አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የቤት ብድር የሚሰጡ ባንኮች
#አለ_ህግ
ብሄራዊ ባንክ ሞርጌጅ ባንኮች ለማቋቋም የሚያስችል ደንብ እያረቀቀ እንደሆነ ሪፖርተር አስነብቧል። መንግሥት ለልዩ ዓላማ ለሚቋቋሙ ባንኮች ራሱን የቻለ ደንብ እንዲያዘጋጅ የፋይናንስ ዘርፉ ሲወተውት የቆዩ ሲሆን፣ በቅርቡ ግን ብሄራዊ ባንክ ኮሚቴ አቋቁሞ ለሞርጌጅ ባንክ ማቋቋሚያ ልዩ ደንብ ማዘጋጀት መጀመሩን አንድ የባንኩ ከፍተኛ ኃላፊ ተናግረዋል። ሞርጌጅ ባንክ በባሕሪው የተለየ እና ለደንበኞቹ የሚሰጠው ብድር የረጅም ጊዜ በመሆኑ፣ ለመደበኛ ባንኮች ከሚውሉት መስፈርቶች ቀለል ያሉ መስፈርቶች ሊዘጋጁለት እንደሚገባ የዘርፉ ባለሙያዎች ጠቁመዋል። ከአምና ጀምሮ ጎህ ባንክ ብቻ የሞርጌጅ ብድር እየሰጠ እንደሆነ የገለጠው ዘገባው፣ ብሄራዊ ባንክ ግን ባንኩን የሚያውቀው እንደ ማንኛውም ንግድ ባንክ እንደሆነ አውስቷል።
ዋዜማ ሬዲዬ
የተሻሻለው የፌደራል ፍ/ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1234/13 አንቀፅ 5(2)
=======/////======= #አለ_ህግ
የክልል ጉዳይ ሆኖ በክልል ፍ/ቤቶች እየታዬ ባለ ክርክር ስልጣንን የሚቀይር ተከራካሪ ወገን ወደ ክርክሩ ቢገባ ክርክሩ የት ይቀጥላል?
~~~~
ጉዳዩ የክልል ጉዳይ ሆኖ ክርክር እየቀጠለ ባለበት ጊዜ ስልጣኑን የሚቀይር የሌላ ክልል ነዋሪ የሆነ ተከራካሪ ወገን ወይም የኢንሹራንስ ተቋም ወደ ክርክሩ ሲገባ ጉዳዩ የፌደራል ፍ/ቤቶች ስልጣን ይሆናል ወይስ አይሆንም? የክልል ፍ/ ቤቶች ስልጣናቸውን ያጣሉ ወይስ አያጡም? ጉዳዩን የያዘው ፍርድ ቤትስ መዝገቡን ስልጣን ላለው ያስተላልፍ ወይስ ይዝጋው? የሚሉት ጉዳዬች በቀድሞው አዋጅ ቁጥር 25/88 ድንጋጌዎችእና ከፍ/ስ/ስ/ህጉ ድንጋጌዎች አንፃር አከራካሪ መሆኑ ይታወቃል። የተሻሻለው አዋጅ ለዚህ ምላሽ በሚሰጥ መልኩ የተቀመጠ ነው።
~~~
በመርህ ደረጃ ነዋሪነታቸው በተለያዩ ክልሎች የሆኑ ሰዎች ወይም በፌደራል የተመዘገበ የኢንሹራንስ ተቋም ተከራካሪ የሆኑበት የፍትሀብሄር ክርክር ጉዳይ ላይ የፌደራል ፍርድ ቤቶች የስረ ነገር ስልጣን ያላቸው ሲሆን በልዩ ሁኔታ ግን የክልል ጉዳይ ሆኖ በክልል ፍርድ ቤቶች በመታየት ላይ እያለ የሌላ ክልል ነዋሪ ወይም የኢንሹራንስ ተቋም በየትኛውም የክርክር ደረጃ በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ 40(2), 41,43, 358ና 418ንም ጨምሮ ወደ ክርክሩ ቢገባ ጉዳዩ በጀመረበት አግባብ የክልል ጉዳይ ሆኖ ከሚቀጥል ውጭ የፌደራል ፍርድ ቤቶች ስልጣን ነው በሚል ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት የሚተላለፍ አይሆንም።
(via voice of justice)
Live stream started
H. R. 6600 01951.pdf
924.9 KB
Share 'H. R. 6600 01951.pdf'
Live stream finished (1 hour)
Live stream started
Live stream finished (1 hour)
የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ (Stop Payment Order) የሚሰጠው መቼ እና እንዴት ነው?

በገዙ አየለ መንግሥቱ

በዚህ ጽሑፍ የሚከተሉት ቁም ነገሮች ያገኛሉ
የቼክ ክፍያ ባንክ አልፈጽምም ሊል የሚችለው መቼ ነው
የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ መስጠት የሚቻልበት መንገድ
የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ ከብሔራዊ ባንክ መመሪያ አንጻር
የቼክ ሂሳብ እንቅስቃሴን በተመለከተ

https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/1800-stop-payment-order
።።።።።።። ይግባኝ ማስፈቀጃ ====
• በህጉ የተቀመጠው የይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ ካለፈ በኋላ ይግባኝ ለማቅረብ እንዲፈቀድ የሚቀርብ አቤቱታ

አንድ ፍ/ቤት ይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜው ያለፈበት ምክንያት በቂ መሆኑን ሲረዳ ይግባኙ እንዲቅርብ ሊፈቅድ እንደሚገባ በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 326/1/ ስር ተመልክቷል፡፡ በመሆኑም ፍ/ቤቱ የቀረበለት ምክንያት በቂ መሆን አለመሆኑን በአግባቡ ሊመረምረው ይገባል፡፡ በእርግጥ በቂ ምክንያት የሚባሉት ነገሮች ሕጉ ዘርዝሮ ያላስቀመጣቸው በመሆኑ ለመወሰን አስቸጋሪ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ በመሆኑም የምክንያቱ በቂ መሆን አለመሆን በእያንዳንዱ ጉዳይ ከሚቀርቡ ፍሬ ነገሮች ጋር ተገናዝበው ሊመዘኑ ይገባል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 38145 ቅጽ 8፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 326/1/

በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 324/1/ መሠረት ለአንድ ፍርድ ቤት መዝገብ ሹም የተሰጠው ሥልጣን ይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ ማለፍ አለማለፉን በመመልከት ይግባኝ መዝገቡ እንዲከፈት ማድረግ ሲሆን ይግባኙ ጊዜውን ጠብቆ ያልቀረበ ከሆነ ማመልከቻውን መመለስ፣ ማመልከቻው የተመለሰበት ወገን የይግባኝ ጊዜው ያለፈበት ሕጋዊ ምክንያት ካለው ማስፈቀጃ አቤቱታውን በማቅረብ ይኸው ጊዜው ያለፈበት ይግባኝ ለማቅረብ እንዲፈቀድለት ራሱን የቻለ አቤቱታ አቅርቦና ይህ መዝገብ ተከፍቶ ጉዳዩ ለችሎት ቀርቦ ችሎቱ የይግባኝ ማስፈቀጃውን በመመርመር በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 325 እና 326 መሠረት ተገቢ ነው ያለውን ትእዛዝ የሚሰጥበት ነው፡፡

የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 324/1/ ከፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 325 እና 326 ድንጋጌዎች ጋር አንድ ላይ ሲነበቡ የመዝገብ ቤት ሹም ጊዜው ያለፈበት ይግባኝ ለችሎት እንዲቀርብ የመፍቀድ ስልጣን የሌለው መሆኑን የሚያሳዩ ሲሆን ፋይሉ ተከፍቶ ቀርቦ ከሆነም ችሎቱ ጉዳዩን መርምሮ ይግባኙ የቀረበው ጊዜው ከአለፈ በኋላ ነው በማለት መዝገቡን ከመዝጋት የሚከለክለው አይደለም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 61843 ቅጽ 11፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 324-326
ማሳሰቢያ አለ_ህግ #law #societies
ሁሉንም የ #አለ_ህግ አባላት የሚያሳትፍ ቀጠሮ፣ ሁሌም እሁድ እሁድ የቀጥታ (Live stream) የድምፅ ውይይት ይኖረናል።
#የህግ ጉዳይ የመወያያ እርዕስ አስቀድማችሁ እንዳትመርጡ እናሳስባለን።
ምክንያቱም፣ ከወዲሁ ተዘጋጅተው ለውይይቱ እንዲመጡና ፍሬአማ ሀሳቦችን እንድናገኝ ይረዳናል።
1. የመወያያ አጀንዳ ይምረጡ
2. ተዘጋጅተው የውይይቱ ተሳታፊ ይሁኑ
3. Share and add ማድረግን አትርሱ
#Ale_Lawsocieties
#አለ_ህግ
https://t.me/lawsocieties

@lawsocieties
#Embassy of Canada#

▪️Position - Common Services Officer (Contracts and Procurement)
▪️Salary - 712,866 ETB per annum
▪️Location - Addis Ababa
▪️Education - Bachelor’s degree in a related field (i.e. business administration) from a recognized university with 3 years of experience
▪️Find More Details Here
👇👇👇👇👇
https://bit.ly/3J0kHFr

▪️Deadline - Apr 08/2022

How to Apply

Applications will only be considered when received through our portal.  Link for this job poster – https://staffing-les.international.gc.ca/en/careers/common-services-officer-contracts-and-procurement-addis-64049-en


#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
የዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በፍርድ ቤቶች
*
በፌዴራል ፍርድ ቤቶች በህብረተሰቡ ዘንድ የህግ ግንዛቤን ለማስጨበጥ በሁለት የተከፈለ ስራ ተሰርቷል፡፡ አንዱ በየትኛውም ደረጃ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በፍርድ ቤት የሚሰጠውን የዳኝነት አገልግሎት መሰረት በማድረግ ሂደቱን እና ተያያዥ ጉዳዮችን የሚያስገነዝብ ሳምንታዊ የቴሌቪዥን ፕሮግራም ሲሆን ሁለተኛው ደግም በተማሪዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር፡፡ በተለይም የዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በፍርድ ቤቶች የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ የተግባር ልምምድ (internship program) እና በዳኞች ቅርብ ክትትል፣ ምክርና አቅጣጫ ጠቋሚነት የአመለካከት፣ እውቀትና ክህሎት የማዳበር (Mentorship) ፐሮግራም ተቀርጾ ተግባራዊ ተደርጓል፡፡ የዚህ ፕሮግራም ፋይዳን የሚዳስስ አጭር ቪዲዮ እንዲህ ቀርቧል፡፡
https://m.youtube.com/watch?v=HD-jNaksHg4

#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ 38 ቦታዎች በ0 አመት የስራ ልምድ በርካታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
👩 position:- 38 ቦታዎች
በ 0 አመት
📚 ትምህርት ዓይነት እና ደረጃ፡-

🔴law
🔴business-law,
🔴commercial-law,
🔴environmental-and-land-law,
peace-security,
tax-and-investment-law,
agribusiness-management,animal-science,anthropology,communication,dairy-and-meat-technology,development-evaluation,doctor-of-veterinary-medicine,ecology, forest-science,forestry,journalism ,natural-resource-management,philosophy,psychology,social-anthropology,soil-and-water-conservation-engineering,special-need-education,

veterinary-pathology,veterinary-pharmacology

🇪🇹 የስራ ቦታ : Oromia- region

🧭የምዝገባ ጊዜ /Deadline/: እስከ ሚያዚያ 04 /2014 ዓ.ም

🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ

https://jobs.amazonethiopia.com/job/selale-university/

https://t.me/LawyerEthiopia
@LawyerEthiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በአዋጁ ላይ አስገዳጅ አንቀጾች መካተታቸው ጠቀሜታው የጎላ ነው ሲል ቋሚ ኮሚቴው ገለጸ

(ዜና ፓርላማ) መጋቢት 26/2014 ዓ/ም፤ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በማህበረሰብ ዓቀፍ የጤና መድህን አዋጁ ላይ አስገዳጅ አንቀጾች መካተታቸው ጠቀሜታው የጎላ ነው ሲል ገልጿል፡፡

ቋሚ ኮሚቴው ይህን ያለው በማህበረሰብ ዓቀፍ የጤና መድህን ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በተወያየበት ወቅት ነው፡፡

ቋሚ ኮሚቴው ከኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት፣ ከጤና ሚኒስቴር እንዲሁም ከክልሎች ከተውጣጡ የስራ ሀላፊዎች ጋር ነው የተወያየው፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ወርቅሰሙ ማሞ በአዋጁ ላይ አስገዳጅ አንቀጾች መካተታቸው ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ተናግረው አገልግሎት አሰጣጡ ላይም የሚስተዋለው መንገላታት ሊቀረፍ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድህን አዋጅ ጽንሰ ሀሳብ፤ አዋጁ ያለፈበትን ሂደት፣ ትግበራው የደረሰበትን ደረጃ እና አዋጁ ባካተታቸው ዋና ዋና ጉዳዮች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

በማብራሪያቸውም አዋጁ 7 ክፍሎች እና 34 አንቀጾች እንዳሉት አስረድተው የጤና አገልግሎት የማግኘት ዋስትናን እንደሚያረጋግጥ፣ ለማህበረሰቡ ቀልጣፋ፣ ወጭ ቆጣቢና የተሻለ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት እንደሚያስገኝም ተናግረዋል፡፡

ሀገራዊ የማህበረሰብ ጤና መድህን አፈጻጸም ከጠቅላላው በሀገሪቱ ካሉ ወረዳዎች አኳያ ያለው አፈጻጸም 78 በመቶ እንደሆነ ዋና ዳይሬክተሯ ተናግረው በ2014 ዓ/ም 867 ወረዳዎች እየተተገበረ እንደሚገኝም ነው ያሰረዱት፡፡

አክለውም የማህበረሰብ ዓቀፍ የጤና መድህን ስርዓት በሙከራና ማስፋፊያ ትግበራ ወቅት አበረታች ውጤት ማሳየቱ ቀጣይነቱን ይበልጥ ለማረጋገጥ የህግ ማዕቀፍ ማውጣት አስፈላጊ እንደሆነ ተሞክሮ ተወስዷል ብለዋል፡፡

የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰሃረላ አብዱላሂ አዋጁ ለአገልጋዩ አስገዳጅ መሆኑ ጤና ተቋማት ላይ አገልግሎት የሚሰጡ የስነ-ምግባር ችግር ያለባቸውን የጤና ባለሙያዎች ተጠያቂ ለማድረግና ተጠቃሚው ህብረተሰብ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች ያካተተ ስለሆነ በየደረጃው ያለው የመንግስት አካል ተከታትሎ ማስፈጸም አለበት ብለዋል፡፡

ቋሚ ኮሚቴው መጋቢት 28/2014 ዓ/ም በሚኖረው መድረክ ተጨማሪ ግብዓት እንደሚሰበሰብ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ጠቁመዋል፡፡
በ መስፍን አለሰው

#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties