አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.87K photos
25 videos
1.87K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
#የከተማ #መሬት #የሊዝ ህግ በኢትዮጵያ
የሊዝ ምንነት

የመሬት ሊዝ ማለት የመሬቱ ባለቤት የሆነ አካል በተጻፈ ውል መሰረት የተወሰነ ብር በማስከፈል ለተወሰነ ጊዜ መሬቱን ሌላ ሰው እንዲጠቀምበት ማከራየት ነው በማለት በመዝገበ ቃላት ተተርጉሟል፡፡ በሀገራችንም አዋጅ ቁጥር 721/2004 በአንቀፅ 2(1) ላይ ሊዝ ማለት በጊዜ በተገደበ ውል መሰረት የከተማ ቦታ የመጠቀም መብት በውል የሚተላለፍበት ወይም የሚያዝበት የመሬት ይዞታ ስሪት ነው በማለት ደንግጓል፡፡ መሬቱን የተከራየው ሰው የመሬቱ ባለይዞታ ስለሆነ በውሉ ላይ በተቀመጠው ስምምነት መሰረት የኪራይ ጊዜው እስከሚያልቅ ድረስ ሙሉ መብት አለው፡፡ ማንኛውም የሊዝ ስምምነት መገኛ ምንጭ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መሬትን በነጻ ከያዘው አካል ሲሆን ይህ አካል የመሬቱ ባለቤትና ወሰን ለሌለው ጊዜ በመሬቱ ላይ መብት ያለው ነው፡፡ የከተማ መሬትን በሊዝ መያዝ አሁን አሁን በብዛት እየተተገበረ ያለ የመሬት አያያዝ መንገድ ነው፡፡

የከተማ መሬትን በሊዝ የመያዝ አላማ/አስፈላጊነት

የከተማ መሬትን በሚመለከት የሚዘረጋ የሊዝ ስርአት የሚከተሉት ጠቀሜታዎች ይኖሩታል
 መሬትን በአግባቡ ለመጠቀም፡- የመሬትን ልማት ለማቀድና ለመቆጣጠር መሬትን ሙሉ ለሙሉ በግለሰቦች ቁጥጥር ስር ከማድረግ ይልቅ በህግ አግባብ በሊዝ እንዲተዳደር ማድረግ ይመከራል፡፡ የከተማ መሬት በግለሰቦች ባለቤትነት ስር በሆነበት ሀገር መሬቱ እንዲለማ ለማድረግ የሁሉንም ስምምነት ለማግኘት ብዙ ጊዜንና ገንዘብን ይጠይቃል፡፡

 ኢንቨስትመንትንና ኢንቨስተሮችን ያበረታታል፡- ሌላው ጠቀሜታው ለኢንቨስትመንት ሲሆን ይኸውም የመሬቱ ዋጋ በሊዝ የሚከፈል በሆነ ጊዜ የመነሻ የመዋእለ ነዋይ ፍሰቱ አነስተኛ የሚሆን ሲሆን ይህም ለኢንቬስተሩ ተጨማሪ ካፒታል ለሌሎች ስራወች እንዲኖረው ያደርገዋል፡፡ በአንጻሩ ግን መሬቱን ለመግዛት የሚገደድ ከሆነ ሁሉንም ዋጋ መክፈል የሚኖርበት በመሆኑ ለዋናው ስራ የሚቀረው ገንዘብ አነስተኛ ወይም ምንም ሊሆን ይችላል፡፡ ይህም የሚገባውን ያህል ኢንቨስት እንዳያደርግ እንቅፋት ይሆንበታል፡፡

 መልሶ የመጠየቅ እድል፡- መሬት ለሌላ አላማ በሚፈለግበት ጊዜ መሬቱ በነጻ ከያዘው ሰው ይልቅ በሊዝ መሬትን ከያዘ ሰው መልሶ መጠየቅ የተሻለ እድል አለው፡፡ በሊዝ ስርአት የተያዘን መሬት እንደገና ለመውሰድ የሚጠይቀው ዋጋ አነስተኛ ነው፡፡

የከተማ መሬት የሊዝ ህግ

1. የኢፌዴሪ ህገመንግስት
ብዙ ሀገራት ዘንድ የመሬት ባለቤትነት ህገመንግስታዊ ጉዳይ አይደለም፤ ነገር ግን በኢትዮጵያ መሬት ባለው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ምክንያት የመሬት ባለቤትነት የፖሊሲ ጉዳይ ከመሆን በላይ በህገመንግስቱ ውስጥ ተካቶ ዘላቂ ውሳኔን ያገኘ ጉዳይ ሆኗል።
በህገመንግስቱ አንቀፅ 40 መሰረት ሁሉም የከተማና የገጠር መሬት ባለቤትነት የኢትዮጵያ ህዝቦችና የመንግስት እንደሆነ ተደንግጓል። በመሆኑም ግለሰብ መሬትን መሸጥ መለወጥ አይችልም ማለት ነው። መንግስት ይህን የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ንብረት የሆነን መሬት በይዞታው ስር አድርጐ በሚያስተዳድርበትና ለልማት በዋና መሳሪታነት በሚገለገልበት ጊዜ ዜጐች በከተማ ቦታ ላይ የሚያፈሯቸዉ ንብረቶች ላይ የሚኖራቸዉ ንብረቶችን በተመለከተ ህገ-መንግስታዊ ዋስትና የተሰጠዉ ሲሆን በዚሁ አንቀፅ ላይ “ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በጉልበቱ ወይም በገንዘቡ በመሬት ላይ ለሚገነባው ቋሚ ንብረት ወይም ለሚያደርገው ቋሚ መሻሻል ሙሉ መብት አለው” በማለት ደንግጓል፡፡ ይህ መብት የመሸጥ የመለወጥ፣ የማውረስ፣ የመሬት ተጠቃሚነት ሲቋረጥ ንብረቱን የማንሳት ባለቤቱን የማዛወር ወይም የካሳ ክፍያ የመጠየቅ መብትን ያካትታል፡፡
2. የሊዝ አዋጅ
የከተማ መሬትን በሊዝ የመያዝ ስርአት በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስራ ላይ የዋለው አዋጅ ቁጥር 80/1986 ከወጣ በኋላ ነው፡፡ ይህ አዋጅም በ1994 ዓ.ም በወጣው አዋጅ ቁጥር 272/94 የተሻረ ሲሆን እንደገና ይህ አዋጅ ደግሞ በአዋጅ ቁጥር 721/2004 ተሸሯል፡፡ ስለዚህ አሁን ሰአት ማንኛውም የከተማ ሊዝ ስርአት የሚስተናገደው በዚህ አዋጅ መሰረት ነው፡፡

በአዋጁ አንቀጽ 5 መሰረት የከተማ መሬትን በሊዝ የመያዝ ስርአት ከመዘርጋቱ በፊት ከተያዙ መሬቶች በስተቀር በኢትዮጵያ የከተማ መሬት መያዝ የሚቻለው በሊዝ ስርአት ብቻ ነው ከዚህ ውጭ በሌላ መንገድ መያዝ የተከለከለ ነው። ሆኖም ግን እንደልዩ ሁኔታ የተቀመጠው በክልሎች የሚገኙ የሊዝ ስርአትን ለመፈጸም የማይችሉ ትናንሽ ከተሞች አዋጁ ተፈጻሚ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ ከአምስት አመት ላልበለጠ ጊዜ የሊዝ ስርአቱ ተፈጻሚ እንዳይሆን ማድረግ ይችላሉ።

