አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.83K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
🔈 #የኢትዮጵያውያንድምጽ

በጅቡቲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ህጋዊ መኖሪያ ማግኘት ያልቻሉበት ምክንያት ምንድነው ?

የጅቡቲ መንግስት ሰነድ አልባ ስደተኞች በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በፈቃዳቸው ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ካወጀ ሰነባብቷል፡፡ የተሰጠው ቀነገደብ በመጠናቀቁም መጠነ ሰፊ አፈሳ እንደሚጀምር አውጇል፡፡

በዚያች ሀገር የሚኖሩ ሰነድ አልባ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በበኩላቸው፣ ሀብት ንብረታችንን ሸጠን የምንወጣበት ጊዜ ይስጠን እያሉ ይማፀናሉ፡፡ ለዚህም ቀነገደቡ እንዲራመዝላቸው ይፈልጋሉ፡፡

ለመሆኑ እነዚህ ሰነድ አልባ ኢትዮጵያውያን (ቁጥራቸው በትንሹ ከ200 ሺህ በላይ ይገመታል) ለምን እስካሁን ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ መያዝ አልቻሉም፡፡

ይህን ጥያቄ ያነሳንላቸው ስማችን አይጠቀስ ያሉ ሶስት ስደተኞች፣ ሕጋዊ ለመሆን ስላለው ሁኔታ የሚከተለውን ሀሳብ ሰጥተዋል፡፡ 
  
ሕጋዊ ለመሆን ያለው ችግር ምንድነው ?

" ሁሉም ሰው ህጋዊ መሆን ይፈልጋል፡፡ ችግሩ የገንዘቡ መብዛት ነው፡፡ ሒደቱም ረጅም የድለላ ሰንሰለትን የሚያልፍ እና በእጅጉ ረዥም፣ አድካሚና ውስብስብ ነው፡፡ የአንድ ሰው የአመት ገቢ እንኳ አይበቃም፡፡

ህጋዊ ለመሆን ለጅቡቲ መንግስት የሚከፈለው ገንዘብ አንድ አመት ሙሉ ሰርቶ ማጠራቀም አይቻልም፡፡ የዚህ ሀገር ህጋዊ መሆኛ አሰራር ለድሀና ለስደተኛ የሚመጥን አይደለም፡፡ እንኳን ግለሰብ ቀርቶ፣ ድርጅቶችም አይችሉትም፡፡

የንግድ ድርጅቶች ለሰራተኞቻቸው ህጋዊ የስራ ፈቃድ ለማውጣት፣ እስከ 200 ሺህ ፍራንክ (160 ሺህ ብር ገደማ) ይጠየቃሉ፤ ለአንድ ሰራተኛ፡፡ ለግለሰብ ደግሞ እስከ 70 ሺህ ፍራንክ ይደርሳል በህጋዊው መንገድ፡፡ ግን አብዛኛውን ጊዜ ህጋዊው አካሔድ ስለማይገኝ በደላሎች በኩል እስከ 120 ሺህ ፍራንክ ትጠየቃለህ፡፡ አሁን በቅርቡ 120 ሺህ ፍራንክ ከፍለው ያወጡ ሰዎች አሉ፡፡ አንዳንዴም ከ150 ሺህ እስከ 200 ሺህ ብር ያስወጣሀል፡፡ ይህን ያህል ከፍለህ የምታገኘው የመኖሪያ ፈቃድ፣ ተሰጠህ ሳይሆን ገዛህ ነው ሊባል የሚችለው፡፡ አንዴ ከፍለህ የሚያበቃ ነገር ደግሞ አይደለም፡፡ በየአመቱ ከ 20 ሺህ እስከ 30 ሺህ ፍራንክ እየከፈልክ ታሳድሳለህ ፈቃድህን፡፡

እንደ ሌሎች ሀገራት ብዙ አመት ከቆየህ በኋላ ህጋዊ ነዋሪ አትሆንም፡፡ ሁሌም ጊዜያዊ ነዋሪ እየተባልክ በየአመቱ ፈቃድህን እያደስክ ትኖራለህ፡፡ የቋሚ ነዋሪነት መታወቂያ አይሰጡህም፡፡ ይህ ችግር አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ስደተኛ፣ ሰነድ አልባ ሆኖ በስጋት ውስጥ እንዲኖር አስገድዶታል፡፡

