አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.88K photos
25 videos
1.87K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
በኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር እና በአክስዮን ማኅበር መካከል ያላቸዉ መሰረታዊ አንድነት እና ልዩነት
1. አባልነት/Membership: -
ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ለማቋቋም የሚያስፈልጉ ሁለት/2/ ሰዎች ብቻ ሲሆኑ አክሲዮን ማኅበር ደግሞ ለመጀመር ቢያንስ አምስት/5/ አባላት ያስፈልጋሉ ፡፡
በአክሲዮን ማህበር ውስጥ በከፍተኛው የአባላት ብዛት ላይ ገደብ የለም ፡፡ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ቢበዛ 50 አባላት ብቻ ሊኖሩት ይችላል ፡፡
2. ዳይሬክተሮች/ Directors፡ -
ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በአንድ ወይም በብዙ ሥራ አስኪያጆች የሚተዳደር ሲሆን አክሲዮን ማኅበሩ ደግሞ አነስተኛ ቁጥራቸው ሦስት በሚሆኑ ዳይሬክተሮች የሚተዳደር ነው ፡፡
3. ፕሮስፔስተስ/ Prospectus: -
አንድ አክሲዮን ማኅበር ለአክሲዮኖቹና ለዕዳ ወረቀቶቹ ደንበኝነት እንዲመዘገብ ህዝቡን መጋበዝ ይችላሉ ፣ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ካፒታሉን ለማሳደግ ወደ ሕዝብ መሄድ አይችልም ፡፡
4. አነስተኛ ምዝገባ /Minimum subscription:-
በአክሲዮን ኩባንያ ውስጥ ሁሉም ካፒታል መፈረም አለባቸው እና ከምዝገባ በፊት የካፒታልው 25% መከፈል አለበት። ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ሙሉ በሙሉ በተከፈለ ካፒታል ይመዘገባል ፡፡
5. የማህበሩ ዋና ገንዘብ / capital፡-
ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ዋና ገንዘብ ከ15,000 ብር በታች መሆን አይችልም፡፡ በአክሲዮን ኩባንያ ደግሞ መነሻ ካፒታሉ ከ50,000 ብር በታች መሆን አይችልም፡፡
6. የተገደበ ሀላፊነት/Limited liability: -
ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ሆነ በአክስዮን ማህበር በማህበሩ ባዋጡት/ባላቸዉ ድርሻ ልክ ብቻ ሀላፊነት አላቸዉ፡፡ ማህበርተኞቹም ለማህበሩ ግዴታዎች አላፊ የሚሆኑት ባላቸዉ ድርሻ ልክ ብቻ ነው፡፡ ስለሆነም በተገደበው የኃላፊነት ደንብ መሠረት የኩባንያው አበዳሪዎች በድርጅቱ በራሱ ንብረት ላይ ብቻ የይገባኛል ጥያቄ ለማቅረብ የተገደቡ ሲሆን የድርጅቱ ባለአክሲዮኖች በግል በያዙት ንብረት ላይ ምንም ዓይነት የይገባኛል ጥያቄ የላቸውም ፡፡
7. የህግ ስዉነት/Legal personality፡-
ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበርም ሆነ አክስዮን ማህበር የራሳቸዉ የሕግ ሰዉነት ያላቸዉ ሲሆን በስማቸዉ የመክሰስ ሆነ የመከሰስ እንዲሁም ማንኛዉንም ስራ የመስራን ሰፊ መብት ተጎናፀፈዋል፡፡
8. የአክስዮኖችን ማስተላለፍን በተመለከተ/Transferable shares፡-
አክስዮን ማህበር ምንም እንኳን በማኅበሩ አንቀጾች ውስጥ የአክሲዮን ነፃ ዝውውርን መገደብ ቢቻልም (አንቀጽ. 333 (1) የአክሲዮን ኩባንያ አጠቃላይ መርሆዎች በነፃነት የሚተላለፉ በመሆናቸው በአክሲዮን ገበያ ሊሸጡ ወይም ሊገዙ ይችላሉ ፡፡ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በአባላቱ መካከል በነፃነት የሚተላለፉ ሲሆን ለሌሎች ግን እንደ አክስዮን ማህበር እንደፈለጉ በነፃነት የሚተላለፍ አይደለም ምክንያቱም ሲመሰረትም ቤተሰባዊ እና ቅርርብን መሰረት ተደርጎ የሚመሰረት ማህበር በመሆኑ ነው፡፡
☞ሰናይ ጊዜ
© Yilkal
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
April 2, 2022
የአክስዮን ማህበር መመስረት የሚያስገኙ ጥቅሞች፡-
የአባላቱ ሀላፊነት የተወሰነ መሆኑ፤
የአክስዮን አባላቱ ቢሞቱም በወራሾች በቀላሉ መቀጠል ስለሚችል የማይሞት መሆኑ፤
አክስዮን ማህበር ትልቅ ካፒታል የሚጠይቅ ስለሆነ ግዙፍ ኢንተርፐራይዞች እንዲኖሩ ማድረግ መቻሉ፤
ጠንካራ የገንዘብ አቅም መኖሩ፤
ድርሻዉ በቀላሉ የሚተላለፍበት እና የአባላትም ቁጥር የሚቀያየር መሆኑ፤
ቦንድ/የብድር ሰነድ/መሸጥ የሚችል መሆኑ፤
የተለያየ የአስተዳደር አካላት ማለትም የዳይሬክቶሮች ቦርድ፤ የባለአክስዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ እና የዉጪ ኦዲተር ያሉት መሆኑ፤
የመስፋፋት እድል መኖሩ፤
የተበተነ አደጋ መኖሩ/Diffused risk/
ከ50 በላይ አባላት ያሉት ማቋቋም ሲፈለግ፤
መዋጮ ከህዝብ መሰብሰብ መቻሉ ማለትም ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ለማቋቋም የአክስዮን ሽያጭ ማስታወቂያ ለህዝብ አስነግሮ ካፒታል መሰብሰብ አይችልም ፡፡ በመሆኑም ብዙ ገንዘብ በሚጠይቁ ዘርፎች ለመሰማራት ካፒታልን ከህዝብ መሰብሰብ የሚያስችል ስለሆነ አክስዮን ማህበር ተመራጭ ያደርገዋል፡፡
ለሶስተኛ ወገኖች የበለጠ አስተማማኝ እና ተቋማዊ ቅርፅ የያዘ መሆኑ፤ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር አሰራሩ ቀላል፤ በህግ የሚደረግበት ቁጥጥር የላላ፤ የአስተዳደር ስርዓቱ በአንፃራዊነት የማያስተማምን ስለሆነ 3ኛ ወገኖችን ብዙ አያስተማምንም፡፡ በተቃራኒዉ አክስዮን ማህበር አሰራሩ ዉስብስብ፤ዝርዝር የህግ ቁጥጥር ያለበት፤ አስተዳደሩ በብዙ አካላት የተደራጀ ስለሆነ ለአባላትም ሆነ ከአክስዮኑ ጋር ግኑኙነት የሚፈጥ የ3ኛ ወገኖች መብት ለማስጠበቅ አስተማማኝ ነው፡፡
አንዳንድ የስራ ዘርፎች በህግ በግልጽ በአክስዮን ማህበር ብቻ የሚሰሩ መሆናቸዉ፤ ምሳሌ ባንክ እና ኢንሹራንስ ስራ በሀላፊነቱ የጠወሰነ የግል ማህበራት የማይሰራ መሆኑ፤
ስለሆነም የአክስዮን ማህበር ከላይ ባየናቸዉ ባህሪያት ያሉት ከአባላቱ የተለየ ሀላፊነት ያለበት ራሱን የቻለ የህግ ሰዉነት ያለዉ ድርጅት መሆኑ ተመራጭ የሚያደርገዉ ቢሆንም የራሱ ሆነ ድክመቶች ያሉት ሲሆን እንደሚከተለዉ እናያለን፡፡
የአክስዮን ማህበር መመስረት ያሉት ጉዳቶች፡-
አክስዮን ማህበር ለመመስረት ዉስብስብ እና አስቸጋሪ ስነ ስርዓት መጠየቁ፤
በምስረታ ሂደት የተለያዩ ባለሙያዎች አስፈላጊ መሆናቸዉ ምሳሌ መመስረቻ ፁሁፍን እና መተዳሪያ ደንቡን ለማዘጋጀት የህግ ባለሙያ ማስፈለጉ፤ በአይነት የሚደረገዉን መዋጮ ለመወሰን የሂሳብ ሰራተኛ እና ማህንዲስ አስፈላጊ መሆኑ በምስረታ ሂደትን ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ መሆኑ፤
በቀጥታ የንብረቱ ባለቤት ያለመሆን፤
የዉሳኔ መዘግየት መኖሩ ምክንያቱም በእያንዳንዱ ወሳኝ ጉዳይ ላይ የጠቅላላ አባላትን እና የተለያዩ አካላትን ዉሳኔን የሚያስፈልግ መሆኑ፤
በጥቂት እጅ የወደቀ እና የተንኮል አስተዳደር የመፈጠር እድሉ ሰፊ ነው ምክንያቱም ባላክስዮኖቹ በየሀገሩ የተበታተኑ እና የማይተዋወቁ በመሆናቸዉ በቀላሉ ለመቆጣጠር እና መብታቸዉን በተደራጀ መልኩ ለማስከበር ይቸገራሉ፡፡ ምሳሌ፡- የባንክ አባሎች የማይተዋዉ ብዙ ቁጥር ያለቸዉ በመሆኑ ቦርድ እና ስራ አስኪያጆችን በየቀኑ ለመቆጣጠር ያስቸግራል፡፡
ሚስጢር ያለመጠበቅ ችግር

ሰናይ ጊዜ 👏
YilkalG.
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
April 2, 2022
April 2, 2022
የቤት ብድር የሚሰጡ ባንኮች
#አለ_ህግ
ብሄራዊ ባንክ ሞርጌጅ ባንኮች ለማቋቋም የሚያስችል ደንብ እያረቀቀ እንደሆነ ሪፖርተር አስነብቧል። መንግሥት ለልዩ ዓላማ ለሚቋቋሙ ባንኮች ራሱን የቻለ ደንብ እንዲያዘጋጅ የፋይናንስ ዘርፉ ሲወተውት የቆዩ ሲሆን፣ በቅርቡ ግን ብሄራዊ ባንክ ኮሚቴ አቋቁሞ ለሞርጌጅ ባንክ ማቋቋሚያ ልዩ ደንብ ማዘጋጀት መጀመሩን አንድ የባንኩ ከፍተኛ ኃላፊ ተናግረዋል። ሞርጌጅ ባንክ በባሕሪው የተለየ እና ለደንበኞቹ የሚሰጠው ብድር የረጅም ጊዜ በመሆኑ፣ ለመደበኛ ባንኮች ከሚውሉት መስፈርቶች ቀለል ያሉ መስፈርቶች ሊዘጋጁለት እንደሚገባ የዘርፉ ባለሙያዎች ጠቁመዋል። ከአምና ጀምሮ ጎህ ባንክ ብቻ የሞርጌጅ ብድር እየሰጠ እንደሆነ የገለጠው ዘገባው፣ ብሄራዊ ባንክ ግን ባንኩን የሚያውቀው እንደ ማንኛውም ንግድ ባንክ እንደሆነ አውስቷል።
ዋዜማ ሬዲዬ
April 3, 2022
የተሻሻለው የፌደራል ፍ/ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1234/13 አንቀፅ 5(2)
=======/////======= #አለ_ህግ
የክልል ጉዳይ ሆኖ በክልል ፍ/ቤቶች እየታዬ ባለ ክርክር ስልጣንን የሚቀይር ተከራካሪ ወገን ወደ ክርክሩ ቢገባ ክርክሩ የት ይቀጥላል?
~~~~
ጉዳዩ የክልል ጉዳይ ሆኖ ክርክር እየቀጠለ ባለበት ጊዜ ስልጣኑን የሚቀይር የሌላ ክልል ነዋሪ የሆነ ተከራካሪ ወገን ወይም የኢንሹራንስ ተቋም ወደ ክርክሩ ሲገባ ጉዳዩ የፌደራል ፍ/ቤቶች ስልጣን ይሆናል ወይስ አይሆንም? የክልል ፍ/ ቤቶች ስልጣናቸውን ያጣሉ ወይስ አያጡም? ጉዳዩን የያዘው ፍርድ ቤትስ መዝገቡን ስልጣን ላለው ያስተላልፍ ወይስ ይዝጋው? የሚሉት ጉዳዬች በቀድሞው አዋጅ ቁጥር 25/88 ድንጋጌዎችእና ከፍ/ስ/ስ/ህጉ ድንጋጌዎች አንፃር አከራካሪ መሆኑ ይታወቃል። የተሻሻለው አዋጅ ለዚህ ምላሽ በሚሰጥ መልኩ የተቀመጠ ነው።
~~~
በመርህ ደረጃ ነዋሪነታቸው በተለያዩ ክልሎች የሆኑ ሰዎች ወይም በፌደራል የተመዘገበ የኢንሹራንስ ተቋም ተከራካሪ የሆኑበት የፍትሀብሄር ክርክር ጉዳይ ላይ የፌደራል ፍርድ ቤቶች የስረ ነገር ስልጣን ያላቸው ሲሆን በልዩ ሁኔታ ግን የክልል ጉዳይ ሆኖ በክልል ፍርድ ቤቶች በመታየት ላይ እያለ የሌላ ክልል ነዋሪ ወይም የኢንሹራንስ ተቋም በየትኛውም የክርክር ደረጃ በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ 40(2), 41,43, 358ና 418ንም ጨምሮ ወደ ክርክሩ ቢገባ ጉዳዩ በጀመረበት አግባብ የክልል ጉዳይ ሆኖ ከሚቀጥል ውጭ የፌደራል ፍርድ ቤቶች ስልጣን ነው በሚል ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት የሚተላለፍ አይሆንም።
(via voice of justice)
April 3, 2022
April 3, 2022
H. R. 6600 01951.pdf
924.9 KB
Share 'H. R. 6600 01951.pdf'
April 3, 2022
April 3, 2022
April 3, 2022
April 3, 2022
April 3, 2022
የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ (Stop Payment Order) የሚሰጠው መቼ እና እንዴት ነው?

በገዙ አየለ መንግሥቱ

በዚህ ጽሑፍ የሚከተሉት ቁም ነገሮች ያገኛሉ
የቼክ ክፍያ ባንክ አልፈጽምም ሊል የሚችለው መቼ ነው
የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ መስጠት የሚቻልበት መንገድ
የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ ከብሔራዊ ባንክ መመሪያ አንጻር
የቼክ ሂሳብ እንቅስቃሴን በተመለከተ

https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/1800-stop-payment-order
April 3, 2022
።።።።።።። ይግባኝ ማስፈቀጃ ====
• በህጉ የተቀመጠው የይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ ካለፈ በኋላ ይግባኝ ለማቅረብ እንዲፈቀድ የሚቀርብ አቤቱታ

አንድ ፍ/ቤት ይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜው ያለፈበት ምክንያት በቂ መሆኑን ሲረዳ ይግባኙ እንዲቅርብ ሊፈቅድ እንደሚገባ በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 326/1/ ስር ተመልክቷል፡፡ በመሆኑም ፍ/ቤቱ የቀረበለት ምክንያት በቂ መሆን አለመሆኑን በአግባቡ ሊመረምረው ይገባል፡፡ በእርግጥ በቂ ምክንያት የሚባሉት ነገሮች ሕጉ ዘርዝሮ ያላስቀመጣቸው በመሆኑ ለመወሰን አስቸጋሪ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ በመሆኑም የምክንያቱ በቂ መሆን አለመሆን በእያንዳንዱ ጉዳይ ከሚቀርቡ ፍሬ ነገሮች ጋር ተገናዝበው ሊመዘኑ ይገባል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 38145 ቅጽ 8፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 326/1/

በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 324/1/ መሠረት ለአንድ ፍርድ ቤት መዝገብ ሹም የተሰጠው ሥልጣን ይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ ማለፍ አለማለፉን በመመልከት ይግባኝ መዝገቡ እንዲከፈት ማድረግ ሲሆን ይግባኙ ጊዜውን ጠብቆ ያልቀረበ ከሆነ ማመልከቻውን መመለስ፣ ማመልከቻው የተመለሰበት ወገን የይግባኝ ጊዜው ያለፈበት ሕጋዊ ምክንያት ካለው ማስፈቀጃ አቤቱታውን በማቅረብ ይኸው ጊዜው ያለፈበት ይግባኝ ለማቅረብ እንዲፈቀድለት ራሱን የቻለ አቤቱታ አቅርቦና ይህ መዝገብ ተከፍቶ ጉዳዩ ለችሎት ቀርቦ ችሎቱ የይግባኝ ማስፈቀጃውን በመመርመር በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 325 እና 326 መሠረት ተገቢ ነው ያለውን ትእዛዝ የሚሰጥበት ነው፡፡

የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 324/1/ ከፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 325 እና 326 ድንጋጌዎች ጋር አንድ ላይ ሲነበቡ የመዝገብ ቤት ሹም ጊዜው ያለፈበት ይግባኝ ለችሎት እንዲቀርብ የመፍቀድ ስልጣን የሌለው መሆኑን የሚያሳዩ ሲሆን ፋይሉ ተከፍቶ ቀርቦ ከሆነም ችሎቱ ጉዳዩን መርምሮ ይግባኙ የቀረበው ጊዜው ከአለፈ በኋላ ነው በማለት መዝገቡን ከመዝጋት የሚከለክለው አይደለም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 61843 ቅጽ 11፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 324-326
April 3, 2022
ማሳሰቢያ አለ_ህግ #law #societies
ሁሉንም የ #አለ_ህግ አባላት የሚያሳትፍ ቀጠሮ፣ ሁሌም እሁድ እሁድ የቀጥታ (Live stream) የድምፅ ውይይት ይኖረናል።
#የህግ ጉዳይ የመወያያ እርዕስ አስቀድማችሁ እንዳትመርጡ እናሳስባለን።
ምክንያቱም፣ ከወዲሁ ተዘጋጅተው ለውይይቱ እንዲመጡና ፍሬአማ ሀሳቦችን እንድናገኝ ይረዳናል።
1. የመወያያ አጀንዳ ይምረጡ
2. ተዘጋጅተው የውይይቱ ተሳታፊ ይሁኑ
3. Share and add ማድረግን አትርሱ
#Ale_Lawsocieties
#አለ_ህግ
https://t.me/lawsocieties

@lawsocieties
April 4, 2022
#Embassy of Canada#

▪️Position - Common Services Officer (Contracts and Procurement)
▪️Salary - 712,866 ETB per annum
▪️Location - Addis Ababa
▪️Education - Bachelor’s degree in a related field (i.e. business administration) from a recognized university with 3 years of experience
▪️Find More Details Here
👇👇👇👇👇
https://bit.ly/3J0kHFr

▪️Deadline - Apr 08/2022

How to Apply

Applications will only be considered when received through our portal.  Link for this job poster – https://staffing-les.international.gc.ca/en/careers/common-services-officer-contracts-and-procurement-addis-64049-en


#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
April 4, 2022
የዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በፍርድ ቤቶች
*
በፌዴራል ፍርድ ቤቶች በህብረተሰቡ ዘንድ የህግ ግንዛቤን ለማስጨበጥ በሁለት የተከፈለ ስራ ተሰርቷል፡፡ አንዱ በየትኛውም ደረጃ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በፍርድ ቤት የሚሰጠውን የዳኝነት አገልግሎት መሰረት በማድረግ ሂደቱን እና ተያያዥ ጉዳዮችን የሚያስገነዝብ ሳምንታዊ የቴሌቪዥን ፕሮግራም ሲሆን ሁለተኛው ደግም በተማሪዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር፡፡ በተለይም የዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በፍርድ ቤቶች የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ የተግባር ልምምድ (internship program) እና በዳኞች ቅርብ ክትትል፣ ምክርና አቅጣጫ ጠቋሚነት የአመለካከት፣ እውቀትና ክህሎት የማዳበር (Mentorship) ፐሮግራም ተቀርጾ ተግባራዊ ተደርጓል፡፡ የዚህ ፕሮግራም ፋይዳን የሚዳስስ አጭር ቪዲዮ እንዲህ ቀርቧል፡፡
https://m.youtube.com/watch?v=HD-jNaksHg4

#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
April 4, 2022
ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ 38 ቦታዎች በ0 አመት የስራ ልምድ በርካታ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
👩 position:- 38 ቦታዎች
በ 0 አመት
📚 ትምህርት ዓይነት እና ደረጃ፡-

🔴law
🔴business-law,
🔴commercial-law,
🔴environmental-and-land-law,
peace-security,
tax-and-investment-law,
agribusiness-management,animal-science,anthropology,communication,dairy-and-meat-technology,development-evaluation,doctor-of-veterinary-medicine,ecology, forest-science,forestry,journalism ,natural-resource-management,philosophy,psychology,social-anthropology,soil-and-water-conservation-engineering,special-need-education,

veterinary-pathology,veterinary-pharmacology

🇪🇹 የስራ ቦታ : Oromia- region

🧭የምዝገባ ጊዜ /Deadline/: እስከ ሚያዚያ 04 /2014 ዓ.ም

🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ

https://jobs.amazonethiopia.com/job/selale-university/

https://t.me/LawyerEthiopia
@LawyerEthiopia
April 4, 2022
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
April 4, 2022
በአዋጁ ላይ አስገዳጅ አንቀጾች መካተታቸው ጠቀሜታው የጎላ ነው ሲል ቋሚ ኮሚቴው ገለጸ

(ዜና ፓርላማ) መጋቢት 26/2014 ዓ/ም፤ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በማህበረሰብ ዓቀፍ የጤና መድህን አዋጁ ላይ አስገዳጅ አንቀጾች መካተታቸው ጠቀሜታው የጎላ ነው ሲል ገልጿል፡፡

ቋሚ ኮሚቴው ይህን ያለው በማህበረሰብ ዓቀፍ የጤና መድህን ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በተወያየበት ወቅት ነው፡፡

ቋሚ ኮሚቴው ከኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት፣ ከጤና ሚኒስቴር እንዲሁም ከክልሎች ከተውጣጡ የስራ ሀላፊዎች ጋር ነው የተወያየው፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ወርቅሰሙ ማሞ በአዋጁ ላይ አስገዳጅ አንቀጾች መካተታቸው ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ተናግረው አገልግሎት አሰጣጡ ላይም የሚስተዋለው መንገላታት ሊቀረፍ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድህን አዋጅ ጽንሰ ሀሳብ፤ አዋጁ ያለፈበትን ሂደት፣ ትግበራው የደረሰበትን ደረጃ እና አዋጁ ባካተታቸው ዋና ዋና ጉዳዮች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

በማብራሪያቸውም አዋጁ 7 ክፍሎች እና 34 አንቀጾች እንዳሉት አስረድተው የጤና አገልግሎት የማግኘት ዋስትናን እንደሚያረጋግጥ፣ ለማህበረሰቡ ቀልጣፋ፣ ወጭ ቆጣቢና የተሻለ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት እንደሚያስገኝም ተናግረዋል፡፡

ሀገራዊ የማህበረሰብ ጤና መድህን አፈጻጸም ከጠቅላላው በሀገሪቱ ካሉ ወረዳዎች አኳያ ያለው አፈጻጸም 78 በመቶ እንደሆነ ዋና ዳይሬክተሯ ተናግረው በ2014 ዓ/ም 867 ወረዳዎች እየተተገበረ እንደሚገኝም ነው ያሰረዱት፡፡

አክለውም የማህበረሰብ ዓቀፍ የጤና መድህን ስርዓት በሙከራና ማስፋፊያ ትግበራ ወቅት አበረታች ውጤት ማሳየቱ ቀጣይነቱን ይበልጥ ለማረጋገጥ የህግ ማዕቀፍ ማውጣት አስፈላጊ እንደሆነ ተሞክሮ ተወስዷል ብለዋል፡፡

የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰሃረላ አብዱላሂ አዋጁ ለአገልጋዩ አስገዳጅ መሆኑ ጤና ተቋማት ላይ አገልግሎት የሚሰጡ የስነ-ምግባር ችግር ያለባቸውን የጤና ባለሙያዎች ተጠያቂ ለማድረግና ተጠቃሚው ህብረተሰብ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች ያካተተ ስለሆነ በየደረጃው ያለው የመንግስት አካል ተከታትሎ ማስፈጸም አለበት ብለዋል፡፡

ቋሚ ኮሚቴው መጋቢት 28/2014 ዓ/ም በሚኖረው መድረክ ተጨማሪ ግብዓት እንደሚሰበሰብ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ጠቁመዋል፡፡
በ መስፍን አለሰው

#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
April 4, 2022
ወደ_ኢትዮጵያ_ሲመጡ_ከቀረጥ_ነጻ_የግል_መገልገያ.pdf
7.4 MB
April 5, 2022
April 5, 2022
🟢🟡🔴 ክስን ስለማንሳት።።።።
ክስ ስለ ማንሳት ማለት ክስ ሂደት ላይ የነበረ ክስ በተለያዩ ምክንያቶች ክስ ሂደቱ እንዲቋረጥና መዝገቡ ለዘለቄታው ወይም ለጊዜው እንዲዘጋ የሚደረግበት ስርዓት ነው።

ክስ የሚነሳበት ምክንያት /ሁኔታ/ በወ/መ /ስ/ስ /ሕጋችን በአንቀፅ 122 ተደንግጎ ይገኛል።

የዚህ አንቀፅ ንኡስ አንቀፅ (1) እንደሚጠቁመው በድሮው የወ/መ/ ሕግ ቁ.522 (በአሁኑ የወ/ሕግ አንቀፅ 539) ወይም በቀድሞው የወ/መ/ሕግ ቁ.637 (በአሁኑ የወ/ሕግ አንቀፅ 671) መሰረት ከቀረበው ክስ በስተቀር ዓ/ሕጉ በተከሳሹ ላይ ያቀረበውን ማንኛውም ክስ በፍርድ ቤቱ ፈቃድ ከፍርድ በፊት ክሱ በሚሰማበት በማንኛውም ጊዜ ክሱን ለማንሳት ይችላል ማለት ነው።

ይህ ማለት፣
ሀ) ከከባድ የሰው ግድያ እና ከከባድ የወንብድና ተግባር ክሶች ውጭ ሌሎች ክሶች ሊነሱ እንደሚችሉ ፣ ለ) አቃቢ ሕጉ ክሱን ማንሳት የሚችለው በፍ/ቤቱ ፈቃድ መሆኑን ፣ እና ሐ) ክሱን ማንሳት የሚቻለው ከፍርድ በፊት በማንኛም ጊዜ መሆኑን ነው።

የወ/መ/ስ/ስ/ ሕጋችን የሁለቱ ከባድ ወንጀሎች ክስን በተመለከተ ማንሳት የከለከለበት ምክንያት ሁለት ነገሮችን ታሳቢ በማድረግ ሊሆን ይችላል ፡ በአንድ በኩል እንደዚህ የመሳሰሉትን ከባድ ወንጀሎች በህዝብ ላይ ስጋት የሚፈጥሩና ሰላምን የሚነሱ በመሆናቸው በእነዚህ ወንጀሎች የተከሰሱ ሰዎች ወንጀሉን መፈፀማቸው የሚያስረዳ ማስረጃ እስከ ቀረበ ድረስ ጥፋተኛ ሆነው ሊቀጡ እንደሚገባና የዚህ ወንጀል ሰለባ የሆኑ ሰዎችም ሕግ ከለላ የሰጣቸው መሆኑን ለማረጋገጥ ሲሆን፤
በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ተከሳሾች በተከሰሱበት ጉዳይ ቁርጣቸውን ኣውቀው እንዳያርፉ፤ አንዴ ክስ ተነስቶ መዝገብ እየተዘጋ ሌላ ጊዜ እየተንቀሳቀሰ ሰላም እንዳይነሳ ነው።

ከፍርድ ቤት ክስ እና ክርክር የራቀ ሰላም ሂይወት ለሁላችሁ።

#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share.....
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
................ @Lawsocieties
April 5, 2022
የዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በፍርድ ቤቶች
*

https://vm.tiktok.com/ZMLQYdo9Y/
April 5, 2022
April 5, 2022
April 5, 2022
ACTION AGAINST HUNGER ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

Position:-Gender and Protection Program

Manager-Re-advertisement
📚ትምህርትዓይነትእናደረጃ:-
University Master and or BA degree in social sciences, psychology, 🔴law, social work, international development, or other relevant field from a recognized institution.