ነባር ይዞታወችን በተመለከተ ከተማው የሊዝ ስርአቱን ከመጀመሩ በፊት በህጋዊ መንገድ የተገኘ መሬት ወይም ነባሩ መሬት ተወስዶ በምትክ በካሳነት የተሰጠ መሬት በሊዝ ውል እስካልተሰጠ ድረስ ነባር ይዞታ ተብሎ ይወሰዳል። እንደመርህ ሁሉም የከተማ መሬት በዚህ አዋጅ በተደነገገው የሊዝ ስርአት መሰረት መተዳደር እንዳለባቸው አንቀጽ 5 ላይ የተደነገገ ቢሆንም ነባር ይዞታወችን በተመለከተ ወደ ሊዝ ስርአት ለመቀየር ህጉ ከሚከተሉት ሁኔታወች አንዱ እንዲሟላ ይጠይቃል፦
- በነባር ይዞታ ላይ ያለው ንብረት ከውርስ በስተቀር በሌላ ማናቸውም መንገድ ለሶስተኛ ወገን የተላለፈ እንደሆነ
- አግባብ ባልሆነ መንገድ ተይዘው የነበሩ ቦታወች አስተዳደሩ በሚያወጣው ደንብ መሰረት ወደ ሊዝ እንዲገቡ ሲደረግ
- ነባር ይዞታና በሊዝ የተያዘ ቦታ እንዲቀላቀል ተፈቅዶ ከሆነ ሁሉም ወደ ሊዝ ስርአት ይገባሉ
የተያዘ መሬት በማንኛዉም ምክንያት ወደ ሊዝ ስርአት ከተቀየረ ይዞታው የሊዝ መሬት የሚባል ሲሆን በአንቀጽ 16 መሰረት ባለይዞታው ከመንግስት ጋር የሊዝ ዘመኑንና የሊዝ ዋጋውን የሚያካትት የሊዝ ውል ይገባል። መሬትን በሊዝ እንዲይዝ የተፈቀደለት ሰው ስሙን፣ የመሬቱን ስፋት፣ አቅጣጫ፣ መሬቱ የሚውልበትን አላማ፣ የሊዝ ዋጋ፣ የሊዝ ዘመንና የመሳሰሉትን ያካተተ የሊዝ ይዞታ ምስክር ወረቀት ይሰጠዋል።
በሊዝ እንዲይዝ የተፈቀደለት ሰው በእያንዳንዱ ከተማ በሚወሰን የሊዝ መነሻ ዋጋ በቦታው ስፋት መጠን ተባዝቶ ይከፍላል። የሊዝ መነሻ ዋጋ ሲሰላ የመሰረተ ልማት መዘርጊያ ወጭን፣ ነባር ግንባታወች ያሉበት ቦታ ከሆነ ለነዚህ ንብረቶች ማስነሻ የወጣውን ወጭ እና ከቦታው ተነሽ ለሆኑ ሰወች የሚከፈል ካሳን እንዲሁም ሌሎች አግባብነት ያላቸውን ሁኔታወች ግምት ውስጥ ያስገባ መሆን አለበት። የሊዝ ይዞታ የተሰጠው ሰው የሚከፍለው ቅድሚያ ክፍያ ከ10% ማነስ የሌለበት ሲሆን ቀሪውን በውሉ መሰረት በተቀመጠ ረጅም የጊዜ ሰሌዳ መሰረት እንዲከፍል ይደረጋል።
በሊዝ አዋጁ መሰረት የከተማ ቦታ የሚገኝባቸው ስልቶች
ቀደም ሲል የነበሩት የከተማ ቦታ ማስተላለፊያ መንገዶች ያልተገቡና ለሙስና መንገድ ከፋች በመሆናቸዉ አሁን ባለው አሰራር ህጉ እውቅና የሰጣቸው ሁለት መሰረታዊ የማስተላለፊያ መንገዶች ጨረታ እና ምደባ ብቻ መሆናቸውን በአንቀጽ 7(2) ላይ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ እንደ መርህ ማንኛውም ለመኖሪያ፣ ለንግድም ሆነ ለሌላ ማንኛውም አላማ የሚፈለግ መሬት ከመንግስት የሚተላለፈው በጨረታ ነው፡፡ ተጫራቾች የሊዝ መነሻ ዋጋን መሰረት በማድረግ የራሳቸውን መግዣ ዋጋ የሚያቀርቡ ሲሆን በዚህ ዋጋና በቅድሚያ በሚከፍለው የገንዘብ መጠንን መሰረት በማድረግ አሸናፊው ይመረጣል፡፡ ..................
1👍1
..............#ለግልጸኝነት እንዲረዳና ካልተገባ አሰራር ነጻ ለማድረግ አዋጁ ዝርዝር የሆነ የጨራታ አካሄድንም አካቶታል።
ጨረታ የከተማ መሬት ማስተላለፊያ ሆኖ በመርህ ቢቀመጥም እንደልዩ ሁኔታ ለህብረተሰቡ ከፍተኛ ጠቀሜታ ላላቸው አካላት መሬት በምደባ ሊተላለፍ ይችላል፡፡ ምደባ የሚለውን ሀሳብ አዋጁ ሲተረጉመው በጨረታ ሊስተናገዱ ለማይችሉ ተቋማት በመሬት ላይ የመጠቀም መብት በሊዝ የሚተላለፍበት ስልት ነው ይለዋል፡፡ መሬት በምደባ ሲተላለፍ የሊዝ መነሻ ዋጋ ይከፈል አይከፈል አዋጁ ላይ አልተገለጸም፡፡ ሆኖም ግን ስለሊዝ መነሻ ዋጋ በግልጽ የተቀመጠው በአንቀጽ 12(3) ላይ ከአዲስ አበባ ውጭ የሆኑ የቀበሌ ቤት ነዋሪ የነበሩ ተነሽ በሚሆኑበት ጊዜ ምትክ ቤት መስጠት ካልተቻለ ቤት የሚሰሩበት ቦታ በምደባ ተሰጥቷቸው የሊዝ መነሻ ዋጋ መክፈል እንዳለባቸው ነው፡፡

በምደባ የከተማ ቦታ የሚሰጣቸው አካላት አንቀጽ 12 ስር ተዘርዝረዋል፡፡ እነሱም፡- ለባለበጀት የመንግስት መስሪያ ቤት ለቢሮ አገልግሎት፣ በመንግስት ወይም በበጎ አድራጎት ድርጅቶች ለሚካሄዱ ማህበራዊ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት፣ በመንግስት ለሚካሄዱ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እና ለራስ አገዝ የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታወች፣ ለእምነት ተቋማት አምልኮ መፈጸሚያ፣ ለማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪወች ልማት፣ ለኤምባሲወችና ለአለምአቀፍ ድርጅቶች አገልግሎት፣ በተለዩ ልዩ አገራዊ ፋይዳ ላላቸው ፕሮጀክቶች የሚውሉ ቦታወች ናቸው፡፡

