አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.88K photos
25 videos
1.87K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የወሊድ መከላከያ ህክምና የወሰደው አባወራ ድጋሚ አባት መሆኑን ተከትሎ ክስ መሰረተ

የአራት ልጆች አባት የሆነው ሰው እርግዝና እንዳይፈጠር የሚከላከል ህክምና ቢያደርግም ሳይፈልግ አምስተኛ ልጅ አባት ለመሆን ተገዷል

የሕክምና ስህተት የሰራው ተቋም ልጄ 18 ዓመት እስኪሞላው ድረስ የማሳደጊያ ይከፈለኝ ሲል ክስ መስርቷል

ተጨማሪ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://bit.ly/3AxaCl6

#የሕግአማካሪ #0920666595
#ጠበቃ #ሚኪያስመላክ #MikiasMelak
አለሕግ #Alehig
👆👆👆👆👆👆👆👆👆

👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties

👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Ale_Hig

👉Website 👈
http://alehig.wordpress.com
August 18, 2024
#ጉምሩክ

" ሰርኩለሩ በዩኒ ሞዳል ተጓጉዘው ወደ አገር ውስጥ የሚገባ እቃዎች ግምት ውስጥ ያላስገባ " - አስመጪዎች

በርካታ የመኪና አስመጪዎች ከጉምሩክ አሰራር ጋር በተያያዘ ቅሬታ እንዳላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

አስመጪዎቹ በጋራ ፈርመው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ባላኩት ደብዳቤ ፤ " መንግስት በሀምሌ 22/2016 ዓ.ም በስራ ላይ እንዲውል ውሳኔ ያስተላለፈው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ከዚህ በፊት የነበሩ ውስብስብ የንግድ መዛባቶችን እና ብሮክራሲዎችን እንደሚያስቀር እንተማመናል " ብለዋል።

ነገር ግን የኢፌዲሪ ጉምሩክ ኮሚሽን ነሐሴ 03/2016 እና ነሐሴ 10/2016 ያወጣቸው ሰርኩላሮች ላይ ቅሬታ እንዳላቸው ጠቁመዋል።

" ይህም ሰርኩላር ይዞ ሊመጣ የሚችለውን ዘርፈ ብዙ ችግር ከግምት ውስጥ ያላስገባ እና ከጉምሩክ ትራንዚት እና መጋዘን አስተዳደር የሚጣረስ በመሆኑ ነው " ብለዋል።

አስመጪዎቹ " የኢትዮያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ ቁጥር FXD/01/2024 ተከትሎ የጉምሩክ ኮሚሽን ከ22/11/2016 በፊት የተመዘገቡ እና ተቀባይነት ያገኙ ሰነዶች ላይ በደብዳቤ ቁጥር 4/0/04/17 ነሐሴ 10 ቀን 2016 ዓ/ም ስርኩለት የተላከ ሲሆን ነገር ግን ሰርኩለር በዩኒ ሞዳል ተጓጉዘው ወደ አገር ውስጥ የሚገባ እቃዎች ግምት ውስጥ ያላስገባ " ነው ብለዋል።

ጉዳዩን ሲያብራሩም ፦

" በጉምሩክ ደንቡ ላይ በግልፅ እንደተቀመጠው የቀረጥ ማስከፈያ የሚወሰነው ዲ/ዬን. በተመዘገበበት እለት ያለው የብሔራዊ ባንክ ምንዛሬ ተመን በመጠቀም ነው።

ይህ ማለት በዮኒሞዳል አሰራር ሕጋዊ ዶክሜንት አሟልተን ዲ/ዬን ሞልተን ክፍያ ፈፅመን ሰነዱን የተሟላ መሆኑን ለጉምሩክ ኦፊሰር ተረጋግጦ ትራንዚት ተፈቅዶልናል፡፡

ትራንዚት ካስፈቀድን በኋላ ደግሞ ሕጉ በሚፈቅደው በአንድ ወር የትራንዚት ጊዜ ገደብ ውስጥ ኘሮሰስ ጨርሰን እቃዎቹን ወደ አገር ውስጥ አስገብተናል የጉምሩክ ሪስክ የሚጣለው ደግሞ እቃዎቹ አገር ውስጥ / መድረሻው ጣቢያ / ሲደርሱ መሆኑን ከግምት ያላስገባ ውሳኔ ነው።

እቃዎቹ ተጓጉዘው በድሬዳዋ መስመር /ደወሌ/ ለሚገቡ በድሬዳዋ ድልድይ ተሰብሮ ከ3 ሳምንት በላይ መቆማቸው ግምት ውስጥ ያላስገባ ውሳኔ ነው " ብለዋል።


" የጉምሩክ ኮሚሽን ከላይ የተገለጸውን ከግምት ውስጥ በማስገባት በአስቸኳይ የውሳኔ ማሻሻያ እንዲደረግልን እና በአዋጁ መሰረት እንድንስተናገድ " ሲሉ ጠይቀዋል።

በሌላ በኩል ከዚህ ቀደም ፤ " ጉምሩክ  ኮሚሽን አዋጅን በሴኩላር በማሻር የማይሆን ስራ እየሰራ ነው " ሲሉ ቅሬታቸውን ያቀረቡ አስመጪዎች አሁንም ተሻሻለ ተብሎ የወጣው ሴኩርላር ያለውን ችግር የሚፈታ አይደለም።

አሁንም ማሻሻያ እንደሚያስፈልግ አስገንዘበዋል።

ጉዳዩ  በገበያና ስራው ላይ ሚያመጣውን ከፍተኛ ተፅእኖ በመረዳት እውቀትን ከወቅታዊ ሁኔታ ጋር በማገናዘብ በውይይት መፍትሄ ሊፈለግለት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

#Customs #Ethiopia

@tikvahethiopia
August 18, 2024
#ወሳኝ_መረጃ!

ፍራንኮ ቫሉታ ተፈቀደ! ክልከላ ከተደረገባቸው ዕቃዎች ውጭ ሁሉም ዕቃዎች በፍራንኮ ቫሉታ እንዲገቡ ተፈቅዷል! (ይህ ውሳኔ በገበያ በሚወሰን የምንዛሬ ተመን ስርዓት ውስጥ ተጠባቂ ነው)::
August 19, 2024
በአስገድዶ ደፋሪዎች ላይ ከስቅላት እስከ ብልት ማኮላሸት የሚደርስ እርምጃ የሚወስዱ የዓለማችን ሀገራት👇👇👇


ቻይና እና ሳውዲ አረቢያ በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ የተባሉ ወንጀለኞችን በሞት ከሚቀጡ ሀገራት መካከል ናቸው

አሜሪካንን ጨምሮ ስድስት የዓለማችን ሀገራት በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ የተባሉ ወንጀለኞችን ብልት እንዲኮላሽ የሚፈቅድ ህግ አላቸው

ተጨማሪ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://bit.ly/3Av2AZS

#የሕግአማካሪ #0920666595
#ጠበቃ #ሚኪያስመላክ #MikiasMelak
አለሕግ #Alehig
👆👆👆👆👆👆👆👆👆

👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties

👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Ale_Hig

👉Website 👈
http://alehig.wordpress.com
August 19, 2024
በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ከባድ ቅጣት የሚጥሉ ሀገራት እነማን ናቸው?


ሰሜን ኮሪያ በአስገድዶ  መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ የተባሉ ወንጀለኞችን በእሳት ተቃጥለው እንዲሞቱ የሚፈቅድ ህግ አላት


ስድስት ሀገራት ደግሞ ብልት እስከ ማኮላሸት ድረስ ወንጀለኞችን ይቀጣሉ

ተጨማሪ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://bit.ly/46PX9AE

#የሕግአማካሪ #0920666595
#ጠበቃ #ሚኪያስመላክ #MikiasMelak
አለሕግ #Alehig
👆👆👆👆👆👆👆👆👆

👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties

👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Ale_Hig

👉Website 👈
http://alehig.wordpress.com
August 19, 2024
በዓለም ላይ ከሚገኙ ሴቶች መካከል 35 በመቶው ለጾታዊ ጥቃት የተጋለጡ ናቸው።

ይሁንና ጥቃቱን ከሚፈጽሙት ውስጥ 10 በመቶዎቹ ብቻ ህግ ፊት ቀርበው ውሳኔ ሲሰጣቸው ቀሪዎቹ በብዙ ምክንያቶች ተገቢውን ፍትህ አያገኙም ይላል ወርልድ ፖፑሌሽን ሪቪው በሪፖርቱ።

የአስገድዶ መድፈር ወንጀል በመላው ዓለም ያለ ክስተት ቢሆንም የተወሰኑ ሀገራት ወንጀሉን ፈጽመዋል በተባሉ ጥፋተኞች ላይ ከባድ ቅጣት እንዲጥሉ የሚፈቅድ ህግ አዘጋጅተዋል።

ሰሜን ኮሪያ በአስገድዶ መድፈር ጥፋተኛ የተባሉ ወንጀለኞች በእሳት ተቃጥለው እንዲሞቱ የሚፈቅድ ህግ አላት።

በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ከባድ ቅጣት የሚጥሉት ሀገራት የትኞቹ ናቸው? በዝርዝር ያንብቡ፦ https://bit.ly/3Av2AZS

#የሕግአማካሪ #0920666595
#ጠበቃ #ሚኪያስመላክ #MikiasMelak
አለሕግ #Alehig
👆👆👆👆👆👆👆👆👆

👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties

👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Ale_Hig

👉Website 👈
http://alehig.wordpress.com
August 20, 2024
August 20, 2024
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Lawyer Mike 🔊የህግ ባለሙያ)
እሁድ እሁድ ስናካሂድ የነበረውን ከምሽቱ 2:30 የእሁድ ችሎት ነፃ ውይይት ላልተወሰነ ጊዜ የተቋረጠ ሲሆን ውይይቱን ስንጀምር የምናሳውቅ ይሆናል‼️

#የእለቱ_ችሎት

#የችሎቱ_ጭብጥ

ፕሮግራም ለአልተወሰነ ጊዜ የተቋረጠ መሆኑን ስለማሳወቅ‼️

#ውሳኔ
ችሎቱ ቢያመልጥዎት በሌሉበት የሚሰማ ይሆናል።

ቀጠሮው እሁድ ማታ በስልክዎት በ @lawsocieties የቴሌግራም ቻናል በመዝገብ ስዓት ቁጥር 2:30 የመገኘት መብትዎ የተከበረ ሆኖ ተራዝሟል።

ወደ ቴሌግራም ቻናላችን ይመለሱ።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
#የሚነበብ#አለ_ህግ ስም አለበት
https://t.me/lawsocieties
August 20, 2024
የትራንስፖርት አበል እና የመጓጓዣ ወጪ ከግብር ነፃ የሚደረግባቸው ሁኔታዎች

ከገቢ ግብር ነፃ የተደረጉ ገቢዎች አፈፃጸም መመሪያ ቁጥር 1/2011 መሰረት የትራንስፖርት አበል እና የመጓጓዣ ወጪ ከግብር ነጻ የሚሆነው፡-

1. በስራ ባህሪው ምክንያት ስራውን ከቦታ ወደቦታ በመዘዋወር የሚያከናውን ተቀጣሪ ለአንድ ወር ጉዞ የሚከፈለው የትራንስፖርት አበል ከገቢ ግብር ነፃ የሚደረገው ከጠቅላላ የወር ደመወዙ ከአንድ አራተኛ(1/4) ባልበለጠ መጠን ብቻ ነው፡፡ ይሁንና የተቀጣሪው ጠቅላላ የወር ደመወዝ አንድ አራተኛ ከብር 2,200 የሚበልጥ ሲሆን ከግብር ነፃ የሚደረገው የትራንስፖርት አበል በማንኛውም ሁኔታ ከብር 2,200 ሊበልጥ አይችልም፡፡

2. አንድ ተቀጣሪ በስራ ባህሪው ምክንያት በመዘዋወር ለሚሰራው ስራ ለነዳጅ ወጪ የሚከፈለው ጥሬ ገንዘብ ለትራንስፖርት አበል እንደተከፈለ ተቆጥሮ ከገቢ ግብር ነፃ የሚደረገው ከጠቅላላ የወር ደመወዙ ከአንድ አራተኛ(1/4) ባልበለጠ መጠን ብቻ ነው፡፡ ይሁንና የተቀጣሪው ጠቅላላ የወር ደመወዝ አንድ አራተኛ ከብር 2200 የሚበልጥ ሲሆን ከግብር ነፃ የሚደረገው የነዳጅ ወጪ በማንኛውም ሁኔታ ከብር 2,200 ሊበልጥ አይችልም፡፡

3. አንድ ተቀጣሪ ከመኖሪያ ቤቱ ወደ ስራው ቦታ እንዲሁም ከስራው ቦታ ወደ መኖሪያ ቤቱ የሚጓጓዝበት የመስርያ ቤቱ የትራንስፖርት ሰርቪስ ቢቀርብም ባይቀርብም ለዚህ ዓይነቱ የትራንስፖርት አበል ከገቢ ግብር ነፃ የሚደረገው ከብር 600 ባልበለጠ መጠን ብቻ ነው፡፡

4. አንድ ተቀጣሪ ከመኖሪያ ቤቱ ወደ ስራ ቦታው እንዲሁም ከስራ ቦታው ወደ መኖሪያ ቤቱ ለመሄድ ለነዳጅ ወጪ በጥሬ ገንዘብ የሚከፈለው የትራንስፖርት አበል ከገቢ ግብር ነፃ የሚደረገው ከብር 600 ባልበለጠ መጠን ብቻ ነው፡፡

5. አንድ ተቀጣሪ ሥራውን ለማከናወን መደበኛ የሥራ ቦታው ከሚገኝበት ከተማ ውጪ ሲንቀሳቀስ ለመጓጓዣ ወጪ የሚሰጠው ክፍያ ከግብር ነፃ ሊሆን የሚችለው በስራ ላይ ባለው የትራንስፖርት ታሪፍ ወይም በሚያቀርበው ማስረጃ ላይ የተመሰረተ ሆኖ ከከፈለው የአየር፣ የውሃ እና የየብስ ትራንስፖርት የአገልግሎት ዋጋ ሊበልጥ አይችልም፡፡

6. አንድ የውጭ አገር ዜጋ ሥራን ለማከናወን ወደ የኢትዮጵያ ሲመጣ እና የውል ዘመኑን ጨርሶ ከሀገር ሲወጣ የሚከፈለው የትራንስፖርት ወጪ ከግብር ነፃ ሊሆን የሚችለው በተፈጸመው የቅጥር ውል መሰረት እና የአየር፣ የውሃ እና የየብስ ትራንስፖርት የአገልግሎት ዋጋ ታሪፍ መሰረት ሆኖ ከግብር ነፃ የሚሆነው ለግል መገልገያ ዕቃዎቹ የሚከፈለው የጭነት ሂሳብ ከ300 ኪሎ ግራም ሊበልጥ አይችልም፡፡

7. አንድ ግብር ከፋይ ከመደበኛ መኖሪያ ቦታቸው ርቀው ሥራቸውን የሚያከናወኑ ሠራተኞች ቤተሰባቸውን ለመጠየቅ የሚያደርጉትን ጉዞ ውጪ የሚሸፍን በሚሆንበት ጊዜ የዚህ ዓይነት ወጪ ከግብር ነፃ ሊሆን የሚችለው በተፈፀመው የቅጥር ውል ውስጥ ቀጣሪው ይህ ግዴታ ያለበት ሆኖ ሲገኝ ነው፡፡ ሆኖም ለዚህ ዓይነቱ ጉዞ የሚከፈለው ወጪ ከግብር ነፃ የሚደረገው በአንድ የግብር ዓመት ከሁለት የደርሶ መልስ ጉዞ ባልበለጠ መጠን ብቻ ነው፡፡
በበኃይሉ ሺመልስ
በድረ ገጽ፦ www.mor.gov.et
ERCA
ministryofrevene
#የሕግአማካሪ #ጠበቃ
https://t.me/Ethiopialegalinfo
August 20, 2024
"ጉዳዩ ለውሳኔ ለሚቀጥለው ዓመት ተቀጥሮ አድሯል" - አማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ

በሕጻን ሄቨን ጉዳይ አማራየ ክልል ፍትሕ ቢሮ የተሰጠ አጭር ማብራሪያ የሰጠ ሲሆን አሰቃቂ የወንጀል ድርጊቱ ተከትሎ ምን ተደረገ? ጉዳዩስ ምን ላይ ነው? የሚለውን የሚዳስስ ነው።

አማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ያስቀመጠው የፍርድ ሂደት፦

ድርጊቱ የተፈጸመው ከፍተኛ በጦር መሳሪያ የተደገፈ ግጭት (ጦርነት) በነበረበት ወቅት መሆኑን፤ ወንጀለኛው በቁጥጥር ሥር ከዋለ በኋላም መለቀቁንና የተጎጅ ቤተሰብን፣ የሕግ አካላትን ሳይቀር ተጽዕኖ ለማድረስ መሞከሩን ያስረዳል።

ተጠርጣሪው ዳግም በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ ምርመራው ተደርጎ በምርመራው እና ባሉት የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎች መነሻነት በተደራራቢ ወንጀል ሁለት ክስ ማቅረብ ተችሏል፡፡

ክሶቹም የግፍ ግድያ የወንጀል ሕጉ 539 እና በመድፈር መግደልን 620 (3) ያጣቀሰ ነበር። ይህም የሞት ፍርድ ወይም የዕድሜ ልክ እስራት ድረስ የሚያስቀጣ ነው ብሏል፡፡

በክርክር ሂደት ተከሳሽ ክዶ ጠበቃ አቁሞ የተከራከረ መሆኑንና ይህም ሕጋዊ አሠራር መሆኑን አንስቷል።

* የክልሉ ፍትህ ቢሮ በማብራሪያው በክርክሩ የታዩ የሙያ ሥነ ምግባር ጉዳዮች ወይም ወንጀል ከተፈጸመ ተጠያቂነት ይኖራል ቢልም በሂደቱ ላይ ምርመራ ስለመጀመሩ ግን አልገለጸም።

የግራ ቀኝ ክርክሩን ሰምቶ [የሥር ፍርድ ቤት] የቀረበው ማስረጃ የግፍ ግድያን ሳይኾን (539) በመደፈር መሞቷን የሚያረጋግጥ መኾኑን በማረጋገጥ ተጠርጣሪው በ25 ዓመት ፅኑ እስራት ሊቀጣ ውሳኔ ማሳለፉን አንስቷል፡፡

ፍርደኛው አሁንም ማረሚያ ቤት እንደሚገኝ የጠቀሰው ማብራሪያው በአሁኑ ወቅት ፍርደኛው የፍርደኛ ይግባኝ አቅርቦ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጉዳዩን በመመርመር ላይ ይገኛል ብሏል። ይሄም ሕጋዊ እና የተለመደ አሠራር ነው ሲል ነው ያስረዳው፡፡

ጉዳዩም ለውሳኔ ለሚቀጥለው ዓመት መቀጠሩን እና አሁንም ፍትሕ ቢሮው ጉዳዩን በአግባቡ እየተከታተለው እንደሚገኝ ጠቁሟል።

"ምናልባት ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የሚሰጠው ውሳኔ #በአሉታዊ ቢኾን ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ በዐቃቢ ሕግ በኩል የሚቀርብ እንደኾነም ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡" ሲል ነው ቢሮው በማብራሪያው የገለጸው።

@tikvahethmagazine
August 20, 2024
የህጻናት ቀለብ አወሳሰን መምሪያ.pdf
2.7 MB
👆👆👆
የሕፃናት ወርሃዊ የቀለብ አወሳሰን የስሌት ሰንጠረዥ
የሕፃናት ቀለብ አወሳሰን መምሪያ 1/2016

