አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
በዋና ጥያቄ ላይ ያልተነሳ
ምስክር መስቀለኛ ጥያቄ በሚጠየቅበት ወቅት በጣም የተለመደው መቃወሚያ በዋና ጥያቄ አልተነሳም የሚል ሲሆን ፍርድ ቤቶች በደፈናው ይቀበሉታል፡፡ ይሁን እንጂ ሁለቱም የስነ ስርዓት ህጎች ለጥያቄ መለኪያ የሚያስቀምጡት አግባብነት /relevance/ እንጂ ጥያቄው በዋና ጥያቄ መነሳት አለመነሳቱ አይደለም፡፡

#ምሳሌ
ምስክሩ በዋና ጥያቄ ወቅት "መስከረም 15 ቀን 2012 ዓ.ም. ጠዋት 3 ሰዓት አካባቢ መኖሪያ ቤቴ አካባቢ ተከሳሽ ተበዳዩን ሲመታው አይቻለው" በማለት ምስክርነት ሰጠ። በቀጣይ የቀረበለት መስቀለኛ ጥያቄ እና የሰጠው መልስ ይህንን ይመስላል።

ጥ---ልጅ አለህ?
መ--አዎ
ጥ--ስንት ልጅ?
መ--አንድ
ጥ--ወንድ ወይስ ሴት?
መ--ሴት
ጥ--መቼ ነው የተወለደችው?
መ--መስከረም 15 ቀን 2012 ዓ.ም.
ጥ--ጥሩ፤ መስከረም 15 ቀን 2012 ዓ.ም. ብለሀል። ጠዋት ነው ወይስ ሌሊት?
መ--ጠዋት። 1 ሰዓት አካባቢ ወደ ሆስፒታል ወስድኳት። 5 ሰዓት አካባቢ ተገላገለች።
ጥ--ባለቤትህን ሆስፒታል ከወስድክበት ጊዜ ጀምሮ እስክትወልድ ድረስ አብረሃት ነበርክ?
መ--አዎ። ከዛ በኋላም እስከ 7 ሰዓት ድረስ አብሬያት ነበርኩኝ።

ቀጣዩ ጥያቄ ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት አይከብድም። ተከሳሽ ተበዳይን ሲመታው አየሁኝ ያለበት ቀንና ሰዓት ሆስፒታል ነበርኩኝ ካለበት ቀንና ሰዓት ጋር ተመሳሳይ ነው። ሆኖም እዚህ ላይ ለመድረስ እስካሁን የተጠየቁት ጥያቄዎች በዋና ጥያቄ ያልተነሱ ናቸው።
ስለሆነም በመስቀለኛ ጥያቄ ወቅት የጠያቂው ግዴታ የጥያቄውን አግባብነት ማስረዳት ብቻ ነው። ይህንን ሲያደርግ ከተቃራኒው ተከራካሪ ጋር ወደ ዳኛው ተጠግቶ አግባብነቱን ማስመዝገብ አለበት።
ምስክሩ እየሰማ የሚናገር ከሆነ ግን ምስክሩ እንዲነቃና ቀድሞ ለመልሱ እንዲዘጋጅበት /ምናልባትም ሐሰተኛ ምስክርነት እንዲሰጥ/ ያደርገዋል።
በአብርሐም ዩሐንስ
ኢትዮ-ሕግ🇪🇹👇
#ethiolawtips
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #ህግ
https://t.me/lawsocieties
ውል መሰረዝ፤
ማፍረስ እና በስምምነት ማቋረጥ
ውል መሰረዝ

