አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.83K photos
25 videos
1.86K files
3.55K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ሠራተኞቹ ከቢሮ ሳይወጡ ከ2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ አላግባብ አበል በልተዋል።


የማዕከሉ ሠራተኞች ባልተሳተፉበት ስብሰባ አበል ያወራርዱ እንደነበር እና ከሕግ አግባብ ውጭ የሆኑ ግዥዎች ሲፈጸሙ ነበር ተብሏል፡፡

በዚህም ከ46 ሺሕ ብር በላይ ከመስሪያ ቤቱ ውጭ ላሉ ባለሙያዎች ክፍያ ተፈጽሟል የተባለ ሲሆን፣ ከ204 ሺሕ ብር በላይም ለጸረ ሙስና ኮሚሽን ባለሙያ በሕግ አግባብ ውጭ የተከፈለ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

አዲስ ማለዳ
via #housinginaddisababa
https://t.me/lawsocieties
የዘንድሮ 12ኛ ክፍል የተማሪዎች አማካይ ውጤት በየትምህርት አይነቱ፤

አጠቃላይ መረጃ፡-  ፈተና የተፈተኑ ብዛት-----908,256 ናቸው፡፡

  አማራ………..30.37%
  ኦሮሚያ…..…27.96%
  ደቡብ………..28.17%
  ሀረሪ…………32.88%
  አዲስ አበባ----38.46%
  ደሬደዋ--------31.42%
  ሲዳማ---------28.34%

2. ከ50% እና በላይ ያስመዘገቡ ተማሪዎች ብዛት ከተፈተኑ መካከል

(እንደ ሀገር ያለፉ 29909 (3.3%) ናቸው

  አማራ………ከ246,675 መካከል 8,810 ((3.6%)
  ኦሮሚያ…..…327,737 መካከል 6,407 (2.0%)
  ደቡብ………..ከ127,345 መካል 2,533 (2.0%)
  ሀረሪ…………ከ1,849 መካከል 194 (10.5%)
  አዲስ አበባ----ከ47,980 መካከል 9,491 (19.8%)
  ደሬደዋ-------- ከ3,726 መካከል 250 (6.7%)
  ሲዳማ---------ከ53,478 መካከል 1247 (2.3%)

3. ተፈጥሮ ሳይንስ  ከ600 እና በላይ እንደ ሀገር 263 ተማሪዎች ያስመዘገቡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ

  አማራ………70 ተማሪዎች
  ኦሮሚያ…..…51 ተማሪዎች
  ደቡብ………..10 ተማሪዎች
  ሀረሪ…………1 ተማሪዎች
  አዲስ አበባ----117 ተማሪዎች
  ደሬደዋ-------- 2 ተማሪዎች
  ሲዳማ---------8 ተማሪዎች

4. ማህበራዊ ሳይንስ  ከ500 እና በላይ እንደሀገር 10 ተማሪዎች ያስመዘገቡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ

  አማራ………1ተማሪ
  አዲስ አበባ----8 ተማሪዎች
  ደሬደዋ-------- 1 ተማሪ

5. ሁሉንም ተማሪዎች 100% ያሳለፉ ት/ቤቶች 7 ትምህርት ቤቶች ሲሆኑ ከነዚህ ውስጥ

  ደሴ ልዩ አዳሪ ት/ቤት
  ባሕር ዳር ስቲም ት/ቤት
  ጎንደር ኮሙኒቲ ስኩል
  ወላይታ ሶዶ ሊቃ ት/ ቤት
  አዳማ ኦዳ አዳሪ ት/ ቤት
ናቸው።

6. ከፍተኛ ውጤት (የዓመቱ ሰቃይ)

👉ከአማራ ክልል ደሴ ልዩ አዳሪ ት/ቤት ተማሪ ሚኪያስ አዳነ 666 አስመዝግቧል።

https://t.me/lawsocieties
#housinginaddisababa
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law https://t.me/lawsocieties
Ministry of Revenues of Ethiopia/የገቢዎች ሚኒስቴር:
ሀብትን በማስተላለፍ የሚገኝ ገቢ
1. አንድ ሰው አንድን ሀብት ሲያስተላልፍ ከዚህ ሀብት የተገኘ ገቢ ሆኖ የሚወሰደው ሀብቱን ሲያስተላልፍ የተቀበለው ወይም የሚቀበለው ጠቅላላ የገንዘብ መጠን ሲሆን፣ ሀብቱ በተላለፈበት ጊዜ በዓይነት የተገኘውን ማንኛውንም ጥቅም ትክክለኛ የገበያ ዋጋ ይጨምራል፡፡
2. ለኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ደርጅት ወይም የኢትዮጵያ ማህበር የሚሰጥን እርዳታ ሳይጨምር ሀብት በስጦታ የተላለፈ እንደሆነ በተላለፈበት ጊዜ ያለው ትክክለኛ የገበያ ዋጋ ከሀብቱ የተገኘ ገቢ እንደሆነ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
3. አንድ ሰው ሀብቱን በማስተላለፍ ያገኘው ገቢ ሀብቱን ከማስተላለፍ ጋር በተያያዘ ከቀረበለት ምርጫ ያገኘውን ጥቅም ይጨምራል፡፡ ሆኖም ይህ ጥቅም እንደገቢ ተደርጐ የሚወሰደው ከቀረበለት ምርጫ ጋር በተያያዘ ባገኘው ጥቅም ላይ ግብር ያልከፈለ ሲሆን ብቻ ነው፡፡
4. አንድ ሀብት የጠፋ ወይም የወደመ እንደሆነ፣ የዚህ ሀብት ዋጋ ነው የሚባለው ባለሀብቱ ሀብቱ በመጥፋቱ ወይም በመውደሙ ምክንያት የተቀበለው ወይም የሚቀበለው የካሳ መጠን ሲሆን የሚከተሉትን ይጨምራል፡-
   ሀ) በመድን ፖሊሲ መሠረት፣ በካሳ ወይም በሌላ ስምምነት ምክንያት የተቀበለውን ወይም የሚቀበለውን የገንዘብ መጠን፤
   ለ) በድርድር ምክንያት የሚቀበለውን የገንዘብ መጠን፤ ወይም
   ሐ) የፍርድ ቤት ውሳኔን ተከትሎ የተቀበለውን ወይም የሚቀበለውን የገንዘብ መጠን፤
5. አንድ ሰው በአንድ ግብይት ሁለትና ከዚያ በላይ የሆኑ ሀብቶችን ያስተላለፈ እንደሆነና የእያንዳንዱ ሀብት ዋጋ ተለይቶ ያልታወቀ እንደሆነ፣ ሀብቶቹ በተላለፉበት ጊዜ ባለው ትክክለኛ የገበያ ዋጋ መሠረት በማስተላለፉ ምክንያት የተቀበለው የገንዘብ መጠን ለተላለፉት ሀብቶች እንደየድርሻቸው ይደለደላል፡፡
6. አንድ ግብር ከፋይ የተላለፈውን ሀብት ዋጋ የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ ያልቻለ እንደሆነ ሀብቱ በተላለፈበት ጊዜ የነበረው ትክክለኛ የገበያ ዋጋ የሀብቱ ዋጋ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
https://t.me/lawsocieties
#housinginaddisababa
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law https://t.me/lawsocieties
Ministry of Revenues of Ethiopia/የገቢዎች ሚኒስቴር:
ሀብትን በማስተላለፍ የሚገኝ ገቢ
https://t.me/lawsocieties
#housinginaddisababa
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law https://t.me/lawsocieties