አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ACSO-User-Manual-AMH-1.pdf
1.2 MB
የበጎ አድራጎት ማህበራትን መመስረት ለምትፈልጉ የህግ ማእቀፉን የሚገልጽ መመሪያ

የዋና ዳይሬክተሩ መልእክት
ማስተባበያ

ምዕራፍ 1 : መግቢያ
አዲስ የህግ ማዕቀፍ አስፈላጊነት
በአዲሱ አዋጅ አዋጅ ቁጥር 1113/2010 የተደረጉ አንኳር ለውጦች

ምዕራፍ 2 : የተፈፃሚነት ወሠን

ምዕራፍ 3 : የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ኤጀንሲ
የኤጀንሲው አላማዎች
የኤጀንሲው ስልጣንና ሃላፊነት
የኤጀንሲው አደረጃጀት
ቦርዱ
ዳይሬክተሩና ምክትል ዋና ዳይሬክተር

ምዕራፍ 4 : ለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምስረታ እና ምዝገ ባ መርሆዎች
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የሚቋቋሙበት መርሆዎች
የምዝገባ ሂደት

ምዕራፍ 5 : የበጎ አድራጎት ድርጅትና ማህበራት አይነቶች
የውጭ እና ሀገር በቀል ድርጅቶች
የውጭ ድርጅቶች
የሀገር በቀል ድርጅቶች

ምዕራፍ 6 : በአዲሱ አዋጅ የተካተቱ የሰራ ጉዳዮች
የስራ ነፃነት
ሀብት፣ የማፈላለግ፣ የመቀበል እና የመጠቀም መብት ውስጣዊ የፋይናንስ ቁጥጥር ስርዓት
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አመራር
ሪፖርት እና ቁጥጥር የሪፖርት አይነቶች እና የሚቀርብበት ጊዜ ሪፖርት እርምጃዎች
መዋሃድ፣ መከፈል እና መለወጥ አስተዳደራዊ እርምጃዎች ማስጠንቀቂያ እገዳ መፍረስ እና ከመዝገብ መሠረዝ የመሰማት መብት የመፍረስ ውጤቶች ራስን የማስተዳደር ማዕቀፍ
ማውጫ
@lawsocieties
#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#የሥራማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሥሩ ለሚገኙ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ጀማሪ ባለሙያዎችን /Intern/ በኮንትራት ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡

በዚሁም መሠረት

- በህግ፣ በኮምፒውተር ሳይንስ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በኮምፒውተር ኢንጅነሪንግ፣ በሶሺዎሎጂ፣ ሶሻል ወርክ፣ በህዝብ አስተዳደር፣ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን፣ በሰው ኃብት አስተዳደር፣ በቢዝነስ ሊደርሺፕ፣ በማርኬቲንግ ማኔጅመንት፣ በአካውንቲንግና ፋይናንስ፣ በኢኮኖሚክስ፣ በግዢ እና ንብረት አስተዳደር፣ በጋዜጠኝነት እና ስነጽሁፍ፣ በግራፊክስ ዲዛይን፣ በፖለቲካል ሳይንስ እና አለምአቀፍ ግንኙነት እንዲሁም ተያያዥ የትምህርት ዘርፎች የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው/ያላት

- አማካይ የመመረቂያ ውጤታቸው 3.5 እና ከዛ በላይ የሆነ፤

- ጥሩ የሆነ የአማርኛ እና የእንግሊዘኛ ቋንቋን ክህሎት (መናገር፣ መጻፍ እና ማንበብ) ያለው/ያላት፤

- የማይክሮሶፍት ኦፊስ (MS Word, Excel, Outlook, and PowerPoint) እውቀት እና በአግባቡ የመጠቀም ችሎታ ያላት/ ያለው፤

- የተቋሙን ደንብና መመሪያ የሚያከብር/ የምታከብር፤

- የማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነ/ች፤

ከላይ የተጠቀሱትን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 7 ቀናት ውስጥ ከዚህ በታች በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ማመልከት የምትችሉ መሆኑን ቦርዱ ገልጿል።

ለመመዝገብ  https://forms.office.com/r/HvBrmNfKaX

* ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ

* ከአማርኛ በተጨማሪ ሌሎች የሀገር ውስጥ ቋንቋዎችን መናገር፣ መጻፍ እና ማንበብ የሚችሉ አመልካቾች ይበረታታሉ፡፡
#tikvahethmagazine
የቅድመ ግብር ክፍያ ስርዓት (1).pdf
2.9 MB
ስለ ቅድመ ግብር ክፍያ ስርዓት (WITHHOLDING) ለአዲስ ግብር ከፋዮች የተዘጋጀ ማብራሪያ

#ethiopia #Tax 🇪🇹
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Entrust🔷ETC)
#አለ_ህግ የእናንተን ድጋፍ የሚፈልግበት ጊዜ አሁን ነው።
የአለ ህግን ዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራብ (Subscribe) በማድረግ ድጋፋችሁን አሳዩን። 🙏👁‍🗨👁‍🗨👁‍🗨👁‍🗨👁‍🗨

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

https://youtube.com/channel/UCXYKAPt4crrhEx62KvcPzBw

#Ale_Hig #አለ_ህግ @Lawsocieties

Subscribe our youtube.
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

https://youtube.com/channel/UCXYKAPt4crrhEx62KvcPzBw
ℹ️ #በጥፋት_ከሥራ_የሚያሰናብቱ_በቂ_ምክንያቶች ⤵️

1/ የሥራ ሰዓት አለማክበር

የሥራ ሰዓት አለማክበር ሲባል በሥራ መግቢያ ሰዓት ማርፈድ፤ ከሥራ መውጪያ ሰዓት ቀደም ብሎ መውጣትና በሥራ ሰዓት የሥራ ቦታን ጥሎ መሄድን ያጠቃልላል፡፡ በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ 1156/2011 አንቀጽ 27(1) ሀ መሠረት 👉በሥራ ውሉ ከተዘረዘሩት ምክንያቶች ውጭ ሠራተኛው የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እየተሰጠው በስድስት ወር ውስጥ በጠቅላላው ለስምንት ጊዜ የስራ ሰዓት ያላከበረ ከሆነ የሥራ ውልን ለማቋረጥ አሠሪው መብት ይኖረዋል ::

2/ ከሥራ መቅረት

በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ 1156/2011 ከተመለከቱ እረፍቶች እና ልዩ ልዩ ፈቃዶች ውጭ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እየተሰጠው #በስድስት ወር ውስጥ ለአምስት ቀናት ከስራ
መቅረት፤ የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ እንሚያቋርጥ በአዋጁ አንቀጽ 27(1) ለ ተመልክቷል፡፡

3/ ማታለል ወይም ማጭበርበር

የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት በዋነኛነት በመተማመን ላይ የተመሰረተ እንደመሆኑ ሠራተኛው ታማኝ ሆኖ የመገኘት ግዴታውን ወደ ጎን በመተው በአሠሪው ላይ የሚፈጽማቸው የማታለልና የማጭበርበር ድርጊቶች የሥራ ውሉን ለማቋረጥ በቂ ተደርገው የመወሰዳቸው አግባብነት የሚያከራክር አይሆንም፡፡ ይሁን እንጂ ማታለል ወይም ማጭበርበር በመፈጸሙ ብቻ የስንብት እርምጃ መውሰድ ተገቢ አይደለም፡፡ ህጉ ማታለል ወይም ማጭበርበር ሲኖር የሥራ ውል የሚቋረጥባቸውን ሁኔታዎች በግልጽ ያስቀመጠ እንደመሆኑ በቅድሚያ ሁኔታዎቹ ተሟልተው ሊገኙ ይገባል፡፡

በአዋጁ አንቀጽ 27(1) ሐ እንደተመለከተው በሥራው ላይ የማታለል ወይም የማጭበርበር ተግባር መፈጸም የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ ለማቋረጥ አንደኛው በቂ ምክንያት ነው፡፡

4/ በአሠሪው ንብረት ወይም ገንዘብ አላአግባብ መጠቀም

ሠራተኛው ለሥራው የተሰጡትን መሣሪዎችና ዕቃዎች ሁሉ በጥንቃቄ የመጠበቅ የህግ ግዴታ ተጥሎበታል፡፡ ስለሆነም ጥሬ ገንዘብን ጨምሮ ሥራውን እንዲያከናውን የሚረዱት ሌሎች ከአሠሪው የተረከባቸውን ንብረቶች በራሱ ወይም በሌላ ሰው ጉዳት እንዳይደርስባቸው ብሎም ለብክነትና ለብልሽት እንዳይዳረጉ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እና ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ ለሚሰራው ሥራ ዓላማ ካልሆነ በስተቀር የግሉን ወይም የሌላ 3ኛ ወገን ብልጽግና በመሻት ሊጠቀምባቸው አይገባም፡፡ ግዴታው የታማኝነቱ ቁልፍ መገለጫ ነው፡፡ የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት በመተማመን ላይ የተመሰረተ እንደመሆኑ በማናቸውም የአሠሪውን ጥቅም በሚመለከቱ ጉዳዮች ሠራተኛው ሁልጊዜ ታማኝ ሆኖ መገኘት አለበት፡፡

በመሆኑም በአዋጁ አንቀጽ 27(1) ሐ መሠረት በአሠሪው ንብረት ወይም ገንዘብ አላአግባብ መጠቀም የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ ለማቋረጥ በቂ ምክንያት ነው፡፡

5/ ጠብ አጫሪነት ወይም አምባጓሮ

በሥራ ቦታ ላይ የሚከሰት ጠብ እና አምባጓሮ ሰላማዊ የሥራ አካባቢን የሚያውክና ስርዓት አልበኝነትን የሚያነግስ በመሆኑ በአጭሩ ካልተቀጨ የአሠሪውን ምርታማነት በእጅጉ ይጎዳል፡፡ አንድ ሠራተኛ ተመድቦ የሚሰራበት ሥራ ከሌላ ሠራተኛ ሥራ ጋር በእጅጉ የተሳሰረ ነው፡፡ ጠብና አምባጓሮ ሲፈጠር ሥራ በቅንጅትና በመግባባት አይሰራም፡፡ ከአሠሪው ድርጅት ምርትና አገልግሎት የሚፈልጉ ደንበኞችም ያርቃል፡፡ የአንቀጽ 27(1) ረ አይነተኛ አላማ በሥራ ቦታ ሰላም እንዲሰፍን በማድረግ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ነው፡፡ በመሆኑም በአዋጁ አንቀጽ 27(1) ረ መሠረት በስራ ቦታ ጠብ አጫሪ መሆን ወይም አምባጓሮ መፍጠር የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ ለማቋረጥ በቂ ምክንያት ነው፡፡

6/ በአሠሪው ንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ

በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ አንቀጽ 27(1) ሸ አነጋገር ሠራተኛው ከሥራ የሚሰናበተው ሆነ ብሎ ወይም በከባድ ቸልተኝነት ጉዳት ሲያደርስና ጉዳቱም የደረሰው በአሠሪው ንብረት ወይም ከድርጅቱ ሥራ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ባለው ማናቸውም ንብረት ላይ መሆኑ ሲረጋገጥ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር አራት የጥፋቱ ማቋቋሚያዎች አንድ ላይ ተሟልተው መገኘት እንዳለባቸው እንረዳለን፡፡ ይኸውም፤

#አንደኛ ጉዳት ደረሰበት የተባለው ነገር “ንብረት” መሆን አለበት፡፡ በሌላ አነጋገር ህጉ ለንብረት የሰጠውን ፍቺ ማሟላት ይኖርበታል፡፡

#ሁለተኛ ንብረቱ የአሠሪው ወይም ከድርጅቱ ሥራ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ያለው ንብረት ሊሆን ይገባል፡፡

#ሶስተኛ አሠሪው በንብረቱ ወይም ከድርጅቱ ሥራ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ባለው ንብረት ላይ የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩ ብሎም በጉዳቱና በድርጊቱ መካከል የምክንያትና ውጤት ግንኙነት ስለመኖሩ ማስረዳት ይኖርበታል፡፡ የምክንያትና ውጤት ግንኙነት ሲባል ሠራተኛው ማድረግ የሌለበትን በማድረጉ ወይም ማድረግ ያለበትን ባለማድረጉ ምክንያት ጉዳት መከሰቱን ለማመልከት ነው፡፡

#አራተኛ ሠራተኛው ጉዳቱን ያደረሰው ሆነ ብሎ ወይም በከባድ ቸልተኝነት ስለመሆኑ መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡

በመሆኑም በአዋጁ አንቀጽ 27(1) ሸ መሠረት በአሠሪው ንብረት ወይም ከድርጅቱ
ሥራ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ባለው ማናቸውም ንብረት ላይ ሆነ ብሎ ወይም በከባድ ቸልተኝነት ጉዳት ማድረስ የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ ለማቋረጥ በቂ ምክንያት ነው፡፡

7/ የወንጀል ጥፋተኝነትና እስራት

የወንጀል ጥፋተኝነት የሥራ ውልን ለማቋረጥ በራሱ በቂ ምክንያት ባይሆንም በውጤቱ ሠራተኛውን ለያዘው ሥራ ብቁ የማያደርገው ከሆነ [አንቀጽ 27(1) ሰ] ወይም የእስራቱ ጊዜ ከሰላሳ ቀን ከበለጠ [አንቀጽ 27(1) በ] ህጋዊ የስራ ውል ማቋረጫ ምክንያት ይሆናል፡፡ በአንቀጽ 27(1) ሰ ከጥፋተኝነት ባለፈ የእስራት ፍርድ እንዲኖር የግድ አይልም፡፡ ሠራተኛው ቅጣቱ ቢገደብለትም ብሎም በገንዘብ መቀጮ ብቻ ቢቀጣም ጥፋተኛ የተባለበት ወንጀል ብቃቱን የሚያሳጣው ከሆነ ከአሠሪው ጋር ያለው ግንኙነት ይቋረጣል፡፡

8/ የሥራ ውጤት መቀነስ (መለገም)

ሠራተኛው መውጫና መግቢያ ሰዓት አክብሮ በሥራ ቦታ መገኘቱ ብቻውን የመስራት ግዴታውን እየተወጣ ነው አያስብልም፡፡ ግዴታውን ሲወጣ መላ ጉልበቱን፤ ችሎታውንና ዕውቀቱን በመጠቀም የተመደበበትን ሥራ ጥንካሬና ትጋት በተሞላበት መልኩ በማከናወን ውጤት ማምጣት አለበት፡፡ በዳተኝነት፤ ልግመኝነትና ንዝህላልነት ሥራን መበደል ካለማስጠንቀቂያ የሚያሰናብት ጥፋት ነው፡፡ የሥራ ችሎታ መቀነስ በአንቀጽ 28(1) ሀ በማስጠንቀቂያ የሥራ ውልን የሚያቋርጥ በቂ ምክንያት ሲሆን ይህም ተፈጥሯዊ በሆነ ምክንያት ሊከሰት ስለሚችል በአንቀጽ 27(1) ሠ ጥፋት ከሆነው የሥራ ውጤት መቀነስ እንዲለይ ተደርጓል፡፡ አንቀጽ 27(1) ሠ ተፈጻሚ የሚሆነው ሠራተኛው የመስራት ችሎታውና ብቃቱ እያለው ሆነ ብሎ ወይም በቸልተኝነት ከሚጠበቅበት በታች በመስራት ሥራ ሲበድል ማለትም ሲያለግም ነው፡፡

የሕግ አማካሪና ጠበቃ ሳሙኤል ግርማ
https://t.me/YehigGuday
እሁድ ማታ 3 ስዓት ቀጥታ ስርጭት 👈👈👈

እሁድ 👇👇👇👇👇👇
3 ስዓት ላይ በዚህ ቴሌግራም ይጠብቁ

ሼር በማደረግ ሰዎቸን ይጋብዙ👆👆👆

Live 🔘 Live on Telegram 👈👈

#አለ_ህግ #Ale_Hig

Topic_"Fair trial under the criminal procedure from the constitution perspective.
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
Topic of the discussion
.
☑️👁‍🗨 "

🔘 Live on Telegram                       

Speaker: ☑️ Kassahun Yibeltal
(Dr. Cand)


Starting Time: 9:00PM -
[Sunday evening]

Join us: https://t.me/lawsocieties

ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉን        
  👉 https://t.me/lawsocieties
Federal Auditor General ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

Postion:5 Positions
1:Senior Lawyer,
2:Procurement Officer and
3: Executive Secretary

📚የትምህርት ዓይነት እና ደረጃ:
LLB degree in Law and College diploma or degree.

🇪🇹 የስራ ቦታ: Addis Ababa

🧭የምዝገባ ጊዜ ፡እስከ ህዳር
1/2015 ዓ.ም

🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ

https://jobs.amazonethiopia.com/job/federal-auditor-general/

🔰https://t.me/lawsocieties
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Lawyer Mike 🔊የህግ ባለሙያ)
እሁድ ማታ 3 ስዓት ቀጥታ ስርጭት 👈👈👈

እሁድ 👇👇👇👇👇👇
3 ስዓት ላይ በዚህ ቴሌግራም ይጠብቁ

ሼር በማደረግ ሰዎቸን ይጋብዙ👆👆👆

Live 🔘 Live on Telegram 👈👈

#አለ_ህግ #Ale_Hig

Topic_"Fair trial under the criminal procedure from the constitution perspective.
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
Topic of the discussion
.
☑️👁‍🗨 "

🔘 Live on Telegram                       

Speaker: ☑️ Kassahun Yibeltal
(Dr. Cand)


Starting Time: 9:00PM -
[Sunday evening]

Join us: https://t.me/lawsocieties

ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉን        
  👉 https://t.me/lawsocieties
ስለ Exit Exam ከሚመለከተው አካል መረጃ አግኝተናል።

በቀነ ቀጠሮ በዚሁ ቻናል በቀጥታ ስርጭት ገብተው ማብራሪያ ይሰጣሉ 👈
የሚመቻቸውን ቀን እንዳሳወቁን እናሳውቃለን🙏
የዛሬ ውይይታችን 3 ስዓት ይጀምራል 👇🏿👇🏿👇🏿👇🏿👇🏿👇🏿👇🏿👇🏿👇🏿👇🏿👇🏿👇🏿👇🏿👇🏿👇🏿 _"Fair trial under the criminal procedure from the constitution perspective. ሼር በማድረግ ተደራሽ አድርጉት 👉🏿👉🏿 https://t.me/lawsocieties
Live stream started
Live stream finished (1 hour)
📢📢አዲስ መረጃ ስለ Exit Exam

ዛሬ በነበረዉ የድምጽ ዉይይት ላይ አለ ህግ ግሩፕ ስለ Exit Exam ቅሬታ ለሚመለከተዉ አካል እንዲያናግርላችሁ ጠይቄዉ ነበር፡፡

አለ ህግም በሰጠኝ ምላሽ 👉 ጉዳዩ ለሚመለከተዉ አካል በእጅ ስልኩ ደዉሎ እንደነበር እና እንደተባለዉም በፈተናዉ ዉጤት ላይ ለቀረቡት ቅሬታዎች በቶሎ ምላሽ ያልተሠጠዉ በ 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና ምክንያት እንደሆነ እና በቅርቡ ለቀረቡት ቅሬታዎች ምላሽ እንደሚሠጡ ገልጿል፡፡
እንዲሁም በተጨማሪ ያለዉን ጠቅላላ ሁኔታ ለማስረዳት ይመች ዘንድ ቀን ተመቻችቶ በዚሁ ቴሌግራም ቻናል ላይ በድምጽ በመግባት በቀጥታ የሚመለከተዉ አካል ለጥያቄያችሁ ሠፊ ማብራሪያ እንደሚሠጡ የአለ ህግ ግሩፕ ነግሮኛል፡፡

👉በመሆኑም ቅሬታ ያሥገባችሁ ተማሪዎች በትግስት እንድትጠብቁ እመክራችኋለዉ፡፡

via ሀብቴ
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
አቢሲንያ ባንክ በሚከተሉት የሥራ መደቦች አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡
1. ለወለድ-ነጻ የባንክ አገልግሎት (IFB) የህግ አማካሪ ; የስራ ቦታ፡- አዲስ አበባ
2. የባንክ ሰልጣኝ ለጉብሬ ቅርንጫፍ ; የስራ ቦታ፡ - ደለል እና ጉራጌ ዞን አካባቢ
3. ክፍል I-ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ ; የስራ ቦታ፡ - ጉንችሬ (Gunchire)
4. የቢሮ ረዳት ;የስራ ቦታ፡ አዲስ አበባ
ለሥራ መደቡ የሚያስፈልገውን መስፈርት፣ የሥራ ልምድ እና የመሳሰሉትን ዝርዝር መረጃዎች ለማግኘት በባንኩ ድረገፅ https://vacancy.bankofabyssinia.com በመግባት ማግኘትና ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#የጠበቆች_የሙያ_ስነ_ምግባር_መርሆዎች
==========================

የሰው ልጆች ሁሉ በሰብዓዊ ፍጡርነታቸው የተቸሩትን መብቶችና መሰረታዊ ነፃነቶች እንዲጎናፀፉ ለማድረግ ብቃት ያለው የህግ ምክር አገልግሎት የሚያገኙበት መንገድ ማመቻቸት አስፈላጊ እንደሆነ የተባበሩት መንግስታት የህግ ሙያተኞችን ሚና ለመወሰን በደነገገው መሰረታዊ መርሆዎች ላይ በሚገባ ተመልክቷል፡፡
A) #የዜጎች መሰረታዊ መብቶችና ነፃነቶች በተለይም ግልጽና ፍትሃዊ የሆነ ዳኝነትን የማግኘት መብት በተለያዩ የአለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ስምምነቶችና መግለጫዎች ላይ የሰፈረ ከመሆኑም ባሻገር በወንጀል ተጠርጥረው የተያዙና፣ የተከሰሱ እንዲሁም በእስር ላይ የሚገኙ ሰዎች በተቻለ መጠን ተገቢ የህግ ምክር አገልግሎት ማግኘት የሚገባቸው መሆኑንና ከጠበቆቻቸውም ጋር የመገናኘትና የመወያየት፣ የውይይቱ ሚስጥራዊነትም እንዲጠበቅላቸው ሙሉ ነፃነት ያላቸው መሆኑ ተደንግጓል፡፡ በአንድ የፍትህ ስርዓት ውስጥ የዜጎች እኩልነት ተከብሮ፣ ፍትህና ርቱዕ የተሞላበት ዳኝነት እንዲያገኙ ከተፈለገ ሁሉም ዜጎች በተቻለው አቅም ሁሉ የህግ አገልግሎት እንዲያገኙ ማስቻል ለፍትሃዊ የህግ ስርዓት መጎልበትና ለሰብአዊ መብቶች መከበር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ በፍትህ ስርዓቱና በህግ የበላይነት ላይም ሰፊው ህብረተሰብ ፅኑ እምነት እንዲያሳድርና የሁሉም ሰው መብት ህግ ባስቀመጠው ወሰንና አግባብ እንዲከበር ጠንካራ የህግ ባለሙያዎች ማህበር ሊኖር የሚገባው ሲሆን ከፍተኛ ስነ ምግባር የተላበሱ የህግ ሙያተኞችና ጠበቆችም እጅግ በጣም አስፈላጊ መሆናቸውን እንገነዘባለን፡፡
እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ1990 ዓ.ም የወጣው የተባበሩት መንግስታት የህግ ሙያተኞች ሚና መሰረታዊ መርሆዎች ከሚደነግጉት ሁኔታዎች መካከል አንዱና ዋንኛው ሁሉም ሰዎች በወንጀል የፍርድ ሂደት መሰረታዊ መብቶቻቸውን በሚገባ ለማስጠበቅና ራሳቸውን ለመላከል ተደራሽነት ያለው የህግ ምክር አገልግሎትና የህግ አማካሪዎችን ወይም ጠበቆችን በቀላሉ ማግኘት እንደሚገባቸውና መንግስታትም በዚህ ረገድ ያለ አንዳች አይነት አድሎአዊ ልዩነት ሁሉም ዜጎች ይህንን አገልግሎት የሚያገኙበት ውጤታማ ስልቶችና ስነስርዓቶች መቀየስ ይጠበቅባቸዋል፡፡
B) #ከዚህ አኳያ መንግስታት የተለየ ኃላፊነት እንዳለባቸውና ይህ ኃላፊነትም በቂ ገንዘብ በመመደብ ድሆችና ሌሎችም የተገፉ የህብረተሰብ ክፍሎች ነፃ የህግ ምክር አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግን ይጨምራል፡፡
C) #የህግ ባለሙያዎች ማህበራትና ጠበቆችም በዚህ ረገድ ከመንግሰታት ጋር በመተባበር ነፃ የህግ አገልግሎት ለመግዛት የኢኮኖሚ አቅማቸው ለማይፈቅድ ዜጎች እንዲመቻች ለማድረግ የበኩላቸውን ጥረት ማድረግ አላባቸው፡፡ ከዚሁ ጎን ለጎን ሁሉም የህብረተሰቡ ክፍል በህግ ስለተረጋገጠላቸው መሰረታዊ መብቶችና ግዴታዎቻቸው እንዲያውቁ ለማድረግ መንግስትና ጠበቆች እንዲሁም የህግ ሙያተኞች ማህበራት በጋራ መረባረብ ይኖርባቸዋል፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ መልኩ በወንጀል የፍርድ ሂደት ውስጥ የተያዙና የተከሰሱ ሰዎች መሰረታዊ መብቶቻቸውና ነፃነቶቻቸው እንዲጠበቁ የማድረግ ኃላፊነት የመንግስት እንደሆነ ልብ ሊባል ይገባል፡፡ ከዚህ አንፃር መንግስት በወንጀል ተጠርጥረው የተያዙ ሰዎች እንደተያዙ ወዲያውኑ በሚመለከታቸው የፍትህ አካላት በሁሉም የወንጀለ ፍትህ አስተዳደር ሂደቶች በፈለጉት ወይም በመረጡት የህግ አማካሪ የመወከልና ተገቢውን የምክር አገልግሎት የማግኘት መብት እንዳላቸው እንዲያዉቁ መደረጉን ማረጋገጥ ይኖርበታል፡፡