🇪🇹 የስራ ቦታ ፡ Wollega- Gimbi, Oromia

🧭የምዝገባ ጊዜ ፡ እስከ ማያዚያ 07 /2014 ዓ.ም


🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ
https://tikusjobs.com/job/gender-and-protection-program-manager-re-advertisement/

#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share.....
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
................ @Lawsocieties
April 6, 2022
።።።።። አስፈላጊ አደራ ።።።
አንድ ሰው የራሱ ንብረት በሆኑት ዕቃዎች ላይ የማይታገድ እርግጠኛ አደጋ የሚደርስባቸው በሆነ ጊዜ እነዚህን ዕቃዎች ከቀረበው አደጋ ለማሸሽ ሲል ሌላ ሰው በአደራ ተቀብሎ እንዲያስቀምጥለት የሰጠ እንደሆነ ይህ አድራጎት አስፈሊጊ አደራ የማስቀመጥ ድርጊት ይባላል።
አስፈላጊ የአደራ ማስቀመጥ ጉዳይ ከማናቸውም የአሠራር ሥርዓት ነፃ እንደሆነ የፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 2802 ንዑስ አንቀፅ 1 የሚደነግግ ሲሆን አንድ ሰው አስፈላጊ አደራ ለሌላ ሰው የሰጠ መሆኑን በማናቸውም አይነት መንገድ ማስረጃ ማቅረብ እንደሚችል የፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 2802 ንዑስ አንቀፅ 2 ይደነግጋል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 64887 ቅጽ 14 ፤ ፍ/ህ/ቁ. 2800፤ 2802

ማስታወሻ

በፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 2800 አስፈላጊ አደራ አለ የሚባለው በንብረት ላይ እርግጠኛ አደጋ የሚደርስ በሆነ ጊዜ እንጂ አስቀማጩ አደጋ ይደርሳል ብሎ ባሰበ ወይም በሰጋ ጊዜ አይደለም። የድንጋጌው ተፈጻሚነት አንድም አደጋው እየደረሰ እያለ ወይም መድረሱ የማይቀር ስለመሆኑ እርግጠኛ የሆነ ሁኔታ ሲከሰት ብቻ ነው።
በሰ/መ/ቁ. 64887 አመልካች በመንገድ ስራ ምክንያት የተከፈለውን ካሳ ወደሚኖርበት ገጠራማ ቦታ ቢወስደው ደህንነቱን ጠብቆ ለማቆየት የማይችል በአንጻሩ ገንዘቡን ለመዝረፍ ሰዎች ሊገድሉት እንደሚችሉ በማስረዳት ሰባ ሺ ብር በአደራ እንዲያስቀምጥለት ለተጠሪ እንደሰጠ በፍሬ ነገር ደረጃ በምስክር እንደተረጋገጠ ተዘግቧል። ፍሬ ነገሩ የአመልካች ከፍ ያለ ስጋት እንጂ የደረሰ አደጋ ሆነ ሊደርስ ያለ እርግጠኛ አደጋ ስለመኖሩ አልተረጋገጠም። ከዚህ አንጻር የችሎቱ የህግ ትርጓሜ በተሳሳተ የፍሬ ነገር መነሻ ላይ የተመሰረተ በመሆኑ የተሳሳተ ነው።
አብርሃም ዮሐንስ
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share.....
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
................ @Lawsocieties
April 6, 2022
HR6600 እና S3199 ረቂቅ ሕጎች ሕግ ሆነው ከመውጣት እንዲዘገዩ የሚያስችል ስምምነት ላይ መደረሱ ተገለፀ
*********************

የአሜሪካ ኮንግረስ HR6600 እና S3199 ረቂቅ ሕጎች ሕግ ሆነው ከመውጣት እንዲዘገዩ የሚያስችል ስምምነት ላይ መደረሱን የኢትዮጵያ አሜሪካ ሲቪክ ካውንስል በትዊተር ገጹ አስታውቋል።

ይሁን እንጂ ኢትዮጵያውያን ረቂቅ ሕጎቹ እንዳይፀድቅ እያደረጉት ያለው የዲፕሎማሲ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ካውንስሉ አሳስቧል።

የኢትዮጵያ አሜሪካ ሲቪክ ካውንስል በኢትዮጵያ ላይ የሚደረገውን ጣልቃ ገብነትና ጫና በመቃወምና ዳያስፖራ ማህበረሰቡን ጭምር በማስተባበር ከፍተኛ የህዝብ ዲፕሎማሲ ስራ በመስራት ላይ ያለ መቀመጫውን በአሜሪካ ያደረገ ተቋም ነው።

