጨው ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 80(3)(ሀ) ሲሆን መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበትን ማናቸውንም የመጨረሻ ውሳኔ ለማረም በሰበር ችሎት የማየት ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡ በዚህም በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/13 አንቀፅ 10 መሰረት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለባቸውን የፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት በይግባኝ አይቶ የመጨረሻ ውሳኔ የሰጠባቸውን ጉዳዮች የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት የመጨረሻ ውሳኔ የሰጠባቸውን ጉዳዮች የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወይም የክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በህገ መንግስቱ በተሰጣቸው የውክልና ስልጣን ፌደራል ጉዳይን አይተው መጨረሻ ውሳኔ የሰጡበት ጉዳይ
የአዲስ አበባ ወይም የድሬደዋ ከተማ ፍርድ ቤት የመጨረሻ ውሳኔ የተሰጠባቸው የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የህገ መንግስቱ ድንጋጌዎች እና የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎቶች አስገዳጅ ውሳኔ ጋር በተያያዘ የመጨረሻ ውሳኔ የተሰጠባቸው ጉዳዮች የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ህግን አለአግባብ ከመተርጎም እና ለጉዳዩ አግባብነት የሌለውን ህግ ከመጥቀስ ጋር በተያያዘ የመጨረሻ ውሳኔ የተሰጠባቸው እና ጉዳዮቹ ለህዝብ ጥቅም ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው ውሳኔዎች በህግ የመዳኘት ስልጣን ተሰጠው አካል ወይም በሌሎች አካላት የተሰጠ የመጨረሻ ውሳኔ አግባብነት ያላቸው የህግ ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆነው በፌደራል ፍርድ ቤት ሊታይ ይችል በነበረ ጉዳይ ላይ በአማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች መሰረት የተሰጡ የመጨረሻ ውሳኔዎች እንዲሁም በሌሎች ህጎች የተጠቀሱ ጉዳዮች በሰበር አይቶ የማረም ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡

አንድ ጉዳይ በሰበር ሲታይ ከአምስት ያላነሱ ዳኞች ሊሰየሙ እንደሚገባ በአዋጁ አንቀፅ 25(2) ተደንግጓል፡፡ ከአምስት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት የሚሰጠው የሕግ ትርጉም በየትኛውም ደረጃ ላይ በሚገኝ የፌዴራል ወይም የክልል ፍርድ ቤት ላይ አስገዳጅነት እንደሚኖረው ከአንቀፅ 10(2) መረዳት ይቻላል፡፡

ይህን አምስት ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት የተሰጠው አስገዳጅ ውሳኔ ሰባት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት በድጋሚ ሊታይ ይችላል፡፡ ይህ የሚሆነው በባለጉዳዮች አመልካችነት ወይም በችሎቱ በራሱ አነሳሽነት ቀድሞ የሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም በተለያዩ ምክንያቶች ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው በሰባት ዳኞች ችሎት እንዲታ በቂ እና አሳማኝ ምክንያቶችን ተንትኖ በመግለፅ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሲያቀርብ እንደሆነ ከአንቀፅ 26(1) መረዳት ይቻላል፡፡ በዚህ መልኩ ጥያቄ ሲቀርብ ፕሬዝዳንቱ ጉዳዩ ሰባት ዳኞች በሚሰየሙበት ችሎት እንዲታይ የሚያደርግ ሲሆን በችሎቱ የሚሰጠው ውሳኔ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በማንኛውም ደረጃ ፍርድ ቤት አስገጃጅ ይሆናል፡፡

በተጨማሪም ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት ቀድሞ የሰጠውን የህግ ትርጉም ከሰባት ባላነሱ ዳኞች በተመሳሳይ ጭብጥ በሌላ ጊዜ ሊሻሻል ይችላል፡፡

ማጠቃለያ

በአጠቃላይ የሰበር ሥርዓት መሰረታዊ ህግ ስህተት ያለበት የመጨረሻ ውሳኔ የተሰጠበት ጉዳይ ለመጨረሻ ጊዜ የሚታይበትና እና የሚታረምበት የዳኝነት ሂደት ነው፡፡ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት ምንነት ደግሞ በአዋጁ የተገለፀ በመሆኑ ለሰበር የሚቀርቡ ጉዳዮች ይህንን ተከትለው መቅረብ አለባቸው፡፡

በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law https://t.me/lawsocieties
Urgent Vacancy for law graduates:

Executive Assistant and Research Associate

Officially licensed in Addis Ababa, Ethiopia, since January 2014 (with License Number: 14/706438/2006), THISAbility Consulting - Ethiopia is a multidisciplinary consultancy and training initiative with for over fifteen years of expertise at national, regional, and international levels focused on multiple crosscutting themes of disability rights law, designing training manuals and guidelines on inclusive practices, project evaluation and management, grant writing, and inclusive development. Further details about the Firm can be found at www.thisabilityethiopia.com.

We are now looking for an outstanding, experienced, demonstrably skilled, and motivated Executive Assistant and Research Associate.

REQUIRED QUALIFICATIONS AND EXPERIENCE:

Education: A minimum of #LLM degree in human rights #law.

At least 5 years of demonstrated experience in evidence-based research, training, consultancy, and project implementation.

Excellent communication skills in all four modalities of the English language (writing, reading, speaking and listening) is essential for this post. Other languages – local or international – would be an asset.

Ability and availability to work efficiently with local and international clients of the Firm.

Availability for local travels.

Demonstrated, genuine interest and motivation to work with/for human rights organizations and organizations of persons with disabilities.

Ability to conceptualize, articulate, and write reports with an advanced content, quality, and clarity.

Demonstrated ability to use Project Life Cycle Management tools.


HOW TO APPLY:

Interested applicants should submit an application letter outlining their motivation and suitability for this post and enclosing a detailed CV with references, two samples of their own written work (published or unpublished), and copies of academic/professional credentials and qualifications to the attention of the Executive Director via email: thisability.consulting@gmail.com.

Closing date for application: 25 April 2024.

Please note:
Only e-mail applications sent by the deadline date will be accepted.
Only short-listed candidates will be contacted for interviews.
Job Title: Lawyer

Job Type: On-site - Permanent (Full-time)

Job Sector: #Law

Work Location: Addis Ababa, Ethiopia

Education Qualification: Bachelor's Degree

Experience Level: Intermediate

Applicants Needed: Female

Salary/Compensation: Monthly

Deadline: July 30th, 2024

Description:
Note:- we need someone near Kality!

We are looking to hire a lawyer with brilliant research and analytical skills. Candidate should be, professional and well informed with a keen interest in upholding the law while protecting our company.
•  Preparing business plan
•  Preparing a sound company policy
•  Preparing employee handbook for each department in our company
•  Preparing a Standard contract agreement
•  Monitor legal risk in documentation and giving guidance on the acceptable assumption of risk
•  Representing the company on legal issues
•  Conduct legal research, gather evidence, Explain the law and give legal advice
•  Ensure that appropriate approvals are in place before documents are executed
•  Facilitate innovative solutions to client and stakeholder problems
Requirements:
•  Bachelor’s degree in law
•  Internship experience in drafting, negotiating and reviewing legal documents.
•  Ability to work under pressure and meet deadlines.
•  Ability to work independently and as part of a team.
•  Excellent interpersonal, communication and public speaking skills.

______

Abosh construction and trading plc
[Verified Company ]

10 Jobs Posted

From: @freelance_ethio | @freelanceethbot
We've just added the following 10 new laws to our comprehensive database. Stay informed and up-to-date on the latest legal developments.

1. Proclamation No. 1341/2024 - Value Added Tax Proclamation

2. Regulation No. 553/2024 - Unity Parks Corporation Establishment Council of Ministers Regulation

3. መመሪያ ቁጥር 1/2016 - የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናት ቀለብ አወሳሰን መምሪያ

4. Proclamation No. 1321/2024 - Personal Data Protection Proclamation

5. Proclamation No.1342/2024 - Export Trade Duty Incentive Schemes (Amendment) Proclamation

6. Proclamation No.1334/2024 - Proclamation to Determine Public Holidays and Celebration of Public Holidays

7. Proclamation No. 1316/2024 - Inte'l Development Association Loan Agreement for financing Ethiopia Education and Skills for Employability Project Ratification Proclamation

8. Proclamation No. 1318/2024 - Italian Republic Loan Agreement for Financing Budget Support Programme dedicated to Ethiopian Energy Sector Ratification Proclamation

9. Proclamation No.1329/2024 - Italian Republic Loan Ag't for financing Support to Job Creation Oriented Skills and Infrastructure Dev't Project” Ratification Proclamation

10. The Foreign Exchange Directive No. FXD/01/2024 - የውጭ ምንዛሪ መመሪያ ቁጥር FXD/01/2024

https://pocketlaw.abyssinialaw.com/
#law #legalupdates #database #newlaws #abyssinialaw