ℹ️ #በጥፋት_ከሥራ_የሚያሰናብቱ_በቂ_ምክንያቶች ⤵️
1/ የሥራ ሰዓት አለማክበር
የሥራ ሰዓት አለማክበር ሲባል በሥራ መግቢያ ሰዓት ማርፈድ፤ ከሥራ መውጪያ ሰዓት ቀደም ብሎ መውጣትና በሥራ ሰዓት የሥራ ቦታን ጥሎ መሄድን ያጠቃልላል፡፡ በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ 1156/2011 አንቀጽ 27(1) ሀ መሠረት 👉በሥራ ውሉ ከተዘረዘሩት ምክንያቶች ውጭ ሠራተኛው የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እየተሰጠው በስድስት ወር ውስጥ በጠቅላላው ለስምንት ጊዜ የስራ ሰዓት ያላከበረ ከሆነ የሥራ ውልን ለማቋረጥ አሠሪው መብት ይኖረዋል ::
2/ ከሥራ መቅረት
በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ 1156/2011 ከተመለከቱ እረፍቶች እና ልዩ ልዩ ፈቃዶች ውጭ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እየተሰጠው #በስድስት ወር ውስጥ ለአምስት ቀናት ከስራ
መቅረት፤ የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ እንሚያቋርጥ በአዋጁ አንቀጽ 27(1) ለ ተመልክቷል፡፡
3/ ማታለል ወይም ማጭበርበር
የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት በዋነኛነት በመተማመን ላይ የተመሰረተ እንደመሆኑ ሠራተኛው ታማኝ ሆኖ የመገኘት ግዴታውን ወደ ጎን በመተው በአሠሪው ላይ የሚፈጽማቸው የማታለልና የማጭበርበር ድርጊቶች የሥራ ውሉን ለማቋረጥ በቂ ተደርገው የመወሰዳቸው አግባብነት የሚያከራክር አይሆንም፡፡ ይሁን እንጂ ማታለል ወይም ማጭበርበር በመፈጸሙ ብቻ የስንብት እርምጃ መውሰድ ተገቢ አይደለም፡፡ ህጉ ማታለል ወይም ማጭበርበር ሲኖር የሥራ ውል የሚቋረጥባቸውን ሁኔታዎች በግልጽ ያስቀመጠ እንደመሆኑ በቅድሚያ ሁኔታዎቹ ተሟልተው ሊገኙ ይገባል፡፡
በአዋጁ አንቀጽ 27(1) ሐ እንደተመለከተው በሥራው ላይ የማታለል ወይም የማጭበርበር ተግባር መፈጸም የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ ለማቋረጥ አንደኛው በቂ ምክንያት ነው፡፡
4/ በአሠሪው ንብረት ወይም ገንዘብ አላአግባብ መጠቀም
ሠራተኛው ለሥራው የተሰጡትን መሣሪዎችና ዕቃዎች ሁሉ በጥንቃቄ የመጠበቅ የህግ ግዴታ ተጥሎበታል፡፡ ስለሆነም ጥሬ ገንዘብን ጨምሮ ሥራውን እንዲያከናውን የሚረዱት ሌሎች ከአሠሪው የተረከባቸውን ንብረቶች በራሱ ወይም በሌላ ሰው ጉዳት እንዳይደርስባቸው ብሎም ለብክነትና ለብልሽት እንዳይዳረጉ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እና ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ ለሚሰራው ሥራ ዓላማ ካልሆነ በስተቀር የግሉን ወይም የሌላ 3ኛ ወገን ብልጽግና በመሻት ሊጠቀምባቸው አይገባም፡፡ ግዴታው የታማኝነቱ ቁልፍ መገለጫ ነው፡፡ የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት በመተማመን ላይ የተመሰረተ እንደመሆኑ በማናቸውም የአሠሪውን ጥቅም በሚመለከቱ ጉዳዮች ሠራተኛው ሁልጊዜ ታማኝ ሆኖ መገኘት አለበት፡፡
