አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.83K photos
25 videos
1.86K files
3.55K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
Vacancy at Wasasa Microfinance S.C

🔰 The Wasasa Micro finance Institution S.C is invites job seekers for an appointment the below Position.

1: Head, Legal Services 🔴

2: Teller I
3: Branch I Manager
4: Junior Savings and Credit Officer

📌ሰለ ሰራው ሙሉ መረጃ ለማየት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ👇👇
👉 Read Detail:- https://bit.ly/3v7xWPI
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share.....
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
................ @Lawsocieties
መልካም ዜና!

ገንዘብ ሚኒስቴር መሠረታዊ የምግብ ሸቀጦች ያለምንም የውጭ ምንዛሬ ፈቃድ በቀጥታ እንዲገቡ ወሰነ!!

የገንዘብ ሚኒስቴር መሰረታዊ የምግብ ሽቀጦች የሆኑት ዘይት፣ስንዴ፣ስኳር፣የህጻናት ወተት እና ሩዝ ያለምንም የውጭ ምንዛሬ ፍቃድ (በፍራንኮ ቫሉታ) በጉምሩክ ኮሚሽን በኩል በቀጥታ እንዲገቡ ወሰነ፡፡

መንግስት በአሁኑ ወቅት እየተስተዋለ ያለውን የዋጋ ንረት ለማረጋጋት እንዲቻል እና በርካታ የውጭ ሀገር የመኖሪያ ፍቃድ ያላቸው ኢትዮጵያዊያን የራሳቸውን ሚና መጫወት እንዲችሉ የፍራንኮ ቫሉታ ፈቃድ በተፋጠነ ሁኔታ እንዲፈቀድላቸው ጥያቄ እያቀረቡ በመሆኑ ነው፡፡

ቀርጥና ታክሱ በሚመለከት በገንዘብ ሚኒስቴር በ22/3/2013 ዓ.ም በቁጥር ማአ.30/7/51 በተጻፈው ደብዳቤ መሰረት እንዲፈጸም ፤ አፈጻጸሙን በተመለከተ ጉዳዩ በሚመለከታቸው አካላት በኩል ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር እንዲደረግበት ተወስኗል፡
Via ethio mereja
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share.....
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
................ @Lawsocieties
The Danish Refugee Council (DRC) ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
Position :- Programme Officer – Information Hub.
የትምህርትዓይነትእናደረጃ:-
Bachelor’s degree in social sciences, law, social work, international development, or other relevant fields from a recognized institution.
🇪🇹 የስራ ቦታ:-Addiss Ababa
🧭የምዝገባ ጊዜ /Deadline/: እስከ ሚያዚያ 13/2014 ዓ.ም
🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ
//https://jobs.amazonethiopia.com/job/programme-officer-information-hub/

#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share.....
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
................ @Lawsocieties
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
Position:- Head, Humanitarian Diplomacy and Communication
📚ትምህርትዓይነትእናደረጃ:-
Second/First degree in Political Science, International Relations, Foreign Policy and Diplomacy, International Law, public Management and, Journalism, Communications and Public relations, Foreign language and literature, Public Administration and Management, Social Work/ Sociology/ Social Psychology/ Social Anthropology/ Governance & Development Studies
🇪🇹 የስራ ቦታ ፡ አዲስ አበባ
🧭የምዝገባ ጊዜ ፡ እስከ ማያዚያ 08 /2014 ዓ.ም
🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ
https://jobs.amazonethiopia.com/job/head-humanitarian-diplomacy-and-communication/

#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share.....
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
................ @Lawsocieties
እጅግ በጣም አሪፍ የሆነ ውይይት ነበረን።
ስለ አደረግነው ውጤታማ የሀሳብ ልውውጥ ለተሳታፊዎች በሙሉ
#አለ_ህግ ከልብ የሆነ ምስጋና ያቀርባል።

#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ
#አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
contact us: @LawsocietiesBot or email us: lawsocieties@gmail.com
ለመንግሥት ሠራተኞች የሚሰጥ የወሊድ ፈቃድ
#አለ_ህግ
==================
ለአንድ የመንግስት ሰራተኛ የተለያዩ ዕረፍት ዓይነቶች ያሉ ስሆን በፌደራል መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1064/2010” አንቀጽ 43 ላይ የተደነገገው የወሊድ ፈቃድ ነው።
ነፍሰጡር የሆነች የመንግሥት ሠራተኛ፣ ከእርግዝናዋ ጋር የተያያዘ ምርመራ ለማድረግ ሐኪም በሚያዘው መሠረት ደመወዝ የሚከፈልበት ፈቃድ ይሰጣታል፤
1. ከመውለዷ በፊት ዕረፍት እንድታደርግ ሐኪም ካዘዘ ደመወዝ የሚከፈልበት ዕረፍት ይሰጣታል፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) የተመለከተው ፈቃድ እንደ ህመም ፈቃድ አይቆጠርም፡፡
3. ነፍሰጡር የሆነች የመንግሥት ሠራተኛ መውለጃዋ ሲደርስ እወልዳለሁ ብላ ከገመተችበት ቀን በፊት 30 ተከታታይ ቀናት የቅድመ ወሊድ ፈቃድ፣ እንዲሁም ስትወልድ ከወለደችበት ቀን ጀምሮ 90 ተከታታይ ቀናት፣ በአጠቃላይ 120 ተከታታይ ቀናት ደመወዝ የሚከፈልበት የወሊድ ፈቃድ ይሰጣታል፡፡
4. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (3) መሠረት ሠራተኛዋ የተሰጣት የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ከማለቁ በፊት ከወለደች ያልተጠቀመችበትን ቀሪ የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ከወለደች በኋላ እንድትጠቀምበት ይደረጋል፡፡
5. ሠራተኛዋ የወሰደችው የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ሲያልቅ ያልወለደች እንደሆነ እስከምትወልድበት ቀን ድረስ ባሉት የሥራ ቀናት የምትቆይበት ዕረፍት በበጀት ዓመቱ ካላት የዓመት ዕረፍት ፈቃድ ወይም በበጀት ዓመቱ የዓመት ፈቃድ የሌላት እንደሆነ ከሚቀጥለው የበጀት ዓመት የዕረፍት ፈቃዷ ይተካል፡፡
6. ሠራተኛዋ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (3) የተወሰነውን የወሊድ ፈቃድ ከጨረሰች በኋላ ብትታመምና ተጨማሪ ፈቃድ የሚያስፈልጋት መሆኑ በሀኪም ከተረጋገጠ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 43(1) በተደነገገው መሠረት የሕመም ፈቃድ መውሰድ ትችላለች፡፡
7. ማንኛዋም ስድስት ወር የሞላት ነፍሰጡር የሆነች የመንግስት ሠራተኛ የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ከመውሰዷ በፊት ጽንሱ የተቋረጠባት ከሆነ ይህንኑ የሚያረጋግጥ የህክምና ማስረጃ ስታቀርብ የ60 ቀን የድህረ ወሊድ ፈቃድ ይሰጣታል፡፡
8. የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ከወሰደች በኋላ የጽንስ መቋረጥ ካጋጠማት የወሰደችው የቅድመ ወሊድ ፈቃዷ ተቋርጦ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (3) የተመለከተው የ90 ቀን የድህረ ወሊድ ፈቃድ ይሰጣታል፡፡
9. ከሦስት እስከ ስድስት ወር ባለው የእርግዝና ጊዜ ውስጥ የፅንስ መቋረጥ ያጋጠማት የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ የሚከፈልበት 30 ተከታታይ ቀን ፈቃድ ይሰጣታል፡፡
10. ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ የትዳር ጓደኛው ስትወልድ ደመወዝ የሚከፈልበት 10 የሥራ ቀን ፈቃድ ይሰጠዋል፡፡
Via Tsegaye Demeke Lawyer

#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ
#አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
contact us: @LawsocietiesBot or email us: lawsocieties@gmail.com
#አለ_ህግ
ፍርድ ቤት፣
በችሎት ውስጥ መደረግ ያለባቸው ተግባራት


• ዳኞች ወደ ችሎት ሲገቡም ሆነ ሲወጡ ችሎት ውስጥ ያሉ ስዎች ከተቀመጡበት መነሳት፤
• ባለጉዳዮች የተስተካከለና የሰዎችን አትኩሮት ሊሰብ የማይችል አለባበስ ልበስ ይኖርባቸዋል፤
•የዳኞችን ትዕዛዝ ብቻ ጠብቆ መናገር ይኖርባቸዋል፤

• የተጠየቁ ጥያቄዎችን ግልፅና አጭር በሆነ መልኩ መግለፅ አለባቸው!

• ዳኛን ለማናገር የአክብሮት ቃል ማለትም ክቡር ዳኛ/ክብርት ዳኛ የተከበረው ችሎት የሚሉትን በጠቀም መናገር ይኖርባቸዋል፤

• አላስፈላጊ ፍርሃት፣ መጨናነቅ፣ መሸማቀቅና መርበትበትን በማስወገድ ሀሳብን ያለፍርሃት መግፅ ያስፈልጋል፤
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ
#አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
contact us: @LawsocietiesBot or email us: lawsocieties@gmail.co
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Entrust🔷ETC)
በኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር እና በአክስዮን ማኅበር መካከል ያላቸዉ መሰረታዊ አንድነት እና ልዩነት
1. አባልነት/Membership: -
ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ለማቋቋም የሚያስፈልጉ ሁለት/2/ ሰዎች ብቻ ሲሆኑ አክሲዮን ማኅበር ደግሞ ለመጀመር ቢያንስ አምስት/5/ አባላት ያስፈልጋሉ ፡፡
በአክሲዮን ማህበር ውስጥ በከፍተኛው የአባላት ብዛት ላይ ገደብ የለም ፡፡ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ቢበዛ 50 አባላት ብቻ ሊኖሩት ይችላል ፡፡
2. ዳይሬክተሮች/ Directors፡ -
ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በአንድ ወይም በብዙ ሥራ አስኪያጆች የሚተዳደር ሲሆን አክሲዮን ማኅበሩ ደግሞ አነስተኛ ቁጥራቸው ሦስት በሚሆኑ ዳይሬክተሮች የሚተዳደር ነው ፡፡
3. ፕሮስፔስተስ/ Prospectus: -
አንድ አክሲዮን ማኅበር ለአክሲዮኖቹና ለዕዳ ወረቀቶቹ ደንበኝነት እንዲመዘገብ ህዝቡን መጋበዝ ይችላሉ ፣ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ካፒታሉን ለማሳደግ ወደ ሕዝብ መሄድ አይችልም ፡፡
4. አነስተኛ ምዝገባ /Minimum subscription:-
በአክሲዮን ኩባንያ ውስጥ ሁሉም ካፒታል መፈረም አለባቸው እና ከምዝገባ በፊት የካፒታልው 25% መከፈል አለበት። ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ሙሉ በሙሉ በተከፈለ ካፒታል ይመዘገባል ፡፡
5. የማህበሩ ዋና ገንዘብ / capital፡-
ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ዋና ገንዘብ ከ15,000 ብር በታች መሆን አይችልም፡፡ በአክሲዮን ኩባንያ ደግሞ መነሻ ካፒታሉ ከ50,000 ብር በታች መሆን አይችልም፡፡
6. የተገደበ ሀላፊነት/Limited liability: -
ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ሆነ በአክስዮን ማህበር በማህበሩ ባዋጡት/ባላቸዉ ድርሻ ልክ ብቻ ሀላፊነት አላቸዉ፡፡ ማህበርተኞቹም ለማህበሩ ግዴታዎች አላፊ የሚሆኑት ባላቸዉ ድርሻ ልክ ብቻ ነው፡፡ ስለሆነም በተገደበው የኃላፊነት ደንብ መሠረት የኩባንያው አበዳሪዎች በድርጅቱ በራሱ ንብረት ላይ ብቻ የይገባኛል ጥያቄ ለማቅረብ የተገደቡ ሲሆን የድርጅቱ ባለአክሲዮኖች በግል በያዙት ንብረት ላይ ምንም ዓይነት የይገባኛል ጥያቄ የላቸውም ፡፡
7. የህግ ስዉነት/Legal personality፡-
ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበርም ሆነ አክስዮን ማህበር የራሳቸዉ የሕግ ሰዉነት ያላቸዉ ሲሆን በስማቸዉ የመክሰስ ሆነ የመከሰስ እንዲሁም ማንኛዉንም ስራ የመስራን ሰፊ መብት ተጎናፀፈዋል፡፡
8. የአክስዮኖችን ማስተላለፍን በተመለከተ/Transferable shares፡-
አክስዮን ማህበር ምንም እንኳን በማኅበሩ አንቀጾች ውስጥ የአክሲዮን ነፃ ዝውውርን መገደብ ቢቻልም (አንቀጽ. 333 (1) የአክሲዮን ኩባንያ አጠቃላይ መርሆዎች በነፃነት የሚተላለፉ በመሆናቸው በአክሲዮን ገበያ ሊሸጡ ወይም ሊገዙ ይችላሉ ፡፡ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በአባላቱ መካከል በነፃነት የሚተላለፉ ሲሆን ለሌሎች ግን እንደ አክስዮን ማህበር እንደፈለጉ በነፃነት የሚተላለፍ አይደለም ምክንያቱም ሲመሰረትም ቤተሰባዊ እና ቅርርብን መሰረት ተደርጎ የሚመሰረት ማህበር በመሆኑ ነው፡፡
☞ሰናይ ጊዜ
© Yilkal
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Entrust🔷ETC)
የአክስዮን ማህበር መመስረት የሚያስገኙ ጥቅሞች፡-
የአባላቱ ሀላፊነት የተወሰነ መሆኑ፤
የአክስዮን አባላቱ ቢሞቱም በወራሾች በቀላሉ መቀጠል ስለሚችል የማይሞት መሆኑ፤
አክስዮን ማህበር ትልቅ ካፒታል የሚጠይቅ ስለሆነ ግዙፍ ኢንተርፐራይዞች እንዲኖሩ ማድረግ መቻሉ፤
ጠንካራ የገንዘብ አቅም መኖሩ፤
ድርሻዉ በቀላሉ የሚተላለፍበት እና የአባላትም ቁጥር የሚቀያየር መሆኑ፤
ቦንድ/የብድር ሰነድ/መሸጥ የሚችል መሆኑ፤
የተለያየ የአስተዳደር አካላት ማለትም የዳይሬክቶሮች ቦርድ፤ የባለአክስዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ እና የዉጪ ኦዲተር ያሉት መሆኑ፤
የመስፋፋት እድል መኖሩ፤
የተበተነ አደጋ መኖሩ/Diffused risk/
ከ50 በላይ አባላት ያሉት ማቋቋም ሲፈለግ፤
መዋጮ ከህዝብ መሰብሰብ መቻሉ ማለትም ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ለማቋቋም የአክስዮን ሽያጭ ማስታወቂያ ለህዝብ አስነግሮ ካፒታል መሰብሰብ አይችልም ፡፡ በመሆኑም ብዙ ገንዘብ በሚጠይቁ ዘርፎች ለመሰማራት ካፒታልን ከህዝብ መሰብሰብ የሚያስችል ስለሆነ አክስዮን ማህበር ተመራጭ ያደርገዋል፡፡
ለሶስተኛ ወገኖች የበለጠ አስተማማኝ እና ተቋማዊ ቅርፅ የያዘ መሆኑ፤ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር አሰራሩ ቀላል፤ በህግ የሚደረግበት ቁጥጥር የላላ፤ የአስተዳደር ስርዓቱ በአንፃራዊነት የማያስተማምን ስለሆነ 3ኛ ወገኖችን ብዙ አያስተማምንም፡፡ በተቃራኒዉ አክስዮን ማህበር አሰራሩ ዉስብስብ፤ዝርዝር የህግ ቁጥጥር ያለበት፤ አስተዳደሩ በብዙ አካላት የተደራጀ ስለሆነ ለአባላትም ሆነ ከአክስዮኑ ጋር ግኑኙነት የሚፈጥ የ3ኛ ወገኖች መብት ለማስጠበቅ አስተማማኝ ነው፡፡
አንዳንድ የስራ ዘርፎች በህግ በግልጽ በአክስዮን ማህበር ብቻ የሚሰሩ መሆናቸዉ፤ ምሳሌ ባንክ እና ኢንሹራንስ ስራ በሀላፊነቱ የጠወሰነ የግል ማህበራት የማይሰራ መሆኑ፤
ስለሆነም የአክስዮን ማህበር ከላይ ባየናቸዉ ባህሪያት ያሉት ከአባላቱ የተለየ ሀላፊነት ያለበት ራሱን የቻለ የህግ ሰዉነት ያለዉ ድርጅት መሆኑ ተመራጭ የሚያደርገዉ ቢሆንም የራሱ ሆነ ድክመቶች ያሉት ሲሆን እንደሚከተለዉ እናያለን፡፡
የአክስዮን ማህበር መመስረት ያሉት ጉዳቶች፡-
አክስዮን ማህበር ለመመስረት ዉስብስብ እና አስቸጋሪ ስነ ስርዓት መጠየቁ፤
በምስረታ ሂደት የተለያዩ ባለሙያዎች አስፈላጊ መሆናቸዉ ምሳሌ መመስረቻ ፁሁፍን እና መተዳሪያ ደንቡን ለማዘጋጀት የህግ ባለሙያ ማስፈለጉ፤ በአይነት የሚደረገዉን መዋጮ ለመወሰን የሂሳብ ሰራተኛ እና ማህንዲስ አስፈላጊ መሆኑ በምስረታ ሂደትን ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ መሆኑ፤
በቀጥታ የንብረቱ ባለቤት ያለመሆን፤
የዉሳኔ መዘግየት መኖሩ ምክንያቱም በእያንዳንዱ ወሳኝ ጉዳይ ላይ የጠቅላላ አባላትን እና የተለያዩ አካላትን ዉሳኔን የሚያስፈልግ መሆኑ፤
በጥቂት እጅ የወደቀ እና የተንኮል አስተዳደር የመፈጠር እድሉ ሰፊ ነው ምክንያቱም ባላክስዮኖቹ በየሀገሩ የተበታተኑ እና የማይተዋወቁ በመሆናቸዉ በቀላሉ ለመቆጣጠር እና መብታቸዉን በተደራጀ መልኩ ለማስከበር ይቸገራሉ፡፡ ምሳሌ፡- የባንክ አባሎች የማይተዋዉ ብዙ ቁጥር ያለቸዉ በመሆኑ ቦርድ እና ስራ አስኪያጆችን በየቀኑ ለመቆጣጠር ያስቸግራል፡፡
ሚስጢር ያለመጠበቅ ችግር

