አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.83K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ማስጠንቀቂያ :- 1ሚሊየን ብር ሊቀጡ ይችላሉ

አለማወቅ ከቅጣት አያድንም

👉 በባህሪው አደገኛ የሆነ ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ በወንዝ ዳርቻ ያሰወገደ ድርጅት አንድ ሚሊዮን ብር ይቀጣል፣

👉 ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ ወንዝ ላይ የጣለ ግለሰብ 500 ሺህ ብር ይቀጣል

👉 ፍቃድ የወሰዱም ሆነ ሳይወስዱ ፍሳሽን ቀጥታ በወንዞች ዳርቻ ሲያስወግዱ ቢገኙ 100 ሺህ ብር ይቀጣሉ፣

👉 በወንዝ ዳርቻና አካባቢ መጸዳዳት ሁለት ሺህ፤

👉 የፈሳሽ ማጣሪያ ሳይኖር በወንዝ ዳርቻና አካባቢ ተሽከርካሪ ማጠብ 400ሺህ ብር፤

👉 እንስሳትን ማሰማራት፣ ማስገባት ከተፈቀደው ውጪ ተሽከርካሪ ማሽከርከር 30 ሺህ ብር

👉 ለመዝናኛ፣ ለመናፈሻና ለፖርክ ከተፈቀደ ውጪ ግንባታ መገንባት 200 ሺህ ብር፤

👉 ከአምራችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ማንኛውም ያልታከመ ቆሻሻ መልቀቅ 300 ሺህ ብር ያስቀጣል፣

👉 ኬሚካል ነክ ቆሻሻዎችን የማከሚያ ዘዴ ሳይጠቀም የለቀቀ ግለሰብ 50 ሺህ፤ ድርጅት 300 ሺህ ብር ይቀጣሉ፣

👉 ማንኛውም በካይ ቆሻሻ ከተፈቀደ የፈሳሽ ማጠራቀሚያ ውጪ ያፈሰስ ግለስብ 50 ሺህ ድረጅት 400 ሺህ ብር፤

👉 የአትክልትና ፍራፍሬ ተረፈ ምርቶችን በወንዝ ዳርቻ ማስወገድ ግለሰብ 20 ሺህ፣ ድርጅት 100 ሺህ፤

👉 ዘይት፣ ጨዋማ ፈሳሽ፣የሞተር ዘይት፣ ነዳጅ ሳሙና ነክ ነገሮችን በወንዝ ዳርቻ ያስወገደ 400 ሺህ ብር ይቀጣል፣

👉 ማንኛውም ያልተጣራ ቆሻሻ ወደ ወንዝ መልቀቅ ግለሰብ 150 ሺህ ድርጀት 300 ሺህ ይቀጣል፣

👉 ፍቃድ ሳይሰጠው ያልታከመ ቆሻሻን ወደ ወንዝ ያስወገደ ግለሰብ 15 ሺህ ብር ድርጅት 40 ሺህ ብር ይቀጣል፣
የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
በአራት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ ተጥሎ የነበረው እገዳ ተነሳ
****
የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል እና የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤን ጨምሮ በአራት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ ተጥሎ የነበረው እገዳ ከዛሬ የካቲት 24 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ መነሳቱን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ።

ኮሚሽኑ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፤ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን በኅዳር ወር 2017 ዓ.ም. የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል፣ የሕግ ባለሙያዎች ለሰብአዊ መብቶች እና ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ የተባሉ ሶስት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ ጥሎት የነበረውን እገዳ ካነሳ በኋላ በታኅሣሥ ወር 2017 ዓ.ም. የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል እና የሕግ ባለሙያዎች ለሰብአዊ መብቶችን በድጋሚ እንዲሁም የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ እና የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማእከልን ማገዱ ይታወሳል ብሏል።

ኢሰመኮ በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ የሚተላለፉ እገዳዎች በሲቪል ምኅዳሩ እና በማኅበር የመደራጀት መብቶች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንዳይፈጥሩ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ ታኅሣሥ 18 ቀን 2017 ዓ.ም. በወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ ማሳሰቡንም አስታውሷል።

በተጨማሪም ኢሰመኮ በድርጅቶቹ እገዳ ላይ ሰፊ የሰብአዊ መብቶች ምርመራ ማከናወኑና በተለይም አዲስ በተሾሙት ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ በኩል ጉዳዩን በልዩ ትኩረት በመከታተል ለጉዳዩ መፍትሔ ለማስገኘት ሢሠራ ቆይቷል ብሏል መግለጫው።
#ShegerTimesMedia
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
#Alehig #አለሕግ AleHig is currently in Nairobi, Kenya💎. Our local phone has not been working for a week, but you can reach us via WhatsApp +251920666595.
#africa #attorney #lawyerlife
East Africa Law Society
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
" በስም ከተለዩት ግለሰቦች መካከል ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ዜጎችም ይገኙበታል " -የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ

የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ከ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ ዕዳ ያለባቸው 62 ግብር ከፋዮች ከሀገር እንዳይወጡ የእግድ ትዕዛዝ ማስተላለፉን ገልጿል፡፡

እግድ የተጣለባቸው 62 ግለሰቦች በተደጋጋሚ ጥሪ ቢደረግላቸውም ዕዳቸውን ለመክፈል  ፈቃደኛ ያልሆኑ ናቸው ተብሏል።

" በስም ከተለዩት ግለሰቦች መካከል ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ዜጎችም ይገኙበታል ዕዳቸውን የማይከፍሉ ከሆነም አዋጁ በሰጠን ሥልጣን መሰረትም በቀጣይ የንብረት እግድ እና ንብረታቸውን በሃራጅ የመሸጥ እርምጃዎች ይወሰዳሉ " ሲሉ የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቢሮው በታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008 አንቀፅ 44 ንዑስ አንቀፅ ከ1-3 ለተቋሙ በተሰጠ ስልጣን መሰረት ከሀገር እንዳይወጡ እግድ የተጣለባቸው ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለፌዴራል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ማስተላለፉን አሳውቋል፡፡

የ62ቱ ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለፌዴራል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የተላከው በትላንትናው ዕለት ነው።

አቶ ሰውነት " በህጉ መሰረት የተቀመጠ ቀነ ገደብ አለ በአዋጁ በተቀመጠው ቀነ ገደብ መሰረት መጥተው እስካልከፈሉ ድረስ ለእዳው ማካካሻ በሚሆን መሰረት ንብረታቸው በሃራጅ ተሽጦ እዳው ይሸፈናል " ብለዋል።

ቢሮው የግብር ዕዳቸውን ሳይወጡ የሚሰወሩ ግብር ከፋዮችን በመከታተል ግዴታቸውን እንዲወጡ ለማስቻል የዕዳ ክትትልና አስተዳደር የስራ ክፍልን በ2017 በጀት ዓመት እንደ አዲስ አዋቅሯል።

በዚህም መሰረት ባለፉት 6 ወራት ከ 6.4 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ እዳ መሰብሰቡን አቶ ሰውነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA
#tikvahethiopia
Welcome to Mikias Melak & Associates Law Office!

🔹 Facebook: AlehigOfficial
🔹 Telegram Channel: AleHig
🔹 Website: alehig.com
📧 Email: mikiasmelak.mm@gmail.com

📞 Direct Contact:
WhatsApp: +251920666595
Telegram: @MikiasMelak

For legal consultations and inquiries, feel free to reach out. We’ll get back to you as soon as possible!
ባልና ሚስት በጋብቻቸው ውስጥ ያፈሩትን ንብረት የመካፈል መብታቸው '#ዘላለማዊ' ነው::
[በእርግጥ በቤተሰብ ሕጉ የባልና ሚስት የጋራ ንብረት ክፍፍል ጥያቄ  ማቅረቢያ የጊዜ ገደብ በግልጽ አልተደነገገም:: እንደሚታወቀው እንዲህ ዓይነት ሁኔታ ባጋጠመ ጊዜ ማለትም አንድ ሕግ ስለ አንድ መብት/ግዴታ መጠየቂያ (ክስ ማቅረቢያ) የጊዜ ገደብ በግልጽ ባልደነገገ ጊዜ ክፍተቱን ለመሙላት በፍ/ሕ 1676(1) እና 1845 የተመለከተው የ10 ዓመት የይርጋ ጊዜ ተግባራዊ ይደረጋል::]

ይሁንና የባልና ሚስት የንብረት ክፍፍልን አስመልክቶ በቤተሰብ ሕጉ የተፈጠረውን የይርጋ ጊዜ ክፍተት ከፍ/ሕ/ቁ. 1676(1) እና 1845 አኳያ ተርጉሞ በመሙላት "በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ንብረት የክፍፍል ጥያቄ ጋብቻው ከፈረሰበት ቀን ጀምሮ በ10 ዓመት ውስጥ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል" የሚል ትርጉም መስጠት 'የተፋቾችን' ሕገ መንግሥታዊ የንብረት መብት የሚጥስ ስለሆነ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 40(1፣ 7)፣ 50(5)፣ 55፣ 79(1)፣ እና 9(1) መሠረት ተፈጻሚነት የለውም::"👴🏽

↪️ፌደሬሽን ም/ቤት መ/ቁ. 77/12
↪️ሰኔ 3/2012 ዓ.ም.)
በሀገር ውስጥ የሚመረቱ የመድኃኒቶች ጥራትና ደህንነትን ለማረጋገጥ ያግዛል የተባለዉ አዲስ መመሪያ ወጣ

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን በሀገር ውስጥ የሚመረቱ የመድኃኒቶች ጥራትና ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚያግዝ አዲስ መመሪያ አውጥቷል።

"የባዮኤክቫለንስ ጥናት ማዕከል እና የባዮአናሊቲካል ላብራቶሪ ቁጥጥር መመሪያ ቁጥር 1043/2017" ተብሎ የሚጠራው ይህ መመሪያ፣ በገበያ ላይ የሚውሉ የመድኃኒት ምርቶች ተመሳሳይ የፈዋሽነት እና የደህንነት ደረጃዎችን ማሟላታቸውን ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።

በተለይም በጽንስ ስም የሚመረቱ መድኃኒቶች ከታወቁ የመድኃኒት ምርቶች ጋር ተመሳሳይ የሆነ የፈዋሽነት እና የደህንነት ደረጃ እንዲኖራቸው ለማድረግ ያለመ ነው።

ይህ መመሪያ "ባዮኢኩዊቫለንስ" የተሰኘ ልዩ ጥናት በማድረግ በጽንስ ስም የሚመረቱ መድኃኒቶች ከታወቁ የመድኃኒት ምርቶች ጋር ያላቸውን ተመሳሳይነት ማረጋገጥ እንደሚጠበቅባቸው ይደነግጋል።

በተጨማሪም፣ መመሪያው የመድኃኒት
ማምረቻ ተቋማትና ላቦራቶሪዎች ፈቃድና ቁጥጥር ላይ እንደሚያተኩር ካፒታል ለመረዳት ችሏል።

መመሪያው በኢትዮጵያ የመድኃኒት ቁጥጥር ላይ ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን፣ ለመድኃኒት ኢንዱስትሪው ዕድገት አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ይጠበቃል። በተጨማሪም፣ ለሕዝብ ተደራሽና ጥራት ያላቸውን መድኃኒቶች ለማቅረብ ያለመ ነው ተብሏል።

Source: capitalethiopia
#Ethiopianbusinessdaily
ጋብቻ ከፈረሰ በኃላ (የንብረት ክፍፍል ከመደረጉ በፊት) የጋራ ንብረት የሆነን የማይንቀሳቀስ ንብረት (ቤት) አንደኛው ወገን ያለሌላኛው ፈቃድ በሽያጭ ያስተላለፉት ከሆነ የቤተሰብ ሕጉ አንቀጽ 69 (1) “ም” ሆነ (2) ድንጋጌዎች ለክርክሩ ተፈጻሚነት ሊኖራቸው የሚችልበት አግባብ አይኖርም፡፡ አግባብነት ያለው የጋራ ንብረትን ለማስተላለፍ የጋራ ባለሀብትን ፈቃድ የሚያስፈልግ ስለመሆኑ በፍ/ሕ/ቁ.1266 የተመለከተው ድንጋጌ ነው።

የቤተሰብ ሕጉ አንቀጽ 69 የሚገኘው በቤተሰብ ሕጉ የጋብቻ ውጤትን በሚመለከተው ምዕራፍ ሦስት ክፍል ሦስት ስር ሲሆን ይህ ክፍልም ጋብቻው ጸንቶ በሚገኝበት ጊዜ በንብረት በኩል የሚያስከትለውን ሕጋዊ ውጤት የሚገዛ ነው፡፡

ዳሩ ግን፣ አንደኛው ወገን ቤቱን በሽያጭ ያስተላለፉት ጋብቻው ከፈረሰ በኃላ (የንብረት ክፍፍል ክፍፍል ከመደረጉ በፊት) ከሆነ ለጉዳዩ ተፈጻሚነት የሚኖረው የጋራ ባለሀብትነትን የሚመለከተው የፍ/ብ/ሕጉ ድንጋጌ ነው።

ይህ ከሆነ ደግሞ፣ አንደኛው ወገን በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ነው የሚለው ንብረት ላይ የተፈጸመው የሽያጭ ውል እንዲፈርስ ክስ ለማቅረብ የሚችለው በምን ያህል ጊዜ ውስጥ እንደሆነ በቤተሰብ ሕጉ ውስጥ በተለይ የተመለከተ ድንጋጌ ባለመኖሩ በዚህ ዓይነት ጉዳዮች ላይ ተፈጸሚነት ሊኖረው የሚገባው በፍ/ብ/ሕ/ቁ.1677(1) ድንጋጌ መሰረት በፍ/ብ/ሕ/ቁ.1845 ድንጋጌ የተመለከተው አጠቃላይ የአስር ዓመት የይርጋ ጊዜ ነው፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ሚያዝያ 12 ቀን 2007 ዓ.ም በሰ/መ/ቁጥር 95338 የሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጉም
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#We are hiring!
Nisir Law Firm wants to hire Advocate's Assistant.

Sex: Female
Qualification:
- obtained LL.B from a recognized university.
- good communication, writing and computer  skill.
- Apart from the Amharic language, having the skill of other languages is a plus.
Salary: by negotiation
Place of work: Around Kirkos Division FFIC, Addis Ababa.
Those of you who fulfill the requirements please send your cover letter and CV via telegram
@SileshiMequanint
የፈተና ውጤት ስለማሳወቅ
የማናቸውም ፍርድ ቤት የጥብቅና ፍቃድ ለማውጣት ታህሳስ 12 ቀን 2017ዓ.ም ፈተና ለወሰዳችሁ በሙሉ ከዚህ በታች ባለው ሰንጠረዥ ውጤታችሁ የተገለጸ ሲሆን ማለፊያ ውጤቱ ከመቶ ሀምሳ መሆኑን እንድታውቁ እና የፈተናው ውጤት ላይ ቅሬታ የሚኖራችሁ ከሆነ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉ 10 የስራ ቀናት ውስጥ ብቻ ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
ጥልቅ የሕግ ትንታኔ እና አመክንዮ የተሰጠበትን የፌዴራሉ ጠቅላይፍርድ ቤት 1ኛ ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ.መ.ቁ 258350 የካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም የሰጠውን ውሳኔ

ሰበር ሰሚ ችሎቱ ዉሳኔ የሰጠበት ጉዳይ በአንድ ሀላፊነቱ የተወሰነ የንግድ ማህበር አባላት መካከል ብርቱ አለመግባባት ተከስቷል በሚል ማህበሩ እንዲፈርስ የቀረበን ክስ የሚመለከት ነው፡፡ 16 ገጾች ካሉት የሰበር ሰሚው ችሎት ውሳኔ ውስጥ 1ዐ ሩ ገጽ የሕግ ትንታኔ እና አመክንዮ የያዘ ነው፡፡ ውሳኔው የአገሪቱን ሕጎች: የአገር ውስጥ እና የውጪ ሐገር የሕግ ትንታኔ ጽሑፎችን: የሕግ መዝገበ ቃላቶችን እና የሐገራችን ምሁራን እና የሕግ ባለሞያዎች ጽሑፍችን በማጣቀሻነት ተጠቅሟል፡፡
በመጨረሻም ሰበር ሰሚ ችሎቱ ተፈጠረ የተባለው አለመግባባት ብርቱ ካለመሆኑ በተጨማሪ የማሕበሩ ዓላማ ከግብ እንዳይደርስ ሊያስተጓጉል የሚችል አለመሆኑ የተረጋገጠ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በንግድ ሕጉ አንቀጽ 181/6 አነጋገር መሠረት በአባላቱ መካከል የማሕበሩን ዓላማ ከግብ ለማድረስ የማያስችል ብርቱ አለመግባባት ቢፈጠር እንኳን በቀሪ አባላት ማሕበሩ ዓላማውን ማሳካት የሚችልበት ሁኔታ ያለ እንደሆነ የተወሰኑት የማህበሩ አባላት ድርሻቸውን ይዘው ከማህበሩ እንዲወጡ ይደረጋል እንጂ ማህበሩ እንዲፈርስ መወሰን አይቻልም ከሚል መደምደሚያ ላይ ደርሷል፡፡ ሙሉውን የውሳኔውን ይዘት ከፍርድ ቤቱ ድሕረገጽ ማግኘት ይቻላል፡፡
በእትመት አሰፋ
#ፌዴራልጠቅላይፍርድቤት
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM