አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.84K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
#የቤት_ኪራይ ውል ጊዜው ከተጠናቀቀ በኋላ ተከራይ ቤቱን ለቆ እንዲያስረክበው ለቆ የማያስረክብ ከሆነ ግን የኪራይ ተመኑ በማስጠንቀቂያው ላይ በተመለከተው ተመን እንደሚሆን በመግለጽ አከራይ ማስጠንቀቂያ ሰጥቶት ተከራዩ ቤቱን ለቆ ካላስረከበ ተከራይ በኪራይ በቤቱ መገልገሉን እንዲቀጥል አከራዩ አለመፍቀዱን በማያሻማ ሁኔታ የሚያሳይ ቢሆንም ተከራይ ሊከፍል የሚገባውን የኪራይ ተመን በተመለከተ ውሉ ላለመራዘሙ ዋናው ምክንያት የኪራይ ተመን አለመግባባት ከሆነና ተከራይ የኪራይ ተመን መጨመርን በግልጽ ከተቃወመ ሊከፍል የሚገባው በማስጠንቀቂያው ላይ በተገለጸው የኪራይ ተመን ሳይሆን በቀድሞው ተመን ነው።
በዚህ መዝገብ ተከራይ ቤቱን ለ4 ዓመታት ተከራይቶ የውሉ ዘመን ሲያልቅ ቤቱን ለቆ እንዲያስረክብ የማያስረክብ ከሆነ የኪራይ ተመኑ ብር 80,000 እንደሚሆን በመግለጽ ማስጠንቀቂያ ቢሰጠውም ሊከፍል የሚገባው በ 20,000 ነው በሚል በሰበር ችሎቱ ውሳኔ ተሰጥቷል።
ሰ/መ/ቁ. 220884 ቀን ጥቅምት 04 ቀን 2015 ዓ/ም
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1234/13
አዋጁ የፍርድ ቤት ውሣኔዎችንና ትዕዛዞችን ስለ መፈጸም እና ይህንኑ ትእዛዝ አለመፈጸም የሚያስከትለውን የወንጀል ቅጣት ያስቀመጠ ሲሆን ይህም በአዋጁ አንቀጸ 51 ላይ የፍርድ ቤት ውሣኔዎችንና ትዕዛዞችን በተመለከተ፤በማንኛውም የፌዴራል ፍርድ ቤት የተሰጠ ውሳኔ እና ትዕዛዝ በህግ እስካልተለወጠ ድረስ የፀና ሆኖ ተፈፃሚ መሆን እንደለበት፤የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የሚሰጧቸዉን ዉሳኔዎች ወይም ትዕዛዞች በሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች ዉስጥ ተፈጸጻሚ እንደሚሆኑ፤በማንኛዉም ክልል ዉስጥ የሚገኝ የመንግስት አካል፣ ተቋም ወይም መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ወይም ማንኛዉም ሰው ውሳኔዎቹን ወይም ትዕዛዞቹን የመፈጸም እና የማስፈጸም ግዴታ እንዳለበት እና ማንኛዉም ሰዉ የፍርድ ቤት ውሣኔዎችንና ትዕዛዞችን የማይወጣ ከሆነ የወንጀል ተጠያቂነት እንዳለበት ይደነግጋል፡፡ አዋጁ በአንቀጽ 52 ስር የወንጀል ተጠያቂነት ያስቀመጠ ሲሆን ይህም፤-
 የፍርድ ቤት ወይም የዳኞችን በነጻነት መስራት የሚጋፋ ወይም በዳኞች ላይ ተጽእኖ የሚያደርግ ወይም ለማድረግ የሞከረ ማንኛውም ሰዉ በሌላ ህግ ከፍ ያለ ቅጣት ከሌለ በቀር ከሦስት ወር እሥራት ባላነሰ ከሁለት ዓመት ባልበለጠ ጽኑ እስራት እንደሚቀጠ እንዲሁም፤
 የፍርድ ቤትን ትዕዛዝ ወይም ዉሳኔ የማይፈጽም ወይም ለመፈፀም መሰናክል የሚፈጥር ወይም ሲጠየቅ ለመፈፀም ተባባሪ የማይሆን ማንኛዉም ሰዉ በሌላ ህግ ከፍ ያለ ቅጣት ከሌለ በቀር ከሁለት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት ወይም ከአምስት ሺህ ብር በማይበልጥ ገንዘብ እንደሚቀጣ ይደነግጋል፡፡

ፍርድ ቤት ሰዎች ሕግን መከታ አድርገው መብታቸውን የሚያስከብሩበት እንደመሆኑ የፍርድ ቤቱን ክብር መጠበቅ የፍትሕ ሥርዓቱን ሕልውና ለመጠበቅ ፤እንዲሁም ኅብረተሰቡ በዳኝነት አካሉ ላይ ያለውን መተማመን ለመጠበቅ ፍርድ ቤትን ማክበር ወሳኝ ነው፡፡
በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና የተዘጋጀ
ፍትህ ሚኒስቴር
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ግብር የማስከፈያ ምጣኔዎች

በፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 979/2008 መሰረት ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ግብር የማስከፈያ ምጣኔዎች እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የሚከተሉትን ይላል፡-

• ከግብር ነፃ ከሆነው በስተቀር ቀጣሪው ለተቀጣሪው በሚከፍለው ማንኛውም የገንዘብ መጠን ላይ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ግብር ይከፈልበታል፡፡
• ቀጣሪ ማለት ተቀጣሪን የቀጠረ ወይም ለተቀጣሪው ደመወዝ የሚከፍል ሰው ነው፡፡
• ተቀጣሪ ማለት ደግሞ ራሱን ችሎ የሚሰራን የስራ ተቋራጭ ሳይጨምር በሌላ ሰው /በቀጣሪው/ መሪነትና ቁጥጥር ስር ሆኖ አገልግሎት ለመስጠት በቋሚነት ወይም በጊዜያዊነት የተቀጠረ ግለሰብ ሲሆን የድርጅት ዳይሬክተር፣ ወይም በድርጅቱ አመራር ውስጥ ኃላፊነት የተሰጠውን ሌላ ሰው እንዲሁም ተሿሚንና የህዝብ ተመራጭን ጨምሮ የመንግስት ስራ ኃላፊን ያጠቃልላል፡፡
የጋራ ንብረት ምንነትና አስተዳደር
የጋራ ንብረትን በተመለከተ የጋራ ንብረት የሚባለው ባልና ሚስት ከተጋቡ በኋላ በግብይት የሚያገኟቸው ንብረቶች፣ ባልና ሚስት በግል ጥረታቸው የሚገኝ ገቢ፣ ከግል እና ከጋራ ንብረታቸው የሚገኟቸው ገቢዎች ሁሉ ናቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በስጦታ ወይም በኑዛዜ በጋራ የተሰጧቸው ንብረቶች የጋራ ንብረቶች ናቸው፡፡ እዚህ ላይ መታወቅ ያለበት አንደኛው ተጋቢ የግል ሀብቱ መሆኑን ካላስረዳ በስተቀር በአንደኛው ተጋቢ ስም የተመዘገበ ሀብትም ቢሆን እንኳን የተጋቢዎች የጋራ ሀብት እንደሆነ የህግ ግምት የሚወሰድበት መሆኑ ነው፡፡
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
18 ሺሕ 576 እግረኞች ተቀጡ! ልብ በሉ እግረኞች?
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ስድስት ወራት 18 ሺህ 576 የትራፊክ ደንብ የተላለፉ እግረኞች መቀጣታቸውን የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን አስታወቀ።

ከእነዚህ ውስጥ 7 ሺ 497 እግረኞች በገንዘብ ሲቀጡ 11 ሺ 79 ያህል ደንብ የተላለፉ እግረኞች ደግሞ በማህበራዊ አገልግሎት መቀጣታቸው ተሰምቷል።

ከቅጣት የተሰበሰበ ከ450 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ለመንግስት ገቢ መደረጉም ተገልጿል።

በከተማዋ በተመረጡ እና የእግረኛ መሰረተ ልማት በተሟሉባቸው 22 ቦታዎች የትራፊክ ቁጥጥር መደረጉን የትራፊክ ቁጥጥር እና ትራፊክ አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ አያሌው ኢቲሳ ለሀገሬ ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

ተግባራዊ የተደረገው የቅጣት አሰራር አሁን ላይ በእግረኞች ላይ እየደረሰ ያለውን የትራፊክ አደጋ ከመቀነስ አንጻር ለውጥ ማምጣቱን ገልጸዋል።