ሰናይ ጊዜ 👏
YilkalG.
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
ስለወጭና ስለኪሳራ /በክርክሩ ምክንያት የወጡ ወጪዎች የሚመለከተው ወገን
#አለ_ህግ
#ስለ ፍርድ ቤቱ ሥልጣን
በሌላ አኳኋን እንዲፈጸም በግልጽ ካልተደነገገ በቀር በክስ ምክንያት ስለሚከፈለው ስለማናቸውም ወጭና ኪሳራ፣ የሚከፈለውን ወገን የወጭንና የኪሳራውን ልክ የሚከፈልበትን የሃብት ምንጭ የአከፋፈሉን ሁኔታ ሌላውንም ተገቢ መስሎ የታየውን ውሳኔ ወይም ትእዛዝ ፍርድ ቤቱ ትክክል በስሎ በሚገመተው ሁኔታ ሊሰጥ ይችላል፡፡
#ስለወጭና ስለኪሳራ ዝርዝር
ተረቺው ለረቺው ኪሳራና ማናቸውንም ወጭ እንዲከፍል ፍርድ ቤቱ ሲያዝ፣ ወጭ ያደረገው ወገን የወጭውን ልክ የሚያሳይ ዝርዝር አዘጋጀቶ ማቅረብ አለበት፡፡
ዝርዝር የሚቀርበው ፍርዱን ለፈረደው ፍርድ ቤት ሲሆን አንዱ ግልባጭ ለከፋዩ ወገን ይሰጣል፡፡
#የወጭው ሂሳብ ስለሚመረመርበት ሁኔታ
የወጭው ሂሳብ ዝርዝር ለፍርድ ቤቱ ከቀረበ በኋላ ትክክለኛነቱ የሚመለመርበትን ቀን ቀጠሮ ወስኖ ባለጉዳዮቹ እንዲቀርቡ ያዛል፡፡
ሂሳቡን መርምሮና ተከራካሪዎቹ ወገኖች የሚያቀርቡትን ሃሳብ ተቀብሎ ከዚህ ቀጥሎ የተመለከቱትን ይፈጽማል፡፡
በቀረበው የሂሳብ ዝርዝር ውስጥ በቂ ባልሆነ ምክንያት ከፍ ብሎ የሚታየውን ገንዘብ ይቀንሳል፡፡ ወይም
በዝርዝሩ ውስጥ የክሱን ጉዳይ ለማስፈጽም ወይም አስፈላጊውን ዳኝነት ለመከታተል ተገቢ ያልሆነ ወጭ ተመልክቶበት የተገኘ እንደ ሆነ ፍርድ ቤቱ ሊቀንሰው ወይም ሊያስቀረው ይችላል፡፡
ወጭው ወይም ኪሳራው ሊከፍለው የሚገባው ወገን የሚጠይቀውን የወጭ ዝርዝር ያላቀረበ እንደ ሆነ ፍርድ ቤቱ ይህንኑ መዝግቦ ሌሎች ወገኖች ያደረጉትን ወጭ መርምሮ ያረጋግጥላቸዋል፡፡ ወይም የሂሳቡን ዝርዝር አንዱ ወገን ባለማቅረቡ ምክንያት ሌሎች ወገኖች እንዳይጎዱ ላላቀረበው ወገን ተገቢ ግምት ያለው ኪሳር ይወስንለታል፡፡
ማንኛውም የወጭ ወይም የኪሳራ ገንዘብ በፍርዱ መሰረት እስኪፈጸም ድረስ ዋናው ፍርድ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በሕግ የተወሰነ ወለድ ይታሰብበታል፡፡
ፍርድ ቤቱ በኪሳራና በወጭ አከፋፈል ምክንያት ለተነሳው ክርክር ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት የፍርድ ቤቱ ሬዢስትራር ወይም የምግብ ቤቱ ሹም የቀረበውን ዝርዝር መርምሮና ተከራካሪዎቹ ወገኖች የሚያቀርቡትን አሳብ ተቀብሎ የተጣራውን ሂሳብ እንዲያቀርብለት ከማዘዝ የዚህ ቁጥር ድንጋጌ አያግደውም፡፡
#ካሳ ስለሚከፈልበት ምክንያት
በማንኛውም ክስ ወይም ክርከር ላይ በክስ ወይም በመከላከያ መልክ ከሳሹ ወይም ተከሳሹ ያቀረበው የመከራከሪያ ወይም የመከላከያ ማስረጃ ወይም ክርክሩ ራሱ ወይም ማስረጃው አሰተኛ ነው ወይም መከራከሪያውንና አሰተኛ ማስረጃ ያቀረበው ወገን በሐሰት የተከራካሪውና አሰተኛ ማስረጃ ያቀረበው ክርክሩን ለማሰናከል፣ ጊዜ ለመፍጀት ወይም አንደኛውን ወገን ለመበደል ወይም ለማጉላላተር ሆነ ብሎ ያደረገው ነው በማለት ወይም የክርክሩንና የማስረጃውን አሰተኛነት እያወቀ ወይም ማወቅ ሲገባው ሆን ብሎ ማቅረቡን ሲያመለክትና ፍርድ ቤቱም ተቃዋሚው ወገን ያቀረበውን ነገር እርግጠኛነት ሲረዳው ይህንኑ በመዝገቡ ላይ አስፍሮ አሰተኛ ማስረጃ ወይም ክስ ወይም መከላከያ ያቀረበው ወገን ላቀረበው ለእያንዳንዱ ሀሰተኛ ማስረጃአንዱን ወገን ለመበደል፣ ለማጉላላት ወይም ጊዜ ለመፍጀት ላቀረበው አሰተኛ ክርክር ከማናቸውም ኪሳራና ከሌላው ወጭ በቀር ከ500 ብር የማይበልጥ ካሳ ለተበዳዩ እንዲከፈል ሊወስንበት ይችላል፡፡
#ይህም በወንጀለኛ መቅጫ ሕግ በቁጥር 446 በተመለከተው መሰረት ሃሰተኛ ማስረጃና ክርክር በማቅረቡ ከመከሰስና ከመቀጣት ነፃ ሊሆን ይችላል፡፡
ካሳ የተወሰነለት ወገን በሀሰት በመከሰሱ ወይም ሃሰተኛ መከላከያ ወይም ክስ የቀረበበት በመሆኑ ካሳና ኪሳራ ይገባኛል ሲል ሌላ ክስ አቅርቦ ካሳ ወይም ኪሳራ የተወሰነለት እንደሆነ በመጀመሪያው ክስ ላይ ከሚወስንለት ኪሳራና ካሳ ላይ ይቀነስበታል፡፡
#ስለ ይግባኝ
ማንኛውም ተከራካሪ ወገን በስረ ነገሩ ላይ ይግባኝ ባያቀርብም፣ በተወሰነበት የወጭ ወይም የኪሳራ አከፋፈል ብይን ላይ ይግባኝ ለማለት ይችላል፡፡ በዚህም ነገር ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የሚሰጠው ውሳኔ የመጨረሻ ይሆናል፡፡
ፀጋዬ ደመቀ ሎየር
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
.......................ተበዳሪውም በአበዳሪው ሳይጠየቅ መክፈል ቢፈልግ ለመክፈል ያለውን ሀሳብ ከአንድ ወር በፊት ካስታወቀ በኋላ ዕዳውን መመለስ እንደሚችል እንዲሁ ተደንግጓል፡፡

በብድር ላይ ሊኖር ስለሚችል ወለድ፡- በብድር ውል ላይ ሊኖር ስለሚችል ወለድም ለተዋዋይ ወገኖች ነፃ ፈቃድ የተተወ ጉዳይ ነው፡፡ ብድሩ ወለድ የሚከፈልበት ስለመሆኑ በውሉ በግልፅ ካልተገለፀ ግን ተበዳሪው በምንም መልኩ ወለድ እንዳይከፍል ሕጉ ጥበቃ ያደርግለታል፡፡ ሕጉ በብድር ውሉ ላይ ወለድ ይኑር አይኑር የሚለውን ጉዳይ በተዋዋይ ወገኖች እንዲወሰን ነፃነት የሰጠ ቢሆንም በወለድ መጠኑ ልክ ላይና ስለሚከፈልበት ጊዜ ወይም ወለዱ ስለሚሰላበት ጊዜ ግን ገደብ አስቀምጧል፡፡ በዚህም መሰረት ተዋዋይ ወገኖች የወለዱን መጠን በዓመት ከ12 በመቶ በላይ ማድረግ እንደማይችሉ ገደብ ጥሏል፡፡ እንዲሁም የወለዱ መጠን በውሉ ላይ ካልተገለፀ እና ወለድ የሚከፈልበት ብድር መሆኑ ብቻ ተገልፆ ከሆነ ወይም ወለዱ ከ12 በመቶ በላይ ይሆናል የሚል የውል ቃል ካለ መከፈል የሚችለው የወለድ መጠን በዓመት 9 በመቶ ብቻ እንደሚሆንና የሚሰላውም ተቃራኒ የሚሆን የውል ቃል ከሌለ ብድሩ ከተሰጠበት ጊዜ ጀምሮ በሚቆጠር በየዓመቱ መጨረሻ ላይ መሆን ይገባዋል ይላል ሕጉ ፡፡

የብድር አከፋፈል (የሚከፈለው ነገር)፡- በብድር አመላለስ ወቅት ሌላው ግለፅ መሆን ያለበት ጉዳይ ብድሩ በየትኛው ሀገር የገንዘብ ዓይነት ነው? ከብድሩ በኋላ የምንዛሬ ዋጋ መለዋወጥ ቢያጋጥምስ ምን ይሆናል? የሚለው ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ የፍትሐብሔር ሕጉ ግልፅ ድንጋጌዎች አሉት፡፡ በዚህም መሰረት የብድር ውሉ የተደረገው በኢትዮጵያ ብር ከሆነ ብድሩ በሚመለስበት ወቅት ባለው ሕጋዊ የኢትዮጵያ የመገበያያ ገንዘብ ወይም ለዚህ የገንዘብ መጠን የሚተካ የውጭ ምንዛሬ በማቅረብ ከዕዳው ነፃ እንደሚሆን ተደንግጓል፡፡ የሚከፈለውን የገንዘብ መጠን በተመለከተ የብድር ውሉ በሚከናወንበት ጊዜ በትክክል የተበደረውን ያክል እንጂ ሌላ ነገር እንደማያካትትና በመሀል ሊያጋጥም የሚችለውን ወይም ያገጠመውን የገንዘቡ ዋጋ መለዋወጥ ግምት ውስጥ መግባት እንደሌለበትም ሕጉ አያይዞ ይገልፃል፡፡ ብድሩ በውጭ አገር ገንዘብ ተደርጎ ከነበረ ደግሞ ብድሩ በሚከፈልበት ጊዜ በዛ አገር ሕጋዊ መገበያያ በሆነው የገንዘብ ኖት መከፈል ያለበት ሲሆን መጠኑም የተበደረውን ያክል ብቻ መሆን እንዳለበት ሕጉ አመልክቷል፡፡ የብድር ውሉ የተደረገው ከገንዘብ ውጪ ባሉ የሀብት ዓይነቶች በሚሆንበት ጊዜ ለምሳሌ፡- ለምግብ የሚሆኑ ነገሮች፣ ሸቀጦች ወይም መአድናት ሲሆኑ ተበዳሪው በተበደረው ልክ ብዛቱንና ዓይነቱን በመክፈል ከዕዳው ነፃ ይሆናል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ከብድሩ በኋላ በሚኖር የዋጋ መለዋወጥ የብድድር አመላለሱን መጠንና ዓይነት ላይ የሚያሳድረው ተፅእኖ የለም።

federal attorney general
You shall Share......
ሼር አድረጉት
ለወዳጅ ዘመድ ጓደኛ አጋሩት፣
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
Attorney I for Effesson Branch

IMMEDIATE INTERNAL/EXTERNAL VACANCY ANNOUNCEMENT


About the Organization:


VisionFund Micro Finance Institution (S.C) is an Institution established according to proclamation No. 40/96 which currently amended to 626/2009 to provide financial services to the productive poor in the rural and urban areas of Ethiopia. VisionFund is currently operating in five of the Regional States of the country. VisionFund MFI is currently looking for candidates for Attorney I role for Effesson Branch. The successful candidates will have skills and experience that meet the following requirements:


1. Major Duties and Responsibilities


• Assists the Branch staff in handling all issues related to collateral & the safe custody of all legal documents on real estate mortgage & chattel mortgage; 

• Assists in registering & discharging mortgaged items;

• Ensures the safe custody of all legal documents on real estate mortgage & chattel mortgage;

• Draws up draft contracts, agreements, forms, letters of guarantee and other transactional documents, etc. that suit a specified purpose;

• Examines judgments & court rulings; analyzes their impact on company business & advises supervisor on approaches to be followed;

• Gathering facts and establishing evidence, conducting investigations, examination analyses of cases and preparation of contracts and claims;

• Ensures the proper & timely delivery of notices to delinquent clients.

• Investigates & takes proper legal actions to rectify theft, forgeries & misappropriation of funds & property;

• Complies & analysis information & statistics that would assist in carrying out court activities & provides legal advice & assistance to the branches in legal matters of limited complexity and gravity & in translation work of legal documents.

• Looks into and analyzes law sources such as statutes, recorded judicial decisions, legal articles and codes to prepare legal documents such as briefs, pleadings, appeals contracts for review, etc.

• Prepares, cases, pleadings, suits, statements of claims, petitions, defenses, affidavits in the name and on behalf of the institution;

• Represents the branches before all levels of courts of law including police stations & public authorities;

• Submits a written report to the branch, Area Legal Coordinator and HO legal & Recovery Director on the status of cases filed at court with collections made through court action. 


Job Requirements:

• Diploma or LLB Degree in law with minimum 2 years for Diploma & 1 year for Degree holder with relevant work experience. 

• Local language knowledge, communication skill & computer skill is advantageous.

• knowledge of civil, commercial codes & analytical skill


• Terms of Employment:  Permanent

• Salary:                             
 As per the Institution salary scale

• Closing Date:                 
 April 24, 2022


How To Apply:

Candidates who fulfil the above requirements can submit the application letter, updated curriculum vitae with names and addresses of up to 3 references and non-returnable copies of credentials online throughVFE_vacancy@wvi.orgor in person to:Effesson BranchorNorth Area Office (Debre birhan)
Posted: 04.18.2022
Deadline: 04.24.2022


Job Category: Legal
Employment: Full time

Salary: As per the Institution salary scale

Location: Effesson, Amhara

https://www.ethiojobs.net/company/6100/VisionFund-Micro-Finance-Institution-S.C/
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
ያለመናገር መብት
መግቢያ

።።።።።።።።።🙏 #አለ_ህግ
በወንጀል ፍትህ አስተዳደር ስርአት ውስጥ የተያዙ ወይም የተከሰሱ ሰዎች
ያለመናገር መብት (the right to remain silent) አላቸው፡፡ ይህ መብት
የተጠረጠሩበትን ወይም የተከሰሱበትን ወንጀል እንዲያምኑ ያለመገደድ
ወይም ቃል እንዲሰጡ በሚጠየቁበት ወቅት ቃላቸውን ላለመስጠት መብት
ያላቸው መሆኑን የሚመለከት ነው፡፡ ለዚህም ሲባል ተጠርጣሪዎች በሚያዙበት
ወቅት የሚናገሩት ነገር የእምነት ቃል ሆኖ በፍርድ ሂደት በማስረጃነት
ሊቀርብባቸው ስለሚችል ላለመናገር መብት ያላቸው መሆኑን የሚጠብቅ
ነው፡፡ ይህ መብት የሚመነጨው መሰረታዊ ከሆነ የወንጀል ህግ እና የሰብአዊ
መብት መርሆች ከሆኑት እራስ ላይ ያለመመስከር ወይም ያለመወንጀል
መርህን (protection against self-incrimination) እና በፍርድ
እስኪረጋገጥ ድረስ ነፃ ሆኖ የመገመት (presumption of innocence
until proven guilty) መሰረት አድርጎ ነው፡፡
መብቱን የማክበርና የማስከበር ግዴታ
ይህ ያለመናገር መብት ለማን የተገባ ወይም የእነማን መብት ነው የሚለውን
ስንመለከት ማናቸውም በፖሊስ ተጠርጥሮ የሚያዝ፣ የተያዘ፣ የሚከሰስ
ወይም የተከሰሱ ሰዎችን የሚመለከት ነው፡፡ ይህን መብት ለማስከበር ግዴታ
ያለባቸው ደግሞ ማናቸውም የወንጀል ምርመራ እንዲሁም የመያዝ ተግባር
የሚፈፅሙ ፖሊሶችና ውሳኔ የሚሰጡ ዓቃቤ ህጎችንም እንዲሁም በፍርድ
ሂደት የሚሳተፉ ዳኞችንም ይጨምራል፡፡ እነዚህ አካላት የምርመራ፣ ውሳኔ
አሰጣጥና ፍርድ ሂደት መብቱን ማክበርና የማስከበር ሀላፊነት አለባቸው፡፡
መብቱ መከበር ያለበት ጊዜና ሂደት
ይህ መብት መቼ የሚፈፀም ወይም መከበር ያለበት እንደሆነ ስንመለከት
በመያዝ፣ በምርመራ፣ በውሳኔ አሰጣጥና በፍርድ ሂደት በአጠቃላይ
በማናቸውም የወንጀል ፍትህ አስተደደር ሂደት ሊከበር የሚገባ መብት ነው፡፡
በዋናነት ተጠርጣሪዎች በሚያዙበት ጊዜ ፖሊሶች መብቱን ማክበርና
ግዴታቸውንም መወጣት ይጠበቅባቸው፡፡ ከዚህ በመቀጠል ባሉ የወንጀል
ፍትህ ሂደቶችም ውስጥ ማለትም የወንጀል ምርመራ፣ የውሳኔ አሰጣጥና
የፍርድ ሂደት ወቅት ሊከበርና ሊጠበቅ ይገባል፡፡
የመብቱ ይዘት
ያለመናገር መብት ተጠርጣሪዎች በሚያዙበት ጊዜ ለሚይዛቸው አካል
ላለመናገር፣ ቃል እንዲሰጡ በሚጠየቁበት ወቅት ላለመናገር እንዲሁም
በፍርድ ሂደት እንዲመሰክሩ ያለመገደድ ናቸው፡፡ ይህ መብት በህገ
መንግስታችን አንቀፅ 19(3) እንደተደነገገው የሚያዙ ሰዎች በሚያዙበት
ወቅት ወዲያውኑ በሚገባቸው ቋንቋ ያለመናገር መብት እንዳላቸውና
የሚሰጡት ማንኛውም ቃል ፍርድ ቤት በማስረጃነት ሊቀርብባቸው
እንደሚችል መረዳት በሚችሉት ቋንቋ እንደተያዙ ወዲያውኑ ማስገንዘቢያ
እንዲሰጣቸው መብት አላቸው፡፡ በተጨማሪም በአንቀፅ 19(5) መሰረት
የተያዙ ሰዎች በራሳቸው ላይ በማስረጃነት ሊቀርብ የሚችል የእምነት ቃል
እንዲሰጡ ወይም ማናቸውም ማስረጃ እንዲያምኑ ሊገደዱ እንደማይገባ እና
በማስገደድ የተገኘ ማስረጃ ተቀባይነት እንደሌለው ይደነግጋል፡፡ በአንቀፅ
20(3) በፍርድ ሂደት ባሉበት ጊዜ በተከሰሱበት ወንጀል እንደ ጥፋተኛ
ያለመቆጠር፣ በምስክርነት እንዲቀርቡ ያለመገደድ መብት አላቸው፡፡ ይህን
መብት ተፈፃሚ ለማድረግ በወንጀል ስነ ስርአት ህግ አንቀፅ 27(2) መሰረት
መርማሪው ፖሊስ የተጠረጠረውን ሰው ቃሉን ለመስጠት ነፃ እንደሆነ እና
ፈቅዶ የሚሰጠው ማናቸውም ቃል በማስረጃነት የሚቀርብ መሆን አስቀድሞ
መንገር እንደሚገባ ይደነግጋል፡፡
በተጨማሪም የምርመራ ስራ በሚከናወንበት ወቅት የምርመራ ቃል መቀበያ
ፎርሞች ይህው ማስገንዘቢያ ተገልጾ እንዲታተሙ የሚደረግ ሲሆን ህጉ
በሚያዘውና በፎርሞቹ ላይ በተቀመጠው መንገድ መብቱን ተግባራዊ ማድረግ
እና ይህን ተግባራዊ ከማድረግና መብቱ ሳይነገር ወደ ጥያቄ ከመግባት
አንፃር ያለውን ክፍተት ማስተካከል ይጠበቃል፡፡
ይህ መብት በተመሳሳይ መልኩ ሀገራችን በተቀበለቻቸው አለም አቀፍ
የሰብአዊ መብቶች ስምምነቶች በግልፅ እና በትርጉም የተካተተ ነው፡፡
በአለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች መግለጫ አንቀፅ 10 በፍትሀዊ የፍርድ
ሂደት መብት (fair trial) ትርጓሜ እና አንቀፅ 11 ነፃ ሆኖ የመገመት መብት
እውቅና የተሰጠው ነው፡፡ በአለም አቀፍ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች
ስምምነት አንቀፅ 14/3/g/ መሰረት በራስ ላይ ለመመስከር ከመገደድ
መጠበቅ እና በአንቀፅ 14/2/ ነፃ ሆኖ የመገመት መብት ተካቶ ይገኛል፡፡
በተመሳሳይ በሌሎች ሀገራትም ይህ መብት እውቅና የተሰጠውና ተግባራዊ
የሚደረግ ስርአት እና የአሰራር ደረጃ (standard) ነው፡፡ ሆኖም ይህ
ያለመናገር መብት ለህግ አስከባሪ አካላት ማንነትን እና አድራሻን ከማሳወቅ
ግዴታ የሚጠብቅ ሳይሆን ከተጠረጠሩበት ወንጀል ጋር በተያያዘ ያለመናገር
መብትን የሚመለከት ነው፡፡
በዚህም መሰረት መብቱን ተፈፃሚ ለማድረግ አንድ ተጠርጣሪ በሚያዝበት
ወቅት በተመሳሳይ ፆታ ሆኖ ማንነትን ወይም ህግ አስከባሪ አካል መሆንን
ማሳወቅ፣ የሚያዘው በፍርድ ቤት ትእዛዝ መሰረት ከሆነ ይህንኑ ማሳየት
ወይም እንደ እጅ ከፍንጅ ባለ ሁኔታ የሚያዝ ከሆነም የመያዙን ህጋዊነት
ማረጋገጥ፣ ቀጥሎም በቁጥጥር ስር የዋለ መሆኑን መንገር፣ የሚያዝበትን
ምክንያት ወይም የተጠረጠረበትን ወንጀል መንገር፣ ያለመናገር መብት
እንዳለው እና የሚናገር ነገር በፍርድ ቤት በማስረጃነት ሊቀርብ የሚችል
መሆኑን ማስገንዘብ፣ በጠበቃ የመወከል መብት እንዳለውም መግለፅና
ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ እነዚህንም በሚገባው ቋንቋ መንገር
ያስፈልጋል፡፡
በአጠቃላይ የዜጎችን መብቶች ተፈፃሚ ለማድረግና አለማአቀፍ የወንጀል
ምርመራ አሰራር ደንቦችን ተግባራዊ ለማድረግ የህግ አስከባሪ አካላት
የተጠርጣሪዎችና የተከሰሱ ሰዎችን መብቶች ማወቅና ተግባራዊ ማድረግ
ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ አንፃር በህገ መንግስታችን እና በሌሎች ህጎች እውቅና
የተሰጠውን የሚያዙና ቃል የሚሰጡ ሰዎችን ያለመናገር መብት እንዳላቸው
እና የሚሰጡት ቃል በፍርድ ቤት በማስረጃነት ሊቀርብ እንደሚችል
በሚያዙበት ጊዜና ቃል እንዲሰጡ በሚጠየቁበት ጊዜ አስቀድሞ ማስገንዘብ
ያስፈልጋል፡፡ ዜጎችም ይህን መብታቸውን አውቀውና ተገንዝበው ይጠቅመናል
በሚሉት መንገድ መጠቀም ይገባል፡፡
ምንጭ የፍትህ ሚኒሥቴር ማህበራዊ ገጽ
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
#1-
ደሀ ደንብ
ዳኝነት ሳይከፈል፣ በነፃ መዝገብ ማስከፈት

ክስ ለማቅረብ የፈለገ ወገን ከፍርዱ ለሚያገኘው የዳኝነት አገልግሎት መክፈል የሚገባውን የዳኝነት ገንዘብ ለመክፈል የሚያስችል የገንዘብ አቅም የሌለው ከሆነ ክሱን ያለዳኝነት ገንዘብ በደሀ ደንብ መሠረት የማቅረብ መብት እንዳለው በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 215 ተደንግጓል፡፡ ክሱን የሚያቀርበው ወገን ድሀ በመሆኑ ምክንያት የዳኝነት ገንዘብ ሳይከፍል ክሱን አቅርቦ እንዲያሰማ ሊፈቅድለት ይገባል? የሚለው ጉዳይ ሊለይ የሚችልበት ዝርዝር አፈፃፀም ደንቡም ፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 467 እና ተከታዩ ድንጋጌዎች ተመልክቷል፡፡ እነዚህ ደንቦች ተፈፃሚነታቸው ክስ ለማቅረብ በፈለገ የተፈጥሮ ሰውም ሆነ በሕግ ሰውነት ያላቸው ወገኖችም ጭምር ነው፡፡
በዚህም መሠረት ድሀ ነኝ፤ መብቴን ለማስከበር ያለኝ ፍላጐቴ በዳኝነት ገንዘብ እንቅፋት ምክንያት ሊሰናከል አይገባም፡፡ ስለሆነም በድሀ ደንብ መሠረት ክሱን በነፃ እንዳሰማ ይፈቀድልኝ የሚል ማናቸውም ከሳሽ ድሀ መሆኑን ሊያመለክት የሚችል የሚገኝበትን የገንዘብ አቋም ማረጋገጥ ይገባዋል፡፡ ይህም ከሳሹ የሚገኝበት የገንዘብ አቋም ከተረጋገጠ በኋላ ለክሱ ሊከፈል የሚገባው የዳኝነት ገንዘብ መጠን ከሳሹ ከሚገኝበት የገንዘብ አቋም አኳያ ተገናዝቦ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 467 መሠረት ድሀ የመሆኑና ያለመሆኑ ጉዳይ ሊለይ ይገባል፡፡
ሰ/መ/ቁ. 79555 ቅጽ 14፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 215፣ 467
አንድ ሰው በፍርድ ሊያልቅ የሚገባው ጉዳይን ፍርድ ቤት ይዞ ሲቀርብ የዳኝነት አገልግሎት ክፍያ መክፈል ያለበት መሆኑን የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 215፣ ከ467 እስከ 479 ድረስ የተደነገጉት ድንጋጌዎች ያሳያሉ፡፡ የዳኝነት አገልግሎት መክፈል የማይችል ሰው ክስ ለማቅረብ የሚችልበት አግባብ ስለመኖሩም ተጠቃሽ ድንጋጌዎች ያስገነዝባሉ፡፡ አንድ የዳኝነት አገልግሎት ክፍያ ለመክፈል የማይችል ሰው በደሃ ደንብ ክስ ለማቅረብ የሚችል ሲሆን ለመክፈል አቅም እያለው ክስ ያቀረበ መሆኑ ከተረጋገጠ ግን መዝገቡ እንደሚዘጋ፣ የተዘጋ መዝገብ ደግሞ የዳኝነት አገልግሎት ክፍያ /ገንዘቡን/ ለመክፈል ዝግጁ እስከሆነ ድረስ የሚንቀሳቀስለት መሆኑን የሥነ ሥርዓት ሕጉ ድንጋጌዎች መንፈስና ይዘት ያስገነዝባሉ።
ሰ/መ/ቁ. 52942 ቅጽ 12፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 215፣ 467-479 ....ይቀጥላል --- source ፦Amharic Legal Glossary Abrham Yohanes
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
የብድር ውል
የብድር ውል (በኢትየጵያ የፍትሐብሔር ሕግ ከቁጥር 2471-2489) ከዚህ እንደሚከተለው ብድር የሚለውን ቃል ፍቺ ይሰጣል፡፡
“የሚያልቅ ነገር ብድር ማለት ከተዋዋዮቹ አንዱ ወገን አበዳሪው ሌላውን ተበዳሪ ሰው የተበደረውን ነገር በዓይነቱ ለመመለስ ተገዳጅ በማደረግ ገንዘብ ወይም በማገልገል የሚያልቅ ሌላ ነገር ለተበዳሪው ለመስጠትና ሀብትነቱን ለማስተላለፍ የሚገደድበት ውል ነው” ይላል፡፡
በተቋማችን የብድር ውል ለመዋዋል ሁለቱም ወገኖች ሊያሟላቸው የሚገባቸውን ዝርዝር ቅድመ ሁኔታዎች ከዚህ እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡
. በተቋሙ የDARIS ስርዓት የተዘጋጀ ሰነድና የአገልግሎት ቁጥር፤
. ተዋዋዮች ከህግ ወይም ከውል የመነጨ ስልጣን ያላቸው መሆኑን ማረጋገጫ ሰነድ፤
. የተዋዋዮች በዘመኑ የታደሰ መታወቂያ፤
. የተዋዋዮች የጋብቻ ማስረጃ ወይም የትዳር አጋር የፈቃድ ስምምነት (ውክልና)፤
. ተበዳሪው የንግድ ማህበር ከሆነ መመስረቻ ጽሑፍ፣ መተዳደሪያ ደንብ፣ የንግድ ዋና ምዝገባ እና እንደ አስፈላጊነቱ ቃለ-ጉባኤ፤
. ገንዘቡ የተላለፈበት (የባንክ ስቴትመንት ስሊፕ) እና የባንክ ደብዳቤ፤
. በተቋማችን ተገልጋዮች ከዚህ በላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች አሟልተው ሲቀርቡ ለአገልግሎቱ የሚወስደው ጊዜ 30 ደቂቃ ነው፡፡
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ( share ) በማድረግ ብልሹ አሰራር እና ሙስናን ይከላከሉ፡፡

#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
#የሚንቀሳቀስ ወይንም የማይንቀሳቀስ ንብረት መያዣ ውል

“የመያዣ ውል ማለት አንድ ባለዕዳ በባለገንዘቡ በኩል የሚገባውን ግዴታ ለመፈጸም መቻሉን ለማረጋገጥ መያዣ ተብሎ የሚጠራውን ዕቃ ለመስጠት የሚገደድበት ውል ነው፡፡” በማለት በፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2825 ላይ ተደንግጎ ይገኛል፡፡

“ዋስትና የተሰጠበት ግዴታ ከፍተኛው ገንዘብ ምን ያህል እንደሆነ በማንኛቸውም ሁኔታ ቢሆን በግልጽ ተጠንቅቆ በመያዣው ውል ውስጥ መመልከት ይገባዋል፡፡ ይህ ካልሆነ ግን ውሉ ፈራሽ ይሆናል” በማለት በፍ/ብ. ቁ 2828(1) ተጠቅሷል፡፡

“የመያዣው ውል ከ500 የኢትዮጵያ ብር በላይ የሆነ እንደሆነ ውሉ በጽሁፍ ካልተደረገና ይኸውም ጽሁፍ እርግጠኛ ቀን ካገኘበት ዘመን ጀምሮ ካልሆነ በቀር አይጸናም፡፡ ይላል፡፡” በፍ/ብ. ቁ 2828 (2)፡፡

“የማይንቀሳቀስ ንብረት መያዣን የሚያቋቁም ውል ወይም ህጋዊ ሰነድ በጽሁፍ ካልተደረገ በቀር ዋጋ የለውም፡፡ በማለት በፍ/ብ.ቁ 3045 (1) ላይ ተጠቅሷል፡፡

በፍ/ብ. ቁ 3045 (2) መሰረት መያዣ የተሰጠበት ገንዘብ ልክ በኢትዮጵያ ገንዘብ ካልተመለከተ በቀር ፈራሽ ነው ::

በዚህም መሰረት በፍ/ብ. ቁ 2825 እና 3041 መሠረት የመያዣ ውል ለመዋዋል ወደ መስሪያ ቤታችን ሲመጡ ተገልጋዮች ማሟላት ያለባቸው ጉዳዮች እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል፡፡

.በተቋሙ የDARIS ስርዓት የተዘጋጀ ሰነድና የአገልግሎት ቁጥር

.የተዋዋዮ በዘመኑ የታደሰ መታወቂያ፤

.የማይንቀሳቀስ ንብረት ከሆነ ሁለት የሰው ምስክሮችና መታወቂያ፤

.ተዋዋዮች ከህግ ወይም ከውል የመነጨ ስልጣን ያላቸው መሆኑን ማረጋገጫ ሰነድ፤

.የተዋዋዮች የጋብቻ ማስረጃ ወይም የትዳር አጋር የፈቃድ ስምምነት (ውክልና)፤

.በመያዣነት የቀረበው ንብረት የባለቤትነት ማረጋገጫ ማስረጃ፤

.የንግድ ማህበር ከሆነ የመመስረቻ ጽሁፍ፤ መተዳደሪያ ደንብ እና ቃለጉባኤ እንደአስፈላጊነቱ ዋና የንግድ ምዝገባ፡፡

ማሳሰቢያ፡- ተገልጋዮች የተባሉትን ነገሮች አሟልተው ሲቀርቡ ለዚህ አገልግሎት የሚወስደው ጊዜ 25 ደቂቃ ነው፡፡

የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
Ethiopian Women Lawyers Association(EWLA) ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

Position :- Legal Officer

የትምህርት ዓይነት እና ደረጃ:-
BA/MA Degree in Law and Human Right/optional

🇪🇹 የስራ ቦታ ፡ አፋር

🧭የምዝገባ ጊዜ /Deadline/: እስከ ሚያዚያ 28 /2014 ዓ.ም

🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ
https://jobs.amazonethiopia.com/job/legal-officer-3/

🔰ወደፊት የምናወጣቸው የስራ ቅጥር ማስታወቂያዎች በፍጥነት እንዲደርስዎ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ይወዳጁ!
ቴሌግራም: https://t.me/Lawsocieties
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
#የውል ማሻሻያ

ተዋዋይ ወገኖች በተለያየ ጊዜና በተለያዩ ምክንያቶች ለህግና ለሞራል ተቃራኒ ካልሆነ፣ ሊተገበር የሚችል ከሆነ እና ተያያዥ ምክንያቶች ቀድሞ የነበረው ውል በመለወጥ ማሻሻል ይችላሉ፡፡
መረጃውን ለሌሎች እንዲደርስ በማድረግ ተቋሙ አላስፈላጊ ወጪ እና እንግልት እንዲሁም ብልሹ አሰራር ለማስቀረት እያደረገ ያለውን ጥረት ያግዙ ፡፡
በመሆኑም ተዋዋይ ወገኖች ውል ለማሻሻል ወደመስሪያቤታችን ሲመጡ ማሟላት የሚገባቸውን መስፈርቶች ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል፡፡


. በተቋሙ የDARIS ስርዓት የተዘጋጀ እና የሚሞላ ሰነድ ወይም የአገልግሎት ቁጥር፤
• ቀደም ሲል የተመዘገበው ወይም የሚሻሻለው የውል ሰነድ፤
• ተዋዋዮች ከህግ ወይም ከውል የመነጨ ስልጣን(ውክልና) ፤
• የተዋዋዮች ጊዜው ያላለፈበት ወይም በዘመኑ የታደሰ መታወቂያ፤
• ውሉ የሚሻሻለው የማይንቀሳቀስ ንብረት ማስተላለፍ ውልን በሚመለከት ሲሆን ሁለት ምስክሮች ፤
• የተዋዋዮች ያላገባ ወይም ያገባ ከሆነ የጋብቻ ማስረጃ እና የትዳር አጋር የፈቃድ ስምምነት (ውክልና)፣
• የንግድ ማህበር ከሆነ የመመስረቻ ጽሁፍ፣ ዋና የንግድ ምዝገባ እና ቀደም ሲል የተመዘገበው ወይም የሚሻሻለው ቃለ-ጉባኤ ወይም የውል ሰነድ፤
ተገልጋዮች ከላይ የተጠቀሱትን ቅድመ ሁኔታዎች(መረጃዎች) ሙሉ በሙሉ አሟልተው ሲመጡ ውሉን ለማጠናቀቅ 25 ደቂቃ ብቻ ነው፡፡
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
#Abyssinia Bank#🚩For Fresh Graduates

▪️1 -Trainee Legal
▪️2 - Trainee Agricultural Engineer
▪️Find More Details Here
👇👇👇👇👇
https://bit.ly/3rJXYYn

▪️ Deadline: April 29 /2022

#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties