አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
Corruption is a human rights issue, which ought to be recognized as such by States, the business community and civil society. Those who peacefully work for the rights of others against corruption should be recognized, celebrated and protected as human rights defenders.
https://t.me/TransparencyEthiopia
በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ መሰረታዊ ነጥቦች
በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ መሰረታዊ ነጥቦች

ይህ አጭር ጽሁፍ ስለ ሀገራዊ ምክክር ምንነት፣ ጥቅሞችና ዓላማዎች፣ መርሆች እና ምክክሩን ለማሳካት የሚከናወኑ ተግባራትን በተመለከተ የሚያትት ሲሆን የሀገራዊ ምክክር ጽንሰ ሃሳብን ከአዋጅ ቁጥር 1265/2014 አንፃርም አጭር ትንተና ያቀርባል፡፡
መልካም ንባብ

1. ስለ አገራዊ ምክክር
ሀገራዊ ምክክር ስር የሰደዱ ሀገራዊ አለመግባባቶችን፣ ግጭቶችን ለመፍታት ጥቅም ላይ የሚውል አንድ አይነት የግጭት መፍቻ ዘዴ ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ድርድር (negotiation) የተለያየ ጥቅምና ፍላጎት የሚወክሉ አካላት በሰጥቶ መቀበል መርህ ልዩነቶቻቸውን የሚፈቱበት ዘዴ ነው፡፡ ሌላው ዘዴ እርቅ (reconciliation) ሲሆን የደረሰ በደል ላይ ጥልቅ ውይይት ማድረግና በመተማመን ይቅር በመባባል ስምምነትን ማስፈኛ ዘዴ ነው፡፡ በመጨረሻም የማስማማት (mediation) የግጭት መፍቻ ዘዴ በሶስተኛ ወገን አማካኝነት ልዩነትን ለማስወገድ ጥቅም ላይ የሚውል ነው፡፡

2. የሀገራዊ ምክክር ከአዋጅ ቁጥር 1265/2014 አንፃር
ከግጭት መፍቻ ዘዴዎች መካከል አንዱ የሆነውን አገራዊ ምክክር (national dialogue) ለማድረግ እንዲቻል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ማቋቋያ አዋጅ ቁጥር 1265/2014 አውጥቷል፡፡ የአዋጁን አላማ እና ይዘት እንደሚከተለው ለማብራራት ተሞክሯል፡፡

የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ማቋቋያ አዋጅ ተግባራዊ ያደረገው ዘዴ አካታች አገራዊ ምክክርን ነው፡፡ አገራዊ ምክክር በአገራችን ወቅታዊና ተጨባጭ ሁኔታ አንፃር ተመራጭ ግጭት መፍቻ ዘዴ ነው፡፡ አገራዊ ምክክር አንድ ወጥ ሀሳብ እና አንድ ወገን ብቻውን የሚመክርበት ሳይሆን በየአጀንዳው የተለያዩ ሀሳቦች፣ ጥቅሞች፣ ፍላጎቶችና መብቶች የሚወከሉበትና ምክክር የሚደረግበት፣ እነዚህን ሀሳቦች የሚወክሉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚወከሉበት ብዝሀነት ያለው መድረክ ነው፡፡ በዚህም በሀገራችን የሚስተዋሉ መሰረታዊ ችግሮችን እና ልዩነቶችን ወደ ጠረጴዛ በማምጣት፣ የተለያዩ ጥቅሞችና የህብረተሰብ ክፍሎች በሚሳተፉበት ምክክር የጋራ መፍትሄ ለማምጣት የተመረጠና ጥቅም ላይ የሚውል ዘዴ ነው፡፡

2.1. የአገራዊ ምክክር ጥቅሞችና ዓላማዎች
የአገራዊ ምክክር ጥቅም በዋናነት ግጭትን ለማስወገድ (peace building)፣ የፖለቲካና ዴሞክራሲ ሽግግርን ለማሳለጥ የሚጠቅም ነው፡፡ በተለይም ግጭቶችን ለመከላከል፣ ለማስተዳደር (conflict management) እና ለመፍታት አይነተኛ መሳሪያ ሆኖ ያገለግላል፡፡ በአለም አቀፍ ደረጃም በበርካታ ሀገራት በተለየዩ ጊዜያት በተለያየ መነሻ ምክንያቶች ሀገራዊ ምክክሮችን አካሂደዋል፡፡ የተወሰኑት የተሳካለቸው ሲሆን በተወሰኑት የሚፈለገውን ግብ ሳያሳካ ቀርቷል፡፡

የሀገራዊ ምክክር አላማዎች መሰረታዊ የሆኑ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ያሉ ልዩነቶችን በማጥበብ መግባባትን ለመፍጠር፣ በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች መካከልና ከመንግስት ጋር ያለን ግንኙነት ለማሻሻል፣ መተማመንን ለማጎልበት፣ የመነጋገር የፖለቲካ ባህልን ለማጎልበት፣ ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት፣ ጠንካራና ቅቡልነት ያለው አገረ መንግስት በጋራ ለመገንባት፣ ልዩነቶችን በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ ለመፍታት፣ የዴሞክራሲና የፖለቲካ ሽግግር (transformation) ለማስቻል፣ ልማትን ለማፋጠን የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

በተጨማሪም የሀገራዊ ምክክር አላማ መሰረታዊ አለመግባባቶች፣ ልዩነቶችና ግጭቶች ምን እንደሆኑ መለየት፣ መሰረታዊ ምክንያታቸውን (root cause) መለየት እና በእነዚህ ላይ ልዩነቶችን በምክንያታዊ፣ በሰለጠነ፣ በመቻቻል መንገድ የጋራ መግባባቶች ላይ ለመድረስ እና የግጭቶቹ መንስኤ የሆኑ ልዩነቶችን ለማጥበብ ካልሆነም በልዩነቶች ላይ በመስማማት በሀሳብ ለመለያየት ብሎም ይህን የሀሳብ ልዩነት በዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ህጋዊ መንገድ መፍታት የሚቻልበትን ዘዴ በጋራ በመቀየስ ተግባራዊ ለማድረግ ለመግባባት የጋራ ጥረት የሚደረግበት መድረክ ነው፡፡

2.2. የአገራዊ ምክክር መርሆች
አገራዊ ምክክር ዓላማን ለማሳካት ምክክሩ ሊከተላቸው የሚገቡ መርሆች ውስጥ አካታችነት፣ ግልፅነት፣ ተአማኒነት፣ መቻቻልና እና መከባበር፣ ምክንያታዊነት፣ የምክረ ሀሳቦች ተግባራዊነት እና አውድ ተኮርነት፣ ገለልተኛ አመቻች፣ የአጀንዳ ጥልቀትና አግባብነት፣ ዴሞክሲያዊነት፣ የህግ የበላይነት በአዋጁ የተጠቀሱ ናቸው፡፡ ከነዚህ በተጨማሪነት ኮሚሽኑ አስፈላጊ የሚላቸውን መርሆች ሊያካትት እንደሚችል ተመልክቷል፡፡ ከዚህ አንፃር ኮሚሽኑ ተሳታፊዎች በቅን ልቦና እንዲሳተፉ እና ፍትሀዊነት መርሆችን ሊያካትት ይችላል፡፡

እነዚህን መርሆች በዝርዝር ስንመለከት በመጀመሪያ የምናገኘው አካታችነትን ይሆናል፡፡ አካታችነት ከህጉ ዝግጅት እና ኮሚሽነሮች ምርጫ ጀምሮ በተቻለ መጠን ሰፊ ተሳትፎን ለማረጋገጥ ጥረት የተደረገበት ነው፡፡ በምክክር ሂደትም መሰረታዊ አገራዊ ጉዳዮችን በሙሉ እንደሚያካትት፣ እነዚህ ሀሳቦችና ጥቅሞችን የሚወክሉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በየደረጃው እንዲሳተፉበት እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡ ስራዎቹንም በግልፅነት ለህብረተሰቡ የደረሰበትን ደረጃ በማሳወቅ እንደሚከውን ይጠበቃል፡፡ ኮሚሽኑ ስራዎቹን በተአማኒነት ለአገር፣ ለህዝብ፣ ለህግ፣ ለመርህ እና ለስነምግባር ተገዢ ሆኖ እንደሚፈፅሙ ይጠበቃል፡፡ ተወያዮችም በመቻቻልና በመከባበር መንፈስ በሰከነና በሰለጠነ መንገድ ምክክር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡ ሌላው መርህ ምክንያታዊነት ሲሆን ይህም በማስረጃ እና በእውነት ላይ የተመሰረት የሀሳብ መግለፅ እንደሚኖር እና ሀሳቦችን በምክንያታዊነት የመቀበልና የመቃወም አካሄድ እንደሚኖር ህጉ ይጠብቃል፡፡ ከሂደቱ ውጤት ስምምነት የሚደረስባቸው የትግበራ አቅጣጫዎችን መንግስት እና የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ ይተገብራሉ ተብሎም እምነት ተይዟል፡፡ በተለይም ልዩነቶች የሚፈቱበት ህጋዊ አካሄድ አቅጣጫ በሚቀመጥበት ወቅት ተግባራዊ እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡

2.3. የሀገራዊ ምክክር ለማሳካት የሚከናወኑ ተግባራት
አገራዊ ምክክር ከሚያልፍባቸው ሂደቶች ውስጥ መነሻ (initiation)፣ ዝግጅት፣ ምክክር እና ትግበራ (implementation) ናቸው፡፡ አሁን ባለንበት የዝግጅት ምእራፍ ሲሆን ከዚህ አንፃር አዋጁ ያካተተው ጉዳይ የኮሚሽኑን ተግባርና ሀላፊነት በሚመለከት ኮሚሽኑ በአላማ የተመለከተውን ጉዳይ ለማሳካት በገለልተኛነት እና በነፃነት መስራት እንደሚጠበቅበት ያስቀምጣል፡፡ በዝርዝርም የምክክር አጀንዳዎችን፣ አወያዮች አመራረጥን፣ የምክክር ስነ ስርአትን፣ የተወያዮች አመራረጥን እና ሌሎች መሰል ጉዳዮችን በነፃነትና በገለልተኝነት በራሱ እንደሚወስን ይጠበቃል፡፡ ምክክር የሚደረግባቸው ደረጃዎች፣ ሂደቶች፣ አካባቢዎችን መወሰን እና ምክክሩንም በአመቻችነት መምራት ይጠበቃል፡፡ ለዚህ አላማ ኮሚሽኑ በአጠቃላይ አስራ አንድ ኮሚሽነሮች ያሉት ሲሆን ከነዚህ ውስጥም አንድ ዋና ኮሚሽነር እና ምክትል ዋና ኮሚሽነር አለው፡፡ ኮሚሽኑ ፅሀፈት ቤት፣ አስፈላጊ ኮሚቴዎች እና አስፈላጊ ሰራተኞች እንደሚኖሩት አዋጁ ይገልፃል፡፡ ይህን የማደራጀት ተግባሩም የሚጠበቅ ነው፡፡ ይህን ለመፈፀም የሚያስችለው የፋይናንስ ነፃነቱንም ለማስጠበቅ በጀት ከመንግስት እና ከሌሎች ህጋዊ ምንጮች ማግኘት እንደሚችል ወጪዎቹንም የመንግስት ፋይናንስ መርሆች መሰረት በኮሚሽኑ በሚፀድቅ ውስጠ ደንብ መሰረት የመፈፀም ሙሉ ነፃነት
እንዳለው ተመልክቷል፡፡

በአጠቃላይ የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክርን ተግባራዊ ለመድረግ እና አላማዎቹን ስኬታማ ለማድረግ የመንግስት አካላት፣ የተለያዩ ማህበራዊ እና የግል አደረጃጀቶች፣ ህዝቡ፣ ግለሰቦች፣ አለምአቀፍ ተቋማት ትልቅ ሀላፊነትና ድርሻ አላቸው፡፡ ህጉም ኮሚሽኑ ለሚያቀርባቸው ህጋዊ ጥያቄዎች መተባበር ግዴታ እንደሆነ ይደነግጋል፡፡ ከዚህ አንፃር ሂደቱ ካለው ፋይዳ አንፃር ሁሉም የበኩሉን ድጋፍ፣ ትብብር፣ ተሳትፎ እንዲያደርግ ይጠበቃል፡፡

በንቃተ ሕግ፣ ትምህርት እና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
በሴቶች ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ሁለተኛዉ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ተከፈተ
ዛሬ መጋቢት 17 ቀን 2014 ዓ.ም
የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት በሴቶች ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ሁለተኛዉን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ዛሬ መክፈቱን አስታወቀ፡፡
መስሪያ ቤቱ ከዚህ በፊት አገልግሎት ይሰጥበት የነበረውን እና መገናኛ ደራርቱ ቱሉ ህንጻ ላይ የሚገኘውን ቅርንጫፍ ሶስት በመባል የሚታወቀውን ጽ/ቤት በሴት ሰራተኞች ብቻ አገልግሎት እንዲሰጥ ማድረጉን ለማወቅ ተችሏል፡፡
አቶ ሙሉቀን አማረ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ሴቶች በተመደቡበት የስራ ኃላፊነት እና ቦታ በታማኝነት እና በጥንቃቄ የሚሰሩ በመሆናቸው ያላቸውን የማገልገል አቅም እና ችሎታ አጠናክረው እንዲቀጥሉበት ለማድረግ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ተከፍቷል ብለዋል፡፡
የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ አሰፋሽ ወ/ገብርኤል በበኩላቸው “ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ መከፈት ከ68 በመቶ በላይ ለሆኑት ሴት ሰራተኞቻችን እውቅና መስጠት በመሆኑ የእንኳን ደስ አላችሁ” በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተስፋፋ የመጣውን የሀሰተኛ ሰነድ መበራከት እና የሙስና አመለካከት ለመዋጋት የሁሉም ሰራተኛ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ የተገለጸ ሲሆን ይህንን በተመለከተ በዋና ዳይሬክተሩ አጠር ያለ ማብራሪያ/አቅጣጫ ተሰጥቷል፡፡ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በሴቶች ብቻ አገልግሎት እንዲሰጥ የተደረገው በአገራችን ለአርባ ስድስተኛ ጊዜ “እኔም የእህቴ ጠባቂ ነኝ!” በሚል መሪቃል የሚከበረውን አለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ ነው፡፡
ከአንድ አመት በፊት የመጀመሪያ የሆነው በሴቶች ብቻ አገልግሎት እንዲሰጥ የተደረገው እና ካዛንቺስ አካባቢ የሚገኘው ቅርንጫፍ ስምንት ጽ/ቤት በአገልግሎት አሰጣጥ ጥሩ አፈጻጸም እንዳለው ተገልጿል፡፡
Legality of Levying Income Tax on Illegal Amounts Received by a Taxpayer ---- Personal Reflection

By:- Natae Ebba Kitila

The central focus this piece wants to press on is the legality of the collection of income tax on illegally driven amounts. In doing so, the writer will try to unpack some important elements from the Income-tax proclamation No 979/2016.

Enjoy reading!

https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/2024-legality-of-levying-income-tax-on-illegal-amounts-received-by-a-taxpayer-personal-reflection
ቅን-ልቦና በሰበር ችሎት ክፍል አንድ
አብርሃም ዮሐንስ
ውክልና
ሰ_መ_ቁ. 14974 ቅጽ 1
ተወካዩ የራሱን ጥቅም የሚመለከት ጉዳይ ሲያጋጥመው ሁኔታውን ለወካዩ ሳያሳውቅና ወካዩ ሳይስማማ ስራውን እንዳይፈጽም ይከላከላል፡፡ ስለወኪልነት የተደነገጉትን የፍ/ብሔር ድንጋጌዎች ስንመለከትም ተወካዩ ከወካዩ ጋር በሚኖረው ግንኙነት ጥብቅ የሆነ ቅን ልቦና ሊኖረው እንደሚገባ እና የውክልና ስልጣኑን የሚያስቀሩ ምክንያቶች እንዳለበት (የፍ/ብ/ህ/ቁ 2208)፣ ተወካዩ ስራውን የሚፈጽመው በተለይ ለወካዩ ጥቅም ሊሰጥ የሚችል መንገድ ብቻ መሆን እንዳለበት (ፍ/ብ/ህ/ቁ 2209(1))፣ እንዲሁም ተወካዩ በራሱ ስም ከወካዩ ጋር የሚያደርገው ውል ወካዩ ካላጸደቀው በቀር ሊፈርስ እንደሚችል (የፍ/ህ/ቁ 2188) መደንገጋቸው ተወካዩ ለወካዩ ፍጹም ታማኝ መሆን እንዳለበት እና ለወካዩ ጥቅም ብቻ መስራት እንዳለበት፣ የጥቅም ግጭት ባለበት ጊዜ ሁሉ ሁኔታውን ለወካዩ የማሳወቅ ግዴታ እንዳለበት የሚያስገነዝቡ ናቸው፡፡ በመሆኑም Aንድ ተወካይ የጥቅም ግጭት ባለበት ጊዜ ለወካዩ ሳያሳውቅ የሚየከናውነውን ስራ ወካዩ ሊቃወመው የሚችል መሆኑን እና በዚህ ሁኔታ የተከናወነው ስራም ወካዩ ካላፀደቀው በቀር ወካዩ ራሱ እንደፈጸመው ሊቆጠር እንደማይገባ ከውክልና ግንኙነት Aጠቃላይ ዓላማ እና ከፍ/ብ/ህጉ ድንጋጌዎች መገንዘብ ይቻላል፡፡
ሰ_መ_ቁ. 26399 ቅጽ 5
ሿሚው በግልጽም ይሁን በዝምታ እንደራሴው ሥልጣኑ ቀሪ ከሆነ በኋላ የሠራውን ሥራ ያልተቀበለው መሆኑ ከተረጋገጠ የዚሁ ያለመቀበል ውጤት በቁጥር 2193 ተደንግጓል፡፡ የዚህን ድንጋጌ ይዘት ስንመለከት aôሚው ይህንኑ የእንደራሴውን ሥራ ካልተቀበለው ምን ጊዜም ይኸው ውል ፈራሽ ነው የሚል Aይደለም፡፡ ይልቁንም ከፍ/ብ/ሕ/ቁ. 1808
እስከ 1818 ድረስ የተመለከቱትን ድንጋጌዎች ተከትሎ የውሉ መፍረስ ወይም መሰረዝ ሊወሰን የሚችል መሆኑን የሚያመለክት ነው፡፡ ይህም እነዚህኑ አግባብነት ያላቸውን ድንጋጌዎች በመከተል ውሉ ሊፈርስ የማይችልበት አጋጣሚ ያለ መሆኑን የሚያሳይና ነገር ግን ውሉ የሚፈርስ ሆኖ በተገኘ ጊዜ ውሉ በመፍረሱ ምክንያት በቅን ልቦና ከእንደራሴው ጋር በተዋዋሉት 3ኛ ወገኖች ላይ ለሚደርሰው ጉዳት ካሣ የሚጠየቅበት መንገድ የሚያመቻች ድንጋጌ ነው፡፡
ሰ_መ_ቁ. 77983 ቅጽ 15
ተወካዩ ከወካዩ ጋር የሚያሰተሳስረው ግንኙነት ውስጥ ጥብቅ የሆነ ቅን ልቦና ሊኖረው እንደሚገባ በፍትሐብሄር ሕግ ቁጥር 2208(1) ስር ተደንግጓል ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ተወካዩ የተወካይነት ሥራውን የሚፈጽመው በተለይ የወካዩን ጥቅም ሊሰጥ በሚችልበት መንገድ ብቻ መሆን እንዳለበት በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2209 (1) ድንጋጌ ያሳያል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ተወካዩ በውክልና ሥራው ላይ በሚገኝባቸው ጊዜዎች ሁሉ በውክልና በተሰጠው አደራ አንድ መልካም የቤተሰብ አባት ቤተሰቡን ለመጠበቅ እንደሚያደርገው ሁሉ በትጋትና በጥንቃቄ መጠበቅ ያለበት መሆኑን በፍትሐብሄር ሕግ ቁጥር 2211(1) ስር በግልጽ ተደንግጓል፡፡
አስፈላጊ ወጪ
ሰ_መ_ቁ. 81081 ቅጽ 14
የፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 2168 ድንጋጌ ይዘት ሲታይም አንድ ሰው ለተወሰነ ጊዜ በእጁ ያቆየውን እቃ እንዲመለስ የተገደደ እንደሆነ ለሕግ ወይም ለውል ተቃራኒ የሚሆን ድንጋጌ ከሌለ በቀር የተባለውን እቃ ከመለዋወጥ የተነሳ ያሉት መብቶችና ግዴታዎች ከድንጋጌው ቀጥለው ባሉት ደንቦች መሰረት የሚወሰን መሆኑን የሚያስገነዝብ ሲሆን በዚሁ ድንጋጌ ስር ከሰፈሩት ደንቦች መካከል አንዱ የሆነው በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 2169 ስር የተቀመጠው ደግሞ የያዘውን እቃ እንዲመልስ የተገደደ ሰው በእቃው ላይ ያደረገው ወጪ ሊመለስለት የሚገባው ወጪው የግድ አስፈላጊ ሁኖ ሲገኝ ስለመሆኑና ወጪው አስፈላጊ ሳይሆን ከቀረ ወይም ወጪው እቃውን እንዲመለስ በተገደደው ሰው ወይም ተገዳጁ ኃላፊ በሚሆንበት ሰው ጥፋት ምክንያት ከሆነ ወጪው ሊመለስ የማይችል መሆኑን ያሳያል፡፡
ሕጉ በአንቀጽ 2171(1) ስርም ለእቃው የተደረገው ወጪ የእቃውን ዋጋ ግምት ከፍ አድርጎት እንደሆነም እቃውን ለመመለስ የተገደደው ሰው ስለዚሁ ጉዳይ ያወጣው ገንዘብ ሊመልስለት እንደሚገባ የደነገገ ሲሆን ይህ ወጪ በክፉ ልቦና ስለመደረጉ የተረጋገጠ ወይም ርትዕም የሚያስገድድ ከሆነ ደግሞ ዳኞች ወጪውን ለመቀነስ ወይም ጭራሹን ለማስቀረት የሚችሉበት አግባብ መኖሩንን የተጠቃሹ ድንጋጌ ቀጣይ የሆነው የፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 2172((1) ይዘት ያሳያል፡፡
ይህ ድንጋጌ አንድን ወጪ በክፉ ልቦና የተደረገ ነው ለማለት የሚቻልበት አግባብም ወጪው በተደረገበት ጊዜ ወጪውን የሚጠይቅ ሰው እቃውን ለመመለስ ግዴታ ያለበት መሆኑን ያውቅ እንደነበረ ወይም ማወቅ ይገባው የነበረና ርትዕም ሲያስገድድ መሆኑን በመለኪያነት አስቀምጧል፡፡
ስለሆነም እነዚህ ድንጋጌዎች ሲታዩ አንድ ሰው የሌላ ሰው ንብረት ይዞ ሲጠቀም ከቆየና ንብረቱን በሚጠቀምበት ጊዜ ንብረቱን ከጥፋት ወይም ከብልሽት ለማዳን ሲል ተገቢውን ወጪ ቢያወጣ ይኼው ወጪ በሕጋዊ ባለሃብቱ እንዲተካለት መጠየቅ የሚችልበት አግባብ የሚኖረው ወጪው የግድ አስፈላጊ ከሆነና በቅን ልቦና የተደረገ መሆኑ ሲረጋገጥ ስለመሆኑ የሚያስገነዝቡ ሲሆን በክፉ ልቦና የተደረገ ስለመሆኑ የተረጋገጠውን ወጪ ግን እቃውን እንዲመለስ የተደረገ ሰው ሊቀነስበት ወይም ጭራሹንም ዳኞች ሊያስቀሩት የሚችሉ ስለመሆኑ ሕግ ስልጣን የሰጣቸው መሆኑን ድንጋጌዎች ያስረዳሉ፡፡
ሽያጭ
ሰ_መ_ቁ. 88084 ቅጽ 15
በህግ ጥበቃ የሚደረግለት መብት ሣይኖር በስሙ የተመዘገበ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነት የምስክር ወረቅተ ከያዘ ሰው ንብረቱን በመንደር ውል የገዛ ገዢ ተገቢውን ማጣራት በማድረግና፣ በጥንቃቄ፣ የገዛና የቅን ልቦና ያለው ነው ለማለት አይቻልም።
ሰ_መ_ቁ. 100931 ቅጽ 17 የልዩነት ሀሳብ
ከሽያጭ ውል ጋር በተያያዘ ሕጉ ጥበቃ የሚያደርገው የቅን ልቦና ገዥ ነኝ ለሚል ሰው ብቻ ሳይሆን የአእምሮ ጉድለት ያለባቸው ግለሰቦችም ሕጋዊ መብታቸው እንዳይጣስ የወራሾችም መብትና ጥቅም ጭምር ለማስከበር እንደሆነ በፍ/ሕ/ቁ. 339 እና ተከታይ ድንጋጌዎች ተመልክቷል፡፡
ቅን-ልቦና በሰበር ችሎት ክፍል ሁለት
#አለ_ህግ
ከውል ውጭ ሀላፊነት
ሰ_መ_ቁ. 82154 ቅጽ 15
አንድ የመንግስት መስሪያ ቤተ ለሰራተኛው ተግባር ኃላፊነት ሊህረው የሚችለው በሰራተኛው የተፈፀመው ጥፋት የሥራ ጥፋት ሆኖ ሲገኝ ሲሆን አንድ ጥፋት የስራ ጥፋት ነው ተብሎ የሚወሰደውም ጥፋት አድራጊው በዚህ ጥፋት ላይ የወደቀው በቅን ልቡና በስልጣኑና ለስራው ክፍል መልካም ያደረገ መስሎት የፈፀመው መሆኑ ሲረጋገጥ ስለመሆኑና ከዚሀ ውጪ በሆነ በማናቸውም ሌላ ጉዳይ ግን ጥፋቱ እንደግል ጥፋት ሁኖ እንማሚቆጠር የፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 2126 እና 2127(1) እና (2) ድንጋጌዎች ይዘትና መንፈስ ያስረዳሉ፡፡ ጥፋቱ በቅን ልቦና ያልተፈፀመ መሆኑም በተቃራኒ ማስረጃ ሊረጋገጥ እንደሚችልና ተቃራኒ ማስረጃ ካልቀረበ ግን የራተኛው አሰራር በቅን ልቦና እንደተሰራ በሕጉ ግምት እንደሚወሰድበት የፍ/ብ/ሕ/ቁጥር
2127/3/ ድንጋጌ ይዘትና መንፈስ ያሳያል፡፡

ሰ_መ_ቁ. 132017 ቅጽ
በግጭት ምክንያት ጉዳት የደረሰበት መኪና በወቅቱ ተጠግኖ ወደ ስራ ቢመለስ በአደጋው ምክንያት የተቋረጠን የገቢ መጠን ለመቀነስ ወይም ለማቅለል በቅን ልቦናና በማስተዋል የተደረገ እንቅስቃሴ ከሌለ በደረሰ ጉዳት መጠን በሙሉ ካሳ ሊጠየቅ ስላለመቻሉ፡

የስነ-ስርዓት ህግ
የሰ/መ/ቁ.81616 ቅጽ 14
በሕጉ አግባብ ስልጣን ባለው ፍ/ቤት ተከራክሮ ያጣውን ወይም የተከለከለውን መብት ከሕግ ስነ-ሥርዓትና ቅን -ልቦና ውጭ በሆነ አኳኃን ፍርዱን በሚያስፈጽመው ፍ/ቤት ለመጐናፀፍ የሚያደርገው እንቅስቃሴ ተገቢነት ያለው ሆኖ አላገኘነውም፡፡
ሰ_መ_ቁ. 91103 ቅስ 15
አንድ ተከራካሪ ወገን በሌላኛው ተከራካሪ ወገን ቅን ልቦና ውጪ በሆነ ተግባር ለክርክር ተዳርጎ መገኘቱ ከተረጋገጠ የወጪና ኪሳራ ጥያቄ ውድቅ ማድረግ የስነ ስርዓት ሕጉ ሊያሳካ ከአሰበው ዓላማ ውጪ በመሆኑ የሕግ መሰረት የሌለው ነው፡፡
የውጪና ኪሳራ ጥያቄን አስመልክቶ ፍርድ ቤቱ በመጠኑ ላይ በሕጉ ስልጣን የተሰጠው መሆኑና ረቺ ሁልጊዜ ወጪና ኪሳራ እንዲተካለት መደረግ የሌለበት መሆኑ ግንዛቤ የሚወሰድበት ቢሆንም ከቅን ልቦና ውጪ ለክርክር የተጋበዘውን ወገን በተመለከተ ግን የክርክሩ ረቺ መሆኑ እስከታወቀ ድረስ ቅን ልቦና ከሌለው ወገን በክርክሩ ምክንያት ያወጣውን ወጪ እንዲተካለት ማድረግ ክርክሮች ያላግባብ እንዳይፈጠሩ የማድረግ ውጤት ያለው በመሆኑ ተግባራዊ ሊደረግ የሚገባው ነው፡፡
ሰ_መ_ቁ. 93987 ቅጽ 16
የዚህ ድንጋጌ ይዘቱና መንፈሱ ሲታይ ክርክሩ መኖሩን ከጅምሩ እያወቀ ውጤቱን በመጠበቅ ከፍርዱ በኋላ የፍርድ መቃወሚያ የሚያቀርበውን ወገን አቤቱታውን በመቀበል ለማስተናገድ አስፈላጊ ያለመሆኑን ሁሉ ያስገነዝባል፡፡ይህም የክርክር አቀራረብ በቅን ልቦና የተመሰረተ ሁኖ በአነስተኛ ወጪ፣ጉልበትና አጭር ጊዜ ፍትሐዊነት ያለውን ውሳኔ ለመስጠት የሚቻልበት አግባብ እንዲኖር እና ሕግ አውጪ ከፈለገበት አላማ ጋር መጣጣም ያለበት መሆኑም የሚታመን ነው፡፡
እንግዲህ አቤቱታውን የሚያቀርበው ወገን የቅን ልቦና ተከራካሪ ሁኖ መሰረታዊ መብቱን ማስከበር የሚችልበት የስነ ስርዓት ሕግ አግባብ እንዲኖር ሕግ አውጪ የፈለገ ሲሆን ይህንኑ መመዘኛ የሚያሟላ አቤቱታ አቅራቢ የሚቃወመው ፍርድ ዋጋ ያለው፣ያልተፈፀመ መሆን እንደአለበትም የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 358 ድንጋጌ ይዘት ያስረዳል፡፡በሌላ አገላለፅ የፍርድ መቃወሚያ የሚቀርብበት ፍርድ ስልጣን ባለው ፍርድ ቤት ያልተሻረና አፈጻጸሙም ያልተጠናቀቀ ሊሆን እንደሚገባ ሕጉ
ያሳያል፡፡
ሰ_መ_ቁ. 101079 ቅጽ 17
በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 358 መሠረት የተዘረጋው ሥርዓት አስቀድሞ በተሰጠው ውሣኔ መብቱ የሚነካበት ወገን ባለበት ውሣኔ እንዳልተሰጠበት ተቆጥሮ እንደገና ክርክር የሚጀምርበት ሥርዓት ነው፡፡ መሰረታዊ አላማም ቅን ልቦና ያላቸው ወገኖች በመሰረታዊ ሕግ የተጠበቀላቸው መብት ባለመከራከር ዋጋ እንዳያጣ ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡
ስጦታ
ሰ_መ_ቁ. 90959 ቅጽ 16
ስጦታው ከቅን ልቦና ውጪ የተደረገ ነው እስከተባለ ድረስ በስጦታ አድራጊው ድርሻ ጭምር ፈራሽ የማይሆንበት ሕጋዊ ምክንያት ያለመኖሩን ከፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 2438(1) ድንጋጌ ይዘትና መንፈስ ተገንዝበናል፡፡
ቼክ ቅጽ 7
የንግድ ሕግ ቁጥር 841 ድንጋጌ መሠረት የቼኩ አውጪ በአምጪው ላይ መቃወሚያ ሊያደርግ የሚችለው ቼኩን ያገኘው ቅን ልቦና በጐደለው ሁኔታ ወይም ቼኩን ሲያገኝ ከባድ ጥፋት ያደረገ መሆኑ ሲረጋገጥ እንደሆነ ነው፡፡
የውል መሰረዝ
24221፤ 24974 ቅጽ 7
የውል ይሰረዝልኝ Aቤቱታም ለፍርድ ቤት በቀረበ ጊዜ ዳኞች ውሉ እንዲሰረዝ ከመወሰናቸው በፊት የተዋዋዮችን
ጥቅምና በቅን ልቦና የሚያስፈልገውን መሠረት ማጤን እንዳለባቸው እንደዚሁም ዓይነተኛ የውል መጣስ ተግባር /fundamእntal brእach of contract/ ካልተፈጸመ ውሉ ይሰረዝ ሊሉ እንደማይችሉ በፍ/ብ/ሕ/ቁ. 1785 ላይ ተመልክቷል።
አብርሃም ዮሐንስ
Capital Increament and Dividend.pdf
1 MB
Forwarded from 🇪🇹የሕግ ጉዳይ (Mikias Melak)
"Golden Rule"⭕️‼️
Treat others only in a ways that you are willing to be treated in the same exact situation.👍
To Apply it,You would imagine yourself in the exact place of the other person on the same receiving end of the action.

if you act in a given way toward another, and yet are unwilling to be treated that way in same circumstances, then, you violate the rule.

finally, ♻️📚📙📘📗📕📒📔
To apply the above Golden Rule adequately, we need knowledge and imagination.💊
🔍we need to know what effect our actions have on the lives of others.📝✏️
and we need to be able to imagine ourselves.🔗
Vividly and adequately, in the others person place on the receiving end of action.🔚🔴
with knowledge, imagination and Golden Rule, we can progress far in our moral thinking....♏️
My last note of Ethics
to you....♊️2011E.C
well noted‼️‼️‼️‼️‼️‼️
https://t.me/LawyerEthiopia
ጠበቃ እና የህግ አማካሪ
Lawyer and Legal Adviser
We offer you Reliable services with a very high sense of responsibility.
Contact us;
EthiopianLawFamily@gmail.com
ማስታወቂያ
**
በቅዳሜና እሁድ መርሃ ግብር መማር ለምትፈልጉ የትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ;
......
የዲላ ዩኒቨርሲቲ በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የግል አመልካቾችን ተቀብሎ በቅዳሜና እሁድ መርሀግብር በተለያዩ የቅድመ ምረቃ ኘሮግራሞች በዲላ፤ ሀዋሳ፤ ይ/ጨፌ እና ሻሸመኔ ማዕከላት አመልካቾችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡
**)

በማህበራዊ ሳይንስና ስነሰብ ኮሌጅ
በህግ ት/ቤት
1 LL.B Degree in law (Hawassa and Dilla)
*****
አመልካቾች ማሟላት የሚገባቸው
1. ከታወቀ ኮሌጅ በዲኘሎማ የተመረቃችሁበትን የትምህርት ማስረጃችሁን (ዲኘሎማና ትራንስክሪፕት) ዋናውን እና ፎቶ ኮፒውን በመያዝ በግንባር በመቅረብ መመዝገብ ትችላላችሁ፡፡
2. ከሁለት አመት ወዲህ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ተፈትነው በዘመኑ ለከፍተኛ ትምህርት የሚያስገባ ውጤት ይዘው መቅረብ ይጠበቅባችኋል፡፡
3. COC የሚያስፈልጋቸው የት/ት መስኮች የ COC የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ
4. የመመዝገቢያ 50 ብር መክፈል ይጠበቅባቸዋል፡፡
 የመመዝገቢያ ቦታ፡-
 ለዲላ ማዕከል አመልካቾች ኦዳያአ ግቢ ሬጅስትራርና አሉምናይ ዳ/ጽ/ቤት በየትኛውም የሥራ ቀናት፤ ለሀዋሳ ማዕከል አመልካቾች ሀዋሳ ታቦር ት/ት ቤት ቅዳሜና እሁድ ማስተባበሪያ ቢሮ፤ለይ/ጨፌ ማዕከል አመልካቾችን ይ/ጨፌ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት እና ለሻሸመኔ ማዕከል አመልካቾችን ሻሸመኔ መሰናዶ ት/ቤት ቅዳሜና እሁድ ማስተባበሪያ ቢሮ፡፡
የመመዝገቢያ ጊዜ፡- ከመጋቢት 15/2014ዓ.ም እስከ ሚያዚያ 16/2014 ዓ.ም
#Addis Ababa City Council#

▪️1 - IT Support Officer III
▪️2 - Documentation Officer
▪️3 - Website Administrator II

▪️4 - 🔴legal drafting specialty
▪️5 - 🔴legal drafting specialty

▪️Find More Details Here
👇👇👇👇👇
https://bit.ly/3JICIcx

▪️Deadline - April 05 , 2022

#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ልዩልዩ #አለ_ችሎት #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ
#አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share.....
👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
ውድ የአለ_ህግ ቤተሰቦች መልካም እሁድ (መልካም ዕለተ ሰንበት)
Dear ALE Families, have a Good Sunday (Happy Sabbath)
#አለ_ህግ #lawsocieties #Ale_lawsocieties @lawsocieties
15 African cities with the highest cost of living index
Addis Ababa: The Ethiopian capital city has the highest cost of living index score in Africa at 58.92. Apparently, the prices of consumer goods are quite high in this Horn of Africa city, compared to other cities across the continent.
15 African cities with the highest cost of living index scores
Business Insider Africa presents a list of 15 African cities with the highest cost of living index scores.
The cost of living index compares the expected average costs of basic necessities such as food, clothing, entertainment, healthcare, etc.
The list is courtesy of Statista's cost of living index across Africa, dated 2021.

Ever wondered how much it would cost you to live comfortably in another city different from yours? The cost of living index could help you with the answer, as it compares the expected average costs of basic necessities such as food, clothing, entertainment and healthcare, etc., across cities.

"The cost of living is the amount of money needed to cover basic expenses such as housing, food, taxes, and healthcare in a certain place and time period. The cost of living is often used to compare how expensive it is to live in one city versus another. The cost of living is tied to wages. If expenses are higher in a city, such as New York, for example, salary levels must be higher so that people can afford to live in that city," explains Investopedia.
Thanks to data obtained from Statista, Business Insider Africa hereby presents a list of 15 African cities with the highest cost of living index scores. Do note that the "cost of living index does not include accommodation expenses such as rent or mortgage," as Statista clearly stated in its report.

Eight cities from two African countries dominated the list. In specific terms, there are four South African cities and four Moroccan cities on the list. However, none of these eight has highest cost of living index in Africa.
Surprisingly, Nigeria's mega city and commercial nerve centre, Lagos, did not make it to the list. And there are only two West African cities on the list.

1. Addis Ababa:
The Ethiopian capital city has the highest cost of living index score in Africa at 58.92. Apparently, the prices of consumer goods are quite high in this Horn of Africa city, compared to other cities across the continent.
2. Abidjan:
The Ivorian capital city has a cost of living index score of 55.73, making it the second highest in Africa.
3. Harare:
This Zimbabwean city has a cost of living index score of 52.33 as of 2021.
4. Johannesburg:
This is the first South African city on the list. Joburg, as it is fondly called by its residents, has a cost of living index score of 46.
5. Pretoria:
This city, which serves as the seat of South Africa's executive branch of government, is equally quite costly to live in. The cost of living index score here is 44.7.
6. Gaborone:
The capital city of Botswana has a cost of living index of 42.84.
7. Cape Town:
This is the third South African city on the list and it has a cost of living index of 42.24.
8. Accra:
This is the second West African city that made it to the list, besides Abidjan. The Ghanaian capital city has a score of 42.18.
9. Marrakesh:
This is one of Africa's most famous cities, attracting tourists in the thousands. It is also a major economic hub in Morocco. Therefore, it is not surprising to see it on this list, with a cost of living index score of 41.73.
10. Windhoek:
Namibia's capital and largest city has a cost of living index score of 41.08.
11. Tangier:
This is the second Moroccan city on the list and it has an index score of 40.18.
12. Durban: This is the last one of the four South African cities on this list. Durban has a cost of living index score of 39.86.
13. Casablanca:
This is the second largest city in Morocco and it has a cost of living index score of 39.81,
14. Nairobi:
Kenya's capital city has a cost of living index score of 38.51.
15. Rabat: Finally, Morocco's capital city has a cost of living index score of 37.95.
የተዋዋይ ወገኖች ፊርማ
አንድ ውል በህግ ፊት የጸና ሆኖ ግዴታዎችን እና መብቶችን ለማቋቋም እንዲቻል ውሉ በጽሁፍ የተደረገ ሲሆን በተዋዋይ ወገኖች መፈረም ይኖርበታል ::
ውል ግዴታ በገባው ሰው እጅ መፈረም ያለበት ስለመሆኑ በፍትሐ ብሄር ህግ ቁጥር 1728 ላይ ተደንግጎ እናገኘዋለን ፡፡ በተለመደው አባባል በእጅ ለመፈረም የማይችል ሰው የጣት ምልክት /በአሻራ መፈረም ያለበት ስለመሆኑ ተደንግጓል ፡፡ ሆኖም ፈራሚዎቹ ማየት የተሳናቸው ወይም መጻፍና ማንበብ የማይችሉ ፤ ያልተማሩ ሰዎች በሆኑ ጊዜ የጣት ምልክት ፊርማው የራሳቸው ፊርማ ስለመሆኑ ካልተረጋገጠ በቀር በውሉ አይገደዱም ፡፡
በተጋባር እንደሚሰራበት እንዲህ አይነት የአካል ውስንነት ያለባቸው ሰዎች በአሻራ ሲፈርሙ ሰነድ አረጋጋጩ/አዋዋዩ አሻራውን በማክበብ በዙሪያው ስማቸውን ይጽፍበታል ፡፡ ይህ ተግባር ፊርማው የራሳቸው መሆኑን ለማረጋገጥ የሚደረግ ጥረት ነው ፡፡ እንግዲህ ህጉ ይህን ግዴታ የሚጥል በመሆኑ ማንኛውንም ውል በጽሁፍ የሚዋዋል ሰው በውሉ መጨረሻ ክፍል ላይ ሙሉ ስሙን ጽፎ መፈረም ይጠበቅበታል ፡፡
ውሉ የተፈጸመው በተዋዋዩ ተወካይ ሲሆን ተወካዩ በውሉ ላይ ሲፈርም ‘’ስለ‘’ በማለት የወኪሉን ስም መጀመሪያ ጽፎ ከዚያም የራሱን ስም በመጨመር ይፈርማል ፡፡ በተለመደው አሰራር ግን ተወካዩ ሲፈርም ‘’ስለ‘’ የሚለውን ቃል አስቀድሞ የራሱን ስም በመጻፍ ይፈርማል ፡፡ ፊርማ ስለማን እንደተፈረመ በግልጽ አያመለክትም ፡፡ አንዳንዴም ወካዩ ፊርማ ከፈረመ በኋላ ‘’ስለ‘’ የሚለውን በማስቀደም የወካዩን ስም ብቻ ይጽፋል ፡፡ እነዚህ አሰራሮች ለውሉ መፈጸም አሳሳች እና አጨቃጫቂ ናቸዉ ፡፡
ስለሆነም ያስተዉሉ ፡ ዉል ያለ መካካድ እንዲፈፀም ከተፈለገ / በአግባቡ ህጉን ተከትሎ የፊርማ ስነ ስርዓቱን ማካሄድ መሠረታዊ እና ወሳኝ መሆኑ ይታመናል። via Samuel Girma