የሚያስገኝ ልዩ አክስዮን ሊኖራቸዉ አይችልም፡፡ በቦርድ አባላት ምርጫ ወቅት የአነስተኛ ባለአክስዮኖች መብት ማስጠበቂያ አሰራር የድምር ድምፅ አሰራር ነዉ፡፡ ይህ ግን በሕጋችን በግልፅ የተቀመጠ ደንብ አይደለም፡፡ ነባሩ ንግድ ሕግ ቀጥር 352 ስለተመጣጣኝ ዉክልና የሚናገር ሲሆን በግልፅ የድምር ድምፅ አሰራር ግን አይደነግግም፡፡
ሌላዉ ከጠቅላላ ጉባዔዉ ዉሳኔ ጋር በተዘዋዋሪ የሚያያዘዉ እና የአነስተኛ ባለአክስዮኖች መብት ላይ ተፅዕኖ ሊፈጥር የሚችል ጉዳይ አዳዲስ አክስዮኖች ሲወጡ እያንዳንዱ አባል ባለዉ ድርሻ መጠን የመግዛት መብት ነዉ፡፡ ይህ በቁጥር 345 (4) እና በቁጥር 470(1) ላይ የተቀመጠ መርህ ነዉ፡፡ የዚህ መርህ ዓላማ በማኅበሩ ዉስጥ ያለዉን የይዞታ ስብጥር ማስጠበቅ ሲሆን ጠቃሚነቱ በማኅበሩ ዉስጥ ያለዉ የኃይል ሚዛን እንዲጠበቅ ያደርጋል፡፡
5. አነስተኛ ባለአክስዮኖች ከኦዲትና ቁጥጥር አንፃር ያላቸዉ መብቶች
ከኦዲት ሥራ ጋር የተያያዘ የአነስተኛ ባለአክስዮኖች መብቶች በአዲሱ የንግድ ሕግ ዉስጥ ተካተዋል፡፡ እነዚህም በቁጥር 343(2) እና በቁጥር 355 ላይ የተቀመጡት ድንጋጌዎች ናቸዉ፡፡ "ከማኅበሩ ዋና ገንዘብ ዉስጥ ቢያንስ 20% ያለዉ ባለአክስዮን (ባለአክስዮኖች) ራሳቸዉ የመረጡትን የውጭ ኦዲተር መሾም ይችላሉ" በማለት የአነስተኛ ባለአክስዮኖች የራሳቸዉን ኦዲተር የመሾም መብት እንዳላቸዉ ይናገራል፡፡ ይህን መብት አነስተኛ ባለአክስዮኖች ከተጠቀሙበት በማኅበሩ ዉስጥ ቢያንስ ሁለት ኦዲተሮች (በጠቅላላ ጉባዔዉ የሚሾምና በአነስተኛ ባለአክስዮኖች የሚሾም) ይኖራሉ ማለት ነዉ፡፡ ይህ ኦዲተሮች ለዳይሬክተሮች ወይም ለአብላጫ ባለአክስዮኖች በመወገን ሊፈጠሩ የሚችሉትን አደጋ ይቀርፋል ተብሎ ይታመናል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ቁጥር 355 ላይ ነፃ ኦዲተር እንዲሾም ለንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ወይም አግባብ ያለዉ ሌላ የመንግስት መስሪያ ቤት ማመልከቻ ስለማቅረብ ይናገራል፡፡ የማኅበሩ ሥራ አመራር አነስተኛ የአክስዮን ድርሻ ያላቸዉን ማኅበርተኞች ወይም ማኅበሩን በሚጎዳ አኳኋን መከናወንና አለመከናወኑን መርምረዉ ሪፖርት የሚያቀርቡ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ኤክስፐርቶች መሾም አለበት፡፡ በዚህ ድንጋጌ መሰረት ከማኅበሩ ካፒታል አስር በመቶ (10%) ያለዉ (ያላቸዉ) ባለአክስዮኖች ለንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴሩ አቤቱታ ማቅረብና ማኅበሩ ኦዲት እንዲረግ መጠየቅ ይችላሉ፡፡ እነዚህ ከኦዲት ስራ ጋር የተያያዙ የአነስተኛ ባለአክስዮኖች መብት ቀላል አይደሉም፡፡ በማኅበሩ አስተዳዳሪዎች ወይም በከፍተኛ ባለ አክስዮኖች የሚደርስባቸውን የመብት ጥሰት ለመግታት እና መብታቸውን ለማስከበር አጅግ ጠቃሚ ናቸዉ፡፡
6. አክስዮን ሸጦ የመውጣት የአነስተኛ ባለአክሲዮኖች መብት
በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 292 መሰረት የማህበሩን ዋና ገንዘብ ዘጠና በመቶ የሚወክለ አክስዮኖች በአንድ ጊዜ በማህበርተኛ የተያዙ እንደሆነ አነስተኛ ባለአክስዮኖች ማህበርተኛው አክስዮኖቻቸውን እንዲገዛቸው የመጠየቅ መብት አላቸው። ጥያቄ አቅራቢው ባአአክስዮን አክስዮኖቹ ስለሚገዙበት ሁኔታ በተለይም የአክስዮኖቹን ዋጋ የንግድ ሕግ ስለወሰነበት መንገድ መረጃ ከጥያቄው ጋር ማቅረብ አለበት። ጥያቄ የቀረበለት ማህበርተኛ የቀረበለትን ዋጋ ያልተቀበለ እንደሆነ ማህበሩ በተመዘገበበት ቦታ ሥልጣን ያለው ፍርድ ቤት የአክስዮኖቹን ዋጋ የሚወስን ባለሞያ መሾም አለበት። አክስኖቹን ለመሸጥ ጥያቄ ያቀረበው ባለአክሲዮን የአክሲዮኖቹን ዋጋ ለመወሰን የወጣውን ወጪ መሸፈን አለበት። ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ አክስዮን እንዲገዛ ጥያቄ የቀረበለት ማህበርተኛ የሰጠው ዋጋ ተማኙ ባለሞያ ከወሰነው ያነሰ እንደሆነ ወጪውን በከፊል ወይም በሙሉ እንዲሸፍን ፍርድ ቤቱ ሊያዘው ይችላል፡፡
በአጠቃላይ የአነስተኛ ባለአክሲዮኖች መብት መጠበቅ የማኅበሩን ህልውና መጠበቅ ነዉ፡፡ ይህም የማኅበሩን መልካም አስተዳደር የተሳካና የንግድ አላማውን ዉጤታማ ያደርገዋል፡፡ በዚህ የተነሳ አነስተኛ ባለአክስዮኖች ከሌሎች ከፍተኛ ድርሻ ካላቸው ባለአክስዮኖች፣ ከዳይሬክተሮች ቦርድ፣ ከጠቅላላ ጉባዔዉ እና በአዲተሮች አማካኝነት ከሚሰነዘሩ ያልተገቡ ጫናዎችና የመብት ጥሰቶች መጠበቂያ መንገዶች በአዲሱ የንግድ ሕግ ተደንግገዉ ይገኛሉ፡፡
ሌላዉ ከጠቅላላ ጉባዔዉ ዉሳኔ ጋር በተዘዋዋሪ የሚያያዘዉ እና የአነስተኛ ባለአክስዮኖች መብት ላይ ተፅዕኖ ሊፈጥር የሚችል ጉዳይ አዳዲስ አክስዮኖች ሲወጡ እያንዳንዱ አባል ባለዉ ድርሻ መጠን የመግዛት መብት ነዉ፡፡ ይህ በቁጥር 345 (4) እና በቁጥር 470(1) ላይ የተቀመጠ መርህ ነዉ፡፡ የዚህ መርህ ዓላማ በማኅበሩ ዉስጥ ያለዉን የይዞታ ስብጥር ማስጠበቅ ሲሆን ጠቃሚነቱ በማኅበሩ ዉስጥ ያለዉ የኃይል ሚዛን እንዲጠበቅ ያደርጋል፡፡
5. አነስተኛ ባለአክስዮኖች ከኦዲትና ቁጥጥር አንፃር ያላቸዉ መብቶች
ከኦዲት ሥራ ጋር የተያያዘ የአነስተኛ ባለአክስዮኖች መብቶች በአዲሱ የንግድ ሕግ ዉስጥ ተካተዋል፡፡ እነዚህም በቁጥር 343(2) እና በቁጥር 355 ላይ የተቀመጡት ድንጋጌዎች ናቸዉ፡፡ "ከማኅበሩ ዋና ገንዘብ ዉስጥ ቢያንስ 20% ያለዉ ባለአክስዮን (ባለአክስዮኖች) ራሳቸዉ የመረጡትን የውጭ ኦዲተር መሾም ይችላሉ" በማለት የአነስተኛ ባለአክስዮኖች የራሳቸዉን ኦዲተር የመሾም መብት እንዳላቸዉ ይናገራል፡፡ ይህን መብት አነስተኛ ባለአክስዮኖች ከተጠቀሙበት በማኅበሩ ዉስጥ ቢያንስ ሁለት ኦዲተሮች (በጠቅላላ ጉባዔዉ የሚሾምና በአነስተኛ ባለአክስዮኖች የሚሾም) ይኖራሉ ማለት ነዉ፡፡ ይህ ኦዲተሮች ለዳይሬክተሮች ወይም ለአብላጫ ባለአክስዮኖች በመወገን ሊፈጠሩ የሚችሉትን አደጋ ይቀርፋል ተብሎ ይታመናል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ቁጥር 355 ላይ ነፃ ኦዲተር እንዲሾም ለንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ወይም አግባብ ያለዉ ሌላ የመንግስት መስሪያ ቤት ማመልከቻ ስለማቅረብ ይናገራል፡፡ የማኅበሩ ሥራ አመራር አነስተኛ የአክስዮን ድርሻ ያላቸዉን ማኅበርተኞች ወይም ማኅበሩን በሚጎዳ አኳኋን መከናወንና አለመከናወኑን መርምረዉ ሪፖርት የሚያቀርቡ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ኤክስፐርቶች መሾም አለበት፡፡ በዚህ ድንጋጌ መሰረት ከማኅበሩ ካፒታል አስር በመቶ (10%) ያለዉ (ያላቸዉ) ባለአክስዮኖች ለንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴሩ አቤቱታ ማቅረብና ማኅበሩ ኦዲት እንዲረግ መጠየቅ ይችላሉ፡፡ እነዚህ ከኦዲት ስራ ጋር የተያያዙ የአነስተኛ ባለአክስዮኖች መብት ቀላል አይደሉም፡፡ በማኅበሩ አስተዳዳሪዎች ወይም በከፍተኛ ባለ አክስዮኖች የሚደርስባቸውን የመብት ጥሰት ለመግታት እና መብታቸውን ለማስከበር አጅግ ጠቃሚ ናቸዉ፡፡
6. አክስዮን ሸጦ የመውጣት የአነስተኛ ባለአክሲዮኖች መብት
በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 292 መሰረት የማህበሩን ዋና ገንዘብ ዘጠና በመቶ የሚወክለ አክስዮኖች በአንድ ጊዜ በማህበርተኛ የተያዙ እንደሆነ አነስተኛ ባለአክስዮኖች ማህበርተኛው አክስዮኖቻቸውን እንዲገዛቸው የመጠየቅ መብት አላቸው። ጥያቄ አቅራቢው ባአአክስዮን አክስዮኖቹ ስለሚገዙበት ሁኔታ በተለይም የአክስዮኖቹን ዋጋ የንግድ ሕግ ስለወሰነበት መንገድ መረጃ ከጥያቄው ጋር ማቅረብ አለበት። ጥያቄ የቀረበለት ማህበርተኛ የቀረበለትን ዋጋ ያልተቀበለ እንደሆነ ማህበሩ በተመዘገበበት ቦታ ሥልጣን ያለው ፍርድ ቤት የአክስዮኖቹን ዋጋ የሚወስን ባለሞያ መሾም አለበት። አክስኖቹን ለመሸጥ ጥያቄ ያቀረበው ባለአክሲዮን የአክሲዮኖቹን ዋጋ ለመወሰን የወጣውን ወጪ መሸፈን አለበት። ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ አክስዮን እንዲገዛ ጥያቄ የቀረበለት ማህበርተኛ የሰጠው ዋጋ ተማኙ ባለሞያ ከወሰነው ያነሰ እንደሆነ ወጪውን በከፊል ወይም በሙሉ እንዲሸፍን ፍርድ ቤቱ ሊያዘው ይችላል፡፡
በአጠቃላይ የአነስተኛ ባለአክሲዮኖች መብት መጠበቅ የማኅበሩን ህልውና መጠበቅ ነዉ፡፡ ይህም የማኅበሩን መልካም አስተዳደር የተሳካና የንግድ አላማውን ዉጤታማ ያደርገዋል፡፡ በዚህ የተነሳ አነስተኛ ባለአክስዮኖች ከሌሎች ከፍተኛ ድርሻ ካላቸው ባለአክስዮኖች፣ ከዳይሬክተሮች ቦርድ፣ ከጠቅላላ ጉባዔዉ እና በአዲተሮች አማካኝነት ከሚሰነዘሩ ያልተገቡ ጫናዎችና የመብት ጥሰቶች መጠበቂያ መንገዶች በአዲሱ የንግድ ሕግ ተደንግገዉ ይገኛሉ፡፡
የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች
____
የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በህክምና፣ ነርሲንግ፣ ሜዲካል ላብራቶሪ ሳይንስ፣ ጤና መኮንን፣ ሚድዋይፈሪ፣ፋርማሲ ፣ አንስቴዥያ ፣ ዴንታል ሜድስን እና ሜዲካል ራዲዮሎጂ ቴክኖሎጂ ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ #ለተመረቁ ባለሙያዎች በሚያዝያ 2014 ዓ.ም የብቃት #ምዘና #ፈተና ለመስጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ ስለሆነም የፈተናው ምዝገባ ከየካቲት 30 እስከ መጋቢት 13/2014 ዓ.ም የሚካሄድ ስለሆነ ተመዛኞች hple.moh.gov.et ላይ በመግባት አስፈላጊውን የትምህርት ማስረጃ በማያያዝ online እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
1) ከግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተመረቃችሁ ተመዛኞች ከምዝገባ በፊት የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን ህጋዊነትና ትክክለኛነት በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን (የቀድሞው የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጄንሲ-HERQA) በኩል ማረጋገጥ (Authenticate ማስደረግ) እና ስማችሁ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ወደ ተቋማችን እንዲተላለፍ ማድረግ ይጠበቅባችኋል፡፡
2) ከዚህ ቀደም የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን Authenticate ያስደረጋችሁ እና ስማችሁ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ወደ ተቋማችን የተላለፈላችሁ ተመዛኞች ድጋሚ Authenticate ማስደረግ አይጠበቅባችሁም፡፡
3) ምዝገባው ለሁሉም ተመዛኞች (የመንግስትም ሆነ የግል ተቋም ተመራቂዎች) online የሚካሄድ ሲሆን online ያልተመዘገበ ተመዛኝ ለፈተና መቀመጥ የማይችል መሆኑን እናሳስባለን፡፡
4) የonline ምዝገባችሁን አጠናቃችሁ Submit ካላችሁ ከ 72 ሰዓት (3 ቀናት) በኋላ ወደ ሲስተሙ በመመለስ ሲስተሙ የሚሰጣችሁን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) መዝግባችሁ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
#Share ለሁሉም ጤና.
____
የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በህክምና፣ ነርሲንግ፣ ሜዲካል ላብራቶሪ ሳይንስ፣ ጤና መኮንን፣ ሚድዋይፈሪ፣
ማሳሰቢያ፡-
1) ከግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተመረቃችሁ ተመዛኞች ከምዝገባ በፊት የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን ህጋዊነትና ትክክለኛነት በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን (የቀድሞው የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጄንሲ-HERQA) በኩል ማረጋገጥ (Authenticate ማስደረግ) እና ስማችሁ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ወደ ተቋማችን እንዲተላለፍ ማድረግ ይጠበቅባችኋል፡፡
2) ከዚህ ቀደም የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን Authenticate ያስደረጋችሁ እና ስማችሁ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ወደ ተቋማችን የተላለፈላችሁ ተመዛኞች ድጋሚ Authenticate ማስደረግ አይጠበቅባችሁም፡፡
3) ምዝገባው ለሁሉም ተመዛኞች (የመንግስትም ሆነ የግል ተቋም ተመራቂዎች) online የሚካሄድ ሲሆን online ያልተመዘገበ ተመዛኝ ለፈተና መቀመጥ የማይችል መሆኑን እናሳስባለን፡፡
4) የonline ምዝገባችሁን አጠናቃችሁ Submit ካላችሁ ከ 72 ሰዓት (3 ቀናት) በኋላ ወደ ሲስተሙ በመመለስ ሲስተሙ የሚሰጣችሁን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) መዝግባችሁ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
#Share ለሁሉም ጤና.
የመክሰር ሕግ በኢትዮጵያ
በአሁኑ ጊዜ በኪሳራ ምክንያት የንግድ ድርጅትን መዝጋትና ንብረቱን ሸጦ ለገንዘብ ጠያቂዎች ማከፋፈል የመጨረሻ እንጂ የመጀመርያ አማራጭ አይደለም። ይህ ሀሳብ በሀገራችን አዲሱ ንግድ ህግ አንድ የንግድ ድርጅት ኪሳራ ሲገጥመው ከተቻለ ድርጅቱን ለማትረፍ፣ ካልተቻለም የተገኘውን ያክል ንብረት ከብክነት በመታደግ ለገንዘብ ጠያቂዎች በፍትሐዊ መንገድ ለማከፋፈል ስለሚቻልበት ሁኔታ የሚደነግጉ የኪሳራ እና የመጠባበቂያ ስምምነትን የሚመለከቱ ድንጋጌዎች ስር ተካቶ ይገኛል፡፡ ይህ ጽሁፍ ስለ መክስር ሥነ ሥርዓት እና አፈፃፀሙን የሚዳስስ ነው፡፡
የመክሰር ትርጉምና ታሪካዊ አመጣጥ
የመክሰር ህግ ታሪካዊ አመጣጥን ዕድገቱ ከሰው ልጆች የግብይት ስርዓት ማደግ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንደሆነና ከጥንት ሮማውያን ጀምሮ ቀስ በቀስ የሀቀኛ ተበዳሪ መክሰርንና ለሌላ ቅጣት ከመዳረግ ይልቅ ዕዳው በንብረቱ ላይ እንዲፈፀም የማድረግ እና የገንዘብ ጠያቂዎችን የንብረት መብት ለማስጠበቅ ታስቦ የመጣ የሕግ ማዕቀፍ መሆኑ ይገለፃል፡፡ የመክሰር ህግ የራሱ የሆነ ጤናማ የኢኮኖሚ ግንኙነት የመፍጠርና ግንኙነቱ ሲደፈርስም ስርዓት ባለው መንገድ አንዱ የሌላውን ሀብት በመውሰድ እንዳይበለፅግና ሁሉም በሀብት ላይ ያለውን የተጠቃሚነት መብቱን እንዲሰራበት ለማስቻል የሚወጣ ሕግ ነው፡፡
የመክሰር ትርጉምን በሚመለከት የተለያዩ ፃህፍት እየተረጎሙት የመጡ ሲሆን ለግንዛቤ ይረዳን ዘንድ እነዚህ ቀጥሎ ያለዉን ትርጓሜ ለማስፈር ተሞክሯል፡፡ የሀገራችን የ1952 ቱ የንግድ ሕግ ቁጥር 969 ስለመክሰር የሚያስፈልግ ሁኔታ በሚል ስር “ማንኛውም ከንግድ የተያያዘውን ዕዳውን መክፈል ያቋረጠና መክሰሩ በፍርድ የተወሰነ ሁሉ የከሰረ ሆኖ የሚቆጠር ነው” በማለት ይደነግጋል፡፡ ከዚህ ትርጓሜ መገንዘብ እንደሚቻለው መክሰር ዕዳን ለመክፈል ካለመቻልና ይሄውም በፍርድ ቤት ከሰሯል የሚል ውሳኔ ሲሰጥበት አንድ ሰው ከስሯል ሊባል እንደሚችል ነው፡፡ በሌላ አባባል አንድ ሰው ዕዳውን መክፈል አለመቻሉ ብቻ እንደከሰረ እንደማያስቆጥረውና ከስሯል ብሎ የመወሰን ስልጣን ለመደበኛ ፍርድ ቤት የተሰጠ መሆኑን ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ብዙ አገሮች መክሰር “Bankruptcy” ከንግድ ጋር ብቻ ተያይዞ መታየት የለበትም ከሚል አመለካከት በመነሳት መክሰር በማንኛውም ዕዳውን ለመክፈል ባልቻለ ግለሰብም ተፈፃሚነት እንዲኖረው የሚያስችል ህግ በማውጣት ላይ ናቸው፡፡
የመክሰር ህግ ተፈፃሚነት
የተለያዩ አገሮች የተለያዩ የመክሰር ህግ (Bankruptcy Law) ያላቸው ሲሆን እንደ አካሄድም የተለያየ አሰራርን የሚከተሉ ናቸው፡፡ በአንዳንድ ሀገራት የመክሰር ህግ ተፈፃሚነት እስከ ግለሰብ የሚዘልቅ ነው፡፡ በሌሎች ሀገራት የህግ ማዕቀፍ የተወሰኑ ልዩነቶችን ብቻ በመፍጠር የመክሰር ህግን በግለሰቦች፣ ነጋዴዎችም ሆኑ ነጋዴ ባልሆኑ ላይ ተፈፃሚነት ያለው ነው፡፡ የሀገራችን ህግ ሲታይ አዲሱ የንግድ ህግ ስንመጣ በዚህ ህግ አንደኛ መፅሐፍ በቁጥር 5 መሰረት ነጋዴ በሆኑ ሰዎችና በዚህ ህግ አንደኛ መፅሐፍ በቁጥር 234 መሰረት የእሽሙር ማህበር ከሆኑት በቀር በንግድ ማህበሮች ሁሉ ላይ ተፈፃሚዎች ይሆናሉ፡፡ ይህ ማለት ግለሰቦች ሆነው በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 5 ላይ የተዘረዘሩ ተግባራትን የሚያከናውኑ ከሆነ ከእሽሙር ማህበር በስተቀር ሌሎች የንግድ ማኅበራት በመክሰር ህግ የሚዳኙ መሆናቸውን የሚደነግግ ነው፡፡
የመክሰር ሥነ-ሥርዓት ስለ መክፈት
በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 705 መሰረት የመክሰር ሥነ ሥርዓት የሚከፈተዉ ክፍያዎችን ያቋረጠ ባለዕዳ አቤቱታ ሲያቀርብ ነዉ፡፡ ባለዕዳዉ በዚህ መጽሐፍ ርዕስ ሦስት መሰረት መልሶ የማደራጀት ሥነ-ሥርዓት ለመክፈት አስቀድሞ አቤቱታ ያቀረበ ካልሆነ በስተቀር ክፍያዎችን ያቋረጠዉ ባለዕዳ በጣም ቢዘገይ በ45 ቀናት ዉስጥ የመክሰር ሥነ-ሥርዓት ለመክፈት ለፍርድ ቤት አቤቱታ ማቅረብ አለበት፡፡ ይህ ግዴታ በኅብረት የሽርክና ማኅበር ዉስጥ በእያንዳንዱ ማኅበርተኛ ላይ እንዲሁም ሁለት ዓይነት ኃላፊነት ባለበት የሽርክና ማኅበር ዉስጥ ኃላፊነታቸዉ ባልተወሰነ ማኅበርተኞች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡ ጊዜው ያልሞላዉ እና የኢኮኖሚ ወይም የፋይናንስ ችግር በተጨባጭ ያጋጠመዉ ወይም ያጋጥመዋል ተብሎ የሚጠበቅ ባለዕዳ ሲያመለክት ብቻ ነዉ፡፡ ባለዕዳዉ የቅርብ ጊዜ የሒሳብ መግለጫዎችን፣ የገንዘብ ችግሮችን ሁኔታ እና የሚፈቱበትን መንገድ የሚያስረዳ ጽሁፍ እንዲሁም የገንዘብ ፍሰት ቅድመ ትንበያ ኪሳራን ለሚመለከተዉ ፍርድ ቤት የሚያቀርብ ሲሆን ፍርድ ቤቱ አስፈላጊ ናቸዉ ብሎ የሚያምናቸዉን ሌሎች ማናቸዉም ሰነዶች እና መረጃዎች ባለዕዳዉ እንዲያቀርብ ትዕዛዝ ሊሰጥ ወይም እንደባንኮች እና የታክስ ባለሥልጣን አካላት ያሉ 3ኛ ወገኖችን እንዲያቀርቡ ትዕዛዝ ሊሰጥ ይችላል፡፡ አስገዳጅ የሆኑ የኢትዮጵያ ሕጎች እንደተጠበቁ ሆነዉ ዕዳን መልሶ የማዋቀር የባለዕዳዉን ንብረቶች እና እዳዎች ወይም ሌላ ማንኛዉንም የባለዕዳዉን የካፒታል መዋቅር ክፍል አወቃቀር፣ ሁኔታዎች ወይም መዋቅር መቀየርን ወይም የንግድ ሥራዉን ንብረቶች ወይም ክፍሎች ወይም አጠቃላይ የንግድ ሥራ እንቅስቃሴዉን በመንቀሳቀስ ላይ እንዳለ የንግድ ሥራ መሸጥን እንዲሁም አስፈላጊ የሆኑ ማናቸዉንም የሥራ ሂደት ለዉጦችን ማድረግን ወይም ከእነዚህ ዉስጥ የተወሰኑትን ወስዶ ማቀናጀትን ሊያካትት ይችላል፡፡
የመክሰር ሥነ-ሥርዓት በማን ይከፈታል
• ከባለዕዳዉ ጋር በአንድነትና በተናጠል ኃላፊ የሆኑ ሰዎች፣
• በባለዕዳዉ ላይ ጊዜዉ የደረሰ እና መከፈል ያለበት የክፍያ ጥያቄ ያላቸዉ አንድ ወይም ከዚያ በላይ ገንዘብ ጠያቂዎች፣
• ከመክሰር ሥነ-ሥርዓት ዉጭ ባለዕዳዉን ንብረት እንዲያጣራ የተሾመ ንብረት አጣሪ፣
• ባለዕዳዉ የንግድ ሥራ ማቋረጡ ባለዕዳዉን ከሚመለከት የወንጀል ሥነ ሥርዓት ግልጽ በሚሆንበት ጊዜ ማንኛዉም ዐቃቤ ሕግ፣አቤቱታ በሚያቀርቡበት ጊዜም እንዲሁ ሊከፈት ይችላል፡፡
• በተጨማሪም በባለዕዳዉ ላይ በመካሄድ ላይ ባለ ሥነ-ሥርዓት የተነሳ ባለዕዳዉ ክፍያዎችን ያቋረጠ መሆኑ ግልጽ በሚሆንበት ጊዜ ፍርድ ቤቱ በራሱ ተነሳሽነትም የመክሰር ሥነሥርዓት ሊያስጀምር ይችላል፡፡ ባለዕዳዉ ክፍያዎችን ያቋረጠ መሆኑን ያረጋገጠዉ ፍርድ ቤት ጉዳዩን በዚህ መጽሐፍ መሰረት የመክሰር ፍርድ ለመስጠት ሥልጣን ወዳለዉ ፍርድ ቤት ይልካል፡፡
ስለ መክሰር የሚሰጥ ፍርድ
ለመጀመሪያ ጊዜ ጉዳዩ በሚሰማበት ጊዜ ወይም አግባብ በሚሆንበት ጊዜ የኪሳራ መርማሪዉ ሪፖርት ሲደርሰዉ ፍርድ ቤቱ፡-
ባለዕዳዉ የከሰረ መሆኑን ያዉጃል፣
ተቆጣጣሪ ዳኛዉን ይሾማል፣
የመክሰር ሥነ-ሥርዓትን ለማከናወን የከሰረዉን ሰዉ ንብረት ጠባቂ ይሾማል፣
ክፍያዎች የተቋረጡበት ቀን መልሶ በማደራጀት ሥነ ሥርዓት ዉስጥ ያልተወሰነ ከሆነ ክፍያዎች የተቋረጡበትን ቀን ይወስናል፡፡
የመክሰርን ሥራ የሚያስፈጽሙ ሰዎችና አባላት
ፍርድ ቤት- የመክሰር ሥነ-ሥርዓትን በመክፈት ረገድ ፍርድ ቤት ሥልጣን እንዳለዉ ከአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 604 እና አንቀጽ 715 መሰረት መረዳት ይቻላል፡፡
በአሁኑ ጊዜ በኪሳራ ምክንያት የንግድ ድርጅትን መዝጋትና ንብረቱን ሸጦ ለገንዘብ ጠያቂዎች ማከፋፈል የመጨረሻ እንጂ የመጀመርያ አማራጭ አይደለም። ይህ ሀሳብ በሀገራችን አዲሱ ንግድ ህግ አንድ የንግድ ድርጅት ኪሳራ ሲገጥመው ከተቻለ ድርጅቱን ለማትረፍ፣ ካልተቻለም የተገኘውን ያክል ንብረት ከብክነት በመታደግ ለገንዘብ ጠያቂዎች በፍትሐዊ መንገድ ለማከፋፈል ስለሚቻልበት ሁኔታ የሚደነግጉ የኪሳራ እና የመጠባበቂያ ስምምነትን የሚመለከቱ ድንጋጌዎች ስር ተካቶ ይገኛል፡፡ ይህ ጽሁፍ ስለ መክስር ሥነ ሥርዓት እና አፈፃፀሙን የሚዳስስ ነው፡፡
የመክሰር ትርጉምና ታሪካዊ አመጣጥ
የመክሰር ህግ ታሪካዊ አመጣጥን ዕድገቱ ከሰው ልጆች የግብይት ስርዓት ማደግ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንደሆነና ከጥንት ሮማውያን ጀምሮ ቀስ በቀስ የሀቀኛ ተበዳሪ መክሰርንና ለሌላ ቅጣት ከመዳረግ ይልቅ ዕዳው በንብረቱ ላይ እንዲፈፀም የማድረግ እና የገንዘብ ጠያቂዎችን የንብረት መብት ለማስጠበቅ ታስቦ የመጣ የሕግ ማዕቀፍ መሆኑ ይገለፃል፡፡ የመክሰር ህግ የራሱ የሆነ ጤናማ የኢኮኖሚ ግንኙነት የመፍጠርና ግንኙነቱ ሲደፈርስም ስርዓት ባለው መንገድ አንዱ የሌላውን ሀብት በመውሰድ እንዳይበለፅግና ሁሉም በሀብት ላይ ያለውን የተጠቃሚነት መብቱን እንዲሰራበት ለማስቻል የሚወጣ ሕግ ነው፡፡
የመክሰር ትርጉምን በሚመለከት የተለያዩ ፃህፍት እየተረጎሙት የመጡ ሲሆን ለግንዛቤ ይረዳን ዘንድ እነዚህ ቀጥሎ ያለዉን ትርጓሜ ለማስፈር ተሞክሯል፡፡ የሀገራችን የ1952 ቱ የንግድ ሕግ ቁጥር 969 ስለመክሰር የሚያስፈልግ ሁኔታ በሚል ስር “ማንኛውም ከንግድ የተያያዘውን ዕዳውን መክፈል ያቋረጠና መክሰሩ በፍርድ የተወሰነ ሁሉ የከሰረ ሆኖ የሚቆጠር ነው” በማለት ይደነግጋል፡፡ ከዚህ ትርጓሜ መገንዘብ እንደሚቻለው መክሰር ዕዳን ለመክፈል ካለመቻልና ይሄውም በፍርድ ቤት ከሰሯል የሚል ውሳኔ ሲሰጥበት አንድ ሰው ከስሯል ሊባል እንደሚችል ነው፡፡ በሌላ አባባል አንድ ሰው ዕዳውን መክፈል አለመቻሉ ብቻ እንደከሰረ እንደማያስቆጥረውና ከስሯል ብሎ የመወሰን ስልጣን ለመደበኛ ፍርድ ቤት የተሰጠ መሆኑን ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ብዙ አገሮች መክሰር “Bankruptcy” ከንግድ ጋር ብቻ ተያይዞ መታየት የለበትም ከሚል አመለካከት በመነሳት መክሰር በማንኛውም ዕዳውን ለመክፈል ባልቻለ ግለሰብም ተፈፃሚነት እንዲኖረው የሚያስችል ህግ በማውጣት ላይ ናቸው፡፡
የመክሰር ህግ ተፈፃሚነት
የተለያዩ አገሮች የተለያዩ የመክሰር ህግ (Bankruptcy Law) ያላቸው ሲሆን እንደ አካሄድም የተለያየ አሰራርን የሚከተሉ ናቸው፡፡ በአንዳንድ ሀገራት የመክሰር ህግ ተፈፃሚነት እስከ ግለሰብ የሚዘልቅ ነው፡፡ በሌሎች ሀገራት የህግ ማዕቀፍ የተወሰኑ ልዩነቶችን ብቻ በመፍጠር የመክሰር ህግን በግለሰቦች፣ ነጋዴዎችም ሆኑ ነጋዴ ባልሆኑ ላይ ተፈፃሚነት ያለው ነው፡፡ የሀገራችን ህግ ሲታይ አዲሱ የንግድ ህግ ስንመጣ በዚህ ህግ አንደኛ መፅሐፍ በቁጥር 5 መሰረት ነጋዴ በሆኑ ሰዎችና በዚህ ህግ አንደኛ መፅሐፍ በቁጥር 234 መሰረት የእሽሙር ማህበር ከሆኑት በቀር በንግድ ማህበሮች ሁሉ ላይ ተፈፃሚዎች ይሆናሉ፡፡ ይህ ማለት ግለሰቦች ሆነው በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 5 ላይ የተዘረዘሩ ተግባራትን የሚያከናውኑ ከሆነ ከእሽሙር ማህበር በስተቀር ሌሎች የንግድ ማኅበራት በመክሰር ህግ የሚዳኙ መሆናቸውን የሚደነግግ ነው፡፡
የመክሰር ሥነ-ሥርዓት ስለ መክፈት
በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 705 መሰረት የመክሰር ሥነ ሥርዓት የሚከፈተዉ ክፍያዎችን ያቋረጠ ባለዕዳ አቤቱታ ሲያቀርብ ነዉ፡፡ ባለዕዳዉ በዚህ መጽሐፍ ርዕስ ሦስት መሰረት መልሶ የማደራጀት ሥነ-ሥርዓት ለመክፈት አስቀድሞ አቤቱታ ያቀረበ ካልሆነ በስተቀር ክፍያዎችን ያቋረጠዉ ባለዕዳ በጣም ቢዘገይ በ45 ቀናት ዉስጥ የመክሰር ሥነ-ሥርዓት ለመክፈት ለፍርድ ቤት አቤቱታ ማቅረብ አለበት፡፡ ይህ ግዴታ በኅብረት የሽርክና ማኅበር ዉስጥ በእያንዳንዱ ማኅበርተኛ ላይ እንዲሁም ሁለት ዓይነት ኃላፊነት ባለበት የሽርክና ማኅበር ዉስጥ ኃላፊነታቸዉ ባልተወሰነ ማኅበርተኞች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡ ጊዜው ያልሞላዉ እና የኢኮኖሚ ወይም የፋይናንስ ችግር በተጨባጭ ያጋጠመዉ ወይም ያጋጥመዋል ተብሎ የሚጠበቅ ባለዕዳ ሲያመለክት ብቻ ነዉ፡፡ ባለዕዳዉ የቅርብ ጊዜ የሒሳብ መግለጫዎችን፣ የገንዘብ ችግሮችን ሁኔታ እና የሚፈቱበትን መንገድ የሚያስረዳ ጽሁፍ እንዲሁም የገንዘብ ፍሰት ቅድመ ትንበያ ኪሳራን ለሚመለከተዉ ፍርድ ቤት የሚያቀርብ ሲሆን ፍርድ ቤቱ አስፈላጊ ናቸዉ ብሎ የሚያምናቸዉን ሌሎች ማናቸዉም ሰነዶች እና መረጃዎች ባለዕዳዉ እንዲያቀርብ ትዕዛዝ ሊሰጥ ወይም እንደባንኮች እና የታክስ ባለሥልጣን አካላት ያሉ 3ኛ ወገኖችን እንዲያቀርቡ ትዕዛዝ ሊሰጥ ይችላል፡፡ አስገዳጅ የሆኑ የኢትዮጵያ ሕጎች እንደተጠበቁ ሆነዉ ዕዳን መልሶ የማዋቀር የባለዕዳዉን ንብረቶች እና እዳዎች ወይም ሌላ ማንኛዉንም የባለዕዳዉን የካፒታል መዋቅር ክፍል አወቃቀር፣ ሁኔታዎች ወይም መዋቅር መቀየርን ወይም የንግድ ሥራዉን ንብረቶች ወይም ክፍሎች ወይም አጠቃላይ የንግድ ሥራ እንቅስቃሴዉን በመንቀሳቀስ ላይ እንዳለ የንግድ ሥራ መሸጥን እንዲሁም አስፈላጊ የሆኑ ማናቸዉንም የሥራ ሂደት ለዉጦችን ማድረግን ወይም ከእነዚህ ዉስጥ የተወሰኑትን ወስዶ ማቀናጀትን ሊያካትት ይችላል፡፡
የመክሰር ሥነ-ሥርዓት በማን ይከፈታል
• ከባለዕዳዉ ጋር በአንድነትና በተናጠል ኃላፊ የሆኑ ሰዎች፣
• በባለዕዳዉ ላይ ጊዜዉ የደረሰ እና መከፈል ያለበት የክፍያ ጥያቄ ያላቸዉ አንድ ወይም ከዚያ በላይ ገንዘብ ጠያቂዎች፣
• ከመክሰር ሥነ-ሥርዓት ዉጭ ባለዕዳዉን ንብረት እንዲያጣራ የተሾመ ንብረት አጣሪ፣
• ባለዕዳዉ የንግድ ሥራ ማቋረጡ ባለዕዳዉን ከሚመለከት የወንጀል ሥነ ሥርዓት ግልጽ በሚሆንበት ጊዜ ማንኛዉም ዐቃቤ ሕግ፣አቤቱታ በሚያቀርቡበት ጊዜም እንዲሁ ሊከፈት ይችላል፡፡
• በተጨማሪም በባለዕዳዉ ላይ በመካሄድ ላይ ባለ ሥነ-ሥርዓት የተነሳ ባለዕዳዉ ክፍያዎችን ያቋረጠ መሆኑ ግልጽ በሚሆንበት ጊዜ ፍርድ ቤቱ በራሱ ተነሳሽነትም የመክሰር ሥነሥርዓት ሊያስጀምር ይችላል፡፡ ባለዕዳዉ ክፍያዎችን ያቋረጠ መሆኑን ያረጋገጠዉ ፍርድ ቤት ጉዳዩን በዚህ መጽሐፍ መሰረት የመክሰር ፍርድ ለመስጠት ሥልጣን ወዳለዉ ፍርድ ቤት ይልካል፡፡
ስለ መክሰር የሚሰጥ ፍርድ
ለመጀመሪያ ጊዜ ጉዳዩ በሚሰማበት ጊዜ ወይም አግባብ በሚሆንበት ጊዜ የኪሳራ መርማሪዉ ሪፖርት ሲደርሰዉ ፍርድ ቤቱ፡-
ባለዕዳዉ የከሰረ መሆኑን ያዉጃል፣
ተቆጣጣሪ ዳኛዉን ይሾማል፣
የመክሰር ሥነ-ሥርዓትን ለማከናወን የከሰረዉን ሰዉ ንብረት ጠባቂ ይሾማል፣
ክፍያዎች የተቋረጡበት ቀን መልሶ በማደራጀት ሥነ ሥርዓት ዉስጥ ያልተወሰነ ከሆነ ክፍያዎች የተቋረጡበትን ቀን ይወስናል፡፡
የመክሰርን ሥራ የሚያስፈጽሙ ሰዎችና አባላት
ፍርድ ቤት- የመክሰር ሥነ-ሥርዓትን በመክፈት ረገድ ፍርድ ቤት ሥልጣን እንዳለዉ ከአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 604 እና አንቀጽ 715 መሰረት መረዳት ይቻላል፡፡
ተቆጣጣሪ ዳኛ- ስለተቆጣጣሪ ዳኛዉ ሹመት እና ሥልጣን አዲሱ የንግድ ሕግ 716 እና 717 ን መመልከት ይቻላል፡፡
የከሰረ ሰዉ ንብረት ጠባቂ- በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 718 መሰረት ፍርድ ቤቱ የመክሰር ሥነ ሥርዓት እንዲከፈት በሚሰጠዉ ፍርድ ዉስጥ አንድ የከሰረ ሰዉ ንብረት ጠባቂ ይሾማል፡፡ በሥነ-ሥርዓቱ ወቅት በማናቸዉም ጊዜ የከሰረዉ ሰዉ ንብረት ጠባቂ በማንኛዉም ገንዘብ ጠያቂ፣ በገንዘብ ጠያቂዎች ኮሚቴ ወይም በዐቃቤ ሕግ በሌላ እንዲተካ ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ ማቅረብ ይቻላል፡፡ ፍርድ ቤቱም በራሱ ሥልጣን የከሰረዉ ሰዉ ንብረት ጠባቂዉን በሌላ ሊተካ ይችላል፡፡ የከሰረሰዉ ንብረት ጠባቂ ሥልጣን እና ግዴታዎችም በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 720 ላይ ተመልክቷል፡፡
የገንዘብ ጠያቂዎች ኮሚቴ- ተቆጣጣሪ ዳኛዉ የመክሰር ሥነ ሥርዓት በተከፈተ በ10 ቀናት ዉስጥ ከፍተኛ መጠን ያላቸዉ የክፍያ ጠያቂዎች ካላቸዉ የገንዘብ ጠያቂዎች መካከል 5 አባላትን የያዘ የገንዘብ ጠያቂዎች ኮሚቴ እንደሚያቋቁም በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 722 ላይ ሰፍሯል፡፡ የኮሚቴዎች መብትና ግዴታም በዚሁ ሕግ ተደንግጎ ይገኛል፡፡
ዐቃቤ ሕግ- በመክሰር ሥነ ሥርዓት ዉስጥ ዐቃቤ ሕግ ሥልጣን ያለዉ ሲሆን ይህን ሥነ ሥርዓት ከማስፈጸም ጋር ግንኙነት ያላቸዉ ማናቸዉንም የባለቤትነት ማረጋገጫዎች መዛግብትና ሰነዶች ተቆጣጣሪ ዳኛዉ እንዲቀርበለት የማዘዝ መብት በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 724 መሰረት አለዉ፡፡ እንዲሁም የዐቃቤ ሕግ መብቶች በዚሁ ሕግ አንቀጽ 740 ሥር ሰፍሮ ይገኛል፡፡
የመክሰር ሥነ ሥርዓት የሚዘጋባቸዉ ምክንያቶች
በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 696 መሰረት የመክሰር ሥነ ሥርዓትን መልሶ መክፈት (እንደገና እንዲጀመር ለፍርድ ቤቱ ማመልከት) መቻሉ እንደተጠበቀ ሆኖ የመክሰር ሥነ ሥርዓት በሚከተሉት ምክንያቶች ሊዘጋ ይችላል፡-
ከንብረት ማጣራት የተገኘዉን ገንዘብ ጨርሶ በማከፋፈል፣
የሚበቃ ንብረት ባለመኖሩ እና
ከንብረቱ የሚፈለግ ዕዳ ባለመኖሩ ሲሆኑ 2ኛ እና 3ኛ ምክንያቶች ዝርዝራቸዉ በዚሁ ሕግ ከአንቀጽ 795 እሰከ 797 ድረስ ተደንግገዉ ይገኛሉ፡፡
የከሰረን ሰው ነፃ ስለመደረግ (Discharge)
ነባሩ የንግድ ሕግ የሚከስሩ ነጋዴዎች ከዕዳ ነፃ የሚወጡበት የሕግ ድንጋጌ አላካተተም። በዚህም ምክንያት ብዙ ነጋዴዎች የኪሳራን ሥነ-ሥርዓት ፈቅደው እንዳያመለክቱ ሊያደርግ ችሏል። ዘመናዊ የሆኑ የኪሳራ ሕጎች ንፁህ ነጋዴዎች በተወሰነ መልኩ የኪሳራ ሥነ-ሥርዓቱ ከተዘጋ በኋላ ነፃ የሚሆኑበትን ሁኔታ ይደነግጋሉ። አዲሱ የንግድ ህጋችን ነጋዴዎች የኪሳራ ሥነ-ሥርዓቱ በሕጉ መሰረት ካበቃ በኋላ ከዕዳ ነፃ የሚሆኑባቸውን የሕግ ድንጋጌዎች በመፅሐፍ ሦስት በርዕስ 5 አንቀጽ 799 ሥር አስቀምጧል። በዚህም መሰረት አንድ የኪሳራ ውሳኔ የተላላፈበት ነጋዴ የኪሳራው ብይን ከተሰጠበት ቀን አንስቶ ከሶስት ዓመት በኋላ ከዕዳ ነፃ ለመሆን ለፍ/ቤት ማመልከት እንደሚችል በአዲሱ የንግድ ሕግ ተካቷል።
ይህ መብት በዘፈቀደ ለሁሉም የሚሰጥ አይደለም። ንጹህ የሆኑ የተፈጥሮ ሰው ነጋዴዎችን ብቻ የሚመለከት ነው። እንደዚህም ሆኖ ከኪሳራ ጋር ተያያዠነት ያላቸውን ወንጀሎች ፈፅሞ የተፈረደበት፤ ንብረት ስለመደበቁ ወይም ማሸሹ ማስረጃ የቀረበበት፤ በኪሳራ ሥነ-ሥርዓት ሂደት ያልተባበረ ወይም ግዴታውን ያልተወጣ ነጋዴ ወይም ተደጋጋሚ የኪሳራ ውሳኔ በአምስት ዓመት ውስጥ ያስተናገደ ነጋዴ ይህን መብት አያገኝም። ከዕዳ ነፃ አይደረግም። በተጨማሪም የተወሰኑ ዕዳዎች ሌሎች ሕጎች በልዩ ሁኔታ ካልፈቀዱ በስተቀር ነፃ እንደማይደረጉ በአዲሱ የንግድ ሕግ ተካቷል።
ቀላል የኪሳራ ሥነ-ሥርዓት
ቀላል የኪሳራ ሥነ-ሥርዓት ዓላማ ሥነ-ሥርዓቱን ቀላል፤ ጊዜና ወጪ ቆጣቢ በማድረግ ለኪሳራ የተዳረጉ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በሥነ-ሥርዓቱ ከንግድ ሥርዓቱ የሚወጡበትን ሥርዓት መዘርጋት ነው። ቀላል የኪሳራ ሥነ-ሥርዓት ሊከፍቱ የሚችሉት አነስተኛና መካከላኛ ኢንተርፕራይዞች ሲሆኑ እነሱም የሚከተሉትን መመዘኛዎች የሚያማሉ ከሆነ ነው፡- 1) ባለፉት 12 ወራት የሒሳብ ሚዛናቸው የሀብት መጠን ከ20 ሚሊዮን ብር ያነሰ ከሆነ፤ 2) የሠራተኛ ቁጥራቸው ከ10 ያነሰ ከሆነ፤ ወይም 3) ባለፉት 12 ወራት ዓመታዊ ሽያጫቸው ከ5 ሚሊዮን ብር ያነሰ ከሆነ ነው።
ይህን ሥነ-ሥርዓት ቀላል የሚያሰኙት ዋና ዋና ባህርያት የሚከተሉት ናቸው፡- 1) የሚቀርቡት ሰነዶችና አባሪዎች ዝርዝር አጭር መሆናቸው፤ 2) በፍ/ቤቱ ተቆጣጣሪነትና በንብረት ጠባቂው ኃላፊነት ብቻ (ተቆጣጣሪ ዳኛና የገንዘብ ጠያቂዎች ኮሚቴ ሳያስፈልግ) ሥነ-ሥርዓቱን ማከናወን መቻሉ፤ 3) የንብረት ማጣራትና መሸጥ ተግባራት የተንዛዛውን መደበኛ ሥነ-ሥርዓቶች የግድ አለመከተላቸው፤ 4) ንብረት ጠባቂው የባለዕዳውን ንብረት አጣርቶ፤ ሸጦ በአንድ ዓመት ውስጥ የማከፋፈል ግዴታ የተጣለበት መሆኑና ሥነ-ሥርዓቱም በአንድ ዓመት የጊዜ ገደብ የታጠረ መሆኑ፤ እና 5) በዚህ ሥነ-ሥርዓት ሥር አልፈው ፋይላቸው የተዘጋላቸው የተፈጥሮ ሰዎች ከዕዳ ነፃ ወዲያውኑ ሊታወጅላቸው መቻሉ፤ናቸው። ፍ/ቤቱም ቀላል የኪሳራ ሥነ-ሥርዓት ከተከፈተ ባንድ ዓመት ውስጥ መጠናቀቁን ማረጋገጥ ይኖርበታል፡፡
በንቃተ ሕግ፣ ትምህርትና ሥልጠና ዳይሬክቶሬት
የከሰረ ሰዉ ንብረት ጠባቂ- በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 718 መሰረት ፍርድ ቤቱ የመክሰር ሥነ ሥርዓት እንዲከፈት በሚሰጠዉ ፍርድ ዉስጥ አንድ የከሰረ ሰዉ ንብረት ጠባቂ ይሾማል፡፡ በሥነ-ሥርዓቱ ወቅት በማናቸዉም ጊዜ የከሰረዉ ሰዉ ንብረት ጠባቂ በማንኛዉም ገንዘብ ጠያቂ፣ በገንዘብ ጠያቂዎች ኮሚቴ ወይም በዐቃቤ ሕግ በሌላ እንዲተካ ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ ማቅረብ ይቻላል፡፡ ፍርድ ቤቱም በራሱ ሥልጣን የከሰረዉ ሰዉ ንብረት ጠባቂዉን በሌላ ሊተካ ይችላል፡፡ የከሰረሰዉ ንብረት ጠባቂ ሥልጣን እና ግዴታዎችም በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 720 ላይ ተመልክቷል፡፡
የገንዘብ ጠያቂዎች ኮሚቴ- ተቆጣጣሪ ዳኛዉ የመክሰር ሥነ ሥርዓት በተከፈተ በ10 ቀናት ዉስጥ ከፍተኛ መጠን ያላቸዉ የክፍያ ጠያቂዎች ካላቸዉ የገንዘብ ጠያቂዎች መካከል 5 አባላትን የያዘ የገንዘብ ጠያቂዎች ኮሚቴ እንደሚያቋቁም በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 722 ላይ ሰፍሯል፡፡ የኮሚቴዎች መብትና ግዴታም በዚሁ ሕግ ተደንግጎ ይገኛል፡፡
ዐቃቤ ሕግ- በመክሰር ሥነ ሥርዓት ዉስጥ ዐቃቤ ሕግ ሥልጣን ያለዉ ሲሆን ይህን ሥነ ሥርዓት ከማስፈጸም ጋር ግንኙነት ያላቸዉ ማናቸዉንም የባለቤትነት ማረጋገጫዎች መዛግብትና ሰነዶች ተቆጣጣሪ ዳኛዉ እንዲቀርበለት የማዘዝ መብት በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 724 መሰረት አለዉ፡፡ እንዲሁም የዐቃቤ ሕግ መብቶች በዚሁ ሕግ አንቀጽ 740 ሥር ሰፍሮ ይገኛል፡፡
የመክሰር ሥነ ሥርዓት የሚዘጋባቸዉ ምክንያቶች
በአዲሱ የንግድ ሕግ አንቀጽ 696 መሰረት የመክሰር ሥነ ሥርዓትን መልሶ መክፈት (እንደገና እንዲጀመር ለፍርድ ቤቱ ማመልከት) መቻሉ እንደተጠበቀ ሆኖ የመክሰር ሥነ ሥርዓት በሚከተሉት ምክንያቶች ሊዘጋ ይችላል፡-
ከንብረት ማጣራት የተገኘዉን ገንዘብ ጨርሶ በማከፋፈል፣
የሚበቃ ንብረት ባለመኖሩ እና
ከንብረቱ የሚፈለግ ዕዳ ባለመኖሩ ሲሆኑ 2ኛ እና 3ኛ ምክንያቶች ዝርዝራቸዉ በዚሁ ሕግ ከአንቀጽ 795 እሰከ 797 ድረስ ተደንግገዉ ይገኛሉ፡፡
የከሰረን ሰው ነፃ ስለመደረግ (Discharge)
ነባሩ የንግድ ሕግ የሚከስሩ ነጋዴዎች ከዕዳ ነፃ የሚወጡበት የሕግ ድንጋጌ አላካተተም። በዚህም ምክንያት ብዙ ነጋዴዎች የኪሳራን ሥነ-ሥርዓት ፈቅደው እንዳያመለክቱ ሊያደርግ ችሏል። ዘመናዊ የሆኑ የኪሳራ ሕጎች ንፁህ ነጋዴዎች በተወሰነ መልኩ የኪሳራ ሥነ-ሥርዓቱ ከተዘጋ በኋላ ነፃ የሚሆኑበትን ሁኔታ ይደነግጋሉ። አዲሱ የንግድ ህጋችን ነጋዴዎች የኪሳራ ሥነ-ሥርዓቱ በሕጉ መሰረት ካበቃ በኋላ ከዕዳ ነፃ የሚሆኑባቸውን የሕግ ድንጋጌዎች በመፅሐፍ ሦስት በርዕስ 5 አንቀጽ 799 ሥር አስቀምጧል። በዚህም መሰረት አንድ የኪሳራ ውሳኔ የተላላፈበት ነጋዴ የኪሳራው ብይን ከተሰጠበት ቀን አንስቶ ከሶስት ዓመት በኋላ ከዕዳ ነፃ ለመሆን ለፍ/ቤት ማመልከት እንደሚችል በአዲሱ የንግድ ሕግ ተካቷል።
ይህ መብት በዘፈቀደ ለሁሉም የሚሰጥ አይደለም። ንጹህ የሆኑ የተፈጥሮ ሰው ነጋዴዎችን ብቻ የሚመለከት ነው። እንደዚህም ሆኖ ከኪሳራ ጋር ተያያዠነት ያላቸውን ወንጀሎች ፈፅሞ የተፈረደበት፤ ንብረት ስለመደበቁ ወይም ማሸሹ ማስረጃ የቀረበበት፤ በኪሳራ ሥነ-ሥርዓት ሂደት ያልተባበረ ወይም ግዴታውን ያልተወጣ ነጋዴ ወይም ተደጋጋሚ የኪሳራ ውሳኔ በአምስት ዓመት ውስጥ ያስተናገደ ነጋዴ ይህን መብት አያገኝም። ከዕዳ ነፃ አይደረግም። በተጨማሪም የተወሰኑ ዕዳዎች ሌሎች ሕጎች በልዩ ሁኔታ ካልፈቀዱ በስተቀር ነፃ እንደማይደረጉ በአዲሱ የንግድ ሕግ ተካቷል።
ቀላል የኪሳራ ሥነ-ሥርዓት
ቀላል የኪሳራ ሥነ-ሥርዓት ዓላማ ሥነ-ሥርዓቱን ቀላል፤ ጊዜና ወጪ ቆጣቢ በማድረግ ለኪሳራ የተዳረጉ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በሥነ-ሥርዓቱ ከንግድ ሥርዓቱ የሚወጡበትን ሥርዓት መዘርጋት ነው። ቀላል የኪሳራ ሥነ-ሥርዓት ሊከፍቱ የሚችሉት አነስተኛና መካከላኛ ኢንተርፕራይዞች ሲሆኑ እነሱም የሚከተሉትን መመዘኛዎች የሚያማሉ ከሆነ ነው፡- 1) ባለፉት 12 ወራት የሒሳብ ሚዛናቸው የሀብት መጠን ከ20 ሚሊዮን ብር ያነሰ ከሆነ፤ 2) የሠራተኛ ቁጥራቸው ከ10 ያነሰ ከሆነ፤ ወይም 3) ባለፉት 12 ወራት ዓመታዊ ሽያጫቸው ከ5 ሚሊዮን ብር ያነሰ ከሆነ ነው።
ይህን ሥነ-ሥርዓት ቀላል የሚያሰኙት ዋና ዋና ባህርያት የሚከተሉት ናቸው፡- 1) የሚቀርቡት ሰነዶችና አባሪዎች ዝርዝር አጭር መሆናቸው፤ 2) በፍ/ቤቱ ተቆጣጣሪነትና በንብረት ጠባቂው ኃላፊነት ብቻ (ተቆጣጣሪ ዳኛና የገንዘብ ጠያቂዎች ኮሚቴ ሳያስፈልግ) ሥነ-ሥርዓቱን ማከናወን መቻሉ፤ 3) የንብረት ማጣራትና መሸጥ ተግባራት የተንዛዛውን መደበኛ ሥነ-ሥርዓቶች የግድ አለመከተላቸው፤ 4) ንብረት ጠባቂው የባለዕዳውን ንብረት አጣርቶ፤ ሸጦ በአንድ ዓመት ውስጥ የማከፋፈል ግዴታ የተጣለበት መሆኑና ሥነ-ሥርዓቱም በአንድ ዓመት የጊዜ ገደብ የታጠረ መሆኑ፤ እና 5) በዚህ ሥነ-ሥርዓት ሥር አልፈው ፋይላቸው የተዘጋላቸው የተፈጥሮ ሰዎች ከዕዳ ነፃ ወዲያውኑ ሊታወጅላቸው መቻሉ፤ናቸው። ፍ/ቤቱም ቀላል የኪሳራ ሥነ-ሥርዓት ከተከፈተ ባንድ ዓመት ውስጥ መጠናቀቁን ማረጋገጥ ይኖርበታል፡፡
በንቃተ ሕግ፣ ትምህርትና ሥልጠና ዳይሬክቶሬት
Sebeawinet Vol. 4.pdf
870.5 KB
Its finally here vol. 4 of Sebeawinet magazine.
ሰብአዊነት_ስብስብ_ለሰብአዊ_መብቶች_በኢትዮጵያ_መጽሄት፟_ዕትም_1.pdf
2.4 MB
ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ ሰብአዊነት የተሰኘውን የመጀመሪያውን በሰብአዊ መብቶች ላይ ያተኮረ መፅሄት ሲያቀርብላችሁ በደስታ ነው፡፡( Association for Human Rights in Ethiopia is happy to announce the launch of its first Magazine ሰብአዊነት dedicated to advocating, informing and educating about Human Rights, Human Rights laws and and current human rights situations in Ethiopia. ) IF YOU ARE INTERESTED YOUR ARTICLE BEING FEATURED IN OUR NEXT "ሰብአዊነት" MAGAZINE, PLEASE CONTACT US VIA FACEBOOK at (Association for Human Rights in Ethiopia Page)
ሰብአዊነት እትም 2 ቁጥር 2.docx
402.5 KB
It is finally Here; Find Sebawinet Magazine Volume 2
ሰብአዊነት_ስብስብ_ለሰብአዊ_መብቶች_በኢትዮጵያ_መጽሄት፟_ዕትም_3_Associciation_for_Human.pdf
430.2 KB
It is out now! Sebeawinet magazine volume 3 by AHRE
Forwarded from አለሕግAleHig ️
የማስረዳት ግዴታ
=================
=====================
• ዓቃቤ ህግ ጉዳዩን የማስረዳት ግዴታና ኃላፊነቱን ተወጥቷል ወይስ አልተወጣም? የሚለው ነጥብ እልባት የሚሰጠው ባቀረበው የወንጀል ክስ ውስጥ የተገለፁትን ፍሬ ጉዳዮች ትክክለኛነት የወንጀል ክሱን ለማስረዳት ባቀረባቸው የተለያዩ ማስረጃዎች የሚያረጋግጡና በወንጀል ክሱ ውስጥ የተገለፀው ፍሬ ጉዳይና ክሱን ለማስረዳት የቀረቡት ማስረጃዎች እርስ በርሳቸው የሚደጋገፉና ተያያዥነት ያላቸው ሆነው ሲገኙ ነው፡፡
የወንጀል ክስ ያቀረበ ከሳሽ ጉዳዩን የማስረዳት ግዴታና ኃላፊነቱን ተወጥቷል ወይም አልተወጣም? የሚለውን ጭብጥ ለመወሰን የመጀመሪያው የማነፃፀሪያና የመመዘኛ መስፈርት ራሱ ከሳሽ ያቀረበው የወንጀል ክስ ማመልከቻ ነው፡፡ አንድ ድርጊት የተፈፀመ መሆኑን በመግለጽ ክስ ያቀረበ ወገን በክሱ የገለፀውን ፍሬ ጉዲይ የማስረዳት ግዴታና ኃላፊነት አለበት የሚለው የማስረጃ ሕግ መርህ ይህንኑ የሚያጠናክር ነው፡፡ ዓቃቤ ህግ ጉዳዩን የማስረዳት ግዴታና ኃላፊነቱን ተወጥቷል ወይስ አልተወጣም? የሚለው ነጥብ እልባት የሚሰጠው ባቀረበው የወንጀል ክስ ውስጥ የተገለፁትን ፍሬ ጉዳዮች ትክክለኛነት የወንጀል ክሱን ለማስረዳት ባቀረባቸው የተለያዩ ማስረጃዎች የሚያረጋግጡና በወንጀል ክሱ ውስጥ የተገለፀው ፍሬ ጉዳይና ክሱን ለማስረዳት የቀረቡት ማስረጃዎች እርስ በርሳቸው የሚደጋገፉና ተያያዥነት ያላቸው ሆነው ሲገኙ ነው፡፡ በአጠቃላይ ከሳሽ ክሱን ለማስረዳት ያቀረባቸው ማስረጃዎች ለጉዳዩ ያላቸው አግባብነት (Relevancy of evidence) እና የከሳሽ ማስረጃ የአስረጅነት ዋጋ ያላቸውና ታዓማኒነት ያላቸው መሆኑ የሚመረመረው ከሳሽ በወንጀል ክስ ማመልከቻው የገለፃቸውን ፍሬ ጉዳዮች መሰረት በማድረግ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 51706 ቅጽ 10
L.C.L
ኢትዮ-ሕግ💎Ethio-Law
#henoktaye
https://t.me/LawyerEthiopia
https://t.me/LawyerEthiopia
=================
=====================
• ዓቃቤ ህግ ጉዳዩን የማስረዳት ግዴታና ኃላፊነቱን ተወጥቷል ወይስ አልተወጣም? የሚለው ነጥብ እልባት የሚሰጠው ባቀረበው የወንጀል ክስ ውስጥ የተገለፁትን ፍሬ ጉዳዮች ትክክለኛነት የወንጀል ክሱን ለማስረዳት ባቀረባቸው የተለያዩ ማስረጃዎች የሚያረጋግጡና በወንጀል ክሱ ውስጥ የተገለፀው ፍሬ ጉዳይና ክሱን ለማስረዳት የቀረቡት ማስረጃዎች እርስ በርሳቸው የሚደጋገፉና ተያያዥነት ያላቸው ሆነው ሲገኙ ነው፡፡
የወንጀል ክስ ያቀረበ ከሳሽ ጉዳዩን የማስረዳት ግዴታና ኃላፊነቱን ተወጥቷል ወይም አልተወጣም? የሚለውን ጭብጥ ለመወሰን የመጀመሪያው የማነፃፀሪያና የመመዘኛ መስፈርት ራሱ ከሳሽ ያቀረበው የወንጀል ክስ ማመልከቻ ነው፡፡ አንድ ድርጊት የተፈፀመ መሆኑን በመግለጽ ክስ ያቀረበ ወገን በክሱ የገለፀውን ፍሬ ጉዲይ የማስረዳት ግዴታና ኃላፊነት አለበት የሚለው የማስረጃ ሕግ መርህ ይህንኑ የሚያጠናክር ነው፡፡ ዓቃቤ ህግ ጉዳዩን የማስረዳት ግዴታና ኃላፊነቱን ተወጥቷል ወይስ አልተወጣም? የሚለው ነጥብ እልባት የሚሰጠው ባቀረበው የወንጀል ክስ ውስጥ የተገለፁትን ፍሬ ጉዳዮች ትክክለኛነት የወንጀል ክሱን ለማስረዳት ባቀረባቸው የተለያዩ ማስረጃዎች የሚያረጋግጡና በወንጀል ክሱ ውስጥ የተገለፀው ፍሬ ጉዳይና ክሱን ለማስረዳት የቀረቡት ማስረጃዎች እርስ በርሳቸው የሚደጋገፉና ተያያዥነት ያላቸው ሆነው ሲገኙ ነው፡፡ በአጠቃላይ ከሳሽ ክሱን ለማስረዳት ያቀረባቸው ማስረጃዎች ለጉዳዩ ያላቸው አግባብነት (Relevancy of evidence) እና የከሳሽ ማስረጃ የአስረጅነት ዋጋ ያላቸውና ታዓማኒነት ያላቸው መሆኑ የሚመረመረው ከሳሽ በወንጀል ክስ ማመልከቻው የገለፃቸውን ፍሬ ጉዳዮች መሰረት በማድረግ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 51706 ቅጽ 10
L.C.L
ኢትዮ-ሕግ💎Ethio-Law
#henoktaye
https://t.me/LawyerEthiopia
https://t.me/LawyerEthiopia
የብድር ውል ‼️
(የፍትሐብሔር ሕግ ከቁጥር 2471-2489)
የብድር ውል ምንነት፡- የተለያዩ ፅሑፎች እንደሚያስረዱት ብድርን በተመለከተ ሁሉንም ሊያግባባ የሚችል አንድ ወጥ የሆነ ትርጉም አናገኝለትም፡፡ የፍትሐብሔር ሕጋችን የሚከተለውን ትርጉም ሰጥቶታል፡- “የሚያልቅ ነገር ብድር ማለት ከተዋዋዮቹ አንዱ ወገን አበዳሪው ሌላውን ተበዳሪ ሰው የተበደረውን ነገር በዓይነቱ ለመመለስ ተገዳጅ በማደረግ ገንዘብ ወይም በማገልገል የሚያልቅ ሌላ ነገር ለተበዳሪው ለመስጠትና ሀብትነቱን ለማስተላለፍ የሚገደድበት ውል ነው” ይላል፡፡ ከዚህ ትርጓሜ መረዳት እንደሚቻለው ብድርን በሚመለከት ሕጉ በሚያልቅ ነገር ላይ ብቻ እንጂ ከዛ ባለፈ ማለትም በማያልቅ ነገር ወይም ቋሚ የሆነ ንብረትን የማያካትት መሆኑን ነው፡፡ የድንጋጌውን አጠቃላይ ይዘት ስናይ አመላለሱ በዓይነት ወይም በአገልግሎት ሊሆን እንደሚችል እና ውሉ አስገዳጅ መሆኑንም ያሳያል፡፡
የዉል አመሠራረት፡- የብድር ውል የውል አንድ አካል እንደመሆኑ መጠን አመሰራረቱም ሆነ አፈፃፀሙ በጠቅላላው የውል ሕግ መርሆች የሚገዛ በመሆኑ የብድር ውልን ዝርዝር ድንጋጌዎች ከማየታችን በፊት ስለውል አመሰራረት ባጭሩ አይተን ብናልፍ የተሻለ ግንዘቤን ይፈጥራል፡፡ ዉል ስምምነት ቢሆንም ከሌሎች ስምምነቶች የሚለየዉ በአፈፃፀሙ ከበስተጀርባዉ የሕግ ድጋፍ ያለዉ ስምምነት መሆኑ ላይ ነዉ፡፡
አንድ ውል የሚፀና ውል ነው ለማለት የሚከተሉትን መርሆች ማሟላት አለበት፡- 1ኛ ዉል የሚፈፀመዉ ለመዋዋል ችሎታ ባላቸዉ ሰዎች መካከል ብቻ መሆኑ (እድሜዉ ለአቅመ አዳም/ሄዋን ያልደረሰ ወይም አይምሮዉ ህመም ያለበት ሰዉ ወይም በፍርድ ቤት የተከለከለ ሰዉ ችሎታ እንደሌለዉ ይቆጠራል፡፡) 2ኛ ዉል የሚደረገው በተወያያቹ ነፃ ፍቃድ ብቻ የሚደረግ መሆኑ፡፡ 3ኛ ተወያይ ወገኖች የሚዋዋሉበት ጉዳይ በእርግጠኝነት የሚቻል እና ህጋዊና ሞራላዊ ጉዳይ ላይ መሆን የሚገባው መሆኑ፡፡ 4ኛ የዉል አቀራረጹ ወይም አፃፃፉ (ፎርም) በህግ ተለይተዉ የተቀመጡ ወይም ተዋዋይ ወገኖች ተለይቶ እንዲቀመጥ ከተስማሙበት የዉል ጉዳይ በቀር የተለየ የዉል ፎርም አያስፈልግም፡፡
የአበዳሪና ተበዳሪ ግዴታዎች፡- አበዳሪና ተበዳሪ የራሳቸው የሆኑ ሊያከብሯቸው የሚገቡ ግዴታዎች አሉባቸው፡፡ በቅድሚያ የአበዳሪው ግዴታዎችን ስናይ ሕጉ የአበዳሪውን ግዴታዎች በተመለከተ የሽያጭ ውልን በሚደነግገው ክፍል ላይ የሻጩ ግዴታዎች ተብለው የተገለፁት ደንቦች በአበዳሪ ላይ ተግባራዊ ይሆናሉ ይላል፡፡ በፍትሐብሔር ሕጉ የሻጭ ግዴታዎች ናቸው የተባሉት ደግሞ የሚከተሉት ናቸው፡፡
1ኛ ዕቃ የማስረከብ ግዴታ፡- የሽያጭ ውል ከተከናወነ በኋላ ሻጭ የግብይት ምክንያት የሆንውን ዕቃ/ንብረት ለገዥ የማስረከብ ግዴታ አለበት፡፡ 2ኛ ስመ-ሀብት የማስተላለፍ ግዴታ፡- ከላይ ለማንሳት እንደተሞከረው የሽያጭ ውል ልዩ መገልጫ ከሆኑት ጉዳዮች ውስጥ ሻጩ የሽጭ ምክንያት የሆነውን ንብረት ስመ-ሀብትን የማስተላለፍ ግዴታ ያለበት መሆኑ ነው፡፡ የባለቤትነት መብት መተላለፍን በተመለከተ የብድር ውል ከሽያጭ ውል ለየት የሚያደርገው ነገር ቢኖር የብድር ውሉ በትርጉም ክፍሉ ላይ እንደሰፈረው አላቂ ዕቃን ብቻ የሚመለከት በመሆኑ ዕቃውን ለተበዳሪው በሚያስረክብበት ወቅት የባለቤትነት መብትም አብሮ መተላለፍ መቻሉ ነው፡፡ 3ኛ ዋስትና የመስጠት ግዴታ፡- ሌላኛው የሻጭ ግዴታ ከተሸጠው ዕቃ ጋር በተገናኘ ለሚፈጠሩ ችግሮች ለገዥው ዋስትና የመስጠት ግዴታ ነው፡፡
የተበዳሪውን ግዴታዎች በተመለከተ ሙሉ ለሙሉ በሚባል ሁኔታ ዕዳውን መልሶ ከመክፈል ጋር የሚገናኝ ነው፡፡ ተበዳሪ የብድር ውል ውስጥ ሲገባ የተበደረውን ነገር በዓይነቱ ለመመለስ ወይም በገንዘብ የሚመለስ ሲሆን እነዚህን በወቅቱ የመመለስ ግዴታ አለበት፡፡ የብድሩ አመላለስ በማገልገል የሚያልቅ ሲሆን ደግሞ ለአበዳሪው ተገቢውን)
የብድር ማስረጃ፡- ማስረጃ ማለት አንድ በፍርድ ቤት ምርመራ ላይ ያለ በጭብጥ የተያዘ አከራካሪ ጉዳይ እውነት መሆንና አለመሆኑን በሚያሳምን ሁኔታ ማረጋገጥ እንዲያስችል በግብአት የሚቀርብ ፍሬ ነገር ስለመሆኑ ብ/ጀነራል ታጠቅ ታደሰ “የማስረጃ ሕግ መሰረተ ሀሳቦች” በሚለው መፅሐፋቸው ገልፀውታል፡፡ ማስረጃ ማለት ይህ ከሆነ በሁለት ሰዎች መካከል የብድር ውል ተደርጓል ወይስ አልተደረገም የሚለውን ጥያቄ በምን ማረጋገጥ እንችላለን? የሚለውን መሰረታዊ ጥያቄ ቀጥለን እናያለን፡፡ የፍ/ሕጋችን በአን. 2472 ስር የብድር ማስረጃ በሚል ርእስ የሚከተለውን ደንግጓል፡-
(1) በብድር የተሰጠው ገንዘብ ከብር 500 በላይ ሲሆን የብድሩን ውል በፅሑፍ ወይም በፍርድ ቤት በተደረገ የእምነት ቃል ወይም መሐላ ካልሆነ በስተቀር ለማስረዳት አይቻልም፡፡
(2) ለብድር ውል ማናቸውም ሌላ ዓይነት ማስረጃ ለማቅረብ አይቻልም ፡፡ (3) እንዲሁም ከብር 500 የበለጠ ገንዘብ የመክፈል ነገር በዚህ ዓይነት ይፈፀማል፡፡ በዚህም መሰረት የብድሩ መጠን ብር 500 እና ከዛ በታች ከሆነ በማንኛውም ዓይነት ማስረጃ ለምሳሌ በቦታው የነበረ የሰው ምስክር በመስማት ማረጋገጥ የሚቻል መሆኑን እና መጠኑ ከዛ በላይ ከሆነ ግን ከሦስቱ የማስጃ ዓይነቶች መካከል በአንዱ ካልሆነ በስተቀር በሌላ በምንም መንገድ ማረጋገጥ የመማይቻል መሆኑን ነው መረዳት የሚቻለው፡፡ እነዚህን ሦስት የማስረጃ ዓይነቶች ቀጥለን እንመልከት፡፡
የመጀመሪያውና የበለጠ አስተማማኝ የሆነው ማስረጃ የፅሑፍ ማስረጃ ነው፡፡ ይህም ማለት ገና ከጅምሩ የብድር ውሉ ሲደረግ በፅሑፍ የተደረገ ሲሆን ያንን ፅሑፍ ለፍርድ ቤት በማቅረብ ማስረዳት ይቻላል፡፡ በሌላ አነጋገር ከብር 500 በላይ የሆነ የብድር ውል በፅሑፍ እንዲሆን ሕጉ አስገዳጅ የሚመስል ድንጋጌ ያስቀመጠ በመሆኑ ከላይ ካነሳነው የውል አመሰራረት መርሆች መካከል የተለየ ፎርም የሚፈልግ መሆኑን ማየት ይቻላል፡፡ ሁለተኛው የማረጋገጫ መንገድ በፍርድ ቤት በተደረገ የእምነት ቃል ነው፡፡ ይህም ማለት ተበዳሪው በፍርድ ቤት ቀርቦ በከሳሹ የቀረበበትን ክስ ማለትም ከከሳሹ ገንዘብ የተበደረ መሆኑን፣ መጠኑ ምን ያክል እንደሆነ በማያሻማ መንገድ ካመነ በቀላሉ የብድሩ መኖር የሚረጋገጥ ይሆናል፡፡ ሦስተኛውና የመጨረሻው የማረጋገጫ መንገድ በመሐላ የማረጋገጥ ሂደት ነው፡፡ መሐላ ማለት በክርክር ወቅት አንድ ተከራካሪ ወገን በሚያቀርበው ማስረጃ ወይም በሚናገረው ፍሬ ነገር እውነትነትን ለማረጋገጥ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀ ቅፅ ላይ የሚሰጡት ማረጋገጫ ነው፡፡
የብድር መመለሻ ጊዜ፡- ብድር ውል እንደመሆኑ መጠን ለተዋዋይ ወገኖች ሰፊ ነፃነት መሰጠት አለበት፡፡ በመሆኑም ሕጉ ስለብድር መመለሻ ጊዜ በተዋዋይ ወገኖች የተወሰነ ጊዜ በሚኖርበት ወቅት ይህንኑ ዕውቅና በመስጠት ክፍያው በዛ ጊዜ መሆን እንደሚገባው ሕጉ አፅንኦት ሰጥቶበታል፡፡ ከዚህም ባለፈ ብድሩ ወለድ የሌለበት ከሆነ የተበደረውን ገንዘብ ለመመለስ ማሰቡን ለአበዳሪው ከአንድ ወር በፊት አስታውቆ የመመለሻ ጊዜው ከመድረሱ በፊት ሊመልስለት እንደሚችልም ሕጉ ይደነግጋል፡፡ የብድሩ መመለሻ ጊዜ በተዋዋይ ወገኖች ያልተወሰ በሚሆን ጊዜ ሕጉ ብድሩ በምን ያክል ጊዜ ውስጥ ሊከፈል እንደሚገባው ደንግጓል፡፡ ይኼውም አበዳሪው መልስልኝ ሲል ከጠየቀበት ቀን አንስቶ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ መመለስ እንዳለበት ተደንግጓል፡፡.........
(የፍትሐብሔር ሕግ ከቁጥር 2471-2489)
የብድር ውል ምንነት፡- የተለያዩ ፅሑፎች እንደሚያስረዱት ብድርን በተመለከተ ሁሉንም ሊያግባባ የሚችል አንድ ወጥ የሆነ ትርጉም አናገኝለትም፡፡ የፍትሐብሔር ሕጋችን የሚከተለውን ትርጉም ሰጥቶታል፡- “የሚያልቅ ነገር ብድር ማለት ከተዋዋዮቹ አንዱ ወገን አበዳሪው ሌላውን ተበዳሪ ሰው የተበደረውን ነገር በዓይነቱ ለመመለስ ተገዳጅ በማደረግ ገንዘብ ወይም በማገልገል የሚያልቅ ሌላ ነገር ለተበዳሪው ለመስጠትና ሀብትነቱን ለማስተላለፍ የሚገደድበት ውል ነው” ይላል፡፡ ከዚህ ትርጓሜ መረዳት እንደሚቻለው ብድርን በሚመለከት ሕጉ በሚያልቅ ነገር ላይ ብቻ እንጂ ከዛ ባለፈ ማለትም በማያልቅ ነገር ወይም ቋሚ የሆነ ንብረትን የማያካትት መሆኑን ነው፡፡ የድንጋጌውን አጠቃላይ ይዘት ስናይ አመላለሱ በዓይነት ወይም በአገልግሎት ሊሆን እንደሚችል እና ውሉ አስገዳጅ መሆኑንም ያሳያል፡፡
የዉል አመሠራረት፡- የብድር ውል የውል አንድ አካል እንደመሆኑ መጠን አመሰራረቱም ሆነ አፈፃፀሙ በጠቅላላው የውል ሕግ መርሆች የሚገዛ በመሆኑ የብድር ውልን ዝርዝር ድንጋጌዎች ከማየታችን በፊት ስለውል አመሰራረት ባጭሩ አይተን ብናልፍ የተሻለ ግንዘቤን ይፈጥራል፡፡ ዉል ስምምነት ቢሆንም ከሌሎች ስምምነቶች የሚለየዉ በአፈፃፀሙ ከበስተጀርባዉ የሕግ ድጋፍ ያለዉ ስምምነት መሆኑ ላይ ነዉ፡፡
አንድ ውል የሚፀና ውል ነው ለማለት የሚከተሉትን መርሆች ማሟላት አለበት፡- 1ኛ ዉል የሚፈፀመዉ ለመዋዋል ችሎታ ባላቸዉ ሰዎች መካከል ብቻ መሆኑ (እድሜዉ ለአቅመ አዳም/ሄዋን ያልደረሰ ወይም አይምሮዉ ህመም ያለበት ሰዉ ወይም በፍርድ ቤት የተከለከለ ሰዉ ችሎታ እንደሌለዉ ይቆጠራል፡፡) 2ኛ ዉል የሚደረገው በተወያያቹ ነፃ ፍቃድ ብቻ የሚደረግ መሆኑ፡፡ 3ኛ ተወያይ ወገኖች የሚዋዋሉበት ጉዳይ በእርግጠኝነት የሚቻል እና ህጋዊና ሞራላዊ ጉዳይ ላይ መሆን የሚገባው መሆኑ፡፡ 4ኛ የዉል አቀራረጹ ወይም አፃፃፉ (ፎርም) በህግ ተለይተዉ የተቀመጡ ወይም ተዋዋይ ወገኖች ተለይቶ እንዲቀመጥ ከተስማሙበት የዉል ጉዳይ በቀር የተለየ የዉል ፎርም አያስፈልግም፡፡
የአበዳሪና ተበዳሪ ግዴታዎች፡- አበዳሪና ተበዳሪ የራሳቸው የሆኑ ሊያከብሯቸው የሚገቡ ግዴታዎች አሉባቸው፡፡ በቅድሚያ የአበዳሪው ግዴታዎችን ስናይ ሕጉ የአበዳሪውን ግዴታዎች በተመለከተ የሽያጭ ውልን በሚደነግገው ክፍል ላይ የሻጩ ግዴታዎች ተብለው የተገለፁት ደንቦች በአበዳሪ ላይ ተግባራዊ ይሆናሉ ይላል፡፡ በፍትሐብሔር ሕጉ የሻጭ ግዴታዎች ናቸው የተባሉት ደግሞ የሚከተሉት ናቸው፡፡
1ኛ ዕቃ የማስረከብ ግዴታ፡- የሽያጭ ውል ከተከናወነ በኋላ ሻጭ የግብይት ምክንያት የሆንውን ዕቃ/ንብረት ለገዥ የማስረከብ ግዴታ አለበት፡፡ 2ኛ ስመ-ሀብት የማስተላለፍ ግዴታ፡- ከላይ ለማንሳት እንደተሞከረው የሽያጭ ውል ልዩ መገልጫ ከሆኑት ጉዳዮች ውስጥ ሻጩ የሽጭ ምክንያት የሆነውን ንብረት ስመ-ሀብትን የማስተላለፍ ግዴታ ያለበት መሆኑ ነው፡፡ የባለቤትነት መብት መተላለፍን በተመለከተ የብድር ውል ከሽያጭ ውል ለየት የሚያደርገው ነገር ቢኖር የብድር ውሉ በትርጉም ክፍሉ ላይ እንደሰፈረው አላቂ ዕቃን ብቻ የሚመለከት በመሆኑ ዕቃውን ለተበዳሪው በሚያስረክብበት ወቅት የባለቤትነት መብትም አብሮ መተላለፍ መቻሉ ነው፡፡ 3ኛ ዋስትና የመስጠት ግዴታ፡- ሌላኛው የሻጭ ግዴታ ከተሸጠው ዕቃ ጋር በተገናኘ ለሚፈጠሩ ችግሮች ለገዥው ዋስትና የመስጠት ግዴታ ነው፡፡
የተበዳሪውን ግዴታዎች በተመለከተ ሙሉ ለሙሉ በሚባል ሁኔታ ዕዳውን መልሶ ከመክፈል ጋር የሚገናኝ ነው፡፡ ተበዳሪ የብድር ውል ውስጥ ሲገባ የተበደረውን ነገር በዓይነቱ ለመመለስ ወይም በገንዘብ የሚመለስ ሲሆን እነዚህን በወቅቱ የመመለስ ግዴታ አለበት፡፡ የብድሩ አመላለስ በማገልገል የሚያልቅ ሲሆን ደግሞ ለአበዳሪው ተገቢውን)
የብድር ማስረጃ፡- ማስረጃ ማለት አንድ በፍርድ ቤት ምርመራ ላይ ያለ በጭብጥ የተያዘ አከራካሪ ጉዳይ እውነት መሆንና አለመሆኑን በሚያሳምን ሁኔታ ማረጋገጥ እንዲያስችል በግብአት የሚቀርብ ፍሬ ነገር ስለመሆኑ ብ/ጀነራል ታጠቅ ታደሰ “የማስረጃ ሕግ መሰረተ ሀሳቦች” በሚለው መፅሐፋቸው ገልፀውታል፡፡ ማስረጃ ማለት ይህ ከሆነ በሁለት ሰዎች መካከል የብድር ውል ተደርጓል ወይስ አልተደረገም የሚለውን ጥያቄ በምን ማረጋገጥ እንችላለን? የሚለውን መሰረታዊ ጥያቄ ቀጥለን እናያለን፡፡ የፍ/ሕጋችን በአን. 2472 ስር የብድር ማስረጃ በሚል ርእስ የሚከተለውን ደንግጓል፡-
(1) በብድር የተሰጠው ገንዘብ ከብር 500 በላይ ሲሆን የብድሩን ውል በፅሑፍ ወይም በፍርድ ቤት በተደረገ የእምነት ቃል ወይም መሐላ ካልሆነ በስተቀር ለማስረዳት አይቻልም፡፡
(2) ለብድር ውል ማናቸውም ሌላ ዓይነት ማስረጃ ለማቅረብ አይቻልም ፡፡ (3) እንዲሁም ከብር 500 የበለጠ ገንዘብ የመክፈል ነገር በዚህ ዓይነት ይፈፀማል፡፡ በዚህም መሰረት የብድሩ መጠን ብር 500 እና ከዛ በታች ከሆነ በማንኛውም ዓይነት ማስረጃ ለምሳሌ በቦታው የነበረ የሰው ምስክር በመስማት ማረጋገጥ የሚቻል መሆኑን እና መጠኑ ከዛ በላይ ከሆነ ግን ከሦስቱ የማስጃ ዓይነቶች መካከል በአንዱ ካልሆነ በስተቀር በሌላ በምንም መንገድ ማረጋገጥ የመማይቻል መሆኑን ነው መረዳት የሚቻለው፡፡ እነዚህን ሦስት የማስረጃ ዓይነቶች ቀጥለን እንመልከት፡፡
የመጀመሪያውና የበለጠ አስተማማኝ የሆነው ማስረጃ የፅሑፍ ማስረጃ ነው፡፡ ይህም ማለት ገና ከጅምሩ የብድር ውሉ ሲደረግ በፅሑፍ የተደረገ ሲሆን ያንን ፅሑፍ ለፍርድ ቤት በማቅረብ ማስረዳት ይቻላል፡፡ በሌላ አነጋገር ከብር 500 በላይ የሆነ የብድር ውል በፅሑፍ እንዲሆን ሕጉ አስገዳጅ የሚመስል ድንጋጌ ያስቀመጠ በመሆኑ ከላይ ካነሳነው የውል አመሰራረት መርሆች መካከል የተለየ ፎርም የሚፈልግ መሆኑን ማየት ይቻላል፡፡ ሁለተኛው የማረጋገጫ መንገድ በፍርድ ቤት በተደረገ የእምነት ቃል ነው፡፡ ይህም ማለት ተበዳሪው በፍርድ ቤት ቀርቦ በከሳሹ የቀረበበትን ክስ ማለትም ከከሳሹ ገንዘብ የተበደረ መሆኑን፣ መጠኑ ምን ያክል እንደሆነ በማያሻማ መንገድ ካመነ በቀላሉ የብድሩ መኖር የሚረጋገጥ ይሆናል፡፡ ሦስተኛውና የመጨረሻው የማረጋገጫ መንገድ በመሐላ የማረጋገጥ ሂደት ነው፡፡ መሐላ ማለት በክርክር ወቅት አንድ ተከራካሪ ወገን በሚያቀርበው ማስረጃ ወይም በሚናገረው ፍሬ ነገር እውነትነትን ለማረጋገጥ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀ ቅፅ ላይ የሚሰጡት ማረጋገጫ ነው፡፡
የብድር መመለሻ ጊዜ፡- ብድር ውል እንደመሆኑ መጠን ለተዋዋይ ወገኖች ሰፊ ነፃነት መሰጠት አለበት፡፡ በመሆኑም ሕጉ ስለብድር መመለሻ ጊዜ በተዋዋይ ወገኖች የተወሰነ ጊዜ በሚኖርበት ወቅት ይህንኑ ዕውቅና በመስጠት ክፍያው በዛ ጊዜ መሆን እንደሚገባው ሕጉ አፅንኦት ሰጥቶበታል፡፡ ከዚህም ባለፈ ብድሩ ወለድ የሌለበት ከሆነ የተበደረውን ገንዘብ ለመመለስ ማሰቡን ለአበዳሪው ከአንድ ወር በፊት አስታውቆ የመመለሻ ጊዜው ከመድረሱ በፊት ሊመልስለት እንደሚችልም ሕጉ ይደነግጋል፡፡ የብድሩ መመለሻ ጊዜ በተዋዋይ ወገኖች ያልተወሰ በሚሆን ጊዜ ሕጉ ብድሩ በምን ያክል ጊዜ ውስጥ ሊከፈል እንደሚገባው ደንግጓል፡፡ ይኼውም አበዳሪው መልስልኝ ሲል ከጠየቀበት ቀን አንስቶ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ መመለስ እንዳለበት ተደንግጓል፡፡.........
.......................ተበዳሪውም በአበዳሪው ሳይጠየቅ መክፈል ቢፈልግ ለመክፈል ያለውን ሀሳብ ከአንድ ወር በፊት ካስታወቀ በኋላ ዕዳውን መመለስ እንደሚችል እንዲሁ ተደንግጓል፡፡
በብድር ላይ ሊኖር ስለሚችል ወለድ፡- በብድር ውል ላይ ሊኖር ስለሚችል ወለድም ለተዋዋይ ወገኖች ነፃ ፈቃድ የተተወ ጉዳይ ነው፡፡ ብድሩ ወለድ የሚከፈልበት ስለመሆኑ በውሉ በግልፅ ካልተገለፀ ግን ተበዳሪው በምንም መልኩ ወለድ እንዳይከፍል ሕጉ ጥበቃ ያደርግለታል፡፡ ሕጉ በብድር ውሉ ላይ ወለድ ይኑር አይኑር የሚለውን ጉዳይ በተዋዋይ ወገኖች እንዲወሰን ነፃነት የሰጠ ቢሆንም በወለድ መጠኑ ልክ ላይና ስለሚከፈልበት ጊዜ ወይም ወለዱ ስለሚሰላበት ጊዜ ግን ገደብ አስቀምጧል፡፡ በዚህም መሰረት ተዋዋይ ወገኖች የወለዱን መጠን በዓመት ከ12 በመቶ በላይ ማድረግ እንደማይችሉ ገደብ ጥሏል፡፡ እንዲሁም የወለዱ መጠን በውሉ ላይ ካልተገለፀ እና ወለድ የሚከፈልበት ብድር መሆኑ ብቻ ተገልፆ ከሆነ ወይም ወለዱ ከ12 በመቶ በላይ ይሆናል የሚል የውል ቃል ካለ መከፈል የሚችለው የወለድ መጠን በዓመት 9 በመቶ ብቻ እንደሚሆንና የሚሰላውም ተቃራኒ የሚሆን የውል ቃል ከሌለ ብድሩ ከተሰጠበት ጊዜ ጀምሮ በሚቆጠር በየዓመቱ መጨረሻ ላይ መሆን ይገባዋል ይላል ሕጉ ፡፡
የብድር አከፋፈል (የሚከፈለው ነገር)፡- በብድር አመላለስ ወቅት ሌላው ግለፅ መሆን ያለበት ጉዳይ ብድሩ በየትኛው ሀገር የገንዘብ ዓይነት ነው? ከብድሩ በኋላ የምንዛሬ ዋጋ መለዋወጥ ቢያጋጥምስ ምን ይሆናል? የሚለው ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ የፍትሐብሔር ሕጉ ግልፅ ድንጋጌዎች አሉት፡፡ በዚህም መሰረት የብድር ውሉ የተደረገው በኢትዮጵያ ብር ከሆነ ብድሩ በሚመለስበት ወቅት ባለው ሕጋዊ የኢትዮጵያ የመገበያያ ገንዘብ ወይም ለዚህ የገንዘብ መጠን የሚተካ የውጭ ምንዛሬ በማቅረብ ከዕዳው ነፃ እንደሚሆን ተደንግጓል፡፡ የሚከፈለውን የገንዘብ መጠን በተመለከተ የብድር ውሉ በሚከናወንበት ጊዜ በትክክል የተበደረውን ያክል እንጂ ሌላ ነገር እንደማያካትትና በመሀል ሊያጋጥም የሚችለውን ወይም ያገጠመውን የገንዘቡ ዋጋ መለዋወጥ ግምት ውስጥ መግባት እንደሌለበትም ሕጉ አያይዞ ይገልፃል፡፡ ብድሩ በውጭ አገር ገንዘብ ተደርጎ ከነበረ ደግሞ ብድሩ በሚከፈልበት ጊዜ በዛ አገር ሕጋዊ መገበያያ በሆነው የገንዘብ ኖት መከፈል ያለበት ሲሆን መጠኑም የተበደረውን ያክል ብቻ መሆን እንዳለበት ሕጉ አመልክቷል፡፡ የብድር ውሉ የተደረገው ከገንዘብ ውጪ ባሉ የሀብት ዓይነቶች በሚሆንበት ጊዜ ለምሳሌ፡- ለምግብ የሚሆኑ ነገሮች፣ ሸቀጦች ወይም መአድናት ሲሆኑ ተበዳሪው በተበደረው ልክ ብዛቱንና ዓይነቱን በመክፈል ከዕዳው ነፃ ይሆናል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ከብድሩ በኋላ በሚኖር የዋጋ መለዋወጥ የብድድር አመላለሱን መጠንና ዓይነት ላይ የሚያሳድረው ተፅእኖ የለም፡፡
federal attorney general
share share
#share #Share
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
በብድር ላይ ሊኖር ስለሚችል ወለድ፡- በብድር ውል ላይ ሊኖር ስለሚችል ወለድም ለተዋዋይ ወገኖች ነፃ ፈቃድ የተተወ ጉዳይ ነው፡፡ ብድሩ ወለድ የሚከፈልበት ስለመሆኑ በውሉ በግልፅ ካልተገለፀ ግን ተበዳሪው በምንም መልኩ ወለድ እንዳይከፍል ሕጉ ጥበቃ ያደርግለታል፡፡ ሕጉ በብድር ውሉ ላይ ወለድ ይኑር አይኑር የሚለውን ጉዳይ በተዋዋይ ወገኖች እንዲወሰን ነፃነት የሰጠ ቢሆንም በወለድ መጠኑ ልክ ላይና ስለሚከፈልበት ጊዜ ወይም ወለዱ ስለሚሰላበት ጊዜ ግን ገደብ አስቀምጧል፡፡ በዚህም መሰረት ተዋዋይ ወገኖች የወለዱን መጠን በዓመት ከ12 በመቶ በላይ ማድረግ እንደማይችሉ ገደብ ጥሏል፡፡ እንዲሁም የወለዱ መጠን በውሉ ላይ ካልተገለፀ እና ወለድ የሚከፈልበት ብድር መሆኑ ብቻ ተገልፆ ከሆነ ወይም ወለዱ ከ12 በመቶ በላይ ይሆናል የሚል የውል ቃል ካለ መከፈል የሚችለው የወለድ መጠን በዓመት 9 በመቶ ብቻ እንደሚሆንና የሚሰላውም ተቃራኒ የሚሆን የውል ቃል ከሌለ ብድሩ ከተሰጠበት ጊዜ ጀምሮ በሚቆጠር በየዓመቱ መጨረሻ ላይ መሆን ይገባዋል ይላል ሕጉ ፡፡
የብድር አከፋፈል (የሚከፈለው ነገር)፡- በብድር አመላለስ ወቅት ሌላው ግለፅ መሆን ያለበት ጉዳይ ብድሩ በየትኛው ሀገር የገንዘብ ዓይነት ነው? ከብድሩ በኋላ የምንዛሬ ዋጋ መለዋወጥ ቢያጋጥምስ ምን ይሆናል? የሚለው ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ የፍትሐብሔር ሕጉ ግልፅ ድንጋጌዎች አሉት፡፡ በዚህም መሰረት የብድር ውሉ የተደረገው በኢትዮጵያ ብር ከሆነ ብድሩ በሚመለስበት ወቅት ባለው ሕጋዊ የኢትዮጵያ የመገበያያ ገንዘብ ወይም ለዚህ የገንዘብ መጠን የሚተካ የውጭ ምንዛሬ በማቅረብ ከዕዳው ነፃ እንደሚሆን ተደንግጓል፡፡ የሚከፈለውን የገንዘብ መጠን በተመለከተ የብድር ውሉ በሚከናወንበት ጊዜ በትክክል የተበደረውን ያክል እንጂ ሌላ ነገር እንደማያካትትና በመሀል ሊያጋጥም የሚችለውን ወይም ያገጠመውን የገንዘቡ ዋጋ መለዋወጥ ግምት ውስጥ መግባት እንደሌለበትም ሕጉ አያይዞ ይገልፃል፡፡ ብድሩ በውጭ አገር ገንዘብ ተደርጎ ከነበረ ደግሞ ብድሩ በሚከፈልበት ጊዜ በዛ አገር ሕጋዊ መገበያያ በሆነው የገንዘብ ኖት መከፈል ያለበት ሲሆን መጠኑም የተበደረውን ያክል ብቻ መሆን እንዳለበት ሕጉ አመልክቷል፡፡ የብድር ውሉ የተደረገው ከገንዘብ ውጪ ባሉ የሀብት ዓይነቶች በሚሆንበት ጊዜ ለምሳሌ፡- ለምግብ የሚሆኑ ነገሮች፣ ሸቀጦች ወይም መአድናት ሲሆኑ ተበዳሪው በተበደረው ልክ ብዛቱንና ዓይነቱን በመክፈል ከዕዳው ነፃ ይሆናል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ከብድሩ በኋላ በሚኖር የዋጋ መለዋወጥ የብድድር አመላለሱን መጠንና ዓይነት ላይ የሚያሳድረው ተፅእኖ የለም፡፡
federal attorney general
share share
#share #Share
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
የ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ማለፊያ ነጥብ ይፋ ሆነ።
የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴኤታ ሳሙኤል (ዶ/ር) ለጋዜጠኞች የ12ኛ ክፍል መለቀቂያ ፈተና መቁረጫ ነጥብ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል።
በሁለት ዙር ለተሰጠው የመልቀቂያ ፈተና የተሰጠው የማለፊያ ነጥብ የተለያየ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዚህም መሰረት በመጀመሪያ ዙር ፈተናቸውን የወሰዱ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች ውጤት የሚከተለውን ይመስላል
በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 363 ለሴት 351 ሲሆን በተፈጥሮ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 351 ለሴት 339 ማለፊያ ነጥብ መሆኑ ተገልጿል።ለተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 300 ሆኗል።በተፈጥሮ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብም 380 ሆኖ መቆረጡ ተገልጿል።
በመጀመሪያው ዙር የተፈተኑ እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 300 ሆኗል።
ለማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች የማለፊያ ነጥብ ለወንድ 264፣ ለሴት 254 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 254፣ ለሴት 250 ማለፊያ ነጥብ ሆኖ ተቆርጧል።
ለማህበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታዎች ማለፊያ ነጥብ 250 መሆኑን እና በማህበራዊ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ለሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 280 እንደሆነ ተገልጿል።
በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የማህበራዊ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 250 ሆኗል።
በሁለተኛ ዙር ፈተናቸውን የወሰዱ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች ውጤትም ይፋ የሆነ ሲሆን በዚህም መሰረት
በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 423 ለሴት 409 ሲሆን በተፈጥሮ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 410 ለሴት 396 ማለፊያ ነጥብ መሆኑ ተገልጿል።ለተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 350 ሆኗል።በተፈጥሮ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብም 443 ሆኖ መቆረጡ ተገልጿል።
በሁለተኛ ዙር የተፈተኑ እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ ከ350 በላይ መሆኑ ተነግሯል።
ለማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች የማለፊያ ነጥብ ለወንድ 317 ፣ ለሴት 305 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 305፣ ለሴት 300 ማለፊያ ነጥብ ሆኖ ተቆርጧል።
ለማህበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታዎች ማለፊያ ነጥብ 300 መሆኑን እና በማህበራዊ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ለሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 335 እንደሆነ ተገልጿል።
በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የማህበራዊ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ ከ 300 በላይ መሆኑም ተገለጿል።
ውጤቱ ለመጀመርያ ዙር ተፈታኞች ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ600 እዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ከ500 የተያዘ መሆኑን እና በሁለተኛ ዙር ተፈታኞች ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ700 እዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ከ600 የተያዘ መሆኑ ተገልጿል።
ምንጭ፦ ትምህርት ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴኤታ ሳሙኤል (ዶ/ር) ለጋዜጠኞች የ12ኛ ክፍል መለቀቂያ ፈተና መቁረጫ ነጥብ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል።
በሁለት ዙር ለተሰጠው የመልቀቂያ ፈተና የተሰጠው የማለፊያ ነጥብ የተለያየ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዚህም መሰረት በመጀመሪያ ዙር ፈተናቸውን የወሰዱ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች ውጤት የሚከተለውን ይመስላል
በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 363 ለሴት 351 ሲሆን በተፈጥሮ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 351 ለሴት 339 ማለፊያ ነጥብ መሆኑ ተገልጿል።ለተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 300 ሆኗል።በተፈጥሮ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብም 380 ሆኖ መቆረጡ ተገልጿል።
በመጀመሪያው ዙር የተፈተኑ እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 300 ሆኗል።
ለማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች የማለፊያ ነጥብ ለወንድ 264፣ ለሴት 254 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 254፣ ለሴት 250 ማለፊያ ነጥብ ሆኖ ተቆርጧል።
ለማህበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታዎች ማለፊያ ነጥብ 250 መሆኑን እና በማህበራዊ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ለሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 280 እንደሆነ ተገልጿል።
በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የማህበራዊ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 250 ሆኗል።
በሁለተኛ ዙር ፈተናቸውን የወሰዱ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች ውጤትም ይፋ የሆነ ሲሆን በዚህም መሰረት
በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 423 ለሴት 409 ሲሆን በተፈጥሮ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 410 ለሴት 396 ማለፊያ ነጥብ መሆኑ ተገልጿል።ለተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 350 ሆኗል።በተፈጥሮ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብም 443 ሆኖ መቆረጡ ተገልጿል።
በሁለተኛ ዙር የተፈተኑ እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ ከ350 በላይ መሆኑ ተነግሯል።
ለማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች የማለፊያ ነጥብ ለወንድ 317 ፣ ለሴት 305 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 305፣ ለሴት 300 ማለፊያ ነጥብ ሆኖ ተቆርጧል።
ለማህበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታዎች ማለፊያ ነጥብ 300 መሆኑን እና በማህበራዊ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ለሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 335 እንደሆነ ተገልጿል።
በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የማህበራዊ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ ከ 300 በላይ መሆኑም ተገለጿል።
ውጤቱ ለመጀመርያ ዙር ተፈታኞች ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ600 እዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ከ500 የተያዘ መሆኑን እና በሁለተኛ ዙር ተፈታኞች ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ700 እዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ከ600 የተያዘ መሆኑ ተገልጿል።