በመሆኑም በአዋጁ አንቀጽ 27(1) ሐ መሠረት በአሠሪው ንብረት ወይም ገንዘብ አላአግባብ መጠቀም የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ ለማቋረጥ በቂ ምክንያት ነው፡፡
5/ ጠብ አጫሪነት ወይም አምባጓሮ
በሥራ ቦታ ላይ የሚከሰት ጠብ እና አምባጓሮ ሰላማዊ የሥራ አካባቢን የሚያውክና ስርዓት አልበኝነትን የሚያነግስ በመሆኑ በአጭሩ ካልተቀጨ የአሠሪውን ምርታማነት በእጅጉ ይጎዳል፡፡ አንድ ሠራተኛ ተመድቦ የሚሰራበት ሥራ ከሌላ ሠራተኛ ሥራ ጋር በእጅጉ የተሳሰረ ነው፡፡ ጠብና አምባጓሮ ሲፈጠር ሥራ በቅንጅትና በመግባባት አይሰራም፡፡ ከአሠሪው ድርጅት ምርትና አገልግሎት የሚፈልጉ ደንበኞችም ያርቃል፡፡ የአንቀጽ 27(1) ረ አይነተኛ አላማ በሥራ ቦታ ሰላም እንዲሰፍን በማድረግ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ነው፡፡ በመሆኑም በአዋጁ አንቀጽ 27(1) ረ መሠረት በስራ ቦታ ጠብ አጫሪ መሆን ወይም አምባጓሮ መፍጠር የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ ለማቋረጥ በቂ ምክንያት ነው፡፡
6/ በአሠሪው ንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ
በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ አንቀጽ 27(1) ሸ አነጋገር ሠራተኛው ከሥራ የሚሰናበተው ሆነ ብሎ ወይም በከባድ ቸልተኝነት ጉዳት ሲያደርስና ጉዳቱም የደረሰው በአሠሪው ንብረት ወይም ከድርጅቱ ሥራ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ባለው ማናቸውም ንብረት ላይ መሆኑ ሲረጋገጥ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር አራት የጥፋቱ ማቋቋሚያዎች አንድ ላይ ተሟልተው መገኘት እንዳለባቸው እንረዳለን፡፡ ይኸውም፤
#አንደኛ ጉዳት ደረሰበት የተባለው ነገር “ንብረት” መሆን አለበት፡፡ በሌላ አነጋገር ህጉ ለንብረት የሰጠውን ፍቺ ማሟላት ይኖርበታል፡፡
#ሁለተኛ ንብረቱ የአሠሪው ወይም ከድርጅቱ ሥራ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ያለው ንብረት ሊሆን ይገባል፡፡
#ሶስተኛ አሠሪው በንብረቱ ወይም ከድርጅቱ ሥራ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ባለው ንብረት ላይ የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩ ብሎም በጉዳቱና በድርጊቱ መካከል የምክንያትና ውጤት ግንኙነት ስለመኖሩ ማስረዳት ይኖርበታል፡፡ የምክንያትና ውጤት ግንኙነት ሲባል ሠራተኛው ማድረግ የሌለበትን በማድረጉ ወይም ማድረግ ያለበትን ባለማድረጉ ምክንያት ጉዳት መከሰቱን ለማመልከት ነው፡፡
#አራተኛ ሠራተኛው ጉዳቱን ያደረሰው ሆነ ብሎ ወይም በከባድ ቸልተኝነት ስለመሆኑ መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡
በመሆኑም በአዋጁ አንቀጽ 27(1) ሸ መሠረት በአሠሪው ንብረት ወይም ከድርጅቱ
ሥራ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ባለው ማናቸውም ንብረት ላይ ሆነ ብሎ ወይም በከባድ ቸልተኝነት ጉዳት ማድረስ የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ ለማቋረጥ በቂ ምክንያት ነው፡፡
7/ የወንጀል ጥፋተኝነትና እስራት
የወንጀል ጥፋተኝነት የሥራ ውልን ለማቋረጥ በራሱ በቂ ምክንያት ባይሆንም በውጤቱ ሠራተኛውን ለያዘው ሥራ ብቁ የማያደርገው ከሆነ [አንቀጽ 27(1) ሰ] ወይም የእስራቱ ጊዜ ከሰላሳ ቀን ከበለጠ [አንቀጽ 27(1) በ] ህጋዊ የስራ ውል ማቋረጫ ምክንያት ይሆናል፡፡ በአንቀጽ 27(1) ሰ ከጥፋተኝነት ባለፈ የእስራት ፍርድ እንዲኖር የግድ አይልም፡፡ ሠራተኛው ቅጣቱ ቢገደብለትም ብሎም በገንዘብ መቀጮ ብቻ ቢቀጣም ጥፋተኛ የተባለበት ወንጀል ብቃቱን የሚያሳጣው ከሆነ ከአሠሪው ጋር ያለው ግንኙነት ይቋረጣል፡፡
8/ የሥራ ውጤት መቀነስ (መለገም)
ሠራተኛው መውጫና መግቢያ ሰዓት አክብሮ በሥራ ቦታ መገኘቱ ብቻውን የመስራት ግዴታውን እየተወጣ ነው አያስብልም፡፡ ግዴታውን ሲወጣ መላ ጉልበቱን፤ ችሎታውንና ዕውቀቱን በመጠቀም የተመደበበትን ሥራ ጥንካሬና ትጋት በተሞላበት መልኩ በማከናወን ውጤት ማምጣት አለበት፡፡ በዳተኝነት፤ ልግመኝነትና ንዝህላልነት ሥራን መበደል ካለማስጠንቀቂያ የሚያሰናብት ጥፋት ነው፡፡ የሥራ ችሎታ መቀነስ በአንቀጽ 28(1) ሀ በማስጠንቀቂያ የሥራ ውልን የሚያቋርጥ በቂ ምክንያት ሲሆን ይህም ተፈጥሯዊ በሆነ ምክንያት ሊከሰት ስለሚችል በአንቀጽ 27(1) ሠ ጥፋት ከሆነው የሥራ ውጤት መቀነስ እንዲለይ ተደርጓል፡፡ አንቀጽ 27(1) ሠ ተፈጻሚ የሚሆነው ሠራተኛው የመስራት ችሎታውና ብቃቱ እያለው ሆነ ብሎ ወይም በቸልተኝነት ከሚጠበቅበት በታች በመስራት ሥራ ሲበድል ማለትም ሲያለግም ነው፡፡
የሕግ አማካሪና ጠበቃ ሳሙኤል ግርማ
https://t.me/YehigGuday
1/ የሥራ ሰዓት አለማክበር
የሥራ ሰዓት አለማክበር ሲባል በሥራ መግቢያ ሰዓት ማርፈድ፤ ከሥራ መውጪያ ሰዓት ቀደም ብሎ መውጣትና በሥራ ሰዓት የሥራ ቦታን ጥሎ መሄድን ያጠቃልላል፡፡ በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ 1156/2011 አንቀጽ 27(1) ሀ መሠረት 👉በሥራ ውሉ ከተዘረዘሩት ምክንያቶች ውጭ ሠራተኛው የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እየተሰጠው በስድስት ወር ውስጥ በጠቅላላው ለስምንት ጊዜ የስራ ሰዓት ያላከበረ ከሆነ የሥራ ውልን ለማቋረጥ አሠሪው መብት ይኖረዋል ::
2/ ከሥራ መቅረት
በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ 1156/2011 ከተመለከቱ እረፍቶች እና ልዩ ልዩ ፈቃዶች ውጭ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እየተሰጠው #በስድስት ወር ውስጥ ለአምስት ቀናት ከስራ
መቅረት፤ የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ እንሚያቋርጥ በአዋጁ አንቀጽ 27(1) ለ ተመልክቷል፡፡
3/ ማታለል ወይም ማጭበርበር
የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት በዋነኛነት በመተማመን ላይ የተመሰረተ እንደመሆኑ ሠራተኛው ታማኝ ሆኖ የመገኘት ግዴታውን ወደ ጎን በመተው በአሠሪው ላይ የሚፈጽማቸው የማታለልና የማጭበርበር ድርጊቶች የሥራ ውሉን ለማቋረጥ በቂ ተደርገው የመወሰዳቸው አግባብነት የሚያከራክር አይሆንም፡፡ ይሁን እንጂ ማታለል ወይም ማጭበርበር በመፈጸሙ ብቻ የስንብት እርምጃ መውሰድ ተገቢ አይደለም፡፡ ህጉ ማታለል ወይም ማጭበርበር ሲኖር የሥራ ውል የሚቋረጥባቸውን ሁኔታዎች በግልጽ ያስቀመጠ እንደመሆኑ በቅድሚያ ሁኔታዎቹ ተሟልተው ሊገኙ ይገባል፡፡