D) #በተለይም የመክፈል አቅምን በማጣት ምክንያት የህግ ምክር አገልግሎት ማግኘት ያልቻሉ ግለሰቦች በቂ ልምድና ብቃት ያለው የህግ አማካሪ በመንግስት ወጪ እንዲያገኙ መደረግ አለበት፡፡
E) #በመንግስት የሚመደብላቸውም የህግ አማካሪ ከተከሰሱበት ጉዳይ ውስብስብነት ጋር በሚመጣጠን መልኩ በቂ ልምድና ችሎታ ያላቸው መሆን ይገባዋል፡፡ ችሎታቸውና ልማዳቸው እምብዛም ያልሆነ የህግ አማካሪዎችን መመደብ በዚህ ረገድ በመንግስት ላይ የተጣለውን ኃላፊነት መንግስት በሚገባ እንዳልተወጣው ነው የሚያስቆጥረው፡፡ በርግጥ በአብዛኛው በወንጀል ጉዳዮች ላይ ነው የመክፈል አቅም ለሌላቸው ግለሰቦች በመንግስት ወጪ ጠበቃን ማቆም የሚገባው፡፡ ይሁን እንጂ ከወንጀል ጉዳይ ዉጪ በሆነ መልኩ ለተያዙ ግለሰቦች በመንግስት በነፃ ጠበቃ የማቆም ግዴታ እንዳለበት ነው ተደንግጎ የሚገኘው፡፡
F) #በአለም አቀፍ መርሆዎች የተደነገገው ደረጃ እንደሚያመለክተው ከሆነ በተለይም የተያዙ ሰዎች ጠበቃ የማቆም አቅም በማይኖራቸው ጊዜ መንግስት በተቻለው አቅም ሁሉ ከተያዙበት ጊዜ አንስቶ በ48 ሰዓታት ውስጥ ነው ነፃ የህግ አገልግሎት የሚሰጣቸውን የህግ አማካሪ ሊመደብላቸው የሚገባው፡፡ ከዚህ የምንረዳው በሁሉም የፍርድ ሂደቶች ዜጎች በህግ አማካሪ ሳይወከሉ በፍርድ ሂደት እንዳያልፉ የሚደረግ መሆኑን የሚያመለክት ነው፡፡ በሌላ አነጋገር አቅም ያጡ ግለሰቦች በድህነታቸው ምክንያት ብቻ የህግ ምክር ሳያገኙ በማንኛውም የፍርድ ሂደት እንዲሳተፉ ወይም ለፍርድ እንዲቀርቡ ከተደረገ የሁሉም ሰዎች ፍትሃዊ፣ሚዛናዊ ግልፅ የሆነ ዳኝነት የማግኘት መብት ተከብሯል ለማለት አያስደፍርንም፡፡
የተያዙ ሰዎች በእስር ወቅት በመንግስት ከተመደበላቸው የህግ አማካሪ ጋር የሚገናኙበትና በነፃነት የሚወያዩበት በቂ እድል ሊሰጣቸው ይገባል፡፡ እነዚህ ሰዎች ከህግ አማካሪዎቻቸው ወይም ጠበቆቻቸው ጋር የሚያደርጉት ምክክርና ውይይት በየትኛውም መልኩ በህግ አስከባሪ ባለስልጣናት ሊደመጥና ይዘቱም ቅድመ ምርመራ ሊደረግበት አይገባም፡፡
G) #ጥብቅና ከፍተኛ ኃላፊነት የሚያስከትልና በፍትህ አስተዳደር ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ ያለው ሙያ በመሆኑ ከጠበቆች ከፍ ያለ ስነ ምግባር ነው የሚጠበቀው፡፡ ከዚህም የተነሳ ጠበቆች በግል ህይወታቸውም ጭምር የሙያውን ክብርና ዝና ከሚያጎድፉ ባህሪያት ራሳቸውን ማግለልና በሚገባ መጠበቅ አለባቸው፡፡ ከዚህም አልፍው የሙያ ባልደረቦቻቸው የስነ ምግባር ጉድለት እንዳያሳዩ የመምከርና የስነ ምግባር ጉድለት ፈፅመው ሲገኙ ደግሞ ለተገቢው አካል የመጠቆም ኃላፊነት አለባቸው፡፡

ለዚህ ነው ጠበቆች ሁሌም ቢሆን የሙያቸውን ክብርና ዝና በመጠበቅ የፍትህ አስተዳደሩ ዋልታ መሆን ይገባቸዋል የሚባለው፡፡
H) #አንድ ጠበቃ የሙያውን ክብርና ዝና ለመጠበቅ የሚከተሉትን እሴቶች ማክበር፣ በተግባርም ማሳየት ይኖርበታል፡፡

#ሙያዊ ነፃነትን፣ ገለልተኝነትን ቅንነትን በስራው ላይ በተጨባጭ ማሳየት፣
#የባለጉዳዩን ምርጫ ፣ፍላጎትን ጥቅም በማስቀደም በርሱ ፍላጎት መሰረት የጥብቅናውን ስራ ማከናወን፣
#የባለጉዳዩን ጥቅም በተቻለ መጠን ሁሉ ለማስጠበቅ ትጋት ማሳየትና ተገቢውን ጥረት ማድረግ፣
#የሙያውን ወይም የራሱን ክብና ዝና በሚያስጠብቅ መልኩ የግል ህይወቱን መምራት፣
#የጥብቅና ስራ የሚጠይቀውን ሙያዊ ኃላፊነትና የስራ ደረጃ አሟልቶ መገኘት፣
#በክርክር ሂደት ለዳኝነት አገልግሎቱ ውጤታማነት ሲባል ፍ/ቤቶች ከፍትሃዊ ውሳኔ እንዲደርሱ ያለበትን ግዴታና ኃላፊነት መወጣት ናቸው፡፡
👇👇👇👇👇👇የቀጠለ👇👇
#ጠበቆች የባለጉዳዮች ወኪል ብቻ ሳይሆኑ የፍትህ አስተዳደሩም ዋልታ በመሆናቸው ጭምር ፍርድ ቤቶች በእውነት ላይ እንዲያደርሱና ፍትሃዊና ሚዛናዊነትን የተላበሰ ውሳኔ እንዲሰጡ መርዳት አለባቸው፡፡
ከዚህ አንፃር የፌዴራል ፍ/ቤቶች ጠበቆች ስነ ምግባር ደንብ የሚከተሉትን ግዴታዎች በጠበቆች ላይ ጥሏል፡፡
I) #በምቀኝነት ወይም በክፉ ልቦና ተነሳስቶ ሌላውን ወገን የሚጎዳ ክስ ወይም ክርክር አለማቅረብ፣
#ደንበኛው የወራዳነት ወይም የማጭበርበር ድርጊት እንዲፈፅም አለማበረታታት ወይም አለመፍቀድ፣
#ዳኛን ወይም ሌላ የፍ/ቤት ሰራተኛን በህግ መሰረት ከማሳመን ውጪ ሌላ ተገቢ ያልሆነ ማንኛውም አይነት ዘዴ በመጠቀም ተፅህኖ ለማሳደር አለመሞከር ወይም ሌላ ሰው እንዲሞክር አለመገፋፋት ፣
#ሆነ ብሎ ፍ/ቤትን የሚያሳስት የተጋነነ ፅሁፈ ንግግር ለፍርድ ቤት አለማቅረብ፣
#በምስክርነት ቃል ወይም የሰነድ ይዘት ላይ የሀሰት ድርጊት በመፈፀም ፍርድ ቤትን ለማሳሳት አለመሞከር፣
#በግልፅ ለጉዳዮ አግባብነት የሌለውን ማስረጃ አግባብነት ያለው አስመስሎ ለፍርድ ቤት አለማቅረብ፣
#ለጉዳዮ በምስክርነት መቅረብ የሚገባው ሰው ፍርድ ቤት እንዳይቀርብ አለማባበል ወይም አለመሞከር
አንድን ምስክር ተገቢ ባልሆነ መንገድ አለማመናጨቅ፣ አለማስጨነቅ፣ወይም አለማስፈራራት ናቸው፡፡
በጥቅሉ የባለጉዳይን ጥቅም ከማስጠበቅ የተሻገረ ኃላፊነት እንዳለበት አውቆ ፍርድ ቤቱ ከእውነተኛና ፍትሃዊ ውሳኔ ላይ እንዲደርስ የበኩሉን አስተዋፅኦ ማድረግ የሚጠበቅበት ሲሆን የጥብቅና ስራውንም በቅን ልቦና ማከናወን ይጠበቅበታል፡፡

ሌላኛውና ዋንኛው የጠበቆች የስነ ምግባር ግዴታ ጠበቆች ከደንበኞቻቸው አንፃር ያለባቸው ግዴታ ነው፡፡
J) #በዚህ ረገድ የጠበቆች ዋንኛ ግዴታ የሚሆነው ባለጉዳዮች ዳኝነት ከጠየቁበት የክርክር ጭብጥ አንፃር ያላቸውን መብትና ግዴታ እንዲሁም መብታቸውን ለማስከበርና ግዴታቸውን ለመወጣት ህጉ የሚደነግጋቸውን አካሄዶችና ስነ ስርዓቶች እንዲያውቁ ማድረግ ነው፡፡ ከዚሀ ጋር ተያይዞ የባለጉዳዮችን መብትና ጥቅም ለማስከበር እነርሱን ወክሎ ክርክር በማቅረብ መብታቸውና ጥቅማቸው እንዲከበር ዕውቀቱንና የስራ ልምዱን ስራ ላይ ማዋል ነው፡፡ ከዚህም በላይ የደንበኛውን ጉዳይ ከመደበኛ ፍርድ ቤት ወይም አስተዳደራዊ የዳኝነት አካላት ዘንድ በመውሰድ የደንበኛውን ጉዳይ በትጋት መከታተል፣ አፋጣኝና ፍትሃዊ ውሳኔ እንዲያገኝም ሙያዊ ጥንቃቄ ብርቱ ጥረት ማድረግ ይገባዋል፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥም ጉዳዩ የደረሰበትን ደረጃ በየጊዜው ለደንበኛው የማሳወቅ ግዴታ አለበት፡፡
ጠበቆች ሁሌም ቢሆን የደንበኞቻቸው ጥቅም ለማስጠበቅ ተገቢውን ጥረት ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡ ለደንበኞቻቸው ጥቅም መከበርም በፍፁም ታማኝነት ማገልገል ይጠበቅባቸዋል፡፡

K) #በዚህ ረገድ በጠበቃውና በደንበኛው፣ ወይም በጠበቃው ዘመዶችና በደንበኛው፣ወይም ጠበቃው በወከላቸው የተለያዩ ደንበኞች መካከል የጥቅም ግጭት እንዳይፈጠር ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል፡፡ እንዲሁም በጥብቅና አገልግሎቱ ምክንያት ያወቃቸውን የደንበኛውን የግል ወይም የስራ ሚስጥሮችን መጠበቅ አለበት፡፡ ደንበኛው ሳይፈቅድለት በሙያው ምክንያት እጁ የገቡትን ማናቸውንም የደንበኛውን ሚስጥሮች ለሌላ አካል አሳልፎ ሊሰጥ አይችልም፡፡ ራሱም ቢሆን በህግ በተፈቀዱለት ጥቂት ሁኔታዎች ካልሆነ በቀር ሊጠቀምበት አይችልም፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ጠበቆች ለሌሎች ሶስተኛ ወገኖችም ቅን የመሆን ግዴታ አለባቸው፡፡ በተለይም ሌሎች ተከራካሪዎችን ለማጉላላት በማሰብ አከራካሪ የሆነ ጭብጥ ወይም በሌላኛው ተከራካሪ ላይ ኃላፊነትን ሊያስከትል የሚችል ውጤት የሌለ መሆኑ በግልፅ አኳኋን የሚታይበት ሁኔታ ቅንነትን በማጣት ተገቢ ያልሆነ ክርክር በተቃራኒ ወገኖች ላይ መጀመር የለበትም፡፡
L) #ከዚህ አንፃር በተለይም ከዚህ በታች ከተገለፁት ድርጊቶች መቆጠብ አለበት፡፡ እነዚህም፡-
ተቃራኒ ወገን ማስረጃ እንዳያገኝ ማንኛውንም እንቅፋት መፍጠር ወይም ሌሎች ሰዎች ይህን መሰል አድራጎት እንዲፈፅሙ መሞከር ወይም መረዳት፣
ማስረጃን ማሳሳት ወይም ሌሎች ሰዎች ይህን መሰል አድራጎት እንዲፈፅሙ መሞከር መርዳት፣
ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት የሌለው ወይም በማስረጀ ሊደገፍ የማይችል ነገር ማቅረብ
በምስክርነት ካልቀረበ በቀር በግል የሚያውቀውን የጭብጥ ነገሮች መሰንዘር ወይም የጉዳዩን ፍትሃዊነት የአንድን ምስክር ተዓሚነት፣ የተከሳሽን ጥፋተኛ ወይም ተጠያቂ መሆንና አለመሆን አስመልክቶ የግል አስተያየቱን መስጠት
ደንበኛው ወይም ምስክርነታቸውን እንዲሰጡ የማይገደዱ ሰዎችን በተመለከተ ካልሆነ በስተቀር ሌላ ማንኛውንም ሰው ለተቃራኒ ወገን የምስክርነት ቃሉን ወይም ሌላ አግባብነት ያለው ማስረጃ እንዳይሰጥ መገፋፋት ናቸው፡፡
በመጨረሻም ጠበቆችም ፍትሃዊ ዳኝነት እንዲጎለብት እንዲሁም የደንበኞቻቸው መብትና ጥቅም እንዲጠበቅ የማድረግ ድርብ ኃላፊነት ሲኖርባቸው እነዚህን ኃላፊነቶች በተጣጣመ መልኩ ነው ማከናወን ያለባቸው፡፡ ከዚህ አኳያ ለሰብአዊ መብቶችና መሰረታዊ ነፃነቶች መከበር በትጋት መቆምና መስራት ይኖርባቸዋል፡፡
M) #በዚህ ረገድ የደንበኛቸውን ጥቅም ማስጠበቅና ለፍትህ መከበርም የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማድረግ መካከል የሚታየውን ክፍተት ለማጣጣመና ሚዛናዊ ለማድረግ መጣር አለባቸው፡፡ ጠበቆች ሙያቸው የግለሰቦች መሠረታዊ መብቶችና ነፃነቶች እንደከበሩና እንዲጐለብቱ የማድረግ ልዩ ኃላፊነት ወይም ግዴታ እንደጣለባቸው በመገንዘብ ይህንን ከፍተኛ የሙያ ግዴታ ለመወጣት ከፍተኛ ስነምግባር መላበስ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ለፍትህ ሥርዓቱ መጐልበትና ለሰብዓዊ መብቶች መከበርም ዘወትር የበኩላቸውን ድርሻ ለማበርከት መሥራት እንደሚገባቸውና በዚህ ሂደት ውስጥም ለሙያቸው ስነምግባር መገዛት እንደሚጠበቅባቸው ግንዛቤ ሊወሰድ ይገባል፡፡
https://t.me/lawsocieties
ክስ መመስረቻ ጊዜ

በሕገመንግሥቱ መሠረት ሰውን ከ48 ሰዓት በላይ ለ1 ሰዓትም እንኳን ማቆየት አይቻልም። በዚህ መሠረት በወንጀል ተጠርጥሮ ምርመራ እስኪጣራ በእስር የሚገኝን ሰው፣ ምርመራው ካለቀ በኋላ ክስ እስኪመሠረት ድረስ በእስር ለማቆየት የተፈለገ እንደሆነ ፍርድ ቤትን ማስፈቀድ ግድ ይላል። ምክንያቱም ከ48 ሰዓት በላይ አልፎም ለቀናት በእስር የነበረውን ሰው ክስ እስከሚመሠረትበት ድረስ በሚል ለተጨማሪ ጊዜ ማቆየት የተፈለገ እንደሆነ ፍርድ ቤት ሳይፈቅድ ማቆየት ጨርሶ ስለማይቻል ነው። የወመሕሥሥቁ 109 ዐቃቤ ሕግን በ15 ቀን ውስጥ ክስ እንዲያዘጋጅ ከሚያስገድድ ውጪ ክሱ እስከሚመሠረት ድረስ ግን ተጠርጣሪው በእስር እንዲቆይ አያዝዝም። ስለዚህ ተከሣሹን በእስር ማቆየት ከተፈለገ ፍርድ ቤትን ማስፈቀድ የግድ ነው።
በተጨማሪም ሕጉ ለዐቃቤ ሕግ የሚሰጠው የ15 ቀን ጊዜ ገደብ ጣሪያው ነው እንጂ ለእያንዳንዱ ጉዳይ እስከ 15 ቀን መቆየት ይችላል ማለት አይደለም ። ስለዚህ ጉዳዩ ግልጽና ብዛት የሌለው ወይም ውስብስብ ካልሆነ ዐቃቤ ሕግ ከ15 ቀንም ቀደም ብሎ ክስ መመሥረት ወይም መወሰን ይጠበቅበታል ማለት ነው። ስለዚህ ፍርድ ቤት ስንት ቀን እንደሚበቃው ጭምር ይወስናል፤ ከተጠየቀው 15 ቀን ውስጥ የሚበቃውን ያህል ብቻ በመፍቀድ ተከሳሹ በሕገመንግስቱ አንቀጽ 37 መሠረት የተፋጠነ ፍትሕ እንዲያገኝ ያደርጋል ማለት ነው።

============
መረጃው: ከኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው!
#በአመክሮ_መፈታት_የሚቻለው_እንዴት_ነው?
=====================
አመክሮ የቅጣት ማስተማሪያነት ከሚገልጽባቸው ሁኔታዎች አንዱ ነው ማለት ይቻላል፡፡ አንድ ተቀጪ ለፈፀመው ወንጀል የተፈረደበትን የእሥራት ጊዜ ሙሉ በሙሉ ከመፈፀሙ በፊት የተወሰነ ጊዜ በመስጠት ቀሪውን የእስር ጊዜ ከእስር ውጩ ሆኖ እንዲያጠናቅቅ የማድረግ ሥርዓት ነው አንድ ተቀጪ በአመክሮ ሊፈታ ይችል ዘንድ በወንጀል ሕጉ የተደነገጉት ቅድመ ሁኔታዎች ሊሟሉ ይገባል፡፡
#በአመክሮ_መፈታት_የሚቻለው_እንዴት_ነው?
=====================
የቀጠለ 👆👆👆👆👆👆


👇👇👇👇👇👇👇👇👉የወ/ሕ/ቁ 201 በተወሰነ ገደብ በአመክሮ መፈታትን አስመልክቶ መርህ አስቀምጧል፡፡ በአመክሮ መፈታት የተቀጪውን ፀባይ ማሻሻያ እና ወደደንበኛው ማህበራዊ ኑሮ መመለሻ ሆኖ መቆጠር እንደሚገባው ይገልፃል፡፡

በአመክሮ ለመፈታት ይቻለው ዘንድ አንድ ተቀጪ ከተፈረደበት ቅጣት 2/3ኛውን መፈፀም ይኖርበታል፡፡ የዕድሜ ልክ ጸኑ እሥራት ፍርደኛ ከሆነም ሃያ አመት ታስሮ ነው ጥያቄውን ማቅረብ የሚችለው፡፡ በአመክሮ የመፈታት ጥያቄ በተቀጪው ወይም “አግባብ ባለው አካል ለፍርድ ቤቱ ይቀርባል” (አንቀጽ202(1) “አግባብ ያለው አካል” ማነው የሚለውን ሕጉ አይመልስም እንደሚታወቀው በወንጀል ጉዳይ ጥፋተኛ ተብሎ እሥራት የተወሰነበት ሰው የሚቆየው ማረሚያ ቤት በመሆኑና የአመክሮ ጥያቄንም ለፍ/ቤት የሚያቀርበው ይኸው ተቋም በመሆኑ አግባብ ያለው አካል ማረሚያ ቤት ነው ማለት ይቻላል፡፡ ሕጉ ግን ምናልባትም ወጣት ጥፋተኞች የሚቆዩበትንም ተቋማትና ሌሎችንም ታሳቢ ያደረገ ይመስላል፡፡

አመክሮን በሚመለከትም ማረሚያ ቤት ስለተቀጪው ፀባይ (አንቀጽ 202 (1) (ሀ)(ለ)) አጣርቶ ለፍ/ቤት ከሚልከው በተጨማሪ ተቀጪው ለደረሰው ጉዳት በተቻለ መጠን ሊከፍል የሚጠበቅበትን በፍርድ ቤት በተወሰነው መሠረት ወይም ከተበዳዮ ጋር በተደረገ ስምምነት መሠረት ካሣ ለመክፈሉ ማረጋገጫ ማቅረብ እንደሚገባ በአንቀጽ 202(1)(ለ) ላይ ተመልክቷል፡፡ ነገር ግን በተግባር ይህ አይደረግም፡፡ ማረሚያ ቤቱ የተቀጪውን ፀባይ መሻሻል ፍርም ሞልቶ ከላከ ያለተጨማሪ ጥያቄ እስረኛው እንዲለቀቅ ይደረጋል፡፡

ሌላው በሕጉ ላይ የተመለከተውና በፍርድ ቤቶች ግን ሲተገበር የማይስተዋለው ጥፋተኛው ሲፈርድበት ቅጣቱን ከመፈፀሙ በፊት ቀደም ብሎ ሊለቀቅ እንደሚችልና ይህን እድል ለማግኘት ሊፈጽማቸው የሚገቡ ነገሮች እንደሚገለፁለት የተመለከተው ነው፡፡

እንደ ገደብ ውሣኔ ሁሉ በአመክሮ የሚለቀቅ ተቀጪም የፈተና ጊዜ ይሠጠዋል ይህም ማለት በተሠጠው የፈተና ጊዜ ውስጥ ፀባዩ ባይሻሻል ወይም ሌላ ወንጀል ሲፈጽም ቢገኝ (አንቀጽ 200 እና 206) በአመክሮ እንዲፈታ የተሰጠው ትእዛዝ ተነስቶ ተመልሦ እንዲታሠር ይደረጋል፡፡ በአመክሮ ቀርቶለት የነበረውን ቀሪ ቅጣትና ለአዲሱ ጥፋት የተወሰነበትን ጊዜ ይታሠራል፡፡

የፈተናው ጊዜ እንደወንጀሉ ክብደት እየታየ የሚሠጥ ነው፡፡ በመርህ ደረጃ የፈተና ጊዜ የሚለው ሳይፈፀም የቀረው የእሥራት ጊዜ ማለትም 1/3ኛው የቅጣት ዘመን ነው፡፡ በአመክሮ ተቀጪው እንዲለቀቅ ፍ/ቤት ሲያዝ የፈተናው ጊዜ ቢያንስ ሁለት ዓመት ሲሆን ከአምስት ዓመት የማይበልጥ ነው፡፡ በአመክሮ የመፈታት ዕድል ያገኘው ተቀጪ የዕድሜ ልክ እስረኛ ከሆነ ግን የፈተና ጊዜው ከ5 ዓመት ማነስ ና ከ7 ዓመት መብለጥ የለበትም (አንቀጽ 204)፡፡
https://t.me/lawsocieties