አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.87K photos
25 videos
1.87K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
United Beverages Share Company በሚከተለው የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

Position:-Legal Assistant

🔷ትምህርት ዓይነት እና ደረጃ:-

Educational Qualification: LLB Degree

Experience Level: 0-2 years (Junior Level)

🇪🇹 የስራ ቦታ:- Addiss Ababa
🧭የምዝገባ ጊዜ /Deadline/: እስከ ሚያዚያ2/2014 ዓ.ም
🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ
https://jobs.amazonethiopia.com/job/legal-assistant/
March 30, 2022
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Lawyer Mike 🔊የህግ ባለሙያ)
አለ_ህግን ለወዳጅ ዘመድዎ እና ለጓደኛዎ አጋርተዋል
አሁኑኑ ሼር ያድርጉት እና ውለታ ይዋሉ።

#አለ_Share..... #Share #Ale_Law #አለ_ስራ #አለ_ችሎት #አለ_ጠበቃ
አለ_ህግ፣ #አለ_ህግ አማካሪ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች፣ ክሶች፣ የውል ፎርሞች፤ የህግ መፅሐፍቶች 🔴ሁሉም ሕጎች በአንድ🔴 All in one, for All.
አለ_ህግ፣ መሰረታዊ የህግ መረጃ እውቀት፤ ሀብት እና ሀይል ነው። contact us: @LawsocietiesBot or email us: lawsocieties@gmail.com
https://t.me/lawsocieties
March 31, 2022
።።።።።።።። ቀብድ የሕግ ውጤቱ ።።።።
#አለ_ህግ #Ale_Lawsocieties
ለዘመናት በተገለገልንበት በኢትዮጵያ ፍትሃብሄር ሕግ ስለ ቀብድ ጠለቅ ያለ ወይም ግልፅ የሆነ ትርጉም የለም።
ነገር ግን Blacks law dictionary ስለ ቃብድ ትርጉም ያስቀምጠዋል"
ቀብድ ማለት ሊሸጥ ወይም ሊተላለፍ የታሰበውን የእቃውንው ወይም የሸቀጡን የተወሰነ ያህል ክፍል ቅድመ ክፍያ ማለት ሲሆን አላማውም ዉል በሚፈፀምበት ጊዜ ገዥው ለመዋዋል ፍቃደኛ መሆኑን እና እንደ ማረጋገጫ የሚያገለግል ነው ይላል"
በአገራችን በኩል ደግሞ የመጀመሪያው ሕጋዊ ውጤት ተዋዋይ ወገኖች እንደ ውላቸው ውሉ ሲፈፀም ሻጩ ሁለት አይነት አማራጭ ይኖሩታል አንደኛው ቀብዱን በማቆየት ቀሪውን ገንዘብ ከሻጩ መቀበል አልያም ቀብዱን በመመለስ ሙሉ ክፍያውን መጠየቅ ይችላል በሚል ፍ/ሕ/ቁ 1884 ይደነግጋል ሀገራችን የተለመደው አሰራር ግን የመጀመሪያው ቀብዱን ከራሱ አቆይቶ ቀሪውን ገንዘብ መጠየቅ ነው በዚህ ሁኔታ ቀብዱ ለመጨረሻው ክፍያ እንደ ተቀናሽ ገንዘብ/down payment/ ይቆጠራል❗️❗️

በፍታብሔር ሕጋችን ስለ ቀብድ ለየት ያለው ውጤት ደግሞ ውሉ ሳይፈፀም በሚቀርበት ጊዜ ቀብድ መኖሩ ተዋዋይ ወገኖች ዉሉን በግላቸው (Unilateraly) እንዲያቋርጡ (termination) ይጠቅማል።
ነገር ግን ይህን ውል የሚሠርዘው ገዥው በሆነ ግዜ ቀድሞ የከፈለው ቀብድ ተመላሽ አይሆንለትም ነገር ግን ውሉን የሚሠርዘው አካል ሻጩ በሆነ ግዜ ቀድሞ በዉሉ የተቀበለውን የቀብድ መጠን እጥፍ (Double) ዋጋ ለገዥው ወይም ለቀብድ ከፋዩ መመለስ እንዳለበት የፍትሃብሄር ህግ ቁጥር 1885 ንዑስ ቁጥር 1 እና 2 ይደነግጋሉ።
ነገር ግን እነዚህ ህጎች ተፈፃሚ የሚሆኑት ሌላ ከዚህ የተለየ የውል ስምምነት ሳይኖር ሲቀር ብቻ ነው።
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ
#አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
March 31, 2022
ሳይበርና የሳይበር ጥቃት ወንጀል ምንነት እንዲሁም ከአለማቀፍ እና ከሀገራችን የህግ ማዕቀፍ አኳያ እንዴት ይታያል የቅጣት ገደቡስ ምን ያህል ነው?