ETV
April 6, 2022
የሽያጭ ውልን የተመለከቱ አንዳንድ ነጥቦች ከሰበር ውሳኔ ጋር ተገናዝቦ የቀረበ
በ፡ ሙሉቀን ሰዒድ ሐሰን
በዚህ ጽሑፍ የሽያጭ ውል ምንነት፣ የማይንቀሳቀስ ንብረት የገዛ ሰው ስላለው መብትና ገዥው ስለሚኖርበት ግዴታ፣ የሽያጭ ውልን መሰረት አድርገው የሚቀርቡ ክርክሮች ይዘታቸው እና የይርጋ ገደባቸው ምን እንደሚመስል እንዲሁም የማይንቀሳቀስ ንብረት የገዛ ሰው ንብረቱን ሊለቅ የሚችልባቸው የሕግ አግባብ ምን ምን እንደሆኑ ከፍትሐብሔር ሕግ እና ከሰበር ውሳኔዎች አንጻር ዳሰሳ ለማድረግ ተሞክሯል፡፡
መልካም ንባብ!
https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/2028-contract-of-sale-in-ethiopia
April 6, 2022
#ተገጣጣሚ_ቤቶች
ከተማ አስተዳደሩ በስምንት ቢሊዮን ብር ሊያስገነባቸው የነበሩ ተገጣጣሚ ቤቶች ግንባታ በፍርድ ቤት ታገደ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስምንት ቢሊዮን ብር በጀት ያስጀመረውና በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ አምስት ወርቁ ሠፈር ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ ሊያከናውነው የነበረው የአምስት ሺሕ ተገጣጣሚ የመኖሪያና የንግድ ቤቶች ሕንፃዎች ግንባታ፣ በፍርድ ቤት ዕግድ እንዲቆም መደረጉ ተገለጸ፡፡

የከተማ አስተዳደሩ በ21.8 ሔክታር መሬት ላይ የተገጣጣሚ ቤቶች ግንባታ ለማስጀመር ጥር 4 ቀን 2014 ዓ.ም. መሠረተ ድንጋይ ቢያስቀምጥም፣ መሬቱ የባለቤትነት ጥያቄ ተነስቶበት ፍርድ ቤት ዕግድ በማውጣቱ ግንባታው እንዲቆም መደረጉን የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮና የቤቶቹን ግንባታ የሚያካሂደው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን አስታውቀዋል፡፡

የኮርፖሬሽኑ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምርያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጥንፉ ሙጬ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ግንባታው ይፋ ከተደረ በኋላ ኮርፖሬሽኑ 291 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የተገጣጣሚ ሕንፃ አካላት ኮንክሪትና ሌሎች ተያያዥ ምርቶችን ወደ ቦታው አስገብቷል፡፡ በግንባታ ቦታው ላይ አሥር ሚሊዮን ብር የሚያወጣ አፈር ጠረጋና ምንጣሮ ሥራ መካሄዱንም አስረድተዋል፡፡

ይሁንና የመሬቱ ባለቤትነት ይገባኛል ያለ ግለሰብ ጥያቄ በማንሳቱ፣ ኮርፖሬሽኑ ሥራ በጀመረ በቀናት ውስጥ ዕግድ ወጥቶበታል፡፡ ኮርፖሬሽኑ እግዱ ቢወጣም የግንባታ ሥራውን እንደቀጠለ ያስረዱት አቶ ጥንፉ፣ ለሁለተኛ ጊዜ ዕግድ ከመጣ በኋላ ግን መሬቱ ላይ ያለው ሥራ እንዲቆም መደረጉን ተናግረዋል፡፡......... ይቀጥላል....
#አለ_ህግ
#አለ_Share....
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
................ @Lawsocieties
April 6, 2022
........የቀጠለ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስምንት ቢሊዮን ብር በጀት ያስጀመረውና በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ አምስት ወርቁ ሠፈር ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ ሊያከናውነው የነበረው የአምስት ሺሕ ተገጣጣሚ የመኖሪያና የንግድ ቤቶች ሕንፃዎች ግንባታ፣ በፍርድ ቤት ዕግድ እንዲቆም መደረጉ ተገለጸ፡፡

የከተማ አስተዳደሩ በ21.8 ሔክታር መሬት ላይ የተገጣጣሚ ቤቶች ግንባታ ለማስጀመር ጥር 4 ቀን 2014 ዓ.ም. መሠረተ ድንጋይ ቢያስቀምጥም፣ መሬቱ የባለቤትነት ጥያቄ ተነስቶበት ፍርድ ቤት ዕግድ በማውጣቱ ግንባታው እንዲቆም መደረጉን የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮና የቤቶቹን ግንባታ የሚያካሂደው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን አስታውቀዋል፡፡

የኮርፖሬሽኑ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምርያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጥንፉ ሙጬ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ግንባታው ይፋ ከተደረ በኋላ ኮርፖሬሽኑ 291 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የተገጣጣሚ ሕንፃ አካላት ኮንክሪትና ሌሎች ተያያዥ ምርቶችን ወደ ቦታው አስገብቷል፡፡ በግንባታ ቦታው ላይ አሥር ሚሊዮን ብር የሚያወጣ አፈር ጠረጋና ምንጣሮ ሥራ መካሄዱንም አስረድተዋል፡፡

ይሁንና የመሬቱ ባለቤትነት ይገባኛል ያለ ግለሰብ ጥያቄ በማንሳቱ፣ ኮርፖሬሽኑ ሥራ በጀመረ በቀናት ውስጥ ዕግድ ወጥቶበታል፡፡ ኮርፖሬሽኑ እግዱ ቢወጣም የግንባታ ሥራውን እንደቀጠለ ያስረዱት አቶ ጥንፉ፣ ለሁለተኛ ጊዜ ዕግድ ከመጣ በኋላ ግን መሬቱ ላይ ያለው ሥራ እንዲቆም መደረጉን ተናግረዋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ሊያስገነባቸው ያቀደው ከ90 በላይ ባለ አራትና ዘጠኝ ፎቅ የተገጣጣሚ ቤት ብሎኮች ግንባታቸው የሚያርፍበት መሬት፣ በሕገወጥነት ተይዞ የነበረና ወደ መሬት ባንክ የገባ መሆኑን አስታውቆ ነበር፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የቤት ልማት ትግበራና የሥራ ዕድል ፈጠራ ክትትልና ቁጥጥር ዳይሬክተር ኪያ በሬቻ (ኢንጂነር)፣ ቢሮው ከከተማው መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ መሬቱን በሊዝ ተረክቦ ካርታ መቀበሉን ተናግረዋል፡፡ ዳይሬክተሩ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ መሬቱን በሊዝ ሊወስድ የሚችለው፣ ይዞት የነበረው ተቋም የሊዝ ውል ሲቋረጥ ወይም ሲመክን መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ይሁንና መሬቱ ከዚህ ቀደም የነበረበትን ሁኔታ መግለጽ የሚችለው የከተማው መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ በመሆኑ፣ የክርክር ሒደቱ አካል የሆነውም ይኸው ቢሮ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ዕጣ ወጥቶባቸው ለዕድለኞች ካልተላለፉት ከ50 ሺሕ በላይ ቤቶች ባሻገር፣ ሁለት ጊዜ በተደረገው ምዝገባ ተካተው ቤት ያልወጣላቸው 700 ሺህ ሰዎች ይገኛሉ፡፡ የቤት የፈላጊዎችን ጥያቄ በተለያዩ አማራጮች ለመፍታት እየሞከረ ያለው የከተማ አስተዳደሩ፣ ግንባታቸውን በቶሎ ለማጠናቀቅ ይቻላል የተባለላቸውን የተገጣጣሚ ቤቶች ግንባታ ከሦስት ወራት ገደማ በፊት አስጀምሯል፡፡

የቤቶቹን ግንባታ የማከናወን ኃላፊነት የተሰጠው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን፣ ለሕንፃ ግንባታው የሚውሉትን የተገጣጣሚ አካላት ቃሊቲ በሚገኘው ፋብሪካው የሚያመርት ሲሆን፣ አምስት ሺሕ ቤቶችን በአንድ ዓመት ውስጥ ገንብቶ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ይዟል፡፡ የኮርፖሬሽኑ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች መምርያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጥንፉ፣ ዕግዱ ባይመጣ ኖሮ ኮርፖሬሽኑ፣ ውል ከተወሰደበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን በርካታ ቤቶችን የመሥራት ዕቅድ ነበረ ብለዋል፡፡ ክረምት ከመግባቱ በፊት ከ90 በላይ የሚሆኑትን ብሎኮች ኮንክሪታቸውን ከአፈር በላይ አውጥቶ የማጠናቀቅ ዕቅድ እንደነበረም ተናግረዋል፡፡

ፍርድ ቤት የግንባታ መሬቱ ላይ ዕግድ ቢጥልም፣ ኮርፖሬሽኑም ሆነ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ፣ እግዱ ለፕሮጀክቱ እክል ይሆናል የሚል ሐሳብ የላቸውም፡፡ ኮርፖሬሽኑ መሬቱ ላይ ያለው ሥራ ቢታገድም አሁንም ድረስ የተገጣጣሚ አካላትን፣ እንዲሁም በርና መስኮቶችን እያመረተ መሆኑን አቶ ጥንፉ ተናግረዋል፡፡ ሁለቱም አካላት ተገጣጣሚ አካላቱ ከተመረቱ መገጣጠሙ ብዙም ጊዜ እንደማይወስድ ገልጸዋል፡፡

ይሁንና ኮርፖሬሽኑ የግንባታ ሥራውን መቀጠል የሚችለው የፕሮጀክቱ ባለቤት የሆነው የከተማ አስተዳደሩ መሬቱን ነፃ ሲያደርግለት መሆኑን አስታውቋል፡፡ ጉዳዩ በፍርድ ቤት የተያዘ ቢሆንም የከተማ አስተደዳሩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተነጋግሮ ቦታውን ያስለቅቃል የሚል እምነት እንዳለው አቶ ጥንፉ አስረድተዋል፡፡

የቤት ልማት ትግበራና የሥራ ዕድል ፈጠራ ክትትልና ቁጥጥር ዳይሬክተሩ ኪያ (ኢንጂነር) በበኩላቸው፣ ከፕሮጀክቱ ባህሪ አንፃር መገጣጠሙ ትንንሽ ጊዜ የሚወስድ በመሆኑ የመሬት ሥራው መቆሙ ሥጋት እንደማይሆን ገልጸው፣ ግንባታው ቢቆምም ለተወሰነ ጊዜ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

በ1997 ዓ.ም. የተጀመረው የመንግሥት የጋራ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት 17 ዓመታት ቢያስቆጥርም፣ እስካሁን የመጀመሪያ ተመዝጋቢዎችን በሙሉ ማዳረስ አልቻለም፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የከተማ አስተዳደሩን የ54 ቢሊዮን ብር ዕዳ ባለቤት አድርጎታል፡፡ የተገጣጣሚ ቤቶቹ ግንባታ ይፋ በተደረገበት ዕለት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣ ለቤቶቹ ግንባታ በተወሰደው ብድርና በተገነቡት ቤቶች ቁጥር መካከል ልዩነት እንዳለ ተናግረው ነበር፡፡

የከተማ አስተዳደሩ እንደሚገልጸው፣ የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ላይ ከፍተኛ ክፍተት ይታይባቸዋል፡፡ በተለይ ከ2006 ዓ.ም. እስከ 2010 ዓ.ም. በአገሪቱ ውስጥ ከነበረው ፖለቲካዊ አለመረጋጋት ጋር ተይይዞ ኮንትራክተሮች ክትትል ሳይደረግባቸው ሥራቸው ‹‹ልቅ›› የነበረ በመሆኑ፣ ፕሮጀክቶቹ ለሌብነትና ለዝርክር አሠራር እንደተጋለጡ ወ/ሮ አዳነች በየካቲት ወር መጀመሪያ ላይ በተካሄደው የከተማዋ ምክር ቤት አንደኛ ዓመት የሥራ ዘመን አንደኛ መደበኛ ጉባዔ መናገራቸው ይታወሳል፡፡
ሪፖርተር
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share.....
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
................ @Lawsocieties
April 6, 2022