በከተማዋ ከሚደርሰው የትራፊክ አደጋ ውስጥ 80 በመቶ የሚሆነው በእግረኞች ላይ የሚደርስ መሆኑን በጥናት መረጋገጡን አክለዋል።
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
112_2008_አንቀጽ_21_ንዑስ_አንቀጽ_3_ማሻሻያ.pdf
1.2 MB
ከጉምሩክ አሠራር ጋር በሚያጋጥሙ ጥፋቶች ላይ የሚወሰዱ አስተዳደራዊ እርምጃዎች ወጥነት ባለው ሁኔታ በሁሉም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እንዲስተናገዱ መመሪያ ቁጥር 112/2008 ተደንግጓል ፡፡ ስለሆነም እነዚህን ጥፋቶች ላለመስረት ቅደመ ጥንቃቄ ማድረግ እንደተጠበቀ ሆኖ ተከስተው ከተገኙ ደግሞ በመመሪያው መሰረት መስተናገድ ይገባል፡፡ በመመሪያውም በአዋጅ ቁጥር 859/2006 (እንደተሸሻለ 1160/2011) እንደተጠበቀ ሆኖ አስተዳደራዊ ቅጣት የሚያስከትሉ ጥፋቶች እና አስተዳደራዊ እርምጃዎች ተዘርዝረዋል፡-
በወጪ እና ገቢ ዕቃዎች ላይ የተጣለ ገደብን አለማክበር
ቀረጥና ታክስ እንዳይከፈል ወይም አሳንሶ እንዲከፈል ማድረግ
ያለ ጉምሩክ ዕውቅና እሽጎችን መፍታትና ምልክቶችን ማንሳት
ናሙናዎችን አለመመለስ
ያጓጓዥ ግዴታዎችን ያለማክበር
የጉምሩክ መጋዘን ግዴታዎችን ያለማክበር
የጉምሩክ ትራንዚት ሥነ ሥርዓት አለማክበር
ከቀረጥ ነጻ የገባ ዕቃ ያለ አግባብ መገልገል
በጊዜአዊነት ወደ ሀገር የገባን ዕቃ ያለ አግባብ መገልገል
ሌሎች ጥፋቶች
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
180017-2025-02-03-67a10ad7ae7f6.pdf
992.3 KB
180/017 የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል ደንብ
በአዲስ አበባ ወደ ተግባር የገባው የወንዞች ዳርቻ ልማትና ብክለት መከላከል ደንብን መተላለፍ የሚያስከትለው ቅጣት⁉️

👉 በባህሪው አደጋኝነት የሆነ ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ በወንዝ ዳርቻ ያሰወገደ ድርጅት አንድ ሚሊዮን ብር ይቀጣል፣

👉 ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ ወንዝ ላይ የጣለ ግለሰብ 500 ሺህ ብር ይቀጣል

👉 ፍቃድ የወሰዱም ሆነ ሳይወስዱ ፍሳሽን ቀጥታ በወንዞች ዳርቻ ሲያስወግዱ ቢገኙ 100 ሺህ ብር ይቀጣሉ፣

👉 በወንዝ ዳርቻና አካባቢ መጸዳዳት ሁለት ሺህ፤

👉 የፈሳሽ ማጣሪያ ሳይኖር በወንዝ ዳርቻና አካባቢ ተሽከርካሪ ማጠብ 400ሺህ ብር፤

👉 እንስሳትን ማሰማራት፣ ማስገባት ከተፈቀደው ውጪ ተሽከርካሪ ማሽከርከር 30 ሺህ ብር

👉 ለመዝናኛ፣ ለመናፈሻና ለፖርክ ከተፈቀደ ውጪ ግንባታ መገንባት 200 ሺህ ብር፤

👉 ከአምራችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ማንኛውም ያልታከመ ቆሻሻ መልቀቅ 300 ሺህ ብር ያስቀጣል፣

👉 ኬሚካል ነክ ቆሻሻዎችን የማከሚያ ዘዴ ሳይጠቀም የለቀቀ ግለሰብ 50 ሺህ፤ ድርጅት 300 ሺህ ብር ይቀጣሉ፣

👉 ማንኛውም በካይ ቆሻሻ ከተፈቀደ የፈሳሽ ማጠራቀሚያ ውጪ ያፈሰስ ግለስብ 50 ሺህ ድረጅት 400 ሺህ ብር፤

👉 የአትክልትና ፍራፍሬ ተረፈ ምርቶችን በወንዝ ዳርቻ ማስወገድ ግለሰብ 20 ሺህ፣ ድርጅት 100 ሺህ፤

👉 ዘይት፣ ጨዋማ ፈሳሽ፣የሞተር ዘይት፣ ነዳጅ ሳሙና ነክ ነገሮችን በወንዝ ዳርቻ ያስወገደ 400 ሺህ ብር ይቀጣል፣

👉 ማንኛውም ያልተጣራ ቆሻሻ ወደ ወንዝ መልቀቅ ግለሰብ 150 ሺህ ድርጀት 300 ሺህ ይቀጣል፣

ፍቃድ ሳይሰጠው ያልታከመ ቆሻሻን ወደ ወንዝ ያስወገደ ግለሰብ 15 ሺህ ብር ድርጅት 40 ሺህ ብር ይቀጣል፣

በታደሠ ብናልፈው

የካቲት 21 ቀን 2017 ዓም
ደንብ_ቁጥር_178_2016_በሆቴልና_መሰል_አገልግሎት_ሰጪ_ተቋማት_ባለሙያዎች_የደንብ_ልብስ_አለባበስ.pdf
1 MB
ደንብ ቁጥር 178/2016 በሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ባለሙያዎች የደንብ ልብስ አለባበስ