ከሳይበር ወንጀል ምንነት እንዲሁም ከአለማቀፍ እና ከሀገራችን የህግ ማዕቀፍ አኳያ እንዴት ይታያል የቅጣት ገደቡስ ምን ያህል ነው? የሚለውን በፍትህ ሚኒስቴር የንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ ከሆኑት ከአቶ ዮሐንስ ግርማ ጋር ቆይታ አድርገን ተከታዩን ማብራሪያ ሰጥተውናል እንደሚከተለው ይቀርባል፡-
ሳይበር ለሚለው ቃል የተለያዩ መዝገበ ቃላት በሰጡት ትርጉም ኮምፒዩተር እና የኮምፒዩተር ኔትዎርክ ማለት ነው ሲሉ አቶ ዮሐንስ ስለሳይበር ምንነት ላነሳንላቸው ጥያቄ ምላሽ ይሰጣሉ በተለምዶ ይላሉ አቶ ዮሐንስ ሳይበርና ኮምፒዩተር የሚሉትን ቃላት ባለሙያዎች በተለዋዋጭነት ሲጠቀሙባቸው ይስተዋላል ለዚህ አጭር ጽሁፍ አላማም የሳይበር ወንጀል ማለት የኮምፕዩተር ወንጀል ማለት ነው ብለዋል፡፡
የሳይበር ጥቃት በሳይበር ክልል የሚፈጸም ወንጀል ሲሆን የሳይበር ክልል ማለት ትስስር ያለው አለማቀፍ ኔትዎርክ ማለት ነው የሳይበር ጥቃት ኮምፒዩተር፣ የኮምፒዩተር ስርአት ወይም የኮምፒዩተር ኔትዎርክን ያለባለቤቱ ፍቃድ ማግኘት ሲሆን አላማውም ጉዳት ማድረስ ነው፤የሚያደርሰውም ጉዳትም ብልሽት፣ ማዛባት፣ ማስወገድ ወይም ኮምፒዩተሩን በመለወጥ ማጥፋት ወይም ማገድ ሲሆን በስርአት ውስጥ ያለ መረጃን ማዛባት ወይም መስረቅንም ይጨምራል ይላሉ ፡፡
 የሳይበር ጥቃት አድራሾች እነማን ናቸው? ስንል ከተል አድርገን ላነሳንላቸው ጥያቄ
የሳይበር ጥቃት የማጥቃት እስትራቴጂ ባለው በማንኛውም ሰው ወይም ቡድን ከየትኛውም ቦታ ሊሰነዘርይ ይችላል ሲሉ የተናገሩ ሲሆን ጥቃቱን የሚፈጽሙ ሰዎች የሳይበር ወንጀለኞች ወይም በተለምዶ ሃከሮች ተብለው ይታወቃሉ ብለዋል፤ የሳይበር ጥቃት አድራሾች በመንግስታት በሚደገፉ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ልሂቃን ቡድኖች እና መንግስትን የሚቃወሙ ሰዎች የሚፈጽሙት ነው ያሉት ዐቃቤ ህጉ የመስኩ ባለሞያዎችም nation-state attackers እና hacktivists ሲሉ ይጠሯቸዋል፡፡በሌላ በኩል ከራሱ ከውስጥ ድርጅቱ ሰራተኞች በኩል የሚፈጸም የሳይበር ጥቃትም አለ፡፡ በሀገራት መካከል በሚኖር ፖለቲካዊ እና ዲፕሎማሲያዊ አለመግባባትን ምክንያት በማድረግ እንደዋነኛ ማጥቂያ መሳሪያ ወይም ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖ ለማሳደር በማሰብ እንዱ ሀገር በሌላው ሀገር መንግሰት ላይ የሚፈጽሙት የሳይበር ጥቃት አይነት የሳይበር ጦርነት (Cyberwarfare) ይባላልም ብለዋል፡፡ በአለማችን አሉ አቶ ዮሐንስ አሁናዊ የሀገራት ግንኘነትም እንዲህ አይነት ሹክቻዎች እንዳሉ ይታወቃል ሲሉ በቴክኖሎጂው በኩል ያለውን ሁኔታ ይዳስሳሉ።

 የሳይበር ክልልን መቆጣጠር እና ማስተዳደር የማን ድርሻ ነው? ስንልም ጠየቅናቸው
የሳይበር ክልልን መቆጣጠር እና ማስተዳደር ከህግ ተቋማት በተጨማሪ የሌሎች አካላት ተሳትፎ ይፈልጋል፡፡ ይሄውም ለኢንተርኔት መፈጠር እና መስፋፋት መሪ ሚና የተጫወቱ እና አገልግሎጭ ሰጪ ተቋማት ማለትም እንደ google, facebook, IPadress,የኢንተርኔት እስታንዳርድ እና ፕሮቶኮል አዘጋጆች፣ ሲቪል ማህበራት (Internet society) እና የመሳሰሉት የዘርፉ ቁልፍ ተዋናይ አካላት ዘርፉን በማስተዳደር እና ከሳይበር ጥቃት ከመከላከል አኳያ ከመንግስታት የህግ አስተዳደር በተጨማሪነት ጉልህ ሚና አላቸው ሲሉ መልሰውልናል፡፡