የሊዝ መብትን ስለማስተላለፍ
ልክ እንደሌሎች የንብረት መብቶች የሊዝ መብትንም ማስተላለፍ የሚቻል ሲሆን በኢትዮጵያ ህግ ግን የተወሰኑ ገደቦች ተቀምጠውበታል፡፡ በአዋጁ አንቀጽ 24(1) ላይ የከተማ ቦታ ላይ የሊዝ ባለይዞታ የሆነ ሰው የይዞታ መብቱን ማስተላለፍ ወይም በከፈለው የሊዝ ክፍያ መጠን ልክ በዋስትና ለማስያዝ ወይም በካፒታል አስተዋጽኦነት መጠቀም እንደሚችል ተደንግጎ ይገኛል፡፡ እዚህ ላይ መረዳት የሚገባው በተከፈለው የሊዝ ክፍያ መጠን ልክ የሚለው የሚያገለግለው መብቱን በዋስትና ማስያዝ ወይም በካፒታልነት ለመጠቀም እንዲሁም በተወሰነ መልኩ ግንባታው ሳይጠናቀቅ ለሚሸጥ ግንባታ ነው፡፡

#የሊዝ ውል ምስረታና ይዘት
በአዋጁ መሰረት የከተማ መሬት በሊዝ እንዲይዝ የተፈቀደለት ማንኛውም ሰው አንቀጽ 16 እንደተመለከተው ከሚመለከተው አካል ጋር የሊዝ ውል ማድረግ አለበት፡፡ የሊዝ ውሉም ግንባታው የሚፈጸምበትን ጊዜ፣ የሚጠናቀቅበትን ጊዜ፣ የክፍያ አፈጻጸም ሁኔታ፣ የችሮታ ጊዜ፣ የውል ሰጭና ተቀባይ መብትና ግዴታ እንዲሁም ሌሎች አስፈላጊ ዝርዝር ሁኔታወችን ያካተተ መሆን አለበት፡፡ እንደውል ሁሉ በአዋጁ የተቀመጠ ልዩ ድንጋጌ ከሌለ በስተቀር በፍትሐ ብሔር ህጉ ላይ ያለው ጠቅላላ የውል ድንጋጌወች ለሊዝ ውልም ተፈጻሚ ይሆናሉ፡፡ የሊዝ ውል አካል ከሆኑት መካከል አንዱና ዋናው የሊዝ ዘመን ነው፡፡ የሊዝ ዘመን እንደከተማው የእድገት ደረጃና የልማት ስራው ዘርፍ ወይም የአገልግሎቱ አይነት የሚለያይ ሆኖ ከ15 እስከ 99 አመት ሊደርስ እንደሚችል በአዋጁ ተደንግጓል፡፡

#የሊዝ ውል መቋረጥ
#በአዋጁ አንቀጽ 25 ላይ የሊዝ ውል የሚቋረጥባቸው ሶስት ሁኔታወች ተቀምጥል እነርሱም፡-
ባለይዞታዉ በሊዝ የተለከበዉን ቦታ በሊዝ ዉሉ ላይ በተገለጸው አግባብ አለመጠቀም(ውልን አለማክበር) ፣ ለህዝብ ጥቅም ሲባል እና የሊዝ ዘመን ሲያበቃና ሳይታደስ ሲቀር ናቸዉ፡፡

https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
ጥቅምት 2002.pdf
1.5 MB
Tikimit 2002 CASSATION DECISIONS (#19) mostly unpublished
ህዳር 2002.pdf
432.7 KB
Hidar 2002 CASSATION DECISIONS (#11) mostly unpublished
ታህሳስ 2002.pdf
1.4 MB
Tahesas 2002 CASSATION DECISIONS (#29) mostly unpublished
ያለደረሰኝ ግብይት የማከናወን ወንጀል

በ:- ወንድዬ ብርሃኑ

የዚህ ጽሑፍ ዋና ዓላማ ያለደረሰኝ ግብይት የማከናወን ወንጀል ላይ መሠረታዊ የሆነ መረዳት እንዲኖር ማድረግ እና ያለደረሰኝ ግብይት ከማከናወን ወንጀል ጋር በተያያዘ እየቀረቡ ያሉ አንዳንድ ማብራሪያዎች (commentaries) ላይ የሚስተዋሉትን ግድፈቶች ማቃናት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ነው፡፡

መልካመ ንባብ!

https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/1994-offences-relating-to-invoices
July 10, 2021 | Founding General Meeting of Ethiopian Law Schools Association (ELSA)
_________________
Feteh organized a one-day general meeting to establish an association of Law Schools in Ethiopia. As founding members, representatives from 36 universities gathered together to officially establish the Ethiopian Law Schools Association (ELSA) and approve the bylaws.

During the meeting executive committees and board members have been selected. Wolaita Sodo University, Debre Brahan University, and Bule Hora University as a three executive committee and the University of Gondar, Bahir Dar University, Haramaya University, Dire-Dawa University, Arba Minch University, Jimma University, and Ambo University as seven board members were elected by voting whereas the hierarchy was arranged by the highest number of votes.

Feteh supported the development of bylaws to establish the Ethiopian Law Schools Association (ELSA). The association is expected to foster cooperation between law schools and serve as an open and independent forum for experience sharing and discussion of diverse ideas about legal education and also enhance and strengthen the role of law in the development of the country through legal education.

#FetehActivityET #USAIDETHIOPIA #Feteh #Lawschools

share share
#share #Share
#Share #Share #Share #Share

https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
👍1😁1
Format of Criminal (3).doc
256.5 KB
የወንጀል ጉዳዮችን የሚመለከቱ ፎርሞች ከወ/ቅጽ-1 እስከ ወ/ቅጽ-48
የፎርሞች ዝርዝር መግለጫ
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
Format Civil (2).doc
1.2 MB
የተለያዩ የሲቪል ቅጾች ናቸው‼️የፍትሐብሄር ጉዳዮችን የሚመለከቱ ፎርሞች ከፍት/ቅጽ-1 እስከ ፍት/ቅጽ-181
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
👍1
ካርታ ማምከን
=====================
• የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነት ማረጋገጫ ማስረጃ /ደብተር ወይም ካርታ/ በመሰረዝ ዋጋ ማሳጣት
አንድ የአስተዳደር አካል የቤት ባለቤትነት ማስረጃ በፈለገው ጊዜ ከሕግ ውጪ እንዲሰረዝ ማስቻል በኢ.ፌ.ዲ. ሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 40/1/ እና /2/ ድንጋጌ ሥር የተከበረውን የንብረት ባለቤትነት መብት ዋጋ የሚያሣጣው ነው፡፡ የፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1195 እና 1196 ድንጋጌዎች አንድ ላይ ሲነበቡም የአስተዳደር አካል በባለቤት ማረጋገጫ ማስረጃ አሰጣጥ ላይ ፍጽም የሆነ አስተዳደራዊ ስልጣን ያለው ስለመሆኑ አያሣዩም፡፡ ይልቁንም ድንጋጌዎች እርስ በእርሣቸውም ሆነ ከፍ/ሕ/ቁጥር 1198 ድንጋጌ ጋር ተዛምደው ሲታዩ የባለቤት ማረጋገጫ ደብተር የሚሰረዘው በሕጉ በተመለከቱት ምክንያቶች ብቻ መሆኑን ከሕጉ ውጪ ተግባሩ ተከናውኖ ከተገኘም መብቱ የተነካው ሠው በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 37፣78 እና 79 ድንጋጌዎች መሠረት ጉዳዩን ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት አቅርቦ አቤቱታው እንዲታይለት የሚያርግበት ጉዳይ እንጂ አስተዳደር አካሉ የሰጠው ውሣኔ በፍርድ ቤት እንዳይታይ የሚገደብበት ስርዓት የሌለ መሆኑን የምንገነዘበው ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 42501 ቅጽ 15፣ ኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ መንግስት አንቀጽ 37፣ 38፣ 79፣ ፍ/ህ/ቁ. 1195፣ 1196፣ 1198
አስተዳደራዊ ተቋማት በሕግ ተለይቶ በተሰጣቸው ጉዳይ የመወሰን ሥልጣን እንዳላቸው የታወቀ ነው፡፡ ይሁንና ለአንድ ባለ ጉዳይ የተሰጠው ካርታ የተሰጠበት እና የተሻረበት አግባብ በሕግ አግባብ መሆን ያለመሆኑን አጣርቶ የመወሰን ሥልጣን የፍርድ ቤቶች ነው፡፡ በዚህ ረገድ አንድ ፍርድ ቤት የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታን የመሰረዝ ሥልጣን የአስተዳደር ክፍል ነው፣ ፍርድ ቤት ጉዳዩን አይቶ የመወሰን ሥልጣን የለውም በማለት የሚደርስበት ድምዳሜ የጉዳዩን የክርክር ባህሪ እና ይዘት ያላገናዘበ ነው፡፡ ፍርድ ቤቶች በአስተዳደር ክፍል የተሰጠው ካርታ የተሰጠበት ወይም የተሻረበት ሥርዓት እና አስተዳደራዊ ውሳኔው ሕግና መመሪያ ያገናዘበ መሆን ያለመሆኑን በማጣራት ውሳኔ የመስጠት ሥልጣን እንዳላቸው ከፍ/ህ/ቁ. 1196 እና በህገ መንግስቱ ስለ ንብረት መብት ከአደረገው ድንጋጌና በፍርድ የሚያልቁ ጉዳዮችን በተመለከተ በህገ መንግስቱ አንቀጽ 37 ከተመለከቱት ድንጋጌዎች ይዘት የምንረዳው ጉዳይ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ 99071 ቅጽ 18፣ ኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ መንግስት አንቀጽ 37፣ ፍ/ህ/ቁ. 1196
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
👍1
የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ ኤጀንሲ የሽያጭና የስጦታ ማረጋገጥ አገልግሎትን አቋረጠ፡፡

የፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ የማይንቀሳቀስ ንብረትን በተመለከተ ሽያጭና ስጦታን የሚመለከቱ አገልግሎቶችን በጊዜያዊነት አገልግሎት መስጠት ማቋረጡን አስታውቋል፡፡

የፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ የአዲስ አበባ የውክልና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያለውን አሰራር ለማሻሻል እና ዘመናዊ ለማድረግ፣ ተቋሙ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን በተመለከተ የሽያጭና ስጦታን አገልግሎት ለተወሰነ ጊዜ ማቋረጡን ተከትሎ አገልግሎቱ የተቋጠበትን ምክንያት በተመለከተ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኤጀንሲውን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን አማረን ስለጉዳዩ ጠይቋል፡፡

አቶ ሙሉቀን እንደነገሩን በተቋሙ የሚሰጡ አገልግሎቶችን በጋራ ለማቀናጀትና የዳታ ሲስተሙን በተሻለ መልኩ አንድ ላይ ለማጣመር የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ በመሆኑ አገልግሎቱን ለማቋረጥ እንዳስፈለገ ነግረውናል፡፡

የዳታ ሲስተሙን ለማዘመን የሚረዱ የማሻሻያ ስራዎችን እየተሰሩ መሆናቸውን ያነሱልን አቶ ሙሉቀን በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ አገልግሎቱን በድጋሚ በተሻለ ፍጥነትና ጥራት ለማስጀመር ጥረት እንደሚደረግ ነግረውናል፡፡

የውልሰው ገዝሙ
ሐምሌ 09 ቀን 2013 ዓ.ም
share share
#share #Share
#Share #Share #Share #Share

https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
e188b0e18a94_2013_e18b93_e1889d_e18aa0e18bb2e188b5_e18aa5e18a93.pdf
3.1 MB
አዲሱ ያገለገሉ እና አዲስ መኪናዎች ቀረጥ
Forwarded from Weye
Selam ale peace nw🙌
I need 2009, 2010 &2012 exit exam please

Hawassa University
ያለደረሰኝ ግብይት የማከናወን ወንጀል

በ:- ወንድዬ ብርሃኑ

የዚህ ጽሑፍ ዋና ዓላማ ያለደረሰኝ ግብይት የማከናወን ወንጀል ላይ መሠረታዊ የሆነ መረዳት እንዲኖር ማድረግ እና ያለደረሰኝ ግብይት ከማከናወን ወንጀል ጋር በተያያዘ እየቀረቡ ያሉ አንዳንድ ማብራሪያዎች (commentaries) ላይ የሚስተዋሉትን ግድፈቶች ማቃናት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ነው፡፡

መልካመ ንባብ!

https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/1994-offences-relating-to-invoices
Live stream scheduled for
የብድር ውል ‼️
(የፍትሐብሔር ሕግ ከቁጥር 2471-2489)
የብድር ውል ምንነት፡- የተለያዩ ፅሑፎች እንደሚያስረዱት ብድርን በተመለከተ ሁሉንም ሊያግባባ የሚችል አንድ ወጥ የሆነ ትርጉም አናገኝለትም፡፡ የፍትሐብሔር ሕጋችን የሚከተለውን ትርጉም ሰጥቶታል፡- “የሚያልቅ ነገር ብድር ማለት ከተዋዋዮቹ አንዱ ወገን አበዳሪው ሌላውን ተበዳሪ ሰው የተበደረውን ነገር በዓይነቱ ለመመለስ ተገዳጅ በማደረግ ገንዘብ ወይም በማገልገል የሚያልቅ ሌላ ነገር ለተበዳሪው ለመስጠትና ሀብትነቱን ለማስተላለፍ የሚገደድበት ውል ነው” ይላል፡፡ ከዚህ ትርጓሜ መረዳት እንደሚቻለው ብድርን በሚመለከት ሕጉ በሚያልቅ ነገር ላይ ብቻ እንጂ ከዛ ባለፈ ማለትም በማያልቅ ነገር ወይም ቋሚ የሆነ ንብረትን የማያካትት መሆኑን ነው፡፡ የድንጋጌውን አጠቃላይ ይዘት ስናይ አመላለሱ በዓይነት ወይም በአገልግሎት ሊሆን እንደሚችል እና ውሉ አስገዳጅ መሆኑንም ያሳያል፡፡
የዉል አመሠራረት፡- የብድር ውል የውል አንድ አካል እንደመሆኑ መጠን አመሰራረቱም ሆነ አፈፃፀሙ በጠቅላላው የውል ሕግ መርሆች የሚገዛ በመሆኑ የብድር ውልን ዝርዝር ድንጋጌዎች ከማየታችን በፊት ስለውል አመሰራረት ባጭሩ አይተን ብናልፍ የተሻለ ግንዘቤን ይፈጥራል፡፡ ዉል ስምምነት ቢሆንም ከሌሎች ስምምነቶች የሚለየዉ በአፈፃፀሙ ከበስተጀርባዉ የሕግ ድጋፍ ያለዉ ስምምነት መሆኑ ላይ ነዉ፡፡