ምንጭ፦ ትምህርት ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
በኮንስትራክሽን ውል ስለ ግንባታ ስራ ርክክብ/Acceptance/
======**=======
#በኮንስትራክሽን ውል ሁለት አይነት የግንባታ ስራ ርክክብ ያለ ሲሆን ይሄውም ግዚያዊ ርክክብ(provisional acceptance) እና የመጨረሻ ርክክብ(final acceptance) የሚያካትት ነው፡፡
#በዚህ ጽሁፍ በዋናነት በኮንስትራክሽን ውል ህግ እውቅና የተሰጣቸውን የርክክብ አይነቶች ምንነትና ተያያዥ ውጤታቸውን አስመልክቶ የህግ ድንጋጌዎችን እና አሁን ላይ በመንግስት ተቋማት እየተሰራበት ያለውን የፒፒኤ 2011 ጀኔራል ኮንዲሽን ድንጋጌዎችን ባካተተ ሁኔታ ለማብራራት ተሞክሯል፡፡
**
#ግዚያዊ ርክክብ/Provisional Acceptance/
#ግዜአዊ ርክክብ በተለይ በኮንስትራክሽን ውል የተመለከቱ የግንባታ ስራዎች ተከናውነው ካበቁ በኋላ ወዲያውኑ ሁለቱ ወገኖች ማለትም አሰሪውና ተቋራጩ ባሉበት በስራው ላይ የሚደረግ የምርመራ ማረጋገጫ ስለመሆኑ የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3274(1) ይደነግጋል፡፡ ይሄውም አሰሪው በትክክል የተገነባውን ግንባታ በእጁ አግብቶ መያዙን ጭምር ያረጋግጣል፡፡ ስለዚህ ጊዜአዊ ርክክብ በዋናነት የተሰራውን የግንባታ ስራ አሰሪው መብቱን ጠብቆ በመጀመሪያ የሚረከብበት ሂደት ነው ማለት ነው፡፡በስራው ላይ ምርመራ መደረጉንም የሚያረጋግጥ ነው፡፡
#ፒፒኤ 2011 ክሎስ 84.1 ላይ የስራ ምርመራ/verification and test/ በመሀንዲሱ ተቋራጭ ባለበት ሊደረግ እንደሚገባ በመርህ ደረጃ ተቀምጧል፡፡ሆኖም ግን ተቋራጩ ምርመራው ከሚካሄድበት እለት ከ30 ቀን በፊት በተገቢ ሁኔታ እንዲያውቀው ተደርጐ በምርመራው እለት ያልተገኘ እንደሆነ የስራ ምርመራው ተቋራጩ በሌለበት ሊካሄድ እንደሚችል ይፈቅዳል፡፡
#እንግዲህ መሀንዲሱ ስራውን ከመረመረ በኋላ ያላመነበትን የስራ ክፍል ፈርሶ እንደገና እንዲሰራ ወይም እንዲጠገን ተደርጐ የጥራት ደረጃውን ባሟላ ሁኔታ እንዲከናወን ለማዘዝ እንደሚችል ፒፒኤ ክሎስ 85 ይፈቅድለታል፡፡
#በዚህም መሰረት ግንባታው የስራ ምርመራውን ካለፈ አሰሪው ግንባታውን የሚረከበው ይሆናል ማለት ነው፡፡ስለዚሁም የጊዜአዊ ርክክብ ሰርተፍኬት ለተቋራጩ የሚሰጠው ይሆናል፡፡በመሰረቱ ተቋራጩ የጊዜአዊ ርክክብ ሰርተፍኬት እንዲሰጠው መጠየቅ ያለበት ስራው ሊጠናቀቅ ይችላል ብሎ ከሚያስብበት ከ15 ቀን በፊት መሆን ይኖርበታል፡፡ከዚያም መሀንዲሱ ጥያቄው በደረሰው በ30 ቀን ውስጥ የስራ ምርመራውን አጠናቆ ሰርተፍኬቱን መስጠት ወይም ጥያቄውን ውድቅ ማድረግ ይኖርበታል፡፡መሀንዲሱ ሰርተፍኬቱን ሳይሰጥ ወይም ጥያቄውን ውድቅ ሳያደርግ 30 ቀኑ ያለፈ እንደሆነ ለተቋራጩ የጊዜአዊ ርክክብ ሰርተፍኬት እንደተሰጠው ግምት እንደሚወሰድ ፒፒኤ ክሎስ 87 ያስቀምጣል፡፡
#ሌላው ተቋራጩ በስራው ላይ ያደረገው መሻሻል/መለወጥ ቢኖር እንኳ በዝምታ ግዜአዊ ርክክብ ከተደረገ መሻሻሉ ተቀባይነት እንዳገኘ የህግ ግምት እንደሚያስወስድ የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3275(2) ይደነግጋል፡፡እዚህ ላይ ተቋራጩ በተሰጠው ዲዛይን መሰረት የመስራት ግዴታ ያለበት መሆኑ ይታዎቅ፡፡ ስለዚህ የህግ ግምቱ እሳቤ ተቋራጩ ከዲዛይኑ በመውጣት አሻሽሎ የሰራው ስራ ኖሮ በግዜአዊ ርክክብ ወቅት በዝምታ አሰሪው ካለፈው እንደተቀበለው ይቆጠራል ነው፡፡
#እንዲሁም ግዜአዊ ርክክብ መደረጉ የመድህንነት ጊዜው(warranty period) መጀመሩን እንደሚያመለክት የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3275(3) ይደነግጋል፡፡
**
#የመድህንነት ጊዜ(warranty period/Defects Liability period)
#የመድህንነት ጊዜ(warranty period) የሚባለው ከጊዜአዊ ርክክብ እስከ መጨረሻ ርክክብ ያለው ጊዜ ሲሆን አሰሪው ግንባታው በተቋራጩ በደህና ሁኔታ ስለመሰራቱ ለመመርመርና ለማረጋገጥ የሚያስችለው ጊዜ ነው፡፡የጊዜው ርዝማኔም በውላቸው ላይ የሚወሰን ስለመሆኑ የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3277 ይደነግጋል፡፡ ሆኖም በውሉ ላይ የመድህንነት ጊዜው ርዝማኔ ያልተጠቀሰ እንደሆነ ከጊዜአዊ ርክክብ ቀን ጀምሮ 365 ቀን ስለመሆኑ የፒፒኤ ክሎስ 88.7 ያስቀምጣል፡፡
#ተቋራጩ በዚሁ በመድህንነት ጊዜ በተለይ የተበላሹ ስራዎችን እንዲያድሳቸው በአሰሪው በታዘዘ ጊዜ የማስተካከል ግዴታ እንዳለበት የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3278 ይደነግጋል፡፡ ለዚህም ለጥገና ወጭ ሲባል ከተቋራጩ ክፍያ ላይ ሪቴንሽን ገንዘብ(retention money or bond) 5% እየተቀነሰ በአሰሪው ይያዛል፡፡
#በመድህንነት ጊዜ ውስጥ የተለዩ ብልሽት ያለባቸው ስራዎችን እንዲያስተካክል ተቋራጩ ተጠይቆ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ያላስተካከለ እንደሆነ አሰሪው የማስተካከያ ስራውን በተቋራጩ ወጭ በራሱ ወይም ሌላ ቀጥሮ ሊያሰራው ወይም ውሉን ሊያቋርጥ ስለመቻሉ ፒፒኤ ክሎስ 88.3 ለአሰሪው መብት ይሰጠዋል፡፡
**
#ከፊል ርክክብ/Partial Acceptance/
-በፒፒኤ ክሎስ 86 ላይ የግንባታ ስራው በከፊል እርክክብ የሚደረግበትንም አማራጭ ያስቀምጣል፡፡ይህ ማለት የተወሰነውን የስራ ክፍል(part of the work) ከአጠቃላይ ውሉ ጊዜ በፊት ለማስረከብ በውል ላይ ከተቀመጠ ተቋራጩ የተወሰነውን የስራ ክፍል ከአጠቃላይ የውሉ ጊዜ በፊት ለማስረከብ ይገደዳል ማለት ነው፡፡በዚህም በአንድ ውል ውስጥ በተለያየ ጊዜ ጊዜአዊ ርክክብ ሊደረግ የሚችልበትን ሁኔታ ይፈጥራል ማለት ነው፡፡
**
#የመጨረሻ ርክክብ/Final Acceptance/
#የመጨረሻ ርክክብ/Final Acceptance/ በተለይ የመድህንነት ጊዜ ካለቀ በኋላ እና ተቋራጩ ጠቅላላ ግዴታዎቹን በደህና ሁኔታ የፈጸመ መሆኑን አሰሪው ሲያረጋግጥ ግንባታውን ሙሉ በሙሉ በእጁ የሚያደርግበት(definitively appropriate) ስለመሆኑ የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3279 ይደነግጋል፡፡
#የመጨረሻ ርክክብ አሰሪውና ተቋራጩ ባሉበት በጽሁፍ መደረግ እንዳለበት በአስገዳጅ ሁኔታ በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3279(2) ላይ ተደንግጓል፡፡ሆኖም ጊዜአዊ ርክክብ/ Provisional Acceptance/ በሚመለከት ግን በጽሁፍ መደረግ እንዳለበት የሚያስገድድ ግልጽ ህግ የለም፡፡ስለዚህ ስራው ተጠናቆ አሰሪው ግንባታውን በእጁ ካስገባ ጊዜአዊ ርክክብ መደረጉን የሚያስገነዝብ ይሆናል ማለት ነው፡፡በእርግጥ በጽሁፍ መደረጉ ይመከራል፡፡
#በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3282 ላይ እንደተቀመጠው ከመጨረሻ ርክክብ በኋላ ተቋራጩ እስከ 10 አመት ድረስ ስለስራው አሰራር ጉድለት ተቋራጩ ሀላፊነት አለበት፣መድህን ሆኖ ይቀጥላል፡፡በመጨረሻ ርክክብ ወቅት የሚታዩ ለነበሩ ጉድለቶች(apparent defect) ግን ተቋራጩ ሀላፊነት የለበትም፡፡ሀላፊነቱ የሚመለከተው ግንባታው በውሉ የተመለከተውን የታለመለትን ጥቅም እንዳይሰጥ የሚያደርጉ ወይም አጠቃቀሙን በጣም ውድ የሚያደርጉና አክሳሪ የሚያደርጉ ጉድለቶችን ነው፡፡
#henoktayelawoffice
======**=======
#በኮንስትራክሽን ውል ሁለት አይነት የግንባታ ስራ ርክክብ ያለ ሲሆን ይሄውም ግዚያዊ ርክክብ(provisional acceptance) እና የመጨረሻ ርክክብ(final acceptance) የሚያካትት ነው፡፡
#በዚህ ጽሁፍ በዋናነት በኮንስትራክሽን ውል ህግ እውቅና የተሰጣቸውን የርክክብ አይነቶች ምንነትና ተያያዥ ውጤታቸውን አስመልክቶ የህግ ድንጋጌዎችን እና አሁን ላይ በመንግስት ተቋማት እየተሰራበት ያለውን የፒፒኤ 2011 ጀኔራል ኮንዲሽን ድንጋጌዎችን ባካተተ ሁኔታ ለማብራራት ተሞክሯል፡፡
**
#ግዚያዊ ርክክብ/Provisional Acceptance/
#ግዜአዊ ርክክብ በተለይ በኮንስትራክሽን ውል የተመለከቱ የግንባታ ስራዎች ተከናውነው ካበቁ በኋላ ወዲያውኑ ሁለቱ ወገኖች ማለትም አሰሪውና ተቋራጩ ባሉበት በስራው ላይ የሚደረግ የምርመራ ማረጋገጫ ስለመሆኑ የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3274(1) ይደነግጋል፡፡ ይሄውም አሰሪው በትክክል የተገነባውን ግንባታ በእጁ አግብቶ መያዙን ጭምር ያረጋግጣል፡፡ ስለዚህ ጊዜአዊ ርክክብ በዋናነት የተሰራውን የግንባታ ስራ አሰሪው መብቱን ጠብቆ በመጀመሪያ የሚረከብበት ሂደት ነው ማለት ነው፡፡በስራው ላይ ምርመራ መደረጉንም የሚያረጋግጥ ነው፡፡
#ፒፒኤ 2011 ክሎስ 84.1 ላይ የስራ ምርመራ/verification and test/ በመሀንዲሱ ተቋራጭ ባለበት ሊደረግ እንደሚገባ በመርህ ደረጃ ተቀምጧል፡፡ሆኖም ግን ተቋራጩ ምርመራው ከሚካሄድበት እለት ከ30 ቀን በፊት በተገቢ ሁኔታ እንዲያውቀው ተደርጐ በምርመራው እለት ያልተገኘ እንደሆነ የስራ ምርመራው ተቋራጩ በሌለበት ሊካሄድ እንደሚችል ይፈቅዳል፡፡
#እንግዲህ መሀንዲሱ ስራውን ከመረመረ በኋላ ያላመነበትን የስራ ክፍል ፈርሶ እንደገና እንዲሰራ ወይም እንዲጠገን ተደርጐ የጥራት ደረጃውን ባሟላ ሁኔታ እንዲከናወን ለማዘዝ እንደሚችል ፒፒኤ ክሎስ 85 ይፈቅድለታል፡፡
#በዚህም መሰረት ግንባታው የስራ ምርመራውን ካለፈ አሰሪው ግንባታውን የሚረከበው ይሆናል ማለት ነው፡፡ስለዚሁም የጊዜአዊ ርክክብ ሰርተፍኬት ለተቋራጩ የሚሰጠው ይሆናል፡፡በመሰረቱ ተቋራጩ የጊዜአዊ ርክክብ ሰርተፍኬት እንዲሰጠው መጠየቅ ያለበት ስራው ሊጠናቀቅ ይችላል ብሎ ከሚያስብበት ከ15 ቀን በፊት መሆን ይኖርበታል፡፡ከዚያም መሀንዲሱ ጥያቄው በደረሰው በ30 ቀን ውስጥ የስራ ምርመራውን አጠናቆ ሰርተፍኬቱን መስጠት ወይም ጥያቄውን ውድቅ ማድረግ ይኖርበታል፡፡መሀንዲሱ ሰርተፍኬቱን ሳይሰጥ ወይም ጥያቄውን ውድቅ ሳያደርግ 30 ቀኑ ያለፈ እንደሆነ ለተቋራጩ የጊዜአዊ ርክክብ ሰርተፍኬት እንደተሰጠው ግምት እንደሚወሰድ ፒፒኤ ክሎስ 87 ያስቀምጣል፡፡
#ሌላው ተቋራጩ በስራው ላይ ያደረገው መሻሻል/መለወጥ ቢኖር እንኳ በዝምታ ግዜአዊ ርክክብ ከተደረገ መሻሻሉ ተቀባይነት እንዳገኘ የህግ ግምት እንደሚያስወስድ የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3275(2) ይደነግጋል፡፡እዚህ ላይ ተቋራጩ በተሰጠው ዲዛይን መሰረት የመስራት ግዴታ ያለበት መሆኑ ይታዎቅ፡፡ ስለዚህ የህግ ግምቱ እሳቤ ተቋራጩ ከዲዛይኑ በመውጣት አሻሽሎ የሰራው ስራ ኖሮ በግዜአዊ ርክክብ ወቅት በዝምታ አሰሪው ካለፈው እንደተቀበለው ይቆጠራል ነው፡፡
#እንዲሁም ግዜአዊ ርክክብ መደረጉ የመድህንነት ጊዜው(warranty period) መጀመሩን እንደሚያመለክት የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3275(3) ይደነግጋል፡፡
**
#የመድህንነት ጊዜ(warranty period/Defects Liability period)
#የመድህንነት ጊዜ(warranty period) የሚባለው ከጊዜአዊ ርክክብ እስከ መጨረሻ ርክክብ ያለው ጊዜ ሲሆን አሰሪው ግንባታው በተቋራጩ በደህና ሁኔታ ስለመሰራቱ ለመመርመርና ለማረጋገጥ የሚያስችለው ጊዜ ነው፡፡የጊዜው ርዝማኔም በውላቸው ላይ የሚወሰን ስለመሆኑ የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3277 ይደነግጋል፡፡ ሆኖም በውሉ ላይ የመድህንነት ጊዜው ርዝማኔ ያልተጠቀሰ እንደሆነ ከጊዜአዊ ርክክብ ቀን ጀምሮ 365 ቀን ስለመሆኑ የፒፒኤ ክሎስ 88.7 ያስቀምጣል፡፡
#ተቋራጩ በዚሁ በመድህንነት ጊዜ በተለይ የተበላሹ ስራዎችን እንዲያድሳቸው በአሰሪው በታዘዘ ጊዜ የማስተካከል ግዴታ እንዳለበት የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3278 ይደነግጋል፡፡ ለዚህም ለጥገና ወጭ ሲባል ከተቋራጩ ክፍያ ላይ ሪቴንሽን ገንዘብ(retention money or bond) 5% እየተቀነሰ በአሰሪው ይያዛል፡፡
#በመድህንነት ጊዜ ውስጥ የተለዩ ብልሽት ያለባቸው ስራዎችን እንዲያስተካክል ተቋራጩ ተጠይቆ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ያላስተካከለ እንደሆነ አሰሪው የማስተካከያ ስራውን በተቋራጩ ወጭ በራሱ ወይም ሌላ ቀጥሮ ሊያሰራው ወይም ውሉን ሊያቋርጥ ስለመቻሉ ፒፒኤ ክሎስ 88.3 ለአሰሪው መብት ይሰጠዋል፡፡
**
#ከፊል ርክክብ/Partial Acceptance/
-በፒፒኤ ክሎስ 86 ላይ የግንባታ ስራው በከፊል እርክክብ የሚደረግበትንም አማራጭ ያስቀምጣል፡፡ይህ ማለት የተወሰነውን የስራ ክፍል(part of the work) ከአጠቃላይ ውሉ ጊዜ በፊት ለማስረከብ በውል ላይ ከተቀመጠ ተቋራጩ የተወሰነውን የስራ ክፍል ከአጠቃላይ የውሉ ጊዜ በፊት ለማስረከብ ይገደዳል ማለት ነው፡፡በዚህም በአንድ ውል ውስጥ በተለያየ ጊዜ ጊዜአዊ ርክክብ ሊደረግ የሚችልበትን ሁኔታ ይፈጥራል ማለት ነው፡፡
**
#የመጨረሻ ርክክብ/Final Acceptance/
#የመጨረሻ ርክክብ/Final Acceptance/ በተለይ የመድህንነት ጊዜ ካለቀ በኋላ እና ተቋራጩ ጠቅላላ ግዴታዎቹን በደህና ሁኔታ የፈጸመ መሆኑን አሰሪው ሲያረጋግጥ ግንባታውን ሙሉ በሙሉ በእጁ የሚያደርግበት(definitively appropriate) ስለመሆኑ የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3279 ይደነግጋል፡፡
#የመጨረሻ ርክክብ አሰሪውና ተቋራጩ ባሉበት በጽሁፍ መደረግ እንዳለበት በአስገዳጅ ሁኔታ በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3279(2) ላይ ተደንግጓል፡፡ሆኖም ጊዜአዊ ርክክብ/ Provisional Acceptance/ በሚመለከት ግን በጽሁፍ መደረግ እንዳለበት የሚያስገድድ ግልጽ ህግ የለም፡፡ስለዚህ ስራው ተጠናቆ አሰሪው ግንባታውን በእጁ ካስገባ ጊዜአዊ ርክክብ መደረጉን የሚያስገነዝብ ይሆናል ማለት ነው፡፡በእርግጥ በጽሁፍ መደረጉ ይመከራል፡፡
#በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3282 ላይ እንደተቀመጠው ከመጨረሻ ርክክብ በኋላ ተቋራጩ እስከ 10 አመት ድረስ ስለስራው አሰራር ጉድለት ተቋራጩ ሀላፊነት አለበት፣መድህን ሆኖ ይቀጥላል፡፡በመጨረሻ ርክክብ ወቅት የሚታዩ ለነበሩ ጉድለቶች(apparent defect) ግን ተቋራጩ ሀላፊነት የለበትም፡፡ሀላፊነቱ የሚመለከተው ግንባታው በውሉ የተመለከተውን የታለመለትን ጥቅም እንዳይሰጥ የሚያደርጉ ወይም አጠቃቀሙን በጣም ውድ የሚያደርጉና አክሳሪ የሚያደርጉ ጉድለቶችን ነው፡፡
#henoktayelawoffice
አለ_ህግ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች፣ ክሶች፣ የውል ፎርሞች፤ መፅሐፍቶች 🔴ሁሉም ሕጎች በአንድ🔴 All in one, for All.
አለ_ህግ፣ መሰረታዊ የህግ መረጃ እውቀት፤ ሀብት እና ሀይል ነው። contact us: @LawsocietiesBot or email us: lawsocieties@gmail.com
https://t.me/lawsocieties
አለ_ህግ፣ መሰረታዊ የህግ መረጃ እውቀት፤ ሀብት እና ሀይል ነው። contact us: @LawsocietiesBot or email us: lawsocieties@gmail.com
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/