 የሳይበር ጥቃት ኢላማ እነማናቸው?
የሳየበር ጥቃት ኢላማዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እና እንደ ጥቃት አድራሾቹ ፍላጎት ይለያያሉ ሲሉ ዐቃቤ ህጉ ብዙውን ጊዜ እንደሚጠቀሰው የንግድ ተቋማት፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የጤና ተቋማት እና የጠበቆች መረጃዎች እና የደህንነት ተቋማት ዋነኛ የሀከሮች ኢላማ ናቸው ብለዋል፡፡ የጥቃት አድራሾቹ ዋነኛ ፍላጎትም የገንዘብ ጥቀም ማግኘት፣ ጥብቅ የሆኑ የግል መረጃዎችን ማግኘት፣ ስም ማጥፋት፣ ዝናማግኘት፣ በቀል፣ ሀገራዊ ቀውስ ማስከተል፣ የፈጠራ መብትን መንጠቅና የመሳሰሉት ይገኙባቸዋል ሲሉ እነዚህን ጥቃት ለመከላከል በመረጃ እና በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ የታገዘ ጥልቅ የሆነ የሳይበር ጥቃት መከላከያ፤ ፖሊሲ እና ይሄንኑ ለማስፈጸም የሚችል የሰው ሀይል እና እውቀት መገንባትና መጠቀም ያስፈልጋልም ሲሉ ይጠቁማሉ፡፡
 የሳይበር ወንጀል አለማቀፍ የህግ ማእቀፍ ምን ይላል? ብለን ላቀረብነውም ጥያቄ
በአለም አቀፍ ደረጃ የኮምፒዩተር ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር እስካሁን ወጥ የሆ ህግ የሌለ መሆኑን አውስተው በአውሮፓ ህብረት ደረጃ ግን በ2004 የወጣው የቡዳፔስቱ የሳይበር ወንጀል ላይ የተፈረመው ስምምነት ተጠቃሽ ህግ ሲሆን በአፍሪካ ደረጃም በህብረቱ በረቂቅ ደረጃ ያለው የሳይበር ደህንነት እና የግለሰብ ዳታ ለመጠበቅ የወጣውን ስምምነት በጉዳዩ ላይ ተጠቃሽ ክፍለ አህጉራዊ ህግጋት ናቸው ብለውናል፡፡ሌሎች የቀጠናው ስምምነቶች አሉ የቡዳቤስቱ ስምምነት 55 አገራት ያጸደቁት ሲሆን ሰፋ ያለ እና በጉዳዩ ላይ አባል አገራት ሊከተሉአቸው የሚገቡ አሰራሮችን የዘረዘረ ሲሆን ከአውሮፓ ህብርት አባል ሀገራት ውጭ ያሉ ከ130 የሚበልጡ አገራት በመቀበል እየተገበሩት ይገኛል ብለዋል በአለማቀፍ ደረጃ ወጥ የሆነ ህግ ባይኖርም አብዛኛው የአለም አገራት የሳይበር ጥቃትን ለመከላከል በማሰብ የኮምፒዩተር ወንጀልን በህግ ስርአታቸው አካተው ይገኛሉ፡፡
 የሳይበር ወንጀል በኢትዮጵያ ህግ ስርአት ምን ይመስላል?
ሀገራችን ዘግይታ ቢሆንም የሳይበር ጥቃትን በወንጀልነት ከደነገጉ ሀገራት መካከል የገባች ሲሆን ይሄንኑ የሳይበር ወንጀልን ለመከላከል በሀገር ደረጃ የተደነገጉ ህግጋትን ስንመለከት የሳይበር ጥቃት በህጋችን የኮምፒዩተር ወንጀል ተብሎ የሚታወቅ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ የተደነገገውም በ1996 ዓ.ም.ተሻሽሎ በወጣው የወንጀል ህግ ሲሆን ይሄውም ከአንቀጽ 706 እስከ 711 ተደንግጎ ይገኛል ሲሉ ያመላክታሉ ነገር ግን ይህ ድንጋጌ ብቻውን በየግዜው እየተወሳሰበ የመጣውን የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ የወንጀል ተጋላጭነት በበቂ ሁኔታ ለመቆጣጠር ባለማስቻሉ በአዲስ መልክ እራሱን ችሎ በአዋጅ እንዲሸፈን ለማድረግ በማሰብ በኮምፒዩተር ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 958/2008 በዝርዝር ተደንግጎ ወጥቷል ያሉ ሲሆን አሁን በስራ ላይ ያለው ይሄው ህግ ነው ብለዋል፡፡

የኮምፒዩተር ወንጀል አይነቶች እና የሚስከትሉት ተጠያቂነት ምንድን ነው?

በአዋጁ አንቀጽ 2 መሰረት የኮምፒውተር ወይም የኮምፒዩተር ሥርዓት ማለት በሶፍትዌር እና ማይክሮቺፕ ቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረተ የዳታ ፕሮሰሲንግ፣ ክምችት፣ ትንተና፣ ስርጭት፣ ግንኙነት ወይም ሌሎች ሂሳባዊ ወይም አመክንዮአዊ ተግባራትን የሚያከናውን ማንኛውም መሳሪያ ሲሆን የመሳሪያው ተገጣሚ አካልንም ይጨምራል ያሉት አቶ ዮሐንስ የኮምፒዩተር ወንጀልም ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሚፈጸም ወንጀል ነው ይላሉ፡፡ በዚሁም መሰረት ወንጀሉ

1. በኮምፒዩተር እና የኮምፒዩተር ስርአት ላይ ጉዳት ለማድረስ የሚፈጸም(attacking the computer itself እና
2. የኮምፒዩተር ስርአትን ሌላ ወንጀል ለመፈጸም በመጠቀም (using computer and computer system as a instrument of crime)
March 31, 2022
በሚል የተደነገገ ሲሆን ከነዚህ ወንጀሎች ከፊሎቹን ስናይ የመጀመሪያው ወንጀል ህገ-ወጥ ደራሽነት(አንቀጽ3) ሲሆን ይሄውም ያለፈቃድ ወይም ከተሰጠው ፈቃድ ውጪ የኮምፒዩተር ስርዓት፣ የኮምፒዩተር ዳታ ወይም ኔትዎርክ ደራሽነት በከፊልም ሆነ በሙሉ ማግኘት ነው ብለዋል ሌላኛው ወንጀል አሉ አቶ ዮሐንስ ህገ-ወጥ ጠለፋ (አንቀጽ 4) ሲሆን እሱም ያለፈቃድ ወይም ከተሰጠው ፈቃድ ውጪ ይፋዊ ያልሆነን የኮምፒዩተር ዳታ ወይም የዳታ ፕሮሰሲንግ አገልግሎት መጥለፍ ነው፡፡ መጥለፍ ማለትም በኮሙኒኬሽን ሂደት ላይ ያለን የኮምፒዩተር ዳታ ወይም የዳታ ፕሮሰሲንግ አገልግሎት መከታተል፣ መቅዳት፣ ማዳመጥ፣ መውሰድ፣ ማየት፣ መቆጣጠር ወይም መሰል ድርጊት መፈጸም ነው ብለው በተመሳሰይ ሁኔታ ሌሎች ዝርዝር ወንጀሎችም በህጉ የተዘረዘሩ መሆኑን ከታች ያሉትን ሀሳቦች አንስተውልና እነሱም ባጭሩ፡-
 በኮምፒዩተር ሥርዓት ላይ ጣልቃ መግባት(አንቀጽ-5)
 በኮምፒዩተር ዳታ ላይ ጉዳት ማድረስ( አንቀት 6)
 ከኮምፒዩተር መሣሪያ ና ዳታ አጠቃቀም ጋር የተያያዙ ወንጀሎች(አንቀጽ 7)
 የኮምፒዩተር ዳታን ወደ ሐሰት መለወጥ (አንቀጽ 9)
 በኮምፒዩተር አማካኝነት የሚፈፀም የማታለል ወንጀል( አንቀጽ 10)እና
 የኤሌክትሮኒክ ማንነት ስርቆት(አንቀት11) ከፊሎቹ ናቸው፡፡

🔴ስለ ቅጣት ገደብ
በመጨረሻም ለዐቃቤ ሕጉ የቅጣጥ ገደቡ ምን ይመስላል ብለን ለጠየቅናቸው ጥያቄ የኮምፒዩተር ወንጀል የሚያስከትለው ቅጣት በአዋጁ መሰረት እንደየ ወንጀሎቹ ክብደት ከ3 አመት በማይበልጥ ቀላል አስራት እስከ 25 አመት በሚደርስ ከባድ እስራት እና ከብር አስር ሺ እስከ ብር ሁለት መቶ ሺ በሚደርስ መቀጮ የሚያስቀጡ ናቸው ያሉን ሲሆን ነገር ግን ወንጀሎቹ የተፈጸሙት፡-
 ለወታደራዊ ጥቅም ወይም ለዓለምአቀፍ ግንኙነት ሲባል በሚመለከተው አካል ጥብቅ ምስጢር ተብሎ በተሰየመ የኮምፒዩተር ዳታ ወይም ዳታው በሚገኝበት የኮምፒዩተር ሥርዓት ወይም ኔትዎርክ ላይ ከሆነ፤ወይም
 አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በታወጀበት ሀገሪቱ በአስጊ ሁኔታ ላይ በምትገኝበት ወቅት ከሆነ፤
 በሕግ የሰውነት መብት ለተሰጠው ተቋም አገልግሎት ብቻ በሚውል የኮምፒዩተር ሥርዓት ላይ እና በቁልፍ መሠረተ ልማት ላይ ከሆነ ጉዳቱ ከፍ ስለሚል ቅጣቱም በዛው ልክ እስከ 25 ዓመት ከባድ የዕስራት ጣሪያ ድረስ ከፍ ብሎ የሚወሰን ይሆናል ብለዋል፡፡

አያይዘውም በአዋጁ አንቀጽ 19 መሰረት የኮምፒዩተር ሥርዓት አማካይነት የሚፈፀም ማናቸውም ዓይነት ወንጀል በልዩ ሕጎች ወይም በወንጀል ሕግ የሚያስቀጣ ሌላ ወንጀል አስከትሎ እንደሆነ፤ ለዚሁ ወንጀል ተገቢነት ያለው ድንጋጌ በተደራቢነት ተፈፃሚ ይሆናል ሲሉ ይህ ማለት በኮምፒዩተር ስርአቱ በመጠቀም የተፈጸመው ወንጀል በወንጀል ህጉ በሌላ ውንጀልም የሚያስጠይቅ ከሆነ በሁለቱም ህጎች ድንጋጌዎች ይቀጣል ማለት ነው ሲሉ ስለቀጣት ገደቡ ግልጽ ማብራሪያ ሰጥጠውናል፡፡

እኛም ከሳይበርና የሳይበር ጥቃት ወንጀል ምንነት እንዲሁም ከአለማቀፍ እና ከሀገራችን የህግ ማዕቀፍ አኳያ አጠቃላይ ይዘት አቶ ዮሐንስ ለሰጡን ማብራሪያ እያመሰገን በቀጣይ በሌላ ፕሮግራም አስክንገኛኝ መልካም ጊዜ ተመኘን፡፡
የኢ.ፌ.ድ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
March 31, 2022
በወንጀል_ጉዳዮች_የዓቃቤ_ህግ_የህግ_ትርጉም_ማብራሪያ.pdf
1.1 MB
March 31, 2022
March 31, 2022
Legal Aid at National Insurance Company of Ethiopia S.C
#አለ_ስራ #አለ_ህግ
Company: National Insurance Company of Ethiopia S.C

Location: Ethiopia
State: Addis Ababa Jobs
Job type: Full-Time
Job category: Legal Jobs
Under supervision of Manager,  Defense  Division

Duties

examines legal data for the preparation of statements;

obtains and serves court summons;

ensures the safety of documents

Job Requirement

Education Background: College Diploma in Law
Work Experience;2 years of relevant experience
Grade:  VI
Work Place: Addis Ababa

Method of Application

Submit your CV, copies of relevant documents and Application to,
hr_gs@niceinsurance-et.com

Use the title of the position as the subject of the email
Closing Date : 1 April. 2022
#አለ_ህግ #አለ_ስራ
March 31, 2022
በፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሃቅ የሚመራው “ሰላምና ልማት ማዕከል” ፈቃዱ ተመለሰለት!