በአዋጁ አንቀጽ 27(1) ሐ እንደተመለከተው በሥራው ላይ የማታለል ወይም የማጭበርበር ተግባር መፈጸም የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ ለማቋረጥ አንደኛው በቂ ምክንያት ነው፡፡
4/ በአሠሪው ንብረት ወይም ገንዘብ አላአግባብ መጠቀም
ሠራተኛው ለሥራው የተሰጡትን መሣሪዎችና ዕቃዎች ሁሉ በጥንቃቄ የመጠበቅ የህግ ግዴታ ተጥሎበታል፡፡ ስለሆነም ጥሬ ገንዘብን ጨምሮ ሥራውን እንዲያከናውን የሚረዱት ሌሎች ከአሠሪው የተረከባቸውን ንብረቶች በራሱ ወይም በሌላ ሰው ጉዳት እንዳይደርስባቸው ብሎም ለብክነትና ለብልሽት እንዳይዳረጉ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እና ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ ለሚሰራው ሥራ ዓላማ ካልሆነ በስተቀር የግሉን ወይም የሌላ 3ኛ ወገን ብልጽግና በመሻት ሊጠቀምባቸው አይገባም፡፡ ግዴታው የታማኝነቱ ቁልፍ መገለጫ ነው፡፡ የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት በመተማመን ላይ የተመሰረተ እንደመሆኑ በማናቸውም የአሠሪውን ጥቅም በሚመለከቱ ጉዳዮች ሠራተኛው ሁልጊዜ ታማኝ ሆኖ መገኘት አለበት፡፡
በመሆኑም በአዋጁ አንቀጽ 27(1) ሐ መሠረት በአሠሪው ንብረት ወይም ገንዘብ አላአግባብ መጠቀም የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ ለማቋረጥ በቂ ምክንያት ነው፡፡
5/ ጠብ አጫሪነት ወይም አምባጓሮ
በሥራ ቦታ ላይ የሚከሰት ጠብ እና አምባጓሮ ሰላማዊ የሥራ አካባቢን የሚያውክና ስርዓት አልበኝነትን የሚያነግስ በመሆኑ በአጭሩ ካልተቀጨ የአሠሪውን ምርታማነት በእጅጉ ይጎዳል፡፡ አንድ ሠራተኛ ተመድቦ የሚሰራበት ሥራ ከሌላ ሠራተኛ ሥራ ጋር በእጅጉ የተሳሰረ ነው፡፡ ጠብና አምባጓሮ ሲፈጠር ሥራ በቅንጅትና በመግባባት አይሰራም፡፡ ከአሠሪው ድርጅት ምርትና አገልግሎት የሚፈልጉ ደንበኞችም ያርቃል፡፡ የአንቀጽ 27(1) ረ አይነተኛ አላማ በሥራ ቦታ ሰላም እንዲሰፍን በማድረግ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ነው፡፡ በመሆኑም በአዋጁ አንቀጽ 27(1) ረ መሠረት በስራ ቦታ ጠብ አጫሪ መሆን ወይም አምባጓሮ መፍጠር የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ ለማቋረጥ በቂ ምክንያት ነው፡፡
6/ በአሠሪው ንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ
በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ አንቀጽ 27(1) ሸ አነጋገር ሠራተኛው ከሥራ የሚሰናበተው ሆነ ብሎ ወይም በከባድ ቸልተኝነት ጉዳት ሲያደርስና ጉዳቱም የደረሰው በአሠሪው ንብረት ወይም ከድርጅቱ ሥራ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ባለው ማናቸውም ንብረት ላይ መሆኑ ሲረጋገጥ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር አራት የጥፋቱ ማቋቋሚያዎች አንድ ላይ ተሟልተው መገኘት እንዳለባቸው እንረዳለን፡፡ ይኸውም፤