የፌዴራል ጠቅላይ  ፍርድ ቤት የህጻናት ቀለብ አወሳሰን መምሪያን ከስር ባለው ሊንክ በመግባት ያግኙ
የፌዴራል ጠቅላይ  ፍርድ ቤት የህጻናት ቀለብ አወሳሰን መምሪያን ከስር ባለው ሊንክ በመግባት ያግኙ
የፌዴራል ጠቅላይ  ፍርድ ቤት  ኮሚዩኒኬሽንና ስትራቴጂያዊ አጋርነት ዳሬክቶሬት
https://t.me/lawsocieties
August 21, 2024
#ኢራን

ኢራን በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ የተባለን ወንጀለኛ በስቅላት ገድላለች።

በማዕከላዊ ኢራን " ዝድ ክልል "አስገድዶ መድፈር መፈጸሙ በፍርድ ቤት የተረጋገጠበት ግለሰብ ሞት ተቀጥቷል።

ግለሰቡ " በጥንቆላ ይተዳደራል " የተባለ ሲሆን ወደሱ የሚመጡ ሴቶችን በማታለል አስገድዶ ሲደፍር እንደነበር ተገልጿል፡፡

ከ12 በላይ የክስ መዝገቦች የተከፈቱበት ይህ ሰው አሱን ጨምሮ ከነ ረዳቱ ጥፋተኛ ሆነው ተገኝተው በሞት ፍርድ እንዲቀጡ ውሳኔ ተላልፎባቸዋል፡፡

በፍርድ ቤቱ ውሳኔ መሰረትም ጥፋተኛ የተባሉት ሰዎች ታንቀው እንዲገደሉ ተደርጓል።

ኢራን በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ በተባሉ ወንጀለኞች ላይ ከባድ ቅጣት ከሚጥሉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት።

መረጃው የአን አይን ኒውስ / አል አረቢያ ነው።
#የሕግአማካሪ #0920666595
#ጠበቃ #ሚኪያስመላክ #MikiasMelak
አለሕግ #Alehig
👆👆👆👆👆👆👆👆👆

👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties

👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Ale_Hig

👉Website 👈
http://alehig.wordpress.com
August 21, 2024
የህግ ባለሙያው ደረጀ ዘለቀ (ዶ/ር) በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል:: 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

የህግ ባለሙያው ደረጀ ዘለቀ (ዶ/ር) ባደረባቸው ህመም በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ነሀሴ 15 ቀን 2016ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል::

የህግ ባለሙያው ደረጀ ዘለቀ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ክፍል በመምህርነት ለረጅም አመታት ያገለግሉና በተለይም ባለፉት ቅርብ አመታት በብዙሃን መገናኛዎች በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ላይ የሚያምኑበትን አቋም በግልፅና በቀጥታ በማቅረብ የሚታወቁ ባለሙያም ነበሩ::

የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር በህግ ባለሙያው ደረጄ ዘለቀ (ዶ/ር) ህልፈት የተሰማውን ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰብ ወዳጅ ዘመድ እና የሙያ ባልደረቦቻቸው መፅናናትን ይመኛል::

የቀብር ስርአታቸው ዛሬ ሀሙስ ነሃሴ 16/2016 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ላይ በጴጥሮስ ወ ጳውሎስ  ቤተክርስቲያን እንደሚፈፀም ከቤተሰቦቻቸው የተገኘው መረጃ ይገልፃል::።
August 22, 2024
vacancy
August 22, 2024
ሞት የተፈረደባቸው እስረኞች ፍርዱ እንዲፈጸምባቸው ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅን ዘውዴን በደብዳቤ ተማፀኑ‼️
በቃሊቲ ማረሚያ ቤት የሚገኙና የሞት ፍርድ የተወሰነባቸው ታራሚዎች ቅጣቱ እንዲፈጸም የሀገሪቱን ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴን በደብዳቤ ጠይቀዋል‼️
የሞት ፍርዱ እንዲፈጸምባቸው የጠየቁት በለጠ አሰፋ አምሜ፣ ጀበሳ ድንቁ ኦርዶፋ፣ ባዩ ጌታነህ ዜና፣ ግርማ ገዛኸኝ ማሞ እና መስታወት ጌታነህ ወ/የስ ናቸው።
ታራሚዎቹ ከ17 ዓመታት በላይ በእስር መቆየታቸውን ቤተሰቦቻቸው ተናግረዋል።

የሲቪልና ፖለቲካ መብቶች አለም አቀፍ ቃል ኪዳን፤ ማንኛውም የሞት ቅጣት የተፈረደበት ሰው ይቅርታ የመጠየቅ ወይም የሞት ቅጣቱ ወደ እስራት እንዲቀየርለት የመጠየቅ መብት እንዳለው ይደነግጋል። በተጨማሪም በሁሉም ጉዳዮች ይቅርታ ወይም ምህረት ማድረግ ወይም የሞት ቅጣቱን ወደ እስራት ቅጣት መለወጥ ይቻላል ይላል።

የሞት ቅጣቱ እንዲፈጸምባቸው የጠየቁት እስረኞቹ ፤ የሞት ፍርዱ ወደ ቁጥር እስራት እንዲቀየር ቢያመለክቱም ምላሽ እንዳላገኙ ነው ቤተሰቦቻቸው ለአዩዘሀበሻ የገለፁት ።
ታራሚዎቹ ፤ አሁን ላይ የኢትዮጵያ ፍትሕ ሚኒስቴር በሚሰጠው ምህረትና ይቅርታ ተጠቃሚ አለመሆናቸውንና ነገ የሚሉት ተስፋ እንደሌላቸው በመግለጽ የሞት ፍርዱ እንዲፈጸምባቸው ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅን በደብዳቤ ጠይቀዋል።

በይቅርታና በምህረት ተጠቃሚ ካለመሆናቸውም በላይ በማረሚያ ቤቱ የሚቀርበው ምግብና ያለው አያያዝ አስከፊ በመሆኑ በሕይወት ከመቆየት መሞትን መምረጣቸውን ገልጸዋል።
Ayu Zehabesha-Official አዩዘሀበሻ
#የሕግአማካሪ #0920666595
#ጠበቃ #ሚኪያስመላክ #MikiasMelak
አለሕግ #Alehig
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/
August 22, 2024
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ የተከሰተው በአንድም በሌላም በተለያየ መንገድ ተፅዕኖ የፈጠሩ ኢትዮጵያውያን የሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም ሕግ እውቀት ተደራሽነት አሳሳቢ መሆኑን በግልጽ ያሳዬ ነው።
ሕግ እና ስርዓት አክብሮ መስራት ለእራስ ነው።
ማንኛውም ሰው ያለ ፈቃዱ መቅረጽ አይቻልም፣ በተለይም የአንድን ተቋም አሰራር እና ደንብ አክብሮ አገልግሎት ማግኘት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው።
ሕግን አለማወቅ ከተጠያቂነት አያድንም!
ስለሆነም የሰሞኑ #የጆን #ዳንኤል ጉዳይ ከሕግ እና ከተከበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሰራር እና ስርዓት ያፈነገጠ ስሜታዊነት የበዛበት ከንቱ ጩኸትና መብትና ግዴታችንን የት እና እንዴት እንዲሁም መቼ እንጠቀማለን፣ እንጠይቃለን የሚሉትን ጥያቄዎች ያልመለሰ ሆኖ አግኝተነዋል።
በጊዜው የነበረው የአየር ሁኔታ ለመብረር አመች አይደለም ተብሎ በባለሙያዎች በረራውን ሲሰረዝ ለግለሰቡም/#ጆን_ዳንኤል ደህንነት አየር መንገዱ የስራ ግዴታ እና ሀላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን ሊሰመርበት ይገባል።
AleHig አለሕግ ከዛሬ ጀምሮ ለማንኛውም ለሶሻል ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች እና ተጠቃሚዎች ነፃ አማራጭ የሕግ እውቀት እንሰጣለን።
መብትና ግዴታችንን የት እና እንዴት እንዲሁም መቼ እንጠይቃለን፣ እንጠይቃለን ከሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም አንፃር።
#አለሕግ
ሕግን አለማወቅ ይቅርታን ሊያስገኝ አይችልም። የፍ/ሕ/ቁ 2035(2)
ለመሰረታዊ የሕግ እውቀት በቴሌግራም
ቤተሰብ ይሁኑ👇
https://t.me/lawsocieties
አማራጭ የሕግ እውቀት አለ
Alternative legal enlightenment/ALE
Legal Information🔵

👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties

👉Facebook Page
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

#Share 👈👈👈👈
August 23, 2024
No one is Above the Law!

The ongoing issue of unnecessary and excessive use of force, including incidents of police brutality and mistreatment during detention, continues to be troubling. According to a report by the Reporter news in 2023, 346 cases of torture or inhuman treatment were documented, with the most frequent occurrences reported in Addis Ababa and the Somali region. Such actions contradict Article 5 of the Universal Declaration of Human Rights, which prohibits torture and cruel, inhuman, or degrading treatment or punishment. As a signatory to international conventions, the Ethiopian government is obligated to uphold these standards.

#RespectHumanRights #TheLawistheLaw #ProtectThePeople #DemocracyAndGoodGovernance
August 23, 2024
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
#ጉምሩክ

🔴 “ በኢንቮይስም ከፍለን እቃው በገባበት ቀን ነው የምንሰራላችሁ አሉን ” - አስመጪዎች

⚫️ “ በሁሉም ጉዳይ አቤቱታ ይቀርባል አቤቱታ የቀረበበት ሁሉ ተቀባይነት የሚያገኝበት ሁኔታ አይኖርም” - ኮሚሽኑ

ጉምሩክ ኮሚሽን ከማክሮ ኢኮኖሚ ፓሊሲ ጋር በተያያዘ ከዚህ ቀደም ባወጣው አዲስ መመሪያ "ከእጥፍ በላይቀረጥ ክፈሉ'' እየተባሉ መሆኑን አስመጪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው የሚታወስ ሲሆን፤ ኮሚሽኑም ከቅሬታው በኋላ ማሻሻያ ማድረጉን መረጃ ነግረናችሁ ነበር።

ሆኖም ከ150 በላይ የሚሆኑ “ በኢነቮይስ ከፍለናል ” የሚሉ አስመጪዎች፣ ኮሚሽኑ ከማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ትግበራወሰ በኋላ ያወረደውና በአስመጪዎች በኩል “ አዋጅን በደብዳቤ ሽሯል ” በሚል ቅሬታ ቀርቦበት ኮሚሽኑ በድጋሚ ማሻሻያ አደረኩበት ያለው ደብዳቤም ቅሬታቸውን እንዳልፈታላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡

በዚህም እንዲያወያያቸው ጭምር ኮሚሽኑን በደብዳቤ እንደጠቁ ሆኖም ምላሽ እንዳልጠሰጣቸው ገልጸው፤ ጉዳዩን በድጋሚ እንዲያጤነው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳስበዋል።

አስመጪዎች በዝርዝር ያቀረቡት ቅሬታ ምንድን ነው ?

“ ደብዳቤው (ማስተካከያ የተደረገበት) መልስ ስላልሰጠን መልሰን ደብዳቤ ፃፍንላቸው፡፡ ምክንያቱም ከማክሮ ኢኮኖሚው ማሻሻያ በፊት የገቡ እቃዎች እንዲስተካከሉ ተብሎ ብዙዎቹም አውጥተዋል፡፡

የእኛ ጥያቄ፤ ቅድሚያ እቃው ዶኩሜንት እንደደረሰን ጂቡቲ ላይ እንዳለ በኢንቮይስ ዲክላራሲዮን ይቆረጣል። ጂቡቲ ጭነት ሊዘገይ ስለሚችል ፤ በየሳምንቱ ደግሞ ሬት ስለሚቀይር ያንን ነገር እንዳይነካው ሁሉም ነጋዴ ከዚህ በፊት ለዓመታት የሰራው በዚህ አይነት አካሄድ ነው፡፡

እቃው ጂቡቲ እያለ ዶኩሜንቱ ከመጣ በኢንቮይስ ይከፈላል። ቀሪ ሂሳብ ደግሞ ከፍተሻ በኋላ 'ይለቀቅ' ሲባል ያኔ ተከፍሎ ይመጣል፡፡ አሁን ግን በኢንቮይስም ከፍለን 'እቃው በገባበት ቀን ነው የምንሰራላችሁ' አሉን፡፡

እኛ ደግሞ አልተስማማንም፡፡ ጉምሩክ  በገባበት ሳይሆን ዶኩሜንት ባስገባንበት፤ ዲክራላሲዮን ባስቆረጥንበት ነው መስተናገድ ያለብን፡፡ 5 ሚሊዮን ስንከፍል የነበርነው 10 ሚሊዮን፣ 10 ሚሊዮን ይከፍል የነበረ 20 ሚሊዮን ብር ከፈሉ እየተባልን ነው፡፡

አሁን ጠዋት አንድ ሬት ከሰዓት ሌላ ሬት አለው ጉምሩክ፤ ድሮ ግን በየሳምንቱ አንድ ሬት ነበረው፡፡ ሐሙስ ቀን የሚቀየር ሬት ብቻ ነበር የሚሰጡት፡፡

ይህ ደግሞ ኪሳራና ተጠቃሚውም ላይ ከፍተኛ ጫና እንደሚጣመጣበት ጉምሩክም ይገነዘባል፡፡ ይህን ነገር ቢያስተካካል ባለው ዋጋ መሸጥ ይቻላል ”
ነው ያሉት፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለቀረበው ቅሬታ የኮሚሽኑ ምላሽ ምንድን ነው ? ኮሚሽኑ ባለፈው አደረኩት ባለው ማሻሻያ የአሁኖቹ ቅሬታ አቅራቢዎችን ጉዳይ አካቶ ምላሽ ሰጥቷል? ከሆነ እንዴት ? ሲል ጉምሩክ ኮሚሽኑንን ጠይቋል።

የኮሚሽን ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዘሪሁን አሰፋ ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።

“ ኮሚሽኑ የተለዬ ምላሽ የለውም ከዚያ ጉዳይ ጋር በተያያዘ። የተሰጠው ምላሽ ሁሉንም ጉዳዮች ከቨር ያደረገ ስለሆነ ቀደም ሲል በወጣ ደብዳቤ ምላሽ የተሰጠበት ጉዳይ ነው፡፡

የተለዬ ኮሚሽኑ የሚያየው ጉዳይ የሌለ መሆኑን ነው የማውቀው። ሁሉም ጉዳዮች እዛ ላይ ቴኪኒካሊ ከጉምሩክ አዋጅ አንጻር ታይተው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።

አጠቃላይ ነው ባለፈውም አቤቱታ የቀረበው፡፡ ስለዚህ ምላሽ የተሰጠበት አግባብ አለ፡፡ በሁሉም ጉዳይ አቤቱታ ይቀርባል አቤቱታ የቀረበበት ሁሉ ተቀባይነት የሚያገኝበት ሁኔታ አይኖርም፤ ይታወቃል።

'መስተናገድ የለብን በዚህ የሚል ጉዳይ' ካለ ኮሚሽኑ የሰጠውን ምላሽ መቃወም መብት ነው። ተራ ቁጥር 1፣ 2፣ 3፣ 4 በሚሉ ተራ ቁጥሮች ላይ ተገልጿል፡፡

የተቀመጡት ኮንዲሽኖች ጂቡቲ ላሉት እቃዎች፣ አገር ውስጥ ላልገባ እቃ በነባሩ የውጭ ምንዛሪ እንስተናገድ ነው ጥያቄያቸው። ያነም ኮሚሽኑ ደብዳቤው ላይ በገለጸው ልክ (ተራቁጥር አራት ይመስለኛል) በግለጽ የተቀመጠ ጉዳይ ነው።

እነርሱ አቤቱታቸውን መቀጠል ይችላሉ፤ ኮሚሽኑ እኮ ከዚህ አንጻር የከለከለው ነገር የለም፡፡ ስለዚህ የተሰተው ምላሽ ይሄው ነው ከዚያ ውጪ የተለየ የሚሰጥ ምላሽ የለንም በዚያ ደብዳቤ ተመልሶ ያለፈ ጉዳይ ስለሆነ”
ብለዋል።

#TikvahethiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
August 23, 2024
የፌደራል_ፍርድ_ቤቶች_የችሎት_ስርዓት_መመሪያ_የፀደቀ_መሆኑን_ስለማሳወቅ.pdf
6.7 MB
ለክቡራን ጠበቆች እና ነ/ፈጆች የአለባበስ ስርዓት /መመሪያ ቁጥር 13/2014/
August 24, 2024
ከባድ የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ ሁለት ተከሳሾች እስከ 70 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ተቀጡ::

👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ በተለያዩ ወረዳዎች በመንቀሳቀስ ከባድ የስርቆት ወንጀሉን በተለያዩ ጊዜያት የፈፀሙት ሳሙኤል ሀይሉ እና ሳቢር ከድር የተባሉት ተከሳሾች መሆናቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

ተከሳሾቹ የግለሰቦችን መኖሪያ ቤት እና የንግድ ቤቶችን በር በመገንጠልና በተመሳሳይ ቁልፍ ከፍተው በመግባት ላፕቶፕ፣ ኮምፒውተር፣ ቴሌቪዥኖች እና ሌሎች የተለያዩ እቃዎችን ሰርቀው መውሰዳቸውን የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የልዩ ልዩ ወንጀሎች ምርመራ ማስተባበሪያ ሀላፊ ዋና ኢንስፔክተር በልሁ ወልደኢየሱስ ገልፀዋል።

ፖሊስ ወንጀል ፈፃሚዎቹን በቁጥጥር ስር አውሎ ባከናወነው ምርመራ የማስፋት ስራ የተሰረቁትን ንብረቶች ማስመለስ መቻሉም ነው የተገለፀውል።

ንብረቶችን ከወንጀል ፈፃሚዎቹ እየተቀበለች በቤቷ ውስጥ ደብቃ ስታስቀምጥ የነበረች ትዕግስት ስመኝ የተባለች ግለሰብም ተይዛ ምርመራ እንደተጣራባት መርማሪው አስረድተዋል።

በሶስቱ ተከሳሾች ላይ በአጠቃላይ ዘጠኝ የክስ መዝገብ የተደራጀባቸው ሲሆን ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት በአምስቱ መዝገቦች ላይ የቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል።

በዚህም መሠረት ተከሳሽ ሳሙኤል ሀይሉ በእያንዳንዱ 5 የክስ መዝገቦች ላይ የተሰጠው ውሳኔ በድምሩ #70 ዓመት እስራት ሲሆን፣ በሁለተኛ ተከሳሽ ሳቢር ከድር ላይ በእያንዳንዱ 5 የክስ መዝገቦች በድምሩ የ65 ዓመት እስራት ቅጣት መወሰኑን ዋና ኢንስፔክተር በልሁ አስረድተዋል።

የተሰረቁትን ንብረቶች በመሸሸግ ወንጀል የተከሰሰችው ትዕግስት ስመኝ ከአምስቱ የክስ መዝገቦች በአራቱ በእያንዳንዱ የሶስት አመት እስራት እንድትቀጣ እና ቅጣቱ በገደብ እንዲሆንላት የተደረገ ሲሆን በአንደኛው መዝገብ በተመሳሳይ በ 3 አመት እስራት እንድትቀጣና ቅጣቷን ማረሚያ ቤት ሆና እንድትፈፅም ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ማስተላለፉን የምርመራ ሃላፊው አብራርተዋል።

ተከሳሾቹ ከተደራጀባቸው ዘጠኝ የክስ መዝገቦች መካከል ውሳኔ ያላገኙት ቀሪ 4 መዝገቦች በሂደት ላይ እንደሚገኙም ሀላፊው ጨምረው ተናግረዋል።
#EBC
#የሕግአማካሪ #0920666595
#ጠበቃ #ሚኪያስመላክ #MikiasMelak
አለሕግ #Alehig
👆👆👆👆👆👆👆👆👆

👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties

👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Ale_Hig

👉Website 👈
http://alehig.wordpress.com
August 24, 2024
የግብር ከፋይ/ተገልጋዮች መብቶች

ግብር ከፋዮቻችን ወይም ተገልጋዮቻችን ከሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን ጋር በሚኖርዎት ግንኙነት የሚከተሉት መብቶች እንዳልዎት ያውቁ ይሆን? ለግንዛቤ እንዲሆንዎ እንደሚከተለው አቅርበንልዎታል፡፡

👉ተገልጋዮች በሥራ ላይ ስላሉ የግብር ድንጋጌዎች፣ ተቋሙ ስለሚሰጣቸው አገልግሎቶችና ቅድመ ሁኔታዎች ተገቢውን መረጃ እንደ አግባብነቱ በስልክ እና በአካል በመቅረብ መረጃዎቹን የመጠየቅ፣ ምላሽ የማግኘት እና አገልግሎቶቹን የመጠቀም መብት አላቸው፡፡
👉 ማንኛውም የተቋሙ ተገልጋይ በጾታ፣ በዘርና ቋንቋ፣ በሃይማኖት፣ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ደረጃው መገለል እና አድልዎ ሳይደርስበት በተገቢው ሁኔታ አገልግሎት የማግኘት መብት አለው፡፡
👉 ማንኛውም ተገልጋይ ክብሩና ስብዕናው ተጠብቆ የመስተናገድ እና ለሚያቀርባቸው አግባብነት ያላቸው የአገልግሎት ጥያቄዎች እንደሁኔታው አዎንታዊ ይሁን አሉታዊ ምላሽ የማግኘት መብት አለው፡፡
👉 ተገልጋዮች ለሚያቀርቡት የአገልግሎት ጥያቄ ወዲያው ምላሽ ለመስጠት የማይቻልበት ሁኔታ ሲኖር እና ቀጠሮ የሚሰጣቸው ከሆነ በሂደት ላይ የሚገኘው ጉዳያቸው ምን ደረጃ ላይ እንደደረሰ እንዲሁም የትና በየትኛው ክፍል እንደሚገኝ (ጉዳዩ እስኪጠናቀቅ በምስጥር መያዝ የሚገባቸውን ጉዳዮች ካልሆኑ በስተቀር) ጠይቀው የመረዳት መብት አላቸው፡፡
👉 የተቋሙ ተገልጋዮች በተቋሙ አሠራር፣ በሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ሥነ ምግባር እና በአጠቃላይ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ቅሬታ ካላቸው ቅሬታቸውን የማቅረብ፣ ተገቢውን ወቅታዊ ምላሽ የማግኘትና የመደመጥ መብት አላቸው፡፡
👉 በተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥና አሠራር ዙሪያ የታዘቡትንና ቢሆን ይሻላል የሚሉትን ተገቢ አስተያየት በማመስገንም ሆነ በመተቸት በነፃነት የመግለጽ መብት አላቸው፡፡
👉 አርአያነት ባለው ሁኔታ የግብር ግዴታቸውን የሚወጡ ግብር ከፋዮች ሽልማት የመቀበል መብት አላቸው፡፡

በመሆኑም ከላይ የተዘረዘሩት መብትዎ መሆኑን ተገንዝበው ይጠቀሙበት፡፡

በድረ ገጽ፦ www.mor.gov.et
#የሕግአማካሪ #0920666595
#ጠበቃ #ሚኪያስመላክ #MikiasMelak
አለሕግ #Alehig
👆👆👆👆👆👆👆👆👆

👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties

👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Ale_Hig

👉Website 👈
http://alehig.wordpress.com
August 24, 2024
August 24, 2024
August 24, 2024
አለሕግAleHig ️
ከባድ የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ ሁለት ተከሳሾች እስከ 70 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ተቀጡ:: 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ በተለያዩ ወረዳዎች በመንቀሳቀስ ከባድ የስርቆት ወንጀሉን በተለያዩ ጊዜያት የፈፀሙት ሳሙኤል ሀይሉ እና ሳቢር ከድር የተባሉት ተከሳሾች መሆናቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል። ተከሳሾቹ የግለሰቦችን መኖሪያ ቤት እና የንግድ ቤቶችን በር በመገንጠልና በተመሳሳይ…
ሚዲያዎች ሙያዊ በሆነ ጉዳይ ላይ ዘገባ ሲሰሩ መጠንቀቅ አለባቸው                
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇        
በሀገራችን የወንጀለኛ መቅጫ ህግ መሠረት ሊጣሉ የሚችሉት የቅጣት አይነቶች የሚከተሉት ናቸው::

➨መቀጮ (ከ10 ብር - 10,000 ብር)
➨ቀላል እስራት (ከ 10 ቀን - 3 አመት)
➨ፅኑ እስራት (ከ 1አመት - 25 አመት) ➨የእድሜ ልክ እስራት እና
➨የሞት ፍርድ ናቸው
በወንጀለኛ መቅጫ ህግ አንቀፅ 108 መሠረት የፅኑ እስራት ቅጣት ከ 1 አመት እስከ 25 አመት ብቻ ሲሆን ፣ ነገር ግን በህግ በልዩ ሁኔታ ተገልፆ ሲገኝ የእድሜ ልክ እስራት ሊወሰን ይችላል።
አንቀፅ 184 ንዑስ አንቀፅ (1) (ለ) ስር በግልፅ እንደሰፈረው ነፃነትን የሚያሳጡ ተደራራቢ ወንጀሎች ባጋጠሙ ግዜ ለያንዳዳቸው ወንጀሎች ቅጣታቸው ተወስኖ ሁሉም ቅጣቶች የሚደመሩ ቢሆኑም በጠቅላላው ክፍል ከተቀመጠው ከፍተኛ ቅጣት መብለጥ ግን አይችልም።
ይህ ማለት ተደራራቢ ወንጀሎቹ በቀላል እስራት የሚስቀጡ ከሆነ  ቅጣታቸው  ተደምሮ ከ 3 አመት ሊበልጥ አይችልም፣ እንዲሁም በፅኑ እስራት የሚያስቀጡ ከሆነ ከተቀመጠው ጣሪያ 25 አመት በላይ መብለጥ አይችልም።
  ከዚህ አንፃር የተወሰነውን ውሳኔ ስንመለከት ፍርድ ቤቱ መሠረታዊ የህግ ስህተት ፈፅሟል። ምክንያቱም በሀገራችን ወንጀለኛ መቅጫ ህግ መሠረት ሊወሰን የሚችለው ከፍተኛ የፅኑ እስራት ቅጣት 25 አመት ብቻ ሆኖ ሳለ ወንጀለኛውን በ 70 አመት እንዲቀጣ መወሰኑ የህግ መሠረት የሌለው ነው።
ህጉ ካስቀመጠው የ25 አመት ፅኑ እስራት ውጪ በህጉ በግልፅ ተደንግጎ ሲገኝ ብቻ 'የሞት ፍርድ' ወይም 'የእድሜ ልክ እስራት' ሊወሰን ይችላል።
በተሻገር ደምስ
ሕግን አለማወቅ ይቅርታን ሊያስገኝ አይችልም። የፍ/ሕ/ቁ  2035(2)
ለመሰረታዊ የሕግ እውቀት በቴሌግራም
ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
አማራጭ የሕግ እውቀት አለ
Alternative legal enlightenment/ALE
Legal Information🔵
📞+251920666595
👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties

👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

👉YouTube 👈
https://www.youtube.com/@Ale_Hig

👉Website 👈
http://alehig.wordpress.com
August 24, 2024
አለሕግAleHig ️
ሚዲያዎች ሙያዊ በሆነ ጉዳይ ላይ ዘገባ ሲሰሩ መጠንቀቅ አለባቸው                 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇         በሀገራችን የወንጀለኛ መቅጫ ህግ መሠረት ሊጣሉ የሚችሉት የቅጣት አይነቶች የሚከተሉት ናቸው:: ➨መቀጮ (ከ10 ብር - 10,000 ብር) ➨ቀላል እስራት (ከ 10 ቀን - 3 አመት) ➨ፅኑ እስራት (ከ 1አመት - 25 አመት) ➨የእድሜ ልክ እስራት እና ➨የሞት ፍርድ ናቸው በወንጀለኛ…
ተከሳሹ በአንድ መዝገብ ላይ በተለያዩ የወንጀል ድንጋጌዎች የተከሰሰ ሲሆን ቅጣቱ ጣሪያውን (25 ዓመት) ሳያልፍ መወሰን አለበት። ነገር ግን ወንጀሉ የተፈጸመበት ጊዜ የተለያየ ሆኖ ወይንም በተለያዩ የወንጀል መዝገቦች ፋይል ተከፍቶ የግል ተበዳዮችም በእያንዳንዱ መዝገብ ላይ የተለያዩ ሆነው በእያንዳንዱ የወንጀል መዝገብ የተሰጠውን ውሳኔ ለማሳየት ተፈልጎ የተለቀቀ መረጃ እንጅ በወንጀል ህጉ የተቀመጠውን ጣሪያ ባለማወቅ የሆነ አይመስለኝም!

እዚህ ጋር ግን እንደ ጥያቄ መነሳት ያለበት ጉዳይ በአንድ ተከሳሽ ላይ ተጣምሮ በአንድ የወንጀል መዝገብ ላይ ባልቀረበ የተለያየ የወንጀል መዝገብ ላይ የተሰጠ ውሳኔ ከጣሪያው (25 ዓመት) ቢያልፍ አፈጻጸሙ ምን ይሆናል?

የወንጀል ህጉ ያስቀመጠው ጣሪያ ቅጣት በአንድ የወንጀል መዝገብ ላይ ተደራርቦ ለቀረበ ክስ ነው ወይንስ በተለያዩ የወንጀል መዝገቦች ላይ (ፋይል) ለቀረቡ የወንጀል ክሶችም የሚሰራ ነው?

ንጋቱ አማኑኤል
August 25, 2024
ፌደራል ፖሊስ የአቪዬሸን አሰራርን ጥሰዋል ባላቸው 6 ተጠርጣሪዎች ላይ የሽብር ወንጀል ምርመራ መጀመሩን ተገለጸ።

ፌደራል ፖሊስ ሰሞኑን ከአዲስ አበባ መቀሌ ለጉዞ በተዘጋጀ አውሮፕላን ውስጥ የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግርና ወከባ በፈጠሩ 6 ተጠርጣሪዎች ላይ የሽብር ወንጀል ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል።

በዚህም መሰረት ተጠርጣሪዎቹ ተብለው ከተቀመጡት መካከል
👉 ዮሀንስ ዳንኤል በርሄ፣
👉አማኑኤል መውጫ አብርሃ፣
👉ናትናኤል ወንድወሰን ሹሜ፣
👉ኤልያስ ድሪባ በዳኔ፣
👉ይዲድያ ነጻነት አበበ እና
👉 እሌኒ ክንፈ ተክለአብ
ናቸው ተብሏል።

የፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ የምርመራ መዝገብ እንደሚያሳየው፥ እነዚህ ተጠርጣሪዎች ተፈጥሮ በፈጠረው የአየር መዛባት ምክንያት አውሮፕላኑ መብረር አይችልም እየተባለ፣ አስገድዶ ለማስኬድ የፈጠሩት አምባጓሮ በወንጀል ሕጉ ተጠያቂ ያደርጋቸዋል ብሏል።

የፖሊስ የምርመራ ቡድን ተጠርጣሪዎች ላይ በወንጀል ተጠያቂ ለማድረግ ከተጀመረው ምርመራ ባሻገር፣ ከጸረሰላም ሃይሎች ተልእኮ ተቀብለው የተንቀሳቀሱ ናቸው በሚል በሽብር ወንጀልም መጠርጠራቸውን ነው የሚያመላክተው።

በወቅቱ የአየር መንገዱ ከደህንነት ኃይሎች ጋር በመሆን በትዕግስት ቢማጸናቸውም፣ ድብቅ አጀንዳቸውን እያራመዱ በመሆናቸው አሻፈረን ማለታቸውንም በምርመራ መዝገቡ አካቷል።

ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ ተግባር መጠቀም ሲገባቸው፣ የሀገር ኩራት እና የራሳቸው ንብረት የሆነውን አየር መንገድ ማንቋሸሻቸው አሳዛኝ ተግባር ስለመሆኑም የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ መግለጹ  ተመላክቷል።

በመሆኑም እነዚህ በቁጥጥር ስር የሚገኙ 6 ተጠርጣሪዎችን ቢሮው በተላለፉት የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ የበረራ አሰራር ጥሰት ብሎም በሽብር ወንጀሎች የምርመራ መዝገብ ነገ ነሀሴ 20 ቀን 2016 ፍርድ ቤት እንደሚያቀርባቸው ለማወቅ ተችሏል ሲል የዘገበው ኢቢሲ ነው።
ሕግን አለማወቅ ይቅርታን ሊያስገኝ አይችልም። የፍ/ሕ/ቁ  2035(2)
ለመሰረታዊ የሕግ እውቀት በቴሌግራም
ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
አማራጭ የሕግ እውቀት አለ
Alternative legal enlightenment/ALE
Legal Information🔵
📞+251920666595
👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties

👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

👉YouTube 👈
https://www.youtube.com/@Ale_Hig

👉Website 👈
http://alehig.wordpress.com
August 25, 2024