የ“ሰላምና ልማት ማዕከል” የተባለው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት በኢትዮጵያ መንቀሳቀስ የሚያስችለው ፈቃድ እንደተመለሰለት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አረጋግጧል። በፕሮሰር ኤፍሬም ይስሐቅ የሚመራው ተቋም ፈቃዱን የተነጠቀው “በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለሽብር ቡድኖች የሞራልም ሆነ የቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግ” የሚለውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ድንጋጌ ተላልፏል በሚል ነበር።

ከህዳር 17 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ፈቃዱ የተሰረዘበት ሰላምና ልማት ማዕከል (Peace And Development Center) የስራ ፈቃዱ ተመልሶለታል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ለአዲስ ዘይቤ እንዳረጋገጠው በአዋጅ 1113/2011 አንቀጽ 88/3/ መሰረት በሰርተፍኬት ቁጥር 2936 ሕጋዊ ፈቃድ አግኝቶ የሚንቀሳቀስ ድርጅት ነው። ተቋሙ እርምጃው የተወሰደበት ህዳር 15 ቀን 2014 ዓ.ም. አሰናድቶች በምስለ ስብሰባ የተካሄደው ውይይት በካናዳዊው ጋዜጠኛ ጄፍ ፒርስ አማካኝነት ይፋ ከተደረገ በኋላ ነው።

እሌኒ ገ/መድህን (ዶ/ር)፣ አምባሳደር ብርሃነ ገ/ክርስቶስን ጨምሮ የውጭ ሐገራት ዲፕሎማቶች የተሳተፉበት ውይይት የሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት ላይ መወሰድ በሚገባው እርምጃ ላይ ያተኮረ ሲሆን ከህዝብ እና ከመንግሥት ከፍተኛ ተቃውሞ እንደገጠመው ይታወሳል።
(ምንጭ :- አዲስ ዘይቤ)
#አለ_ዜና #አለ_ህግ #አለ_ህግአማካሪ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩
@lawsocieties
🟨
@lawsocieties
🟥
@lawsocieties
March 31, 2022
ROAD TRANSPORT PROCLAMATION (ENGLISH).docx
40.7 KB
የመንገድ ትራንስፖርት ረቂቅ አዋጅ
🟥 @lawsocieties
March 31, 2022
Global Insurance Company S.C ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

Position:- Senior Anti-Corruption Officer

📚ትምህርትዓይነትእናደረጃ:-

BA Degree in LAW, Management and related fields of study

🇪🇹 የስራ ቦታ:- አዲስ አበባ

🧭የምዝገባ ጊዜ /Deadline/: እስከ ሚያዚያ 02 /2014 ዓ.ም
🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ
https://jobs.amazonethiopia.com/job/senior-anti-corruption-officer/

#አለ_ዜና #አለ_ህግ #አለ_ህግአማካሪ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
April 1, 2022
Vacancy at National Insurance Company of Ethiopia S.C

❇️ Position: 👇👇


2: Legal Aide

❇️ ሰለ ሰራው ሙሉ መረጃ ለማየት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ👇👇
👉Read Detail:- https://bit.ly/2VPnjU8
April 1, 2022
QR Code

You scan this QR code❗️❗️
#አለ_ዜና #አለ_ህግ #አለ_ህግአማካሪ
#አለ_Share.....
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
April 1, 2022
base.apk
3.2 MB
QR scanner

ውድ የአለ_ህግ ለቤተሰቦች፣
ሰላም🙏
ሁላችንም
እንደዘመኑ ለመራመድ እና ከጊዜውና ቴክኖሎጂ ጋር አብሮ ለመራመድ ግድ ይለናል።

ስለሆነም QR scanner የዘመኑ አስፈላጊ አፕሊኬሽን በመሆኑ፣ በዘመናዊ ሆቴሎች በአሁኑ ስዓት የምግብ ሜኑ፣ የመጠጥ አጠቃላይ አግልግሎቶች ዝርዝር እና ዋጋ በወረቀት ማቅረብ እየቀረ ነው።

ስለዚህ በየጠረጴዛው የምታገኟቸውን QR code scan በማድረግ ማየት ይጠበቅባችኋል።
ስለሆነም ይህ አፕሊኬሽን ሊኖራችሁን ይገባል እንላለን።
Install it now.
You scan the above QR code and join us.
#አለ_ዜና #አለ_ህግ #አለ_ህግአማካሪ
#አለ_Share.....
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
April 1, 2022
#United Beverages SC#for fresh& Exp

▪️Position - Legal Assistant
▪️Qualification - LLB Degree
▪️Experience Level - 0-2 years(Junior Level)
▪️Find More Details Here
👇👇👇👇👇
https://bit.ly/3qQFrtd

▪️Deadline - April 09/22
April 2, 2022
በኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር እና በአክስዮን ማኅበር መካከል ያላቸዉ መሰረታዊ አንድነት እና ልዩነት
1. አባልነት/Membership: -
ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ለማቋቋም የሚያስፈልጉ ሁለት/2/ ሰዎች ብቻ ሲሆኑ አክሲዮን ማኅበር ደግሞ ለመጀመር ቢያንስ አምስት/5/ አባላት ያስፈልጋሉ ፡፡
በአክሲዮን ማህበር ውስጥ በከፍተኛው የአባላት ብዛት ላይ ገደብ የለም ፡፡ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ቢበዛ 50 አባላት ብቻ ሊኖሩት ይችላል ፡፡
2. ዳይሬክተሮች/ Directors፡ -
ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በአንድ ወይም በብዙ ሥራ አስኪያጆች የሚተዳደር ሲሆን አክሲዮን ማኅበሩ ደግሞ አነስተኛ ቁጥራቸው ሦስት በሚሆኑ ዳይሬክተሮች የሚተዳደር ነው ፡፡
3. ፕሮስፔስተስ/ Prospectus: -
አንድ አክሲዮን ማኅበር ለአክሲዮኖቹና ለዕዳ ወረቀቶቹ ደንበኝነት እንዲመዘገብ ህዝቡን መጋበዝ ይችላሉ ፣ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ካፒታሉን ለማሳደግ ወደ ሕዝብ መሄድ አይችልም ፡፡
4. አነስተኛ ምዝገባ /Minimum subscription:-
በአክሲዮን ኩባንያ ውስጥ ሁሉም ካፒታል መፈረም አለባቸው እና ከምዝገባ በፊት የካፒታልው 25% መከፈል አለበት። ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ሙሉ በሙሉ በተከፈለ ካፒታል ይመዘገባል ፡፡
5. የማህበሩ ዋና ገንዘብ / capital፡-
ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ዋና ገንዘብ ከ15,000 ብር በታች መሆን አይችልም፡፡ በአክሲዮን ኩባንያ ደግሞ መነሻ ካፒታሉ ከ50,000 ብር በታች መሆን አይችልም፡፡
6. የተገደበ ሀላፊነት/Limited liability: -
ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ሆነ በአክስዮን ማህበር በማህበሩ ባዋጡት/ባላቸዉ ድርሻ ልክ ብቻ ሀላፊነት አላቸዉ፡፡ ማህበርተኞቹም ለማህበሩ ግዴታዎች አላፊ የሚሆኑት ባላቸዉ ድርሻ ልክ ብቻ ነው፡፡ ስለሆነም በተገደበው የኃላፊነት ደንብ መሠረት የኩባንያው አበዳሪዎች በድርጅቱ በራሱ ንብረት ላይ ብቻ የይገባኛል ጥያቄ ለማቅረብ የተገደቡ ሲሆን የድርጅቱ ባለአክሲዮኖች በግል በያዙት ንብረት ላይ ምንም ዓይነት የይገባኛል ጥያቄ የላቸውም ፡፡
7. የህግ ስዉነት/Legal personality፡-
ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበርም ሆነ አክስዮን ማህበር የራሳቸዉ የሕግ ሰዉነት ያላቸዉ ሲሆን በስማቸዉ የመክሰስ ሆነ የመከሰስ እንዲሁም ማንኛዉንም ስራ የመስራን ሰፊ መብት ተጎናፀፈዋል፡፡
8. የአክስዮኖችን ማስተላለፍን በተመለከተ/Transferable shares፡-
አክስዮን ማህበር ምንም እንኳን በማኅበሩ አንቀጾች ውስጥ የአክሲዮን ነፃ ዝውውርን መገደብ ቢቻልም (አንቀጽ. 333 (1) የአክሲዮን ኩባንያ አጠቃላይ መርሆዎች በነፃነት የሚተላለፉ በመሆናቸው በአክሲዮን ገበያ ሊሸጡ ወይም ሊገዙ ይችላሉ ፡፡ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በአባላቱ መካከል በነፃነት የሚተላለፉ ሲሆን ለሌሎች ግን እንደ አክስዮን ማህበር እንደፈለጉ በነፃነት የሚተላለፍ አይደለም ምክንያቱም ሲመሰረትም ቤተሰባዊ እና ቅርርብን መሰረት ተደርጎ የሚመሰረት ማህበር በመሆኑ ነው፡፡
☞ሰናይ ጊዜ
© Yilkal
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
April 2, 2022
የአክስዮን ማህበር መመስረት የሚያስገኙ ጥቅሞች፡-
የአባላቱ ሀላፊነት የተወሰነ መሆኑ፤
የአክስዮን አባላቱ ቢሞቱም በወራሾች በቀላሉ መቀጠል ስለሚችል የማይሞት መሆኑ፤
አክስዮን ማህበር ትልቅ ካፒታል የሚጠይቅ ስለሆነ ግዙፍ ኢንተርፐራይዞች እንዲኖሩ ማድረግ መቻሉ፤
ጠንካራ የገንዘብ አቅም መኖሩ፤
ድርሻዉ በቀላሉ የሚተላለፍበት እና የአባላትም ቁጥር የሚቀያየር መሆኑ፤
ቦንድ/የብድር ሰነድ/መሸጥ የሚችል መሆኑ፤
የተለያየ የአስተዳደር አካላት ማለትም የዳይሬክቶሮች ቦርድ፤ የባለአክስዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ እና የዉጪ ኦዲተር ያሉት መሆኑ፤
የመስፋፋት እድል መኖሩ፤
የተበተነ አደጋ መኖሩ/Diffused risk/
ከ50 በላይ አባላት ያሉት ማቋቋም ሲፈለግ፤
መዋጮ ከህዝብ መሰብሰብ መቻሉ ማለትም ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ለማቋቋም የአክስዮን ሽያጭ ማስታወቂያ ለህዝብ አስነግሮ ካፒታል መሰብሰብ አይችልም ፡፡ በመሆኑም ብዙ ገንዘብ በሚጠይቁ ዘርፎች ለመሰማራት ካፒታልን ከህዝብ መሰብሰብ የሚያስችል ስለሆነ አክስዮን ማህበር ተመራጭ ያደርገዋል፡፡
ለሶስተኛ ወገኖች የበለጠ አስተማማኝ እና ተቋማዊ ቅርፅ የያዘ መሆኑ፤ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር አሰራሩ ቀላል፤ በህግ የሚደረግበት ቁጥጥር የላላ፤ የአስተዳደር ስርዓቱ በአንፃራዊነት የማያስተማምን ስለሆነ 3ኛ ወገኖችን ብዙ አያስተማምንም፡፡ በተቃራኒዉ አክስዮን ማህበር አሰራሩ ዉስብስብ፤ዝርዝር የህግ ቁጥጥር ያለበት፤ አስተዳደሩ በብዙ አካላት የተደራጀ ስለሆነ ለአባላትም ሆነ ከአክስዮኑ ጋር ግኑኙነት የሚፈጥ የ3ኛ ወገኖች መብት ለማስጠበቅ አስተማማኝ ነው፡፡
አንዳንድ የስራ ዘርፎች በህግ በግልጽ በአክስዮን ማህበር ብቻ የሚሰሩ መሆናቸዉ፤ ምሳሌ ባንክ እና ኢንሹራንስ ስራ በሀላፊነቱ የጠወሰነ የግል ማህበራት የማይሰራ መሆኑ፤
ስለሆነም የአክስዮን ማህበር ከላይ ባየናቸዉ ባህሪያት ያሉት ከአባላቱ የተለየ ሀላፊነት ያለበት ራሱን የቻለ የህግ ሰዉነት ያለዉ ድርጅት መሆኑ ተመራጭ የሚያደርገዉ ቢሆንም የራሱ ሆነ ድክመቶች ያሉት ሲሆን እንደሚከተለዉ እናያለን፡፡
የአክስዮን ማህበር መመስረት ያሉት ጉዳቶች፡-
አክስዮን ማህበር ለመመስረት ዉስብስብ እና አስቸጋሪ ስነ ስርዓት መጠየቁ፤
በምስረታ ሂደት የተለያዩ ባለሙያዎች አስፈላጊ መሆናቸዉ ምሳሌ መመስረቻ ፁሁፍን እና መተዳሪያ ደንቡን ለማዘጋጀት የህግ ባለሙያ ማስፈለጉ፤ በአይነት የሚደረገዉን መዋጮ ለመወሰን የሂሳብ ሰራተኛ እና ማህንዲስ አስፈላጊ መሆኑ በምስረታ ሂደትን ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ መሆኑ፤
በቀጥታ የንብረቱ ባለቤት ያለመሆን፤
የዉሳኔ መዘግየት መኖሩ ምክንያቱም በእያንዳንዱ ወሳኝ ጉዳይ ላይ የጠቅላላ አባላትን እና የተለያዩ አካላትን ዉሳኔን የሚያስፈልግ መሆኑ፤
በጥቂት እጅ የወደቀ እና የተንኮል አስተዳደር የመፈጠር እድሉ ሰፊ ነው ምክንያቱም ባላክስዮኖቹ በየሀገሩ የተበታተኑ እና የማይተዋወቁ በመሆናቸዉ በቀላሉ ለመቆጣጠር እና መብታቸዉን በተደራጀ መልኩ ለማስከበር ይቸገራሉ፡፡ ምሳሌ፡- የባንክ አባሎች የማይተዋዉ ብዙ ቁጥር ያለቸዉ በመሆኑ ቦርድ እና ስራ አስኪያጆችን በየቀኑ ለመቆጣጠር ያስቸግራል፡፡
ሚስጢር ያለመጠበቅ ችግር

ሰናይ ጊዜ 👏
YilkalG.
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
April 2, 2022
April 2, 2022
የቤት ብድር የሚሰጡ ባንኮች
#አለ_ህግ
ብሄራዊ ባንክ ሞርጌጅ ባንኮች ለማቋቋም የሚያስችል ደንብ እያረቀቀ እንደሆነ ሪፖርተር አስነብቧል። መንግሥት ለልዩ ዓላማ ለሚቋቋሙ ባንኮች ራሱን የቻለ ደንብ እንዲያዘጋጅ የፋይናንስ ዘርፉ ሲወተውት የቆዩ ሲሆን፣ በቅርቡ ግን ብሄራዊ ባንክ ኮሚቴ አቋቁሞ ለሞርጌጅ ባንክ ማቋቋሚያ ልዩ ደንብ ማዘጋጀት መጀመሩን አንድ የባንኩ ከፍተኛ ኃላፊ ተናግረዋል። ሞርጌጅ ባንክ በባሕሪው የተለየ እና ለደንበኞቹ የሚሰጠው ብድር የረጅም ጊዜ በመሆኑ፣ ለመደበኛ ባንኮች ከሚውሉት መስፈርቶች ቀለል ያሉ መስፈርቶች ሊዘጋጁለት እንደሚገባ የዘርፉ ባለሙያዎች ጠቁመዋል። ከአምና ጀምሮ ጎህ ባንክ ብቻ የሞርጌጅ ብድር እየሰጠ እንደሆነ የገለጠው ዘገባው፣ ብሄራዊ ባንክ ግን ባንኩን የሚያውቀው እንደ ማንኛውም ንግድ ባንክ እንደሆነ አውስቷል።
ዋዜማ ሬዲዬ
April 3, 2022
የተሻሻለው የፌደራል ፍ/ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1234/13 አንቀፅ 5(2)
=======/////======= #አለ_ህግ
የክልል ጉዳይ ሆኖ በክልል ፍ/ቤቶች እየታዬ ባለ ክርክር ስልጣንን የሚቀይር ተከራካሪ ወገን ወደ ክርክሩ ቢገባ ክርክሩ የት ይቀጥላል?
~~~~
ጉዳዩ የክልል ጉዳይ ሆኖ ክርክር እየቀጠለ ባለበት ጊዜ ስልጣኑን የሚቀይር የሌላ ክልል ነዋሪ የሆነ ተከራካሪ ወገን ወይም የኢንሹራንስ ተቋም ወደ ክርክሩ ሲገባ ጉዳዩ የፌደራል ፍ/ቤቶች ስልጣን ይሆናል ወይስ አይሆንም? የክልል ፍ/ ቤቶች ስልጣናቸውን ያጣሉ ወይስ አያጡም? ጉዳዩን የያዘው ፍርድ ቤትስ መዝገቡን ስልጣን ላለው ያስተላልፍ ወይስ ይዝጋው? የሚሉት ጉዳዬች በቀድሞው አዋጅ ቁጥር 25/88 ድንጋጌዎችእና ከፍ/ስ/ስ/ህጉ ድንጋጌዎች አንፃር አከራካሪ መሆኑ ይታወቃል። የተሻሻለው አዋጅ ለዚህ ምላሽ በሚሰጥ መልኩ የተቀመጠ ነው።
~~~
በመርህ ደረጃ ነዋሪነታቸው በተለያዩ ክልሎች የሆኑ ሰዎች ወይም በፌደራል የተመዘገበ የኢንሹራንስ ተቋም ተከራካሪ የሆኑበት የፍትሀብሄር ክርክር ጉዳይ ላይ የፌደራል ፍርድ ቤቶች የስረ ነገር ስልጣን ያላቸው ሲሆን በልዩ ሁኔታ ግን የክልል ጉዳይ ሆኖ በክልል ፍርድ ቤቶች በመታየት ላይ እያለ የሌላ ክልል ነዋሪ ወይም የኢንሹራንስ ተቋም በየትኛውም የክርክር ደረጃ በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ 40(2), 41,43, 358ና 418ንም ጨምሮ ወደ ክርክሩ ቢገባ ጉዳዩ በጀመረበት አግባብ የክልል ጉዳይ ሆኖ ከሚቀጥል ውጭ የፌደራል ፍርድ ቤቶች ስልጣን ነው በሚል ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት የሚተላለፍ አይሆንም።
(via voice of justice)
April 3, 2022
April 3, 2022
H. R. 6600 01951.pdf
924.9 KB
Share 'H. R. 6600 01951.pdf'
April 3, 2022
April 3, 2022
April 3, 2022
April 3, 2022
April 3, 2022
የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ (Stop Payment Order) የሚሰጠው መቼ እና እንዴት ነው?

በገዙ አየለ መንግሥቱ

በዚህ ጽሑፍ የሚከተሉት ቁም ነገሮች ያገኛሉ
የቼክ ክፍያ ባንክ አልፈጽምም ሊል የሚችለው መቼ ነው
የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ መስጠት የሚቻልበት መንገድ
የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ ከብሔራዊ ባንክ መመሪያ አንጻር
የቼክ ሂሳብ እንቅስቃሴን በተመለከተ

https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/1800-stop-payment-order
April 3, 2022
።።።።።።። ይግባኝ ማስፈቀጃ ====
• በህጉ የተቀመጠው የይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ ካለፈ በኋላ ይግባኝ ለማቅረብ እንዲፈቀድ የሚቀርብ አቤቱታ

አንድ ፍ/ቤት ይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜው ያለፈበት ምክንያት በቂ መሆኑን ሲረዳ ይግባኙ እንዲቅርብ ሊፈቅድ እንደሚገባ በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 326/1/ ስር ተመልክቷል፡፡ በመሆኑም ፍ/ቤቱ የቀረበለት ምክንያት በቂ መሆን አለመሆኑን በአግባቡ ሊመረምረው ይገባል፡፡ በእርግጥ በቂ ምክንያት የሚባሉት ነገሮች ሕጉ ዘርዝሮ ያላስቀመጣቸው በመሆኑ ለመወሰን አስቸጋሪ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ በመሆኑም የምክንያቱ በቂ መሆን አለመሆን በእያንዳንዱ ጉዳይ ከሚቀርቡ ፍሬ ነገሮች ጋር ተገናዝበው ሊመዘኑ ይገባል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 38145 ቅጽ 8፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 326/1/

በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 324/1/ መሠረት ለአንድ ፍርድ ቤት መዝገብ ሹም የተሰጠው ሥልጣን ይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ ማለፍ አለማለፉን በመመልከት ይግባኝ መዝገቡ እንዲከፈት ማድረግ ሲሆን ይግባኙ ጊዜውን ጠብቆ ያልቀረበ ከሆነ ማመልከቻውን መመለስ፣ ማመልከቻው የተመለሰበት ወገን የይግባኝ ጊዜው ያለፈበት ሕጋዊ ምክንያት ካለው ማስፈቀጃ አቤቱታውን በማቅረብ ይኸው ጊዜው ያለፈበት ይግባኝ ለማቅረብ እንዲፈቀድለት ራሱን የቻለ አቤቱታ አቅርቦና ይህ መዝገብ ተከፍቶ ጉዳዩ ለችሎት ቀርቦ ችሎቱ የይግባኝ ማስፈቀጃውን በመመርመር በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 325 እና 326 መሠረት ተገቢ ነው ያለውን ትእዛዝ የሚሰጥበት ነው፡፡

የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 324/1/ ከፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 325 እና 326 ድንጋጌዎች ጋር አንድ ላይ ሲነበቡ የመዝገብ ቤት ሹም ጊዜው ያለፈበት ይግባኝ ለችሎት እንዲቀርብ የመፍቀድ ስልጣን የሌለው መሆኑን የሚያሳዩ ሲሆን ፋይሉ ተከፍቶ ቀርቦ ከሆነም ችሎቱ ጉዳዩን መርምሮ ይግባኙ የቀረበው ጊዜው ከአለፈ በኋላ ነው በማለት መዝገቡን ከመዝጋት የሚከለክለው አይደለም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 61843 ቅጽ 11፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 324-326
April 3, 2022
ማሳሰቢያ አለ_ህግ #law #societies
ሁሉንም የ #አለ_ህግ አባላት የሚያሳትፍ ቀጠሮ፣ ሁሌም እሁድ እሁድ የቀጥታ (Live stream) የድምፅ ውይይት ይኖረናል።
#የህግ ጉዳይ የመወያያ እርዕስ አስቀድማችሁ እንዳትመርጡ እናሳስባለን።
ምክንያቱም፣ ከወዲሁ ተዘጋጅተው ለውይይቱ እንዲመጡና ፍሬአማ ሀሳቦችን እንድናገኝ ይረዳናል።
1. የመወያያ አጀንዳ ይምረጡ
2. ተዘጋጅተው የውይይቱ ተሳታፊ ይሁኑ
3. Share and add ማድረግን አትርሱ
#Ale_Lawsocieties
#አለ_ህግ
https://t.me/lawsocieties

@lawsocieties
April 4, 2022
#Embassy of Canada#

▪️Position - Common Services Officer (Contracts and Procurement)
▪️Salary - 712,866 ETB per annum
▪️Location - Addis Ababa
▪️Education - Bachelor’s degree in a related field (i.e. business administration) from a recognized university with 3 years of experience
▪️Find More Details Here
👇👇👇👇👇
https://bit.ly/3J0kHFr

▪️Deadline - Apr 08/2022

How to Apply

Applications will only be considered when received through our portal.  Link for this job poster – https://staffing-les.international.gc.ca/en/careers/common-services-officer-contracts-and-procurement-addis-64049-en


#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ #አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
April 4, 2022