አንድ ውል የሚፀና ውል ነው ለማለት የሚከተሉትን መርሆች ማሟላት አለበት፡- 1ኛ ዉል የሚፈፀመዉ ለመዋዋል ችሎታ ባላቸዉ ሰዎች መካከል ብቻ መሆኑ (እድሜዉ ለአቅመ አዳም/ሄዋን ያልደረሰ ወይም አይምሮዉ ህመም ያለበት ሰዉ ወይም በፍርድ ቤት የተከለከለ ሰዉ ችሎታ እንደሌለዉ ይቆጠራል፡፡) 2ኛ ዉል የሚደረገው በተወያያቹ ነፃ ፍቃድ ብቻ የሚደረግ መሆኑ፡፡ 3ኛ ተወያይ ወገኖች የሚዋዋሉበት ጉዳይ በእርግጠኝነት የሚቻል እና ህጋዊና ሞራላዊ ጉዳይ ላይ መሆን የሚገባው መሆኑ፡፡ 4ኛ የዉል አቀራረጹ ወይም አፃፃፉ (ፎርም) በህግ ተለይተዉ የተቀመጡ ወይም ተዋዋይ ወገኖች ተለይቶ እንዲቀመጥ ከተስማሙበት የዉል ጉዳይ በቀር የተለየ የዉል ፎርም አያስፈልግም፡፡

የአበዳሪና ተበዳሪ ግዴታዎች፡- አበዳሪና ተበዳሪ የራሳቸው የሆኑ ሊያከብሯቸው የሚገቡ ግዴታዎች አሉባቸው፡፡ በቅድሚያ የአበዳሪው ግዴታዎችን ስናይ ሕጉ የአበዳሪውን ግዴታዎች በተመለከተ የሽያጭ ውልን በሚደነግገው ክፍል ላይ የሻጩ ግዴታዎች ተብለው የተገለፁት ደንቦች በአበዳሪ ላይ ተግባራዊ ይሆናሉ ይላል፡፡ በፍትሐብሔር ሕጉ የሻጭ ግዴታዎች ናቸው የተባሉት ደግሞ የሚከተሉት ናቸው፡፡
1ኛ ዕቃ የማስረከብ ግዴታ፡- የሽያጭ ውል ከተከናወነ በኋላ ሻጭ የግብይት ምክንያት የሆንውን ዕቃ/ንብረት ለገዥ የማስረከብ ግዴታ አለበት፡፡ 2ኛ ስመ-ሀብት የማስተላለፍ ግዴታ፡- ከላይ ለማንሳት እንደተሞከረው የሽያጭ ውል ልዩ መገልጫ ከሆኑት ጉዳዮች ውስጥ ሻጩ የሽጭ ምክንያት የሆነውን ንብረት ስመ-ሀብትን የማስተላለፍ ግዴታ ያለበት መሆኑ ነው፡፡ የባለቤትነት መብት መተላለፍን በተመለከተ የብድር ውል ከሽያጭ ውል ለየት የሚያደርገው ነገር ቢኖር የብድር ውሉ በትርጉም ክፍሉ ላይ እንደሰፈረው አላቂ ዕቃን ብቻ የሚመለከት በመሆኑ ዕቃውን ለተበዳሪው በሚያስረክብበት ወቅት የባለቤትነት መብትም አብሮ መተላለፍ መቻሉ ነው፡፡ 3ኛ ዋስትና የመስጠት ግዴታ፡- ሌላኛው የሻጭ ግዴታ ከተሸጠው ዕቃ ጋር በተገናኘ ለሚፈጠሩ ችግሮች ለገዥው ዋስትና የመስጠት ግዴታ ነው፡፡

የተበዳሪውን ግዴታዎች በተመለከተ ሙሉ ለሙሉ በሚባል ሁኔታ ዕዳውን መልሶ ከመክፈል ጋር የሚገናኝ ነው፡፡ ተበዳሪ የብድር ውል ውስጥ ሲገባ የተበደረውን ነገር በዓይነቱ ለመመለስ ወይም በገንዘብ የሚመለስ ሲሆን እነዚህን በወቅቱ የመመለስ ግዴታ አለበት፡፡ የብድሩ አመላለስ በማገልገል የሚያልቅ ሲሆን ደግሞ ለአበዳሪው ተገቢውን)
የብድር ማስረጃ፡- ማስረጃ ማለት አንድ በፍርድ ቤት ምርመራ ላይ ያለ በጭብጥ የተያዘ አከራካሪ ጉዳይ እውነት መሆንና አለመሆኑን በሚያሳምን ሁኔታ ማረጋገጥ እንዲያስችል በግብአት የሚቀርብ ፍሬ ነገር ስለመሆኑ ብ/ጀነራል ታጠቅ ታደሰ “የማስረጃ ሕግ መሰረተ ሀሳቦች” በሚለው መፅሐፋቸው ገልፀውታል፡፡ ማስረጃ ማለት ይህ ከሆነ በሁለት ሰዎች መካከል የብድር ውል ተደርጓል ወይስ አልተደረገም የሚለውን ጥያቄ በምን ማረጋገጥ እንችላለን? የሚለውን መሰረታዊ ጥያቄ ቀጥለን እናያለን፡፡ የፍ/ሕጋችን በአን. 2472 ስር የብድር ማስረጃ በሚል ርእስ የሚከተለውን ደንግጓል፡-
(1) በብድር የተሰጠው ገንዘብ ከብር 500 በላይ ሲሆን የብድሩን ውል በፅሑፍ ወይም በፍርድ ቤት በተደረገ የእምነት ቃል ወይም መሐላ ካልሆነ በስተቀር ለማስረዳት አይቻልም፡፡
(2) ለብድር ውል ማናቸውም ሌላ ዓይነት ማስረጃ ለማቅረብ አይቻልም ፡፡ (3) እንዲሁም ከብር 500 የበለጠ ገንዘብ የመክፈል ነገር በዚህ ዓይነት ይፈፀማል፡፡ በዚህም መሰረት የብድሩ መጠን ብር 500 እና ከዛ በታች ከሆነ በማንኛውም ዓይነት ማስረጃ ለምሳሌ በቦታው የነበረ የሰው ምስክር በመስማት ማረጋገጥ የሚቻል መሆኑን እና መጠኑ ከዛ በላይ ከሆነ ግን ከሦስቱ የማስጃ ዓይነቶች መካከል በአንዱ ካልሆነ በስተቀር በሌላ በምንም መንገድ ማረጋገጥ የመማይቻል መሆኑን ነው መረዳት የሚቻለው፡፡ እነዚህን ሦስት የማስረጃ ዓይነቶች ቀጥለን እንመልከት፡፡
የመጀመሪያውና የበለጠ አስተማማኝ የሆነው ማስረጃ የፅሑፍ ማስረጃ ነው፡፡ ይህም ማለት ገና ከጅምሩ የብድር ውሉ ሲደረግ በፅሑፍ የተደረገ ሲሆን ያንን ፅሑፍ ለፍርድ ቤት በማቅረብ ማስረዳት ይቻላል፡፡ በሌላ አነጋገር ከብር 500 በላይ የሆነ የብድር ውል በፅሑፍ እንዲሆን ሕጉ አስገዳጅ የሚመስል ድንጋጌ ያስቀመጠ በመሆኑ ከላይ ካነሳነው የውል አመሰራረት መርሆች መካከል የተለየ ፎርም የሚፈልግ መሆኑን ማየት ይቻላል፡፡ ሁለተኛው የማረጋገጫ መንገድ በፍርድ ቤት በተደረገ የእምነት ቃል ነው፡፡ ይህም ማለት ተበዳሪው በፍርድ ቤት ቀርቦ በከሳሹ የቀረበበትን ክስ ማለትም ከከሳሹ ገንዘብ የተበደረ መሆኑን፣ መጠኑ ምን ያክል እንደሆነ በማያሻማ መንገድ ካመነ በቀላሉ የብድሩ መኖር የሚረጋገጥ ይሆናል፡፡ ሦስተኛውና የመጨረሻው የማረጋገጫ መንገድ በመሐላ የማረጋገጥ ሂደት ነው፡፡ መሐላ ማለት በክርክር ወቅት አንድ ተከራካሪ ወገን በሚያቀርበው ማስረጃ ወይም በሚናገረው ፍሬ ነገር እውነትነትን ለማረጋገጥ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀ ቅፅ ላይ የሚሰጡት ማረጋገጫ ነው፡፡

የብድር መመለሻ ጊዜ፡- ብድር ውል እንደመሆኑ መጠን ለተዋዋይ ወገኖች ሰፊ ነፃነት መሰጠት አለበት፡፡ በመሆኑም ሕጉ ስለብድር መመለሻ ጊዜ በተዋዋይ ወገኖች የተወሰነ ጊዜ በሚኖርበት ወቅት ይህንኑ ዕውቅና በመስጠት ክፍያው በዛ ጊዜ መሆን እንደሚገባው ሕጉ አፅንኦት ሰጥቶበታል፡፡ ከዚህም ባለፈ ብድሩ ወለድ የሌለበት ከሆነ የተበደረውን ገንዘብ ለመመለስ ማሰቡን ለአበዳሪው ከአንድ ወር በፊት አስታውቆ የመመለሻ ጊዜው ከመድረሱ በፊት ሊመልስለት እንደሚችልም ሕጉ ይደነግጋል፡፡ የብድሩ መመለሻ ጊዜ በተዋዋይ ወገኖች ያልተወሰ በሚሆን ጊዜ ሕጉ ብድሩ በምን ያክል ጊዜ ውስጥ ሊከፈል እንደሚገባው ደንግጓል፡፡ ይኼውም አበዳሪው መልስልኝ ሲል ከጠየቀበት ቀን አንስቶ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ መመለስ እንዳለበት ተደንግጓል፡፡.........