ህጋዊ ሰነድ ለማግኘት ደግሞ ፓስፖርትህ ላይ ቪዛ መመታት አለበት ይሉሀል፡፡ ይህን ቪዛ ለማስመታት ከጅቡቲ ትወጣና እንደገና መግባት አለብህ፣ ቪዛ ለማግኘት የግድ ከጅቡቲ መውጣት አለብህ በየአመቱ፡፡ ተመልሰህ ስትገባ ኤርፖርት ቪዛ ይሰጠሀል፡፡ አዲስ አበባ እና ድሬዳዋም ይመታልሀል፡፡ ግን ቅድመ ሁኔታው በጣም ብዙ ነው፣ አሰልቺም ጭምር፡፡ በዚህ መልኩ፣ ህጋዊ የመሆኛው ሒደት ውድና አድካሚ ነው፡፡ ምንም አይነት ግልፅ የሆነ ህጋዊ አሰራር የላቸውም፡፡     

ይህን የምታደርገው ደግሞ ፓስፖርት ካለህ ነው፡፡ ፓስፖርት ይዘን ነው፣ ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የምትጠይቀው፡፡ የእኛ ኤምባሲ ፓስፖርት ለመስጠት 200 ዶላር ይጠይቃል፡፡ በጅቡቲ ፍራንክ ሳይሆን፣ በዶላር ክፈል ነው የምትባለው፡፡ ይህ ራሱ በጣም ብዙ ነው፡፡

ከአንድ አመት በፊት የኢትዮጵያ ፓስፖርት ለመውሰድ ክፍያው ዝቅተኛ ነበር፡፡ 100 ዶላር፣ 150 ዶላር የነበረበት ወቅት ነበር፡፡ አሁን በጣም ነው የጨመረው፡፡ አዲስ ፓስፖርት ተቀይሯል ተብሎ ነው የጨመረው፡፡ አንድ የጥበቃ ሰራተኛና አንዲት የቤት ሰራተኛ የሆኑ ስደተኞች የአንድ ወር ሙሉ ደመወዛቸው ለፓስፖርት ማውጫ አይበቃቸውም፡፡ ሙሉ ደመወዝ ለዚህ ብቻ ልታውለው አትችልም፡፡ መብላት መጠጣት መልበስ የሚባሉ ነገሮች አሉ፡፡ 200 ዶላር ለመቆጠብ ጊዜ ይፈጃል፡፡ ሰዉ ደግሞ የተወሰነ አመት ሰርቶ፣ ገንዘብ አጠራቅሞ ወደ ሀገሩ መመለስ ነው እንጂ፣ ያገኛትን ገንዘብ ለመኖሪያ ፈቃድና ለፓስፖርት መጨረስ አይፈልግም፡፡

ስለዚህ በኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል ያለው የፓስፖርት ክፍያ ቢቀንስ ጥሩ ነበር፡፡ እንደው 100 ዶላር እንኳን ቢያደርግልን፡፡ በሁሉም አቅጣጫ፣ ህጋዊ ሰነድ ማግኘት የምትችልበት ሁኔታ ነው መፈጠር ያለበት፡፡ ኤምባሲያችን ይህ ጉዳይ እንዲቀረፍ መስራት አለበት፡፡

የጅቡቲ መንግስት የመኖሪያ ፈቃዱ ቀለል ባለ መንገድ እንዲገኝ ማድረግ አለበት፡፡ የኢትዮጵያ ኤምባሲም ለዚህ ጫና ማድረግና የመኖሪያ ፈቃድ ለማግኘት በደላሎች እየተበዘበዘ ያለውን ህዝብ ችግር ከግምት አስገብቶ መስራት አለበት፡፡ ሁሉም ሰው ህጋዊ መሆን ይፈልጋል፡፡ ስርዓቱ ለዚህ መመቸት አለበት ነው የምንለው፡፡ "

ስደተኞቹ ህጋዊ ሰነድ ለመያዝ ይገጥሙናል ስላሉዋቸው ችግሮች እንዲሁም የኢትዮጵያን ፓስፖርት ለማውጣት እስከ 200 ዶላር መክፈል አግባብ አይደለም በማለት ላቀረቡት ቅሬታ፣ በጅቡቲ ካለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ማብራሪያ ካገኘን እናቀርባለን፡፡  ሆኖም የፓስፖርት የአገልግሎት ክፍያን በተመለከተ በህገደንብ የተወሰነ መሆኑን ማረጋገጥ ችለናል፡፡

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለሚሰጣቸው አገልግሎቶች የሚከፈል የአገልግሎት ክፍያን ለመወሰን የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 520/2016 ላይ እንደተገለፀው፣ በውጭ ሀገራት በኤምባሲ በኩል የሚሰጥ ባለ 32 ገፅ መደበኛ ፓስፖርት የአገልግሎት ክፍያው 200 ዶላር መሆኑን ተመልክተናል፡፡ በኦንላይንና በእድሳት ደግሞ 250 ዶላር እንደሚያስከፍል ይጠቅሳል ደንቡ፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
" የተሽከርካሪ ታርጋ አይፈታም ክልክል ነው ፤ ደንቡም ላይ ተቀምጧል " - የመንገድ ደኅንነት እና መድን ፈንድ

➡️ " ተሳፋሪን ለማውረድ ክልክል የነበሩ ቦታዎች እየተፈቀዱ ነው ተጨማሪ ቦታዎችም እየታዩ ቅሬታ የሚነሳባቸው ቦታዎች ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተነጋገርን ነው ! "

ከነሐሴ 13 ቀን 2016 ዓም ጀምሮ በስራ ላይ የዋለው " የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ ቁጥር 557/2016 " ተግባራዊ ከሆነ ስምንት ወራት ተሻግሯል።

ነባሩ ደንብን በመተካት ተሻሽሎ የወጣው ደንብ የጥፋት እርከንን በሦስት በመክፈል የትራፊክ ቅጣቱንም ከ500 ብር እስከ 1,500 ብር ከፍ አድርጓል።

ደንቡ የከተማ የፍጥነት ወሰንን በ 50 ኪሜ በሰዓት ከመወሰኑ በተጨማሪ ፣ የራዳር መቆጣጠሪያ የሚያውኩ መሳሪያዎችን ይዞ መንቀሳቀስን ይከለክላል።

በተጨማሪም አደጋ አድርሰው በአደጋው ህይወታቸው ያለፈ አሽከርካሪዎች የአደጋውን ምክንያት ለመመርመር ህይወታቸው ካለፈ በኋላም የደም ናሙና እንዲወሰድ የሚፈቅዱ አዳዲስ ጉዳዮችን አካቷል።

ደንቡ ተግባራዊ ከሆነ ጀምሮ " የቅጣት ገንዘቡ የተጋነነ ነው " የሚሉ ቅሬታዎችን ጨምሮ " ያለ አግባብ እየተቀጣን ነው " የሚሉ ቅሬታዎች በአሽከርካሪዎች ዘንድ ይሰማል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ደንቡ ተግባራዊ ከሆነ ጀምሮ ውጤታማነቱ ተገምግሟል ወይ ? ስለሚነሱት ቅሬታዎችን ምን ምላሽ አላቹ ? ሲል የሚመለከተውን አካል ጠይቋል።

የመንገድ ደኅንነት እና መድን ፈንድ ህግ ትግበራ ዴስክ ሃላፊ ወ/ሮ ብርክቲ ባህሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?

" ደንቡ ከወጣ ጊዜ ጀምሮ ሁሉም ክልሎች እንዲደርሳቸው ተደርጓል ከደረሳቸውም በኋላ የማስተዋወቅ እና ምን ምን ተሻሻለ የሚለውን ነገር የማሳወቅ ስራ ሰርተናል።

ጀምረዋል አልጀመሩም የሚለውን አንድ ዙር ተገምግሟል አብዛኛው ክልል ጀምሯል ማለት ይቻላል አጀማመራቸው እኩል ባይሆንም።

' ቅጣቱ ተጋኗል ' የሚል ቅሬታ በሚመለከት ከዚህ በፊት የነበረው ቅጣት አስተማሪ አልነበረም በጣም አነስተኛ ነበር።

ዋናው አላማችን አደጋን መቀነስ ነው ቅጣቶቹ የተቀመጡት ከአደጋ አንጻር ነው።

ቢያንስ ግንዛቤ እየኖረው ነው ' ቅጣቱ ይሄን ያህል ነው ' የማለት የመጠንቀቅ ነገር አለ ለውጥ አለ።

ደረጃ አንድ፣ ሁለት ፣ ሦስት እና ልዩ ጥፋት እርከን ተብሎ ነው የተቀመጠው።

አሽከርካሪዎች ደጋግመው ሊያጠፏቸው ይችላሉ የተባሉትን ጥፋቶች ከመጠናቸውም አንጻር ታይቶ በአንደኛ ደረጃ የጥፋት እርከን ነው የተቀመጡት።

ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡት ከበድ ያለ አደጋ ሊያደርሱ ይችላሉ ተብለው የተለዩ ጥፋቶች ናቸው ቅጣታቸውም 1,500 ብር ነው።

' ተጋኗል ' የሚል ካለ የማያጠፋን አይመለከትውም ቅጣት የሚመለከተው አጥፊውን ብቻ ነው።

ስፒድ ሊሚተር የሚገጠምላቸው አሽከርካሪዎች አሉ ይህንን ሲፒድ ሊሚተር በትክክል እንዳያሳይ የሚያበላሽ አለ እንደዚህ አይነት ቴክኖሎጂዎችን የሚያሰናክሉ ካሉ የገጠሙት ነገር ይወረሳል ፣በወንጀልም ይጠየቃሉ ቅጣትም አለው።

ይህን አይነቱን ጥፋት የሚያጠፉ አሽከርካሪዎች እንዳሉ ከዚህ ቀደም በተሰሩ ጥናቶች በመታወቁ በደንቡ ላይ እንዲካተቱ ሆኗል።

ከዚህ ቀደም በነበረው ድንብ ላይ ጠጥቶ ወይም አደንዛዥ እጽ ተጠቅሞ አደጋ ያደረሰ እና ህይወቱ ያለፈ አሽከርካሪ ላይ ጠጥቶ ይሁን አይሁን ለማረጋገጥ የሚቻልበት መንገድ አያስቀምጥም ነበር።

በአሁኑ ደንብ አሽከርካሪው በህይወት ባይኖርም የደም ናሙና እንዲወሰድ ይፈቅዳል አተገባበሩ ላይ መመሪያ እየተዘጋጀ ነው።

ተሳፋሪን ለማውረድ ክልክል የነበሩ ቦታዎች እየተፈቀዱ ነው ተጨማሪ ቦታዎችም እየታዩ ቅሬታ የሚነሳባቸው ቦታዎች ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተነጋገርን ነው።

ህጉ ገና መውጣቱ ነው ረዥም ጊዜው አይደለም መሬት ላይ ያለው ሁኔታ ምን ላይ ነው ያለው ? የሚለውን ከሁሉም ክፍል የተወጣጣ ቡድን በስራ ላይ ነው።

ከዚህ ቀደም አሽከርካሪዎች ተደጋጋሚ ጥፋት ስለሚያጠፉ የትራፊክ ፖሊሶች ታርጋ ይፈቱ ነበር መንጃ ፈቃድም ይወስዱ ነበር።

አሁን ላይ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ይህንን የሚያስቀር መተግበሪያ አበልጽጓል።

ከዚህ በኋላ ሰሌዳ መፍታትም ሆነ መንጃ ፈቃድ መውሰድ ሳያስፈልግ አሽከርካሪን የሚቀጣበት አሰራር ነው።

ከዚህ በኋላ ታርጋ አይፈታም ክልክል ነው ደንቡም ላይ ተቀምጧል።

ሲስተሙ ይፋ ተደርጓል ወደ ተግባር እየገቡበት ነው ተሞክሮው ተወስዶ ወደ ክልሎችም የማስተዋወቅ ስራ ይሰራል።

በህጉ መሰረት እንደማይፈቀድ ሁሉም ግንዛቤ እስከሚኖረው ድረስ ጊዜ ይጠይቃል ነገር ግን ታርጋ መፍታት አይፈቀድም " ብለዋል።

ከዚህ ቀደም " የተሽከርካሪን ሰሌዳን መፍታት ክልክል ነው " የሚለው ህግ በተጨባጭ ለምን ተግባራዊ አልሆነም ? የሚል ጥያቄ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን አቶ ክበበው ሚደቅሳ አቀርቦላቸው ነበር።

አቶ ክበበው " ሰሌዳ ቁጥሩ የሚፈታበት አጋጣሚ ይኖራል፣ እሱም የሚሆነው የቅጣት እግድ የደረሱ ከሆነ፣  መንጃ ፍቃዳቸው ላይ ያለው ስልክ ቁጥራቸው የማይሰራ ወይም የክፍለ ሀገር ከሆነ ይፈታል፣ ምክንያቱም አስገዳጅ ምክንያቶች ስለሆኑ በሂደት ግን የሁሉም ሰው አንዳይፈታ እናደርጋለን " ሲሉ መልሰው ነበር።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
143_2011_143_2011ለውጦችን_ስለማሳውቅ.pdf
1.2 MB
ውድ ግብር ከፋዮቻችን የታክስ እንቅስቃሴ ለውጥ ላይ ከሆነ በመመሪያ 143 /2011 መሰረት ለውጥ የተካሄደባቸውን እንቅስቃሴዎች ያሳውቁ
ማንኛውም ድርጅት ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ የመመስረቻ ጽሑፍ፣ የመተዳደሪያ ደንብ፣ የሽርክና ማህበር ስምምነት ወይም ሌላ የመመስረቻ ወይም የምዝገባ ሰነድ ቅጂ ለባለሥልጣኑ መቅረብ አለበት፡፡ እነዚህ ሰነዶች ላይ ማንኛውም ለውጥ ሲደረግ ድርጅቱ ለውጡ በተደረገ በ30 ቀናት ውስጥ ለውጡን በጽሑፍ ለባለሥልጣኑ ማሳወቅ አለበት፡፡
ሀ. በንግድ ድርጅቱ ስያሜ ላይ የተደረገ ለውጥ፤
ለ. በድርጅቱ ስም የተመዘገበ፡-
i. ቋሚ የንግድ ሥራ፣ የቢሮ እና የመኖሪያ አድራሻ ለውጥ፣
ii. በማምረቻ ቦታ ወይም ታክስ ከፋዩ በሚጠቀምበት መጋዘን ላይ የተደረገ የአድራሻ ለውጥ፤
iii. በፖስታ ወይም በመደበኛ እና በተንቀሳቃሽ ሰልክ፣ ፋክስ ወይም ኢ-ሜል አድራሻ ላይ የተደረገ ለውጥ፤
ሐ. በዋነኛ የሥራ እንቅስቃሴው ወይም በቅርንጫፍ ወይም በንግድ ሥራው ዘርፍ ወይም መስክ ላይ የተደረገ ለውጥ፤
መ. በድርጅቱ መተዳደሪያ ደንብ ወይም የመመስረቻ ጽሑፍ ወይም የሽርክና ስምምነት ላይ የተደረገ ለውጥ፤
ሠ. በአክሲዮን ባለድርሻ አባላት ላይ የተደረገ ለውጥ፤
ረ. በድርጅቱ ወይም በታክስ እንደራሴው የባንክ ሂሳብ ወይም የባንክ ቅርንጫፍ አድራሻ ላይ የተደረገ ለውጥ፤
ሰ.በታክስ እንደራሴው እና ከሚኒስቴሩ ጋር ግንኙነት በሚያደርግበት የኤሌክትሮኒክስ አድራሻ ላይ የተደረገ ለውጥ፤
ሸ. በተመዘገበና በተከፈለ ካፒታል ላይ የተደረገ ለውጥ፤……………..
ሙሉን ለማግኘት ከላይ የተቀመጠውን መመሪያ ያንብቡ
እናመሰግናለን !!
የአማራ ክልል ዳኞች በፖለቲካ ጉዳዮች ላይ በማንኛውም ማህበራዊ ሚዲያ ላይ “ሃሳብ እንዳይሰጡ” የሚከለክል ደንብ ወጣ

በአማራ ክልል የሚገኙ ዳኞች፤ በፖለቲካ፣ በሃይማኖት ወይም “አወዛጋቢ በሆኑ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ “በየትኛውም” ማህበራዊ ሚዲያ “ሃሳብ እንዳይሰጡ” የሚከለክል ደንብ ጸደቀ። ደንቡ በክልሉ የሚገኙ ዳኞች “ሀሰተኛ” ማህበራዊ ሚዲያዎችን “እንዳይጠቀሙ”፣ “እንዳይከተሉ” እና “አባል እንዳይሆኑ” ይከለክላል።

የዳኞች እና የጉባኤ ተሿሚዎችን የስነ-ምግባር እና የዲሲፕሊን የሚመለከተው ይህ ደንብ የጸደቀው ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ ግንቦት 5፤ 2017 ነው። ደንቡን ያጸደቀው የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የዳኞች አስተዳደር አብይ ጉባኤ፤ ደንቡ ከዚሁ ዕለት ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆን ውሳኔ አስተላልፏል።

የአማራ ክልል ፍርድ ቤቶች የዳኞች አስተዳደር ጉባኤን ለማሻሻል በ2014 የወጣው አዋጅ፤ ለዳኞች እና ለጉባኤ ተሿሚዎች የስነ ምግባር እና የዲሲፒሊን ደንብ የማውጣት ስልጣን የሰጠው በጠቅላይ ፍርድ ቤት ስር ላለው አብይ ጉባኤ ነው። እስካሁን በስራ ላይ የቆየው የስነ ምግባር እና የዲሲፒሊን ደንብ የወጣው በ2007 ዓ.ም ነበር።

ይህ ደንብ “በርካታ ጉዳዮችን ያካተተ ቢሆንም ግልጽነት የጎደላቸው ጉዳዮችን ይበልጥ ግልጽ ለማድረግ” በአዲስ መልክ እንዲዘጋጅ መደረጉን የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በትላንትናው ዕለት ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። አዲሱ ደንብ እንዲዘጋጅ ከተደረገባቸው ምክንያቶች አንዱ፤ በቀድሞው ደንብ ያልነበረ “የዳኞች ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን” ማካተት በማስፈለጉ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ገልጿል።

🔴ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15924/
የፋይዳ ብሄራዊ መታወቂያ ወይም FAN ቁጥር ካልያዙ አገልግሎት እንደማያገኙ የፌደራል ጠበቆች እና የህግ አማካሪዎች ተገቢውን ዝግጅት እንድታደርጉ ማህበሩ ያሳስባል::
#ID #አለሕግ
አዲሱ የ ፍትሕ ሚኒስቴር ህግጋት የመረጃ ቋት
👇👇👇👇👇💎💎💎
https://mojcdn.com
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#Tigray

ዛሬ በመቐለ ማእከላይ ፍርድ ቤት ምንድን ነው የተከሰተው ? 

እንስት ዘውዱ ሃፍቱ ከሁለት ዓመት በፊት በግፍ ከተገደሉት ሴቶች አንድዋ ናት።

የሟችዋ ጉዳይ በፓሊስ ተጣርቶ መዝገቡ ወደ ፍርድ ደርሶ ለሁለት ዓመት ያህል ውሳኔ ሳያገኝ በይዋል ይደር ረጅም ጊዜ መውሰዱ የተበዳይዋ ቤተሰብና የፍትህ ፈላጊዎች ሁሉ መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል።

ይህ በእንዲህ አንዳለ የመቐለ ማእከላይ ፍርድ ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ/ም ከሰዓት በፊት የመጨረሻው ውሳኔ ለመስጠት ችሎት ይቀመጣል።

ፍርድ ቤቱ በግድያ ወንጀሉ በተጠረጠሩት ላይ የመጨረሻ ያለውን የጥፋተኝነት የቅጣት ውሳኔ ይሰጣል።

ይህንን ተከትሎ ችሎቱ በሚከናወንበት አዳራሽ የነበሩት ብዛት ያላቸው የተጠርጣሪ ወገኖች ጠረጴዛ በመደብደብና የተለያዩ ድምፆች በማሰማት ረብሻ ይጀምራሉ።

ከረብሻ በዘለለ ዳኞቹን " እናንተም  እንደመስሳቹሃለን ፤ ቀናችሁን ጠብቁ " የሚሉ የስድብ ናዳና ዛቻ ያወርዳሉ።

በችሎት አዳራሹ በቂ የሆነ ስርዓት አስከባሪ ባለመኖሩና ዳኞቹ ሁኔታው ከአቅማቸው በላይ እና አስፈሪ በመሆኑ ምክንያት ውሳኔውን ሳይቋጩ ለግንቦት 18/2017 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ስጥተዋል።

የችሎት መድፈር ተግባሩ የማህበራዊ የትስስር ገፅ ሰፊ መነጋገሪ ሆኖዋል።

ጠበቃ ሚኪኤለ ፍስሃ የተባሉ የሟች ጠበቃ " በፍርሃት ስራዬን አላቋርጥም፤ የተበዳይን እንባ ለማበስ ነገም ዛሬም እሰራለሁ " ሲሉ በማህበራዊ ሚድያ የትሰስር ገጻቸው ላይ ሀሳባቸውን አስፍረዋል።

በርካቶች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የህግ ልዕልና እንዲከበር አገልግሎት በሚሰጠው ፍርድ ቤትና ዳኞች ላይ የተፈፀመ ድፍረት በምሬትና በቁጣ ሲያወግዙት ተስተውለዋል።

የመቐለ ማእከላይ ፍ/ቤት በያዝነው ሳምንት ብቻ የእንስት ዘውዱን ጨምሮ 4 በግፍ የተበደሉ ሴቶችን ጉዳይ መመልከቱን የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ከቦታው መረጃውን አድርሷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia 
ከ21 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ትንባሆ ሲሸጡ እና ሲጠቀሙ ከተገኙ እርምጃ እወስዳለሁ ሲል ባለስጣኑ አስታወቀ‼️
***
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምግብ እና መድኃኒት ባለስልጣን አዲስ አበባን ከትምባሆ ጭስ ነፃ ለማድረግ በተቀረፀው በመደበኛ ቁጥጥር በጤና ተቋማት፣ የህዝብ መሰብሰቢያ ስፍራዎች እና የተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ሙሉ በሙሉ ከትምባሆ ጭስ ነፃ የማድረግ ስራ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡

ባለስልጣኑ በአዋጅ 1112/2011መሰረት  ከ21 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች በተለያዩ የሱቅ መደብሮች እና በየመንገዱ ትንባሆ ሲሸጡ እና ሲጠቀሙ ከተገኙ እርምጃ እንደሚወስድ በባለስልጣኑ የምግብና ጤና ነክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት አቶ እስጢፋኖስ ጌታቸው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

ትንባሆ ማጨስ የሚያስከትላቸው ከባድ አደጋዎች እንዳሉ በህክምና ባለሙያዎች የሚገለፅ ሲሆን ከእነዚህም መካከል ካንሰር፣ የልብ ህመም፣ ስትሮክ፣ የሳንባ እና የስኳር በሽታ እንዲሁም የቆዳ እርጅና ማፋጠን ዋንኛዎቹ ናቸው።

በትምባሆ እና በኒኮቲን ምርቶች ላይ የትምባሆ ኢንዱስትሪ ስልቶች ማጋለጥ'' በሚል መሪ ቃል ሜይ 31 የዓለም ትምባሆ የማይጨስበት ቀን በማስመልከት  ከተማ አቀፍ የፀረ-ትምባሆ ንቅናቄ ከሚያዚያ 25   እስከ ግንቦት 23/2017 ዓ.ም እንደሚካሄድ ተገልፆል፡፡
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👉National champion Team/የውድድሩ አሸናፊ ቡድን ባህርዳር ዩኒቨርስቲ ሁኖል

የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ህግ ትምህርት ቤት ከፌደራል ፍትህ እና ህግ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ከአርብ ግንቦት 8 ቀን 2017 ጀምሮ እስከ ዛሬ እሁድ ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ ሲካሄድ የቆየው 9ኛው ዙር ሀገር አቀፍ የህግ ትም/ት ቤቶች የምስለ ችሎት ውድድር ፍጻሜውን አግኝቶል ።

በውድድሩ ላይ 12 ዪኒቨርሲቲይዎች የተሳተፉ ሲሆን።የውድድሩ የመጨረሻ ውጤትም የሚከተለው ነው።

👉National champion Team/የውድድሩ አሸናፊ ቡድን ባህርዳር ዩኒቨርስቲ ሁኖል

1.ቤተልሔም ገበየሁ ጸጋነህ
2.ዮናስ ሙጨ ዳኘ
3.እዮብ ይመች

👉Best Runner Up Team (2ኛ ደረጃን) የያዙት ሰላሌ ዩኒቨረሲቲ ናቸው

1.ሄርሜላ መስፍን
2 ሀዴሳ መረከቡ
3.አብዲ ረታ

👉Second runner up team(3ኛ ደረጃን የያዙት) ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ሰሆን
1.ፋሲል ዘለቀ ዘውደ
2.ወርቁ ማስሬ አበበ
3. ፈቲያ ኑረድን መሃመድ

👉Best Memorial Applicant

ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ

👉Best Memorial Respondet winner

ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ
👉Best orator of the preliminary round competition
እዮብ ይመች ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ

👉Best Femal orator of the preliminary round Competition
ቤተልሔም ገበየሁ ጸጋነህ ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ

👉Best orator of the final round competition competition

እዮብ ይመች ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ

via:- Law Students Union
ጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#የዳኞችስነምግባር #አለሕግ #ህግ
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
The recent disqualification of Dire Dawa University’s all-women moot court team from the 9th Ethiopian Law Schools National Moot Court Competition is deeply disappointing and raises serious concerns about fairness and accountability. Despite a formal request for reconsideration, the Organizing Committee ignored the appeal and threatened future exclusion for challenging their decision. As the coach of last year's undefeated team, I can attest to the current team's dedication and skill, making their dismissal particularly disheartening.

Dire Dawa University has always championed women's empowerment in line with our constitutional values, and this decision undermines those principles. The committee's failure to apply rules with a moral compass reflects a troubling disregard for gender equity and educational integrity, risking further deterring women from pursuing legal careers.

In light of these events, we must reconsider our participation in competitions that do not uphold fairness and justice. I urge stakeholders in Ethiopian legal education to reflect on the purpose of such competitions and commit to fostering an environment of growth and equity for all students.

Via Alemseged Dejenie 
Lecturer at DDUSOL

As a member of the Dire Dawa University (DDU) Moot Court Team, I want to share a story of dedication, discrimination, and the fight for fairness. 
The Preparation: Unshakable Confidence 
Our coach molded us into an unstoppable team, sharpening our skills and knowledge until we stood as some of the best orators. We went to Mizan Tepi University with unshakable confidence—not because we hoped to win, but because we knew we had given everything. 
The Shock: Disqualified for Being Women 
After dominating the preliminary rounds, we waited for results—not to see if we passed, but to see by how much we had won. Then came the blow: disqualification. Not for lack of skill, not for weak arguments, but because we were an all-female team180 points deducted.  For a moment, I thought it was a mistake. Then came the justification: "Gender composition." 

The Reality: A Rule Designed to Exclude 
This wasn’t about procedure—it was about bias

1. "I might be biased if a female orator stands before me," one judge admitted. Should women be penalized because of someone else’s prejudice? Would a case be dismissed because the lawyer is a woman? 
2. "Gender composition" was twisted to mean exclusion, not inclusion. In a world where men dominate opportunities, how does barring women promote equality? 
3. They knew. The committee saw our team at registration, during memorial submissions (where we ranked top out of 30+ universities), and even issued us tickets for the oral rounds—yet stayed silent until the last moment. 
The Fight Isn’t Just for Us—It’s for Every Sister Who Comes Next 
I can’t undo what happened to my team. But I can ensure no other woman faces this injustice. If this decision stands, it sets a dangerous precedent: that women must conform to arbitrary rules rather than compete on merit. 
A Call for Justice 
We don’t seek pity—we demand fairness. The law should empower, not exclude. If "gender composition" is meant to ensure diversity, then why punish women for succeeding? 

This is bigger than one competition. It’s about whether our sisters will face the same barriers tomorrow

I stand for change. Who will stand with me? 

#MootCourt #GenderEquality #JusticeForDDU #WomenInLaw #EqualOpportunity