📌 #የከተማ መሬትና ቤት ይዞታ ስመ-ንብረት ዝውውር እንዴት ይፈፀማል ❓
በስመ ንብረት ዝውውር ወቅት መሟላት ያለባቸው መረጃዎች የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀፅ 33 ንዑስ አንቀፅ 2 አንፃር ሲታይ
🛑 1.1. የከተማ ቤትና ይዞታ ስመ-ንብረት ዝውውር ስለመፈጸም የሚከተሉት ማስረጃዎች/ሰነዶች ሲሟሉ የስመ ንብረት ዝውውር የሚፈጸም ይሆናል፤ 👇
1) ህጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት/ካርታ፣
2) ጸድቆ የተሰጠ የግንባታ ፕላን፣ የስራ ዝርዝር ግምት ወይም የጸደቀ የነባር ግንባታ ፕላን፣
3) ጸድቆ በተሰጠው የግንባታ ፕላን መሰረት ስለመገንባቱ እና ግንባታው ያለበት ደረጃ የተረጋገጠበት ማስረጃ/50% እና በላይ/፤
4) ውዝፍ የሊዝ/ኪራይ ዕዳ የሌለበት ስለመሆኑ የተሰጠ የማረጋገጫ ደብዳቤ ወይም ቀሪ የሊዝ ክፍያ ዕዳውን ገዥው ለመክፈል በፊርማ ያረጋገጠበት የስምምነት ደብዳቤ ፣
5) በንብረቱ ላይ የባንክ እዳ/የፍ/ቤት ዕግድ የሌለበት ስለመሆኑ ማረጋገጫ ሲቀርብ፣
6) የቤትና ይዞታ ስም ዝውውር ጥያቄው የቀረበው በህግ ባለመብት/በውርስ/በፍርድ አፈጻጸም ወይም በውክልና ከሆነ ይህንኑ የሚገልጽ ማስረጃ፤
7) በግለሰቦች ግዥና ሽያጭ ወይም ስጦታ ስምምነት ከሆነ በዉልና ማስረጃ በአካል ቀርቦ በእማኞች የተፈረመ የስምምነት የውል ማስረጃ ሲቀርብ፣
🛑 1.2. በሽያጭ/በስጦታ የሚተላለፍ ቤትና ይዞታ ስም-ዝውውር መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች፣ 👇
1) ግንባታው በዋስትና ያልተያዘ እንዲሁም እዳ የሌለበት መሆኑ ሲረጋገጥ ወይም እዳው በሚመለከተው አካል በደብዳቤ መነሳቱ ሲረጋገጥ፣
2) የቤትና ይዞታ ሽያጭ ወይም የስጦታ ውሉ በምስክሮች ሲረጋገጥና በፍትህ ወይም በመሪ ማዘጋጃ ቤት ፊት ቀርቦ ሲጸድቅ፣
3) ግንባታው ጸድቆ በተሰጠው ዲዛይን መሰረት 50 በመቶና በላይ የተሰራ መሆኑ በባለሙያ ተረጋግጦ ሲቀርብ፣
4) በይዞታው ላይ ውዝፍ የቦታ ኪራይ የሌለበት ስለመሆኑ ወይም ውዝፍ የቦታ ኪራይ ክፍያ አጠናቆ የከፈለ ስለመሆኑ የቀረበ ክፍያ ደረሰኝ ማረጃ ሲቀርብ፣
5) የአገልግሎትና የገቢዎች ክፍያ በቤቱ ግምት መሰረት ስለመከፈሉ ሲረጋገጥ፣
🛑 #ዝውውሩ የሚፈፀመው #በሊዝ በተገኘ ይዞታና ግንባታ ላይ ከሆነ
1) የሊዝ ይዞታ ባለቤትነት ኦሪጅናል ካርታና ውል ሲቀርብ፣
2) በሊዝ ውል መሰረት ክፍያው የተጠናቀቀና ሌሎች ግዴታዎቹን የተወጣ መሆኑ ሲረጋገጥ ወይም የሊዝ እዳው ያልተጠናቀቀ ከሆነ ስም የሚዞርለት ወገን እዳውን ለመክፈል እና ነባሩን የሊዝ ውል ግዴታዎች የተቀበለ ስለመሆኑ ከከተማው በጽሁፍና በፊርማ አረጋግጦ ሲያቀርብ፣
3) በሊዝ የተገዛን የመሬት ይዞታ ለሌላ ሰው ለማስተላለፍ በቅድሚያ በገባው የሊዝ ውል መሰረት በተቀመጠው የጊዜ ገደብ የሚፈለገውን የግንባታ ደረጃ ያሟላ መሆኑ ወይም የግንባታ ፈቃድ የጊዜ ገደብ ያላለፈ ወይም የግንባታ ማራዘሚያ የተፈቀደለት መሆኑ ሲረጋጥ፣
4) የከተማ ቤትና ይዞታ ሽያጭ ወይም የስጦታ ውሉ በምስክሮች ሲረጋጥና በዉልና ማስረጃ ቀርቦ ሲጸድቅ ይሆናል፡፡
🛑 1.3. በውርስ የተገኘ ይዞታና ቤት የባለቤትነት ስመ-ንብረት ዝውውር አፈፃፀም፣
(ሀ) በውርስ የተላለፈ #ነባር_ይዞታ ዝውውር ለመፈፀም መሟላት ያለባቸው፡-
1) የሚዛወረው የመሬት ይዞታ ወይም ቤት ህጋ የባለቤትነት ማስረጃ/ካርታ ሲኖረው፣
2) ወራሾች የውርስ ባለመብትነትን የሚያረጋግጥ የፍርድ ቤት ውሳኔ ማስረጃ ሲያቀርቡ፣
3) ወራሾች በውርስ ያገኙትን ይዞታ ወይም ቤት በየግላቸው የባለቤትነት ማስረጃ ለመያዝ ሲፈልጉ ለእያንዳንዳቸው ድርሻ መጠን በፍ/ቤት የፀደቀ ማስረጃ ሲያቀርቡ ወይም የሁሉም ወራሾች የጋራ ስምምነት በውል አፅዳቂ አካል ጸድቆ ሲቀርብ፣
4) የእያንዳንዱ ወራሽ የድርሻ መጠን በፍርድ ቤት ያልተረጋገጠ ከሆነ የስም ዝውውሩ በሁሉም ወራሾች ስም በጋራ የሚፈፀም ይሆናል፡፡
የፍርድ ቤቱ የውርሱ ውሳኔ የይዞታ ክፍፍልን የሚያስከትል ሆኖ ሲገኝ የሚፈፀመው የወቅቱን አነስተኛ የይዞታ መጠን መስፈርት የሚያሟላ ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ይህ ካልሆነም በተነፃፃሪ የመሬት ይዞታ ድርሻ ህግ ወይም በጋራ ሰነድ/ካርታ መሰረት ይስተናገዳል፡፡
ይዞታው በውሉ መሰረት ግንባታ ለመጀመር የተሰጠውን የጊዜ ገደብ ያለፈበት እና ግንባታው ያልተጀመረ ከሆነ በውርስ ሊተላለፍ አይችልም፡፡
(ለ) #በሊዝ የተያዘ ይዞታ ለህጋዊ ወራሽ የሚተላለፈውና ዝውውር የሚፈፀመው፡-
1) አውራሹ በገባው የሊዝ ውል ግዴታ መሰረት አመታዊውን የሊዝ ክፍያ የፈፀመና ሌሎች የሊዝ ግዴታችን በተገቢው መንገድ የተወጣ ሲሆን፣
2) ወራሽ አውራሽ የገባቸውን የውል ስምምነቶች(የሊዝ መብት፣ክልከላና ኃላፊነት) ሙሉ በሙሉ የተቀበለ መሆኑን በፊርማው ሲያረጋግጥና ