አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.83K photos
25 videos
1.86K files
3.55K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች
____

የጤና ሚኒስቴር ከከተኛ ትምህርት ተቋማት በህክምና፣ ነርሲንግ፣ ሜዲካል ላብራቶሪ ሳይንስ፣ ጤና መኮንን፣ ሚድዋይፈሪ፣ ፋርማሲአንስቴዥያ፣ ዴንታል ሜድስን እና ሜዲካል ራዲዮሎጂ ቴክኖሎጂ ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ #ለተመረቁ ባለሙያዎች በሚያዝያ 2014 ዓ.ም የብቃት #ምዘና #ፈተና ለመስጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ ስለሆነም የፈተናው ምዝገባ ከየካቲት 30 እስከ መጋቢት 13/2014 ዓ.ም የሚካሄድ ስለሆነ ተመዛኞች hple.moh.gov.et ላይ በመግባት አስፈላጊውን የትምህርት ማስረጃ በማያያዝ online እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡

ማሳሰቢያ፡-

1) ከግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተመረቃችሁ ተመዛኞች ከምዝገባ በፊት የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን ህጋዊነትና ትክክለኛነት በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን (የቀድሞው የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጄንሲ-HERQA) በኩል ማረጋገጥ (Authenticate ማስደረግ) እና ስማችሁ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ወደ ተቋማችን እንዲተላለፍ ማድረግ ይጠበቅባችኋል፡፡

2) ከዚህ ቀደም የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን Authenticate ያስደረጋችሁ እና ስማችሁ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ወደ ተቋማችን የተላለፈላችሁ ተመዛኞች ድጋሚ Authenticate ማስደረግ አይጠበቅባችሁም፡፡

3) ምዝገባው ለሁሉም ተመዛኞች (የመንግስትም ሆነ የግል ተቋም ተመራቂዎች) online የሚካሄድ ሲሆን online ያልተመዘገበ ተመዛኝ ለፈተና መቀመጥ የማይችል መሆኑን እናሳስባለን፡፡

4) የonline ምዝገባችሁን አጠናቃችሁ Submit ካላችሁ ከ 72 ሰዓት (3 ቀናት) በኋላ ወደ ሲስተሙ በመመለስ ሲስተሙ የሚሰጣችሁን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) መዝግባችሁ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
#Share ለሁሉም ጤና.