ከተዋዋይ ወገኖች መካከል አንደኛው እንደ ውሉ ባለመፈጸሙና የውሉን ግዴታ በመጣሱ በተዋዋዩ ወይም በፍርድ ቤት ውሉን ወይም በውሉ የተቋቋሙትን ግዴታዎች ቀሪ ማድረግ
ውል የሚሰረዘው ከመሠረቱ ግድፈት ስላለው አይደለም፡፡ ይልቁንም የውል መሠረዝ ምክንያት ከተዋዋይ ወገኖች የውል ግዴታን ከመፈፀምና ካለመፈፀም ጋር ተያይዞ የሚከሠት ነው፡፡ የውል መሠረዝ ሥርዓትም የራሱ የሆነ አካሄድ አለው፡፡ ይኸውም ውሉን የመሠረዝ ፍላጐት ያለውን ወገን የውሉ ግዴታ ባለመፈፀሙ የተነሳ ከህግ ወይም ከውሉ ከራሱ ባገኘው መብት ተጠቅሞ ውሉን ሊሰርዝ ይችላል፡፡ ይህ መብት ተግባራዊ የሚሆንበት አጋጣሚም ግዴታው ባለመፈፀሙ የተነሳ የደረሰውን ጉዳት ከማረጋገጥ ጋር ተያይዞ የሚታይ እንጂ ጥያቄ አቅራቢው ሁል ጊዜ ተቀባይነት የሚያገኝበት አይደለም፡፡ በመሆኑም የውል ይሰረዝልኝና ተያያዥነት ያላቸው ጥያቄዎች በህጉ አግባብ የሚስተናገዱ ስለመሆኑ የፍ/ህ/ቁ. 1784 እና ተከታዮቹ ድንጋጌዎች ያስገነዝባሉ፡፡
ሰ/መ/ቁ. 32299 ቅጽ 8
ውል በተናጠል መሰረዝ
አንደኛው ተዋዋይ ወገን የፍታብሓር ሕግ ቁጥር 1787 ድንጋጌን መሠረት በማድረግ ውልን በተናጠል ለመሠረዝ የሚችለው ከሚከተለት ሶስት ሁኔታዎች አንደኛው የተሟላ መሆኑን ለማስረዳት ሲችል ነው፡፡
• የመጀመሪያው ባለዕዳው በውሉ ላይ በተመለከተው መሠረት የውሉን ግዴታ የሚፈፅምበት ቁርጠኛ ጊዜ በውሉ ላይ በግልፅ ተመልክቶ እንደሆነና በውሉ ላይ የተገለፀው ቁርጥ የሆነ የውል መፈፀሚያ ጊዜ ያለፈ እንደሆነ ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ አንደኛው ተዋዋይ ወገን በተናጠል ውሉን ለመሰረዝ የሚችል መሆኑን የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 እና የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1775(ለ) ድንጋጌዎች በማገናዘብ ለመረዳት ይቻላል፡፡
• ሁለተኛው ምክንያት ባለዕዳው ውሉን ያልፈፀመበትን ምክንያትና ሌሎች የአካባቢ ሁኔታዎችን በማገናዘብ ዳኞች ባለዕዳው ውሉን የሚፈፅምበት የችሮታ ጊዜ ከሰጡት በኋላ ባለእዳው በዳኛ ውሣኔ በተሰጠው የችሮታ ጊዜ ውስጥ ግዴታውን ሳይፈጽም የቀረ እንደሆነ መሆኑን ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 እና ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1770 ድንጋጌዎች ለመረዳት ይቻላል፡፡
ሶስተኛው ባለገንዘቡ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1774 በተደነገገው መሠረት ሌላኛው ተዋዋይ (ባለዕዳው) በውል የገባውን ግዴታ የሚፈፅምበትን ጊዜ በመግለፅ ማስጠንቀቂያ የሰጠ ሲሆንና በማስጠንቀቂያው በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ሳይፈፅም ሲቀር መሆኑን ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1774 እና ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 ድንጋጌ ለመረዳት ይቻላል፡፡ አንደኛው ተዋዋይ ወገን ሌላኛው ተዋዋይ ወገን በውሉ መሠረት እንዲፈፅም ለመጠየቅና ማስጠንቀቂያ ለመስጠት የሚችለው በመጀመሪያ እሱ የበኩሉን ግዴታ የፈፀመ ወይም ለመፈፀም የተዘጋጀ ሲሆን እንደሆነ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1857 በግልፅ ይደነግጋል፡፡
ስለሆነም ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 ድንጋጌ መሠረታዊ ዓላማና ግብ እንደዚሁም የድንጋጌውን የተፈፃሚነት ወሰን ለመረዳት የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 ድንጋጌ ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1771 ንዑስ አንቀጽ 1 እና ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1757 ድንጋጌዎች ጋር በማጣመር መመርመር ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ አንፃር ስንመዝነው አንደኛው ተዋዋይ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1771 ንዑስ አንቀጽ 1 ሌላኛው ተዋዋይ ውሉን እንዲፈፅምለት ለመጠየቅ፤ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1774 ድንጋጌዎች መሠረት የውል መፈፀሚያ ጊዜ ግልፅ ማስጠንቀቂያ በመስጠትና በፍትሐብሔር ቁጥር 1787 በተደነገገው መሠረት ውሉን በተናጠል ለመሠረዝ በመጀመሪያ በእሱ በኩል በውል የተጣለበትን ግዴታ የፈፀመ ወይም ለመፈፀም ዝግጁ መሆኑ በማስረጃ ለማረጋገጥ የቻለ መሆን እንዳለበት የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1771፣ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1774፣ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1757 እና የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 ድንጋጌዎችን ይዘትና መሠረታዊ ግብ በማገናዘብ ለመረዳት ይቻላል፡፡
ሕግ አውጭው በውል ለገባው ግዴታ ተገዥ በመሆን በእሱ በኩል ያለውን ግዴታ ያልፈፀመ ወይም ለመፈፀም ዝግጁ መሆኑን በበቂ ሁኔታ ለማረጋገጥ ያልቻለ አንድ ተዋዋይ ወገን ሌላኛውን ተዋዋይ ወገን ቀድሞ ማስጠንቀቂያ በመስጠት ውሉን በተናጠል እንዲሰርዝ በማሰብ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1787 ድንጋጌን አውጇል ተብሎ አይገመትም፡፡ አንድ ተዋዋይ የውሉን መፈፀሚያ የጊዜ ገደብ በመግለጽ ለሌላኛው ወገን ማስጠንቀቂያ በመስጠት ውል በተናጠል ለመሰረዝ የሚችለው በመጀመሪያ እሱ በውሉ የገባውን ግዴታ የፈፀመ ወይም ለመፈፀም ዝግጁ መሆኑ ሲረጋገጥ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 57280 ቅጽ 13፣ ፍ/ህ/ቁ. 1770፣ 1771፣ 1774፣ 1757፣ 1787
ውል ማፍረስ
በህጉ የተቀመጡት የውል አመሰራረት መስፈርቶችን ያለሟላና ግድፈት ያለበት በመሆኑ የተነሳ የውሉ ወይም በውሉ የተቋቋሙትን ግዴታዎች መቅረት
ውል ማፍረስና ውል መሠረዝ በውል የተቋቋሙት ግዴታዎች ከሚቀሩባቸው መንገዶች ውስጥ የሚካተቱ ቢሆንም ምክንያታቸውና ውጤታቸው የተለያዩ ነው፡፡ የውል ማፍረስ ከውል አመሠራረት ጋር ተያይዞ የሚነሳ ሲሆን ሲሆነ
ውሉ ከአመሰራረቱ በህጉ የተመለከቱትን ሁኔታዎች ባለማሟላቱ ግድፈት ያለበት መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ በሌላ በኩል የውል መሰረዝ ጉዳይ ከውል አመሰራረት ችግር የሚነሳ ሳይሆን ከተዋዋይ ወገኖች የውል ግዴታውን ካለመወጣት የሚመነጭ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 32299 ቅጽ 8
ውል በስምምነት ማቋረጥ /ቀሪ ማድረግ/
ተዋዋይ ወገኖች በውል አቋቁመውት የነበረውን ግዴታ በፍታሐብሔር ሕግ ቁጥር 1819 ንዑስ አንቀጽ 1 መሠረት በስምምነት ቀሪ ሲያደርጉ የተለየ ፎርም መከተል እንዳለባቸው የሚደነግግ አስገዳጅ ድንጋጌ የለም፡፡ የውለታ በተዋዋዮች ስምምነት መቋረጥ (terminate) መደረግ ከውል መፍረስ ወይም ከውል መሠረዝ የተለየ ባህሪና ውጤት ያለው መሆኑን አግባብነት ያላቸውን የፍታብሔር ድንጋጌዎች ይዘት በማገናዘብ ለመረዳት ይቻላል፡፡ እንደዚሁም ውል በስምምነት ቀሪ ማድረግ (termination of contract) ውልን ከማሻሻል (ውል ከመለወጥ) (variation of contract) እና ውል ከመተካት (Novation of contract) የተለየ ባህሪ፣ ይዘትና ውጤት ያለው መሆኑን፣ የፍታሐብሔር ሕግ ቁጥር 1819 እና ተከታይ ድንጋጌዎችን፣ የፍታብሔር ሕግ ቁጥር 1722 እና የፍታብሔር ሕግ ቁጥር 1826 እና ተከታይ ድንጋጌዎችን ይዘት በማገናዘብ ለመረዳት ይቻላል፡፡
የውሉ በተዋዋዮቹ ፈቃድና ስምምነት መቋረጥ (ቀሪ) መሆን የተዋዋይ ወገኖች የወደፊት የውል የመፈፀም ግዴታ የሚያስቀር መሆኑን የፍታብሔር ሕግ ቁጥር 1819 ንዑስ አንቀጽ 2 ይደነግጋል፡፡ እንደዚሁም የውሉ መቋረጥ /ቀሪ/ መሆን ያለፈውን ሁኔታ የማይነካ መሆኑን የፍታብሔር ሕግ ቁጥር 1819 ንዑስ አንቀጽ 3 ይደነግጋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የውል ቀሪ መሆን (termination of contract) ተዋዋዮቹ በውል አቋቋመውት የነበረውን መብትና ግዴታ ቀሪ የማድረግ ውጤት የሚኖረው መሆኑን ከፍታብሔር ሕግ ቁጥር 1807 /ለ/ ድንጋጌ ይዘት መንፈስና ዓላማ በማገናዘብ ለመረዳት ይቻላል፡፡
ሰ/መ/ቁ. 63063 ቅጽ 14፣ ፍ/ህ/ቁ. 1682-84፣ 1722
በአብላጫ ድምፅ የተሰጠ
#ethiolawtips
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
የ737 ማክስ አደጋ ሰለባ ዘመዶች ፍርድ ቤት ቃላቸውን ሊሰጡ ነው
አውሮፕላን አምራቹ ቦይንግ ኩባንያ እንዲከሰስ የዩናይትድ ስቴትስ ፌደራል ፍርድ ቤት ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት፣ በሁለቱ የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖች ላይ በደረሰው አደጋ ህይወታቸውን ያጡ ዘመዶች በመጪው ፍርድ ቤት ቀርበው ቃላቸውን እንደሚሰጡ ከፍርድ ቤታ ያገኘውን መረጃ ጠቅሶ ሮይተርስ ዘግቧል።
ኢትዮጵያ የሚበላ ምግብ ዋጋ ውድ ከሆነባቸው የአፍሪካ ሃገራት ከቀዳሚዎቹ ተርታ ነች ተባለ

ከአለም 8ተኛ ደረጃ ላይ መሆኗን ሰምተናል፡፡

ከዚምባቡዌ ቀጥላ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት ያለባት ሃገር እንደሆነች በጥናት ተረጋግጧል፡፡

የኢትዮጵያ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት በዋጋ ግሸበት ምክንያቶችና መፍትሄ ላይ ያደረገውን ጥናት ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል ይፋ አድርጓል፡፡

አጠቃላይ የዋጋ ግሽበቱ 49.1 በመቶ ነው የተባለ ሲሆን የምግብ የዋጋ ንረት ከፍተኛውን ድርሻ ይዟል፡፡

ይህም ከክልል ክልል የተለያየ መሆኑ በጥናቱ ተጠቅሷል፡፡

በአማራና ደቡብ ክልል ያለው የዋጋ ግሽበት ከሃገራዊ ምጣኔው ከፍ ያለ ነው ተብሏል፡፡

በተለይ ለምግብ የዋጋ ንረቱ የምርት መጠን ከፍላጎት ጋር አለመመጣጠን አንዱ ምክንያት ነው ብለዋል ጥናቱን ያቀረቡት ዶ/ር ታደሰ ኩማ፡፡

ገበሬው ከሚያመርተው ምርት ከራሱ ፍጆታ ተርፎት ለገበያ የሚያቀርበው በአማካይ ከ20 በመቶ አይበልጥም ተብሏል፡፡

ከሚመረተው በቆሎ 85 በመቶው ገበሬው ለእለት ፍጆታው ያውለዋል ተብሏል፡፡

በሌላ በኩል ከሚመረተው ጤፍ ለገበያ ቀርቦ ከተማው የሚሸምተው 30 በመቶውን ብቻ ነው ተብሏል፡፡

ይህም ምርታማነት ጨምሯል ቢባልም አብዛኛው አነስተኛ አምራች ገበሬ በመሆኑ የሚያመርተው እህል እምብዛም ከራሱ የሚያልፍ በመሆኑ ዋጋ እንዲንር ምክንያት መሆኑን ሰምተናል፡፡

ማምረት እንደተቻለ ከውጭ ማስመጣት ደግሞ ሌላው ምክንያት ሆኖ ቀርቧል፡፡

ኢትዮጵያ ከ97 በመቶ በላይ የዘይት ፍላጎቷን ከውጭ ገዝታ እንደምታመጣም በጥናቱ ተጠቅሷል፡፡

ከፍላጎትና አቅርቦት አለመመጣጠን ባሻገር እሴት የማይጨምሩ ደላሎች በገበያ ሰንሰለቱ በብዛት መሳተፍ ፣ መንግስትም ተገቢውን ቁጥጥርና የእርምት እርምጃ አለመውሰድ የዋጋ ንረቱን አባብሶታል ይላል ጥናቱ፡፡

በዚህም ምክንያት ምርት አምራቹ ከሚሸጥበት 58 በመቶ ዋጋው ከፍ ብሎ ሸማቹ ጋር እንዲደርስ አድርጓል ተብሏል፡፡

ይህን ሁኔታ ለመቀየር መንግስት የፖሊሲ ለውጥ እንዲያደርግ ጥናቱ መክሯል፡፡

ገበያውን ማዘመን፣ የገበያውን ምርታማነት ለመጨመር ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል ተብሏል፡፡

በተጨማሪም የተቋማት አደረጃጀትና አሰራርን በመፈተሽ ተገቢውን እና መልክ ያጣውን የገበያ ሥርዓት ማስተካልም የመንግስት የቤት ስራ ነው ተብሏል፡፡

ትዕግስት ዘሪሁን
#Ethiopia #ShegerWerewoch
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law
https://t.me/lawsocieties
ሰብለ ንጉሴ የተባለች የፍቅር አጋሩን ሳኒታይዘር በማርከፍከፍ በእሳት ተቃጥላ እንድትሞት አድርጓል የተባለው ዳግማዊ አራጋው የሞት ፍርድ ተፈረደበት!!

በፍትሕ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ በሴቶችና ሕጻናት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ÷ ዳግማዊ አራጋው በፈጸመው ከባድ የግድያ ወንጀል በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሰው ግድያና ከባድ ውንብድና ወንጀል ችሎት ክስ መስርቶ የክርክር ሂደቱን ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡

የዐቃቤ ሕግ የክስ መዝገብ እንደሚያመላክተው ተከሳሽ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 539/1/ሀ ላይ የተደነገገውን ድንጋጌ ተላልፏል ፡፡

ታኅሣሥ 30 ቀን 2014 ዓ.ም ከሌሊቱ በግምት ከ9፡00 እስከ 10፡00 ሰዓት ባለው ጊዜ በአዲስ አበባ ከተማ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 ሳሬም ሆቴል ጀርባ ባለው መኖሪያ ቤት የወንጀል ድርጊቱን መፈጸሙ ተመላክቷል፡፡ ተከሳሽ በዕለቱ በፍቅር ግንኙነት አብራው የምትኖረውን ሟች ሰብለ ንጉሴን በተፈጠረ አለመግባባት ድብደባ እና በስለት ጉዳት ማድረሱ በክሱ ተብራርቷል፡፡

በተጨማሪም ሳኒታይዘር ሰውነቷ ላይ በማርከፍከፍ በእሳት እንድትቃጠል ማድረጉን የወንጀል አፈጻጸም ድርጊቱ ያስረዳል፡፡

ተከሳሽ ክሱ ተነቦለት የወንጀል ድርጊቱን አልፈጸምኩም በማለት ክዶ የተከራከረ ቢሆንም ተከላከል በተባለበት የወንጀል ድንጋጌ ስር ክሱን ማስተባበል ባለመቻሉ ጥፋተኛ ነህ በማለት የፍርድ ውሳኔ ተላልፏል፡፡ዛሬ የተሰየመው ችሎትም በከሳሽ ዐቃቤ ሕግ የቀረቡ ማስረጃዎችንና በተከሳሽ የቀረቡ የመከላከያ ማስረጃዎችን መዝኖ ተከሳሹ ጥፋተኛ መሆኑን የዐቃቤ ሕግ ማስረጃ በበቂ ማስረዳቱ ተገልጿል፡፡

በዚህም ተከሳሽ በሞት እንዲቀጣ ሲል የቅጣት ውሳኔ እንደተላለፈበት ከፍትሕ ሚ/ር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
#አለ_ህግ #ale_hig
#ሰበር_ዜና #Breaking_News

ከ2014 የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የማለፊያ ውጤት ያመጡት ሦስት በመቶ ብቻ ናቸው ተባለ 😳

ኩረጃን ለማስቀረትና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚል፣ በልዩ ሁኔታ ከተሰጠው የ2014 የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ የመልቀቂያ ፈተና ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት (የማለፊያ ነጥብ) ያገኙ ተማሪዎች 28 ሺሕ ብቻ መሆናቸውን አዲስ ማለዳ ከአስተማማኝ ምንጮቿ መስማቷን ዘግባለች።
#atc_newsbot
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law
https://t.me/lawsocieties
መሰረታዊ የሕግ ስህተት በአዲሱ የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
አንድ ጉዳይ የመጨረሻ ፍርድ ከተሰጠው በኋላ መሰረታዊ የህግ ስህተት ተፈፅሞበታል የሚባል ከሆነ መሰረታዊ የህግ ስህተቱ ሳይታረም እንዳይቀር በሰበር ለመታየት ዕድል ይሰጠዋል፡፡ ቀደም ሲል መሰረታዊ የህግ ስህተት ምንነት የህግ ትርጉም ያልተሰጠው የነበረ በመሆኑ ጉዳዮች መሰረታዊ የህግ ስህተት አለባቸው በሚል በብዛት ሲቀርቡ ይስተዋል ነበር፡፡ ይህን ለማስቀረት አዲሱ የፍርድ ቤቶች አዋጅ መሰረታዊ የህግ ስህተትን ምንነት ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ የመሠረታዊ የሕግ ስህተት ምንነትን እና ተያያዥ ጉዳዮችን እንመለከታለን፡፡

የመሠረታዊ የሕግ ስህተት ምንነት

በአዲሱ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀፅ 2(4) መሠረት “መሠረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት” ማለት

. የሕገ-መንግሥቱን ድንጋጌዎች የሚቃረን

ለ. ሕግን አላግባብ የሚተረጉም ወይም ለጉዳዩ አግባብነት የሌለውን ሕግ የሚጠቅስ

ሐ. ለክርክሩ አግባብነት ያለው ጭብጥ ያልተያዘበት ወይም ከክርክሩ ጋር የማይዛመድ አግባብነት የሌለው ጭብጥ የተያዘበት

መ. በዳኝነት ታይቶ ሊወሰን የሚገባውን ጉዳይ ውድቅ የተደረገበት

ሠ. በፍርድ አፈፃፀም ሂደት ከዋናው ፍርድ ጋር የማይገናኝ ትእዛዝ የተሰጠበት

ረ. ጉዳዩን አይቶ የመወሰን የዳኝነት ሥልጣን ሳይኖር ውሳኔ የተሰጠበት

ሰ. የአስተዳደር አካል ወይም ተቋም ከሕግ ውጭ ውሳኔ የሰጠበት

ሸ. የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎትን አስገዳጅ ውሳኔ በመቃረን የተወሰነ
እና ፍትህን የሚያዛባ ጉልህ የሕግ ስህተት ያለበት የመጨረሻ ውሳኔ፣ ፍርድ፣ ብይን፣ ትዕዛዝ ሲሆን መሰል ስህተት ያለባቸው ጉዳዮች በዚህ አዋጅ አንቀፅ 10 መሠረት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሚታረሙ ይሆናል፡፡ የመጨረሻ ውሳኔ ማለት በፍርድ ቤት፣ በህግ የመዳኘት ስልጣን በተሰጠው አካል፣ በተቋማት ወይም በአማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች የተሰጠ እና ለጉዳዩ እልባት የሚሰጥ ፍርድ፣ ብይን፣ ትዕዛዝ ውሳኔ ሲሆን የይግባኝ ሂደቶችን የጨረሰ ፍርድ፣ ብይን፣ ትዕዛዝ ወይም ውሳኔን እንደሚጨምር በአዋጁ አንቀፅ 2(5) ትርጓሜ ተሰጥቶታል፡፡

የጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ስልጣን

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ስልጣን የመነጨው ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 80(3)(ሀ) ሲሆን መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበትን ማናቸውንም የመጨረሻ ውሳኔ ለማረም በሰበር ችሎት የማየት ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡ በዚህም በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/13 አንቀፅ 10 መሰረት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለባቸውን የፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት በይግባኝ አይቶ የመጨረሻ ውሳኔ የሰጠባቸውን ጉዳዮች የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት የመጨረሻ ውሳኔ የሰጠባቸውን ጉዳዮች የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወይም የክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በህገ መንግስቱ በተሰጣቸው የውክልና ስልጣን ፌደራል ጉዳይን አይተው መጨረሻ ውሳኔ የሰጡበት ጉዳይ
የአዲስ አበባ ወይም የድሬደዋ ከተማ ፍርድ ቤት የመጨረሻ ውሳኔ የተሰጠባቸው የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የህገ መንግስቱ ድንጋጌዎች እና የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎቶች አስገዳጅ ውሳኔ ጋር በተያያዘ የመጨረሻ ውሳኔ የተሰጠባቸው ጉዳዮች የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ህግን አለአግባብ ከመተርጎም እና ለጉዳዩ አግባብነት የሌለውን ህግ ከመጥቀስ ጋር በተያያዘ የመጨረሻ ውሳኔ የተሰጠባቸው እና ጉዳዮቹ ለህዝብ ጥቅም ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው ውሳኔዎች በህግ የመዳኘት ስልጣን ተሰጠው አካል ወይም በሌሎች አካላት የተሰጠ የመጨረሻ ውሳኔ አግባብነት ያላቸው የህግ ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆነው በፌደራል ፍርድ ቤት ሊታይ ይችል በነበረ ጉዳይ ላይ በአማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች መሰረት የተሰጡ የመጨረሻ ውሳኔዎች እንዲሁም በሌሎች ህጎች የተጠቀሱ ጉዳዮች በሰበር አይቶ የማረም ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡

አንድ ጉዳይ በሰበር ሲታይ ከአምስት ያላነሱ ዳኞች ሊሰየሙ እንደሚገባ በአዋጁ አንቀፅ 25(2) ተደንግጓል፡፡ ከአምስት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት የሚሰጠው የሕግ ትርጉም በየትኛውም ደረጃ ላይ በሚገኝ የፌዴራል ወይም የክልል ፍርድ ቤት ላይ አስገዳጅነት እንደሚኖረው ከአንቀፅ 10(2) መረዳት ይቻላል፡፡

ይህን አምስት ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት የተሰጠው አስገዳጅ ውሳኔ ሰባት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት በድጋሚ ሊታይ ይችላል፡፡ ይህ የሚሆነው በባለጉዳዮች አመልካችነት ወይም በችሎቱ በራሱ አነሳሽነት ቀድሞ የሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም በተለያዩ ምክንያቶች ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው በሰባት ዳኞች ችሎት እንዲታ በቂ እና አሳማኝ ምክንያቶችን ተንትኖ በመግለፅ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሲያቀርብ እንደሆነ ከአንቀፅ 26(1) መረዳት ይቻላል፡፡ በዚህ መልኩ ጥያቄ ሲቀርብ ፕሬዝዳንቱ ጉዳዩ ሰባት ዳኞች በሚሰየሙበት ችሎት እንዲታይ የሚያደርግ ሲሆን በችሎቱ የሚሰጠው ውሳኔ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በማንኛውም ደረጃ ፍርድ ቤት አስገጃጅ ይሆናል፡፡

በተጨማሪም ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት ቀድሞ የሰጠውን የህግ ትርጉም ከሰባት ባላነሱ ዳኞች በተመሳሳይ ጭብጥ በሌላ ጊዜ ሊሻሻል ይችላል፡፡

ማጠቃለያ

በአጠቃላይ የሰበር ሥርዓት መሰረታዊ ህግ ስህተት ያለበት የመጨረሻ ውሳኔ የተሰጠበት ጉዳይ ለመጨረሻ ጊዜ የሚታይበትና እና የሚታረምበት የዳኝነት ሂደት ነው፡፡ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት ምንነት ደግሞ በአዋጁ የተገለፀ በመሆኑ ለሰበር የሚቀርቡ ጉዳዮች ይህንን ተከትለው መቅረብ አለባቸው፡፡

በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law https://t.me/lawsocieties
ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ
ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ማለት
ሠራተኛው ካለፈው፣ አሁን ካለው ወይም ወደፊት ከሚመጣው የቅጥር ውል ጋር በተያያዘ የሚያገኘው ደመወዝ/ምንዳ፣ አበል፣ ጉርሻ፣ ኮሚሽን፣ የመልካም ሥራ አፈፃፀም ማበረታቻ ስጦታ ወይም ሌላ የአገልግሎት ዋጋ ክፍያ፣ ተቀጣሪው ከስራ ሲቀነስ ወይም ከስራ ሲለቅ ወይም ስራን እንዲለቅ ለማግባባት የሚከፈል ገንዘብ ወይም የስራ ውል በመቋረጡ ምክንያት በፈቃደኝነት፣ በስምምነት፣ በዳኝነት ውሳኔ መሠረት በጥሬ ገንዘብ (በዓይነት) የተቀበለው ማንኛውም የገንዘብ መጠን ከታክስ ነጻ ከተደረገው ውጪ እንደ ገቢ ተቆጥሮ ታክስ የሚሰላበት ይሆናል፡፡
* አንድ ተቀጣሪ ከመቀጠር የሚያገኘው ገቢ በኢትዮጵያ የመነጨ ነው የሚባለው፡-
1. ክፍያው የሚፈፀመው ስፍራ ግምት ውስጥ ሳይገባ ኢትዮጵያ ውሰጥ ከሚከናወነው የቅጥር አገልግሎት የተገኘ ገቢ ከሆነ ወይም
2. የቅጥር አገልግሎቱ የትም ቢከናወን በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት ስም ክፍያው ለተቀጣሪው ከተፈፀመ ነው፡፡
* ተቀጣሪው ከመቀጠር በሚያገኘው ገቢ የሚያወጣው ማንኛውም ወጪ በተቀናሽ ሊያዝለት አይችልም፡፡
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law https://t.me/lawsocieties
Federal_Supreme_Court_Cassation_Decisions_Table_of_content_Volume.pdf
6.6 MB
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሕግ ትርጉም የሰጠባቸው ውሣኔዎች ዝርዝር ማውጫ ሰንጠረዥ ከቅጽ 1 እስከ 25

በ፦ ዋስይሁን ኃይለማርያም እና የኋላሸት ታምሩ

አዘጋጆቹ በዚህ ጊዜ በመስፍን ታፈሰ እና ጓዶቹ (MTA) የሕግ ቢሮ በአሶሲየትነት በመስራት ላይ የሚገኙ ሲሆኑ ይህን ስራ አዘጋጆቹ በግላቸው የሰሩት እና የሚሰሩበትን ተቋም ያካተተ ወይም የሚወክል አይደለም። ይህ ማውጫ የሚያገለግለው ለትምህርት እና ለመረጃ ምንጭነት ብቻ ነው። በዚህ ማውጫ ዝግጅት ላይ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያዘጋጀው ከ ቅጽ 1 እስከ 16 ማውጫን በመጠቀም የቀሩትን ቅጾች አጠቃለን አዘጋጅተናል።

አዘጋጆቹ ይህን ማውጫ በሚያዘጋጁበት ጊዜ በውስጡ ያሉትን መረጃዎች እውነታነት ለማረጋገጥ አስፈላጊውን ጥረት አድርገዋል፡፡ ይህ ማውጫ ሲዘጋጅም ትክክለኛ መረጃ እንዲይዝ በማሰብ ነው፡፡ ሆኖም ግን በዚህ ማውጫ ላይ ሊኖሩ በሚችሉ ስህተቶች፣ ግድፈቶች፣ ጉድለቶች እንዲሁም አለመስማማቶች ሊከሰቱ ለሚችሉ ጉዳቶችም ሆነ ኪሳራ አዘጋጆቹ ምንም አይነት ኃላፊነት እንደማይወስዱ ያሳውቃሉ።

ይህ ማውጫ በዋነኛነት የመረጃ ምንጭ እንዲሆን እና ለሕግ ማህበረሰቡ ቀላል እና ፈጣን ማጣቀሻ እንዲሆን የተዘጋጀ ቢሆንም ቀጥታ የባለሞያ ምክር ወይም ድጋፍ አይተካም። ይህን አይነት አገልግሎት ከተፈለገ ከባለሞያ መጠየቅ አለበት፡፡

አዘጋጆቹን አቢሲኒያሎውን ከልብ ያመሰግናል!
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law https://t.me/lawsocieties
የዘንድሮ 12ኛ ክፍል የተማሪዎች አማካይ ውጤት በየትምህርት አይነቱ፤

አጠቃላይ መረጃ፡-  ፈተና የተፈተኑ ብዛት-----908,256 ናቸው፡፡

  አማራ………..30.37%
  ኦሮሚያ…..…27.96%
  ደቡብ………..28.17%
  ሀረሪ…………32.88%
  አዲስ አበባ----38.46%
  ደሬደዋ--------31.42%
  ሲዳማ---------28.34%

2. ከ50% እና በላይ ያስመዘገቡ ተማሪዎች ብዛት ከተፈተኑ መካከል

(እንደ ሀገር ያለፉ 29909 (3.3%) ናቸው

  አማራ………ከ246,675 መካከል 8,810 ((3.6%)
  ኦሮሚያ…..…327,737 መካከል 6,407 (2.0%)
  ደቡብ………..ከ127,345 መካል 2,533 (2.0%)
  ሀረሪ…………ከ1,849 መካከል 194 (10.5%)
  አዲስ አበባ----ከ47,980 መካከል 9,491 (19.8%)
  ደሬደዋ-------- ከ3,726 መካከል 250 (6.7%)
  ሲዳማ---------ከ53,478 መካከል 1247 (2.3%)

3. ተፈጥሮ ሳይንስ  ከ600 እና በላይ እንደ ሀገር 263 ተማሪዎች ያስመዘገቡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ

  አማራ………70 ተማሪዎች
  ኦሮሚያ…..…51 ተማሪዎች
  ደቡብ………..10 ተማሪዎች
  ሀረሪ…………1 ተማሪዎች
  አዲስ አበባ----117 ተማሪዎች
  ደሬደዋ-------- 2 ተማሪዎች
  ሲዳማ---------8 ተማሪዎች

4. ማህበራዊ ሳይንስ  ከ500 እና በላይ እንደሀገር 10 ተማሪዎች ያስመዘገቡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ

  አማራ………1ተማሪ
  አዲስ አበባ----8 ተማሪዎች
  ደሬደዋ-------- 1 ተማሪ

5. ሁሉንም ተማሪዎች 100% ያሳለፉ ት/ቤቶች 7 ትምህርት ቤቶች ሲሆኑ ከነዚህ ውስጥ

  ደሴ ልዩ አዳሪ ት/ቤት
  ባሕር ዳር ስቲም ት/ቤት
  ጎንደር ኮሙኒቲ ስኩል
  ወላይታ ሶዶ ሊቃ ት/ ቤት
  አዳማ ኦዳ አዳሪ ት/ ቤት
ናቸው።

6. ከፍተኛ ውጤት (የዓመቱ ሰቃይ)

👉ከአማራ ክልል ደሴ ልዩ አዳሪ ት/ቤት ተማሪ ሚኪያስ አዳነ 666 አስመዝግቧል።

https://t.me/lawsocieties
#housinginaddisababa
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law https://t.me/lawsocieties
Ministry of Revenues of Ethiopia/የገቢዎች ሚኒስቴር:
ሀብትን በማስተላለፍ የሚገኝ ገቢ
1. አንድ ሰው አንድን ሀብት ሲያስተላልፍ ከዚህ ሀብት የተገኘ ገቢ ሆኖ የሚወሰደው ሀብቱን ሲያስተላልፍ የተቀበለው ወይም የሚቀበለው ጠቅላላ የገንዘብ መጠን ሲሆን፣ ሀብቱ በተላለፈበት ጊዜ በዓይነት የተገኘውን ማንኛውንም ጥቅም ትክክለኛ የገበያ ዋጋ ይጨምራል፡፡
2. ለኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ደርጅት ወይም የኢትዮጵያ ማህበር የሚሰጥን እርዳታ ሳይጨምር ሀብት በስጦታ የተላለፈ እንደሆነ በተላለፈበት ጊዜ ያለው ትክክለኛ የገበያ ዋጋ ከሀብቱ የተገኘ ገቢ እንደሆነ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
3. አንድ ሰው ሀብቱን በማስተላለፍ ያገኘው ገቢ ሀብቱን ከማስተላለፍ ጋር በተያያዘ ከቀረበለት ምርጫ ያገኘውን ጥቅም ይጨምራል፡፡ ሆኖም ይህ ጥቅም እንደገቢ ተደርጐ የሚወሰደው ከቀረበለት ምርጫ ጋር በተያያዘ ባገኘው ጥቅም ላይ ግብር ያልከፈለ ሲሆን ብቻ ነው፡፡
4. አንድ ሀብት የጠፋ ወይም የወደመ እንደሆነ፣ የዚህ ሀብት ዋጋ ነው የሚባለው ባለሀብቱ ሀብቱ በመጥፋቱ ወይም በመውደሙ ምክንያት የተቀበለው ወይም የሚቀበለው የካሳ መጠን ሲሆን የሚከተሉትን ይጨምራል፡-
   ሀ) በመድን ፖሊሲ መሠረት፣ በካሳ ወይም በሌላ ስምምነት ምክንያት የተቀበለውን ወይም የሚቀበለውን የገንዘብ መጠን፤
   ለ) በድርድር ምክንያት የሚቀበለውን የገንዘብ መጠን፤ ወይም
   ሐ) የፍርድ ቤት ውሳኔን ተከትሎ የተቀበለውን ወይም የሚቀበለውን የገንዘብ መጠን፤
5. አንድ ሰው በአንድ ግብይት ሁለትና ከዚያ በላይ የሆኑ ሀብቶችን ያስተላለፈ እንደሆነና የእያንዳንዱ ሀብት ዋጋ ተለይቶ ያልታወቀ እንደሆነ፣ ሀብቶቹ በተላለፉበት ጊዜ ባለው ትክክለኛ የገበያ ዋጋ መሠረት በማስተላለፉ ምክንያት የተቀበለው የገንዘብ መጠን ለተላለፉት ሀብቶች እንደየድርሻቸው ይደለደላል፡፡
6. አንድ ግብር ከፋይ የተላለፈውን ሀብት ዋጋ የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ ያልቻለ እንደሆነ ሀብቱ በተላለፈበት ጊዜ የነበረው ትክክለኛ የገበያ ዋጋ የሀብቱ ዋጋ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
https://t.me/lawsocieties
#housinginaddisababa
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law https://t.me/lawsocieties
Ministry of Revenues of Ethiopia/የገቢዎች ሚኒስቴር:
ሀብትን በማስተላለፍ የሚገኝ ገቢ
https://t.me/lawsocieties
#housinginaddisababa
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law https://t.me/lawsocieties
እሁድ እሁድ ስናካሂድ የነበረውን ከምሽቱ 2:30 የእሁድ ችሎት ነፃ ውይይት ላልተወሰነ ጊዜ የተቋረጠ ሲሆን ውይይቱን ስንጀምር የምናሳውቅ ይሆናል‼️

#የእለቱ_ችሎት

#የችሎቱ_ጭብጥ

ፕሮግራም ለአልተወሰነ ጊዜ የተቋረጠ መሆኑን ስለማሳወቅ‼️

#ውሳኔ
ችሎቱ ቢያመልጥዎት በሌሉበት የሚሰማ ይሆናል።

ቀጠሮው እሁድ ማታ በስልክዎት በ @lawsocieties የቴሌግራም ቻናል በመዝገብ ስዓት ቁጥር 2:30 የመገኘት መብትዎ የተከበረ ሆኖ ተራዝሟል።

ወደ ቴሌግራም ቻናላችን ይመለሱ።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
#የሚነበብ#አለ_ህግ ስም አለበት
https://t.me/lawsocieties
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Lawyer Mike 🔊የህግ ባለሙያ)
የጋብቻ መፈፀም የሚያስከትለው ውጤት
#ጋብቻ አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታዎችን በማሟላት በሁለት ሰዎች (ባልና ሚስት) መካከል የሚፈጠም ህብረት እንደሆነ ይጠቀሳል፡፡ የሀገራችን ቤተሰብ ህግ ለጋብቻ ትርጉም ያልሰጠ ሲሆን ጋብቻ ለማቋቋም ሊሟሉ የሚገባቸውን ቅድመ ሁኔታዎችን እና ጋብቻ የሚፈፀመው በአንድ ወንድና በአንዲት ሴት መካከል እንደሆነ ያስቀምጣል፡፡

በህግ ፊት የፀና ጋብቻ ለመፈጸም የተለያዩ ቅድመ ሁኔታዎች መሟላት አለባቸው፡፡ በዚህ መሰረት የሁለቱ ሰዎች ፈቃድ መኖር፣ በህጉ የተቀመጠው ዝቅተኛ እድሜ መሟላት፣ የዝድና አለመኖር፣ በጋብቻ ላይ ጋብቻ አለመኖር መሟላት ያለባቸው ቅድመ ሁኔታዎች ናቸው፡፡

ጋብቻ በተለያዩ ሶስት መንገዶች ሊፈጸም ይችላል፡፡
እነዚህም በክብር መዝገብ ሹም ፊት የሚፈፀም፣ የሀይማኖት ጋብቻ እና የባህል ጋብቻ ናቸው፡፡ በእነዚህ መንገዶች የተፈፀመ ጋብቻ ተመሳሳይ ውጤት ያለው ሲሆን በእነዚህ መንገዶች አስፈላጊውን ሁኔታ በማሟላት የተፈጸመ ጋብቻ የሚያስከትለው ውጤቶች እንደሚከተለው ተብራርተዋል፡፡

1. ጋብቻ በተጋቢዎች ግላዊ ግንኙነት ላይ የሚያስከትለው ውጤት

i. አብሮ መኖር
ባልና ሚስት ጋብቻ ከፈፀሙ በኋላ አብረው እንዲኖሩ በህግ ግዴታ ተጥሎባቸዋል፡፡ የመኖሪያ ቦታቸውንም አብረው የሚወስኑ ይሆናል፡፡ ሆኖም ባልና ሚስቱ ለተወሰነ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ ተለያይተው ለመኖር መስማማት አይከለከሉም፡፡ ይህ ስምምነት መቀየሩ አግባብ ካልሆነ በስተቀርም ተጋቢዎች ወይም ከሁለት አንዳቸው አስበው ሊቀይሩትም ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ የባልና ሚስቱ የሥራ ቦታ ሊለያይ የሚችልበት አጋጣሚ ሲፈጠር ሁለቱም በያሉበት ሆነው ሥራቸውን ለመሥራት ሊስማሙ የሚችሉ ሲሆን አመቺ ሆኖ ካላገኙትም ሀሳባቸውን መቀየር ይችላሉ፡፡

ይህ ብቻ ሳይሆን ተጋቢዎች ጋብቻ ተሳስረው ሲኖሩ ለጤናቸው አደገኛ ካልሆነ በስተቀር ከጋብቻ የሚጠበቀውን መደበኛ የሩካቤ ሥጋ መፈፀምም ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይህን የሚቃረን ስምምነት ውጤት አይኖረውም፡፡ በተጨማሪም በማንኛውም ሁኔታ አንዳቸው ለሌላኛው ታማኝ የመሆን ግዴታ አለባቸው፡፡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ አንዳቸው ሳይታመኑ የአመንዝራነት ድርጊት ቢፈፅሙ በተበደለው ተጋቢ አቤቱታ አቅራቢነት በእስራት ወይም በመቀጮ ሊያስቀጣ የሚችል የወንጀል ተጠያቂነት የሚያስከትል ነው፡፡

ii. መከባበር፣ መተጋገዝና መደጋገፍ

ባልና ሚስት በትዳር በሚኖሩበት ጊዜ አንዳቸው ሌላኛውን የማገዝና የመደገፍ እንዲሁም ተከባብሮ የመኖር ሀላፊነት ተጥሎባቸዋል፡፡ ይህንን ሀላፊነት በስምምነት ፈፅሞ ሊያስቀሩት እንደማይችሉ በህግ ተደንግጓል፡፡

iii. ቤተሰብን በጋራ መምራት

ጋብቻ በሁለቱ ተጋቢዎች ተወስኖ የማይቀርና ልጆችን የሚፈጥርና የቤተሰብ መሰረት የሚሆን ተቋም ነው፡፡ በዚህም የልጆች አስተዳደግ፣ ትምህርት፣ ጤና ወዘተ የመሳሰሉ ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች በተጋቢዎች እንዲሟሉ ይጠበቃል፡፡ ከዚህ አንፃር ባልና ሚስት እኩል መብት እንዳላቸው በቤተሰብ ህግ ደንግጓል፡፡ በዚህም በማናቸውም ረገድ የቤተሰቡን ደህንነትና ጥቅም ለማስጠበቅ፣ ልጆቻቸው በመልካም ሥነ ምግባር እንዲታነፁ፣ ተገቢ ትምህርት እንዲቀርሙና ሀላፊነት የሚሰማቸው ዜጎች ሆነው እንዲያድጉ ለማድረግ ባልና ሚስቱ መተባበር ይጠበቅባቸዋል፡፡

2. ጋብቻ በንብረት ረገድ የሚያስከትለው ውጤት

ጋብቻ በተጋቢዎች ግላዊ ግንኙነት ላይ ውጤት እንዳለው ሁሉ በንብረት ረገድም የራሱ የሆነ ውጤት የሚያስከትል ነው፡፡ ንብረትን በተመለከተ ጋብቻ የግል እና የጋራ ንብረት ውጤት የሚስከትል ነው፡፡

i. የግል ንብረት ምንነትና አስተዳደር

የግል ንብረት የምንለው ሁለቱ ተጋቢዎች ከጋብቻው በፊት በየግል የነበሯቸው ንብረቶች ወይም ከጋብቻው በኋላ በውርስ ወይም በየግላቸው በስጦታ ያገኟቸው ንብረቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ንብረቶች በጋብቻውም ዘመን የግላቸው ሆነው ይቀጥላሉ፡፡ እነዚህን ንብረቶች ሸጦ የሚገዛው ንብረት የራሱ የሚሆን ሲሆን ይህ የሚሆነው ግን በፍርድ ቤት የግሌ ይባልልኝ ብሎ ሲጠይቅና ሲፀድቅለት ነው፡፡

የግል ንብረት አስተዳደርን በተመለከተ የግል ንብረቱ ባለቤት የሆነው ተጋቢ ሊያዝበት የሚችል ሲሆን ሌላኛው ተጋቢ እንዲያስተዳድረው በጋብቻ ውል ሊስማሙ የሚችሉ ከመሆኑም በላይ ውክልና በመስጠት ሌላኛው ተጋቢ እንዲያስተዳደር ሊያደርግ ይችላል፡፡

ii. የጋራ ንብረት ምንነትና አስተዳደር

የጋራ ንብረትን በተመለከተ የጋራ ንብረት የሚባለው ባልና ሚስት ከተጋቡ በኋላ በግብይት የሚያገኟቸው ንብረቶች፣ ባልና ሚስት በግል ጥረታቸው የሚገኝ ገቢ፣ ከግል እና ከጋራ ንብረታቸው የሚገኟቸው ገቢዎች ሁሉ ናቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በስጦታ ወይም በኑዛዜ በጋራ የተሰጧቸው ንብረቶች የጋራ ንብረቶች ናቸው፡፡ እዚህ ላይ መታወቅ ያለበት አንደኛው ተጋቢ የግል ሀብቱ መሆኑን ካላስረዳ በስተቀር በአንደኛው ተጋቢ ስም የተመዘገበ ሀብትም ቢሆን እንኳን የተጋቢዎች የጋራ ሀብት እንደሆነ የህግ ግምት የሚወሰድበት መሆኑ ነው፡፡

በንብረት አስተዳደር ረገድ የጋራ ንብረታቸውን አንደኛው ተጋቢ እንዲያስተዳድረው ካልተስማሙ፣ ችሎታ የለውም በሚል ካልተወሰነ፣ ንብረት የማስተዳደር መብቱ ካልተገፈፈ፣ ወይም በማናቸውም ምክንያት ንብረታቸውን ማስተዳደር የማይችል ሆኖ ካልተገኘ በስተቀር የጋራ ንብረታቸውን በጋራ ያስተዳድራሉ፡፡ ሆኖም በተጠቀሱት ምክንያቶች አንደኛው ተጋቢ ብቻውን ንብረቱን የሚያስተዳድር ከሆነ ለሌላኛው ተጋቢ መረጃ የመስጠት ሃላፊነት አለበት፡፡

በገቢ ረገድ ሁለቱም ተጋቢዎች ገቢያቸውን በየራሳቸው መቀበል የሚችሉ እንዲሁም በግል ወይም በጋራ የባንክ ሂሰብ ከፍተው ማስቀመጥ ይችላሉ፡፡ ይህ ማለት ግን አንደኛው ተጋቢ ሌላኛው ተጋቢ እንዲቀበልለት ስልጣን ለመስጠት የሚከለክለው ነገር የለም፡፡ በየግል የሚያገኙትንም ገቢ ሌላኛው ተገቢ ሲጠይቅ ማሳወቅ ግዴታ አለበት፡፡

ከንብረት በተጨማሪ በጋብቻ ውስጥ እዳ ሊኖር እንደሚችል የሚጠበቅ ነው፡፡ ልክ እንደንብረት ሁሉ እዳም የግል ወይም የጋራ ተብሎ የሚከፈል ነው፡፡ እዳው ለባልና ሚስት እና ለልጆቻቸው የዕለት ኑሮ አስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን ለማሟላት ወይም ባል ወይም ሚስት ቀለብ የመስጠት ግዴታቸውን ለመወጣት የተገቡ እዳዎች እንዲሁም ከባልና ሚስት በአንደኛው ወይም በዕዳ ጠያቂው አመልካችነት ለትዳር ጥቅም ስለመሆኑ ፍርድ ቤት የተቀበለው እዳ በጋራ የሚከፍሉት ነው፡፡ ከዚህ ውጪ የሚኖረው እዳ የግል ይሆናል ማለት ነው፡፡ አከፋፈሉ ሲታይ የጋራ እዳ ከባልና ሚስቱ የጋራ ሀብት የሚከፈል ሲሆን ዕዳውን ለመሸፈን በቂ በማይሆን ጊዜ ከባል ወይም ከሚስት የግል ሀብት የሚከፈል ይሆናል፡፡

በአንፃሩ የግል ዕዳ ከባለዕዳው ተጋቢ የግል ሀብት የሚከፈል ሲሆን ዕዳው ለመሸፈን በቂ በማይሆንበት ጊዜ ከጋራ ሀብት የሚከፈል ይሆናል፡፡ እዚህ ላይ ልብ ሊባል የሚገባው ጉዳይ ከጋራ ሀብት ሲባል በድርሻው ልክ እንጂ የሌላኛውን ተጋቢ ጥቅም በሚነካ መልኩ ሊሆን እንደማይችል ነው፡፡
የንቃተ ህግ፣ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት
#አለ_ህግ #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share #lawsocieties
..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
#Vacancy for Lawyers
የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማህበር ምስረታ  አንደኛ ዓመት መታሰቢያ በማህበሩ መ/ቤት ታስቦ ውሏል!!
***
በኢትዮጵያ የህግ ስርዓት ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያው የሆነውና ለአስርት ዓመታት በተከታታይ የህግ ሙያ ትውልዶች ትግል ሲደረግበት የቆየው በርካታ ባለሙያዎች በየወቅቶቻቸው አስተዋፅኦ ያደረጉበት የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር በአዋጅ ቁጥር 1249/13 ከአንድ አመት በፊት ጥር 15 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ኢንተርሌግዥሪ (ኢንተርኮቲነንታል) ሆቴል ከ ከአንድ ሺህ ስድስት መቶ (1600) በላይ ጠበቆች ፣ ሚኒስትሮች ፣ የፌደራልና የክልል የጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝደንቶች ፣ የክልል ጠቅላይ ዐቃቢያነ ህግ እና ሌሎች በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች በተገኙበት በታሪክ የመጀመሪያው የሆነውን ታሪካዊ ጠቅላላ ጉባኤውን አደረገ::

ማህበሩ በህግ ከተቋቋመበት የመጀመሪያ መስራች ጉባኤው ጀምሮ ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴዎች እያደረገ ሲሆን የተቋም መሰረት የመጣልና ተቋም የመፍጠር ስራው ቅድሚያ ተሰጥቶት እየተሰራበት ያለ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በሀገር የህግ ስርአት ላይ የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት በርካታ ጥረቶችን እያደረገ ይገኛል:: ተቋሙ እያሳያቸው ያሉ ጅምሮች ተጠናክረው በመቀጠል  ለሀገርና ለህዝብ እንዲተርፍ ለማስቻል ዘንድ የመላው አባላቱ ፣ የህግ ማህበረሰቡ እና የባለድርሻ አካላት ድጋፍ የሚያስፈልግ ነው::

በዛሬው እለትም የማህበሩ መሪዎች በተገኙበት በማህበሩ መ/ቤት የታሪካዉን ምስረታ አንደኛ አመት ያከበረ ሲሆን በእለቱም በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውይይቶች ተደርገዋል::

የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
ጥር 15 2015ዓ.ም
አዲስ አበባ
#አለ_ህግ  #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share
https://t.me/lawsocieties
ኢትዮጵያ በ2022ቱ የሀገራት የሙስና ደረጃ ስንተኛ ላይ ተቀመጠች?

ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል የ2022 የሀገራት የሙስና ተጋላጭነት ደረጃን ይፋ አድርጓል።

ኢትዮጵያም 38 ነጥብ በማምጣት ከ180 ሀገራት 94ኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን የትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ሪፖርት አመላክቷል።

ተቋሙ "በሙስና የተደናቀፉ መንግስታት ህዝባቸውን የመጠበቅ አቅም የላቸውም፤ የህዝቡ ቅሬታም ወደ ብጥብጥ የመቀየር እድሉ ከፍተኛ ነው" ብሏል።
ዝርዝሩን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ https://am.al-ain.com/article/corruption-perceptions-index-2022
#አለ_ህግ  #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share
https://t.me/lawsocieties
የሂሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ላይ የተደረጉ ማሻሻያያዎች
ሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 152/2011 ተሽሮ በመመሪያ ቁጥር 176/2014 ተተክቷል፡
መመሪያውን ማሻሻል ካስፈለገባቸው ምክንያቶች ውስጥ ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው፡-
1. የታክስ ሒሳብ መዝገብ ሲዘጋጅ ሊሟሉ የሚገባቸው ዝርዝር ሁኔታዎች በነባሩ መመሪያ በግልጽ ስላለተገለፁ፣
2. በታክስ ባለስልጣኑ ቅ/ጽ/ቤቶች ተመሳሳይ አተረጓጎም ወይም አፈጻጸም እንዲኖር እና አገልግሎት አሰጣጡን የተቀላጠፈ ለማድረግ፤
3. የነባሩ መመሪያ አቀራረጽ ከታክስ ህግ ያለፈ እይታ ያለው ይመስል ስለነበር ይሕን ብዥታ ለመቅረፍ፣
4. ግብይት ሳይኖር ወይም ሕገ-ወጥ ደረሰኞች ሲቀርቡ ተቀባይነት እንደሌላችው በግልጽ ማመላከት በማስፈለጉ ምክንያት መመሪያውን ማሻሻል አስፈልጓል፡፡

በዚህም መሰረት በአዲሱ መመሪያ ውስጥ እንዲካተቱ ከተደረጉት ውስጥ ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው፡-
1. የውጪ ምንዛሬ ትርፍ ወይም ኪሳራ መቼ መመዝገብ እንዳለበት፤
2. የብድር ውል ሰነድን የመመዝገብ ስልጣን ባለው አካል ቀሪ ሆኖ ነገር ግን ብድሩ በባንክ የተከፈለ ስለመሆኑ የሚያሳይ ሰነድ መቅረብ እንዳለበት፤
3. የቴምብር ቀረጥ በብድሩ ላይም ሆነ ሰራተኛ ሲቀጠር መከፈል እንዳለበት እና
4. ለወጪም ሆነ ለገቢ የሚቀርቡ ማስረጃዎች ህጋዊ ብቻ እንዲሆኑ ሲባል በመመሪያው እንዲካተት ተደርጓል፡፡
በአጠቃላይ የተሻሻለው የሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 176/2014 ታክስ ከፋዩ የተቀላጠፈ አገልግሎት አግኝቶ የንግድ ሥራ እንቅስቃሴውን እንዲያከናውን በሚያመች ሁኔታ የተዘጋጀ መመሪያ ነው፡፡
የገቢዎች ሚኒስቴር
#አለ_ህግ #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share #lawsocieties
https://t.me/lawsocieties