#አንደኛ ጉዳት ደረሰበት የተባለው ነገር “ንብረት” መሆን አለበት፡፡ በሌላ አነጋገር ህጉ ለንብረት የሰጠውን ፍቺ ማሟላት ይኖርበታል፡፡
#ሁለተኛ ንብረቱ የአሠሪው ወይም ከድርጅቱ ሥራ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ያለው ንብረት ሊሆን ይገባል፡፡
#ሶስተኛ አሠሪው በንብረቱ ወይም ከድርጅቱ ሥራ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ባለው ንብረት ላይ የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩ ብሎም በጉዳቱና በድርጊቱ መካከል የምክንያትና ውጤት ግንኙነት ስለመኖሩ ማስረዳት ይኖርበታል፡፡ የምክንያትና ውጤት ግንኙነት ሲባል ሠራተኛው ማድረግ የሌለበትን በማድረጉ ወይም ማድረግ ያለበትን ባለማድረጉ ምክንያት ጉዳት መከሰቱን ለማመልከት ነው፡፡
#አራተኛ ሠራተኛው ጉዳቱን ያደረሰው ሆነ ብሎ ወይም በከባድ ቸልተኝነት ስለመሆኑ መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡
በመሆኑም በአዋጁ አንቀጽ 27(1) ሸ መሠረት በአሠሪው ንብረት ወይም ከድርጅቱ
ሥራ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ባለው ማናቸውም ንብረት ላይ ሆነ ብሎ ወይም በከባድ ቸልተኝነት ጉዳት ማድረስ የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ ለማቋረጥ በቂ ምክንያት ነው፡፡
7/ የወንጀል ጥፋተኝነትና እስራት
የወንጀል ጥፋተኝነት የሥራ ውልን ለማቋረጥ በራሱ በቂ ምክንያት ባይሆንም በውጤቱ ሠራተኛውን ለያዘው ሥራ ብቁ የማያደርገው ከሆነ [አንቀጽ 27(1) ሰ] ወይም የእስራቱ ጊዜ ከሰላሳ ቀን ከበለጠ [አንቀጽ 27(1) በ] ህጋዊ የስራ ውል ማቋረጫ ምክንያት ይሆናል፡፡ በአንቀጽ 27(1) ሰ ከጥፋተኝነት ባለፈ የእስራት ፍርድ እንዲኖር የግድ አይልም፡፡ ሠራተኛው ቅጣቱ ቢገደብለትም ብሎም በገንዘብ መቀጮ ብቻ ቢቀጣም ጥፋተኛ የተባለበት ወንጀል ብቃቱን የሚያሳጣው ከሆነ ከአሠሪው ጋር ያለው ግንኙነት ይቋረጣል፡፡
8/ የሥራ ውጤት መቀነስ (መለገም)
ሠራተኛው መውጫና መግቢያ ሰዓት አክብሮ በሥራ ቦታ መገኘቱ ብቻውን የመስራት ግዴታውን እየተወጣ ነው አያስብልም፡፡ ግዴታውን ሲወጣ መላ ጉልበቱን፤ ችሎታውንና ዕውቀቱን በመጠቀም የተመደበበትን ሥራ ጥንካሬና ትጋት በተሞላበት መልኩ በማከናወን ውጤት ማምጣት አለበት፡፡ በዳተኝነት፤ ልግመኝነትና ንዝህላልነት ሥራን መበደል ካለማስጠንቀቂያ የሚያሰናብት ጥፋት ነው፡፡ የሥራ ችሎታ መቀነስ በአንቀጽ 28(1) ሀ በማስጠንቀቂያ የሥራ ውልን የሚያቋርጥ በቂ ምክንያት ሲሆን ይህም ተፈጥሯዊ በሆነ ምክንያት ሊከሰት ስለሚችል በአንቀጽ 27(1) ሠ ጥፋት ከሆነው የሥራ ውጤት መቀነስ እንዲለይ ተደርጓል፡፡ አንቀጽ 27(1) ሠ ተፈጻሚ የሚሆነው ሠራተኛው የመስራት ችሎታውና ብቃቱ እያለው ሆነ ብሎ ወይም በቸልተኝነት ከሚጠበቅበት በታች በመስራት ሥራ ሲበድል ማለትም ሲያለግም ነው፡፡
የሕግ አማካሪና ጠበቃ ሳሙኤል ግርማ
https://t.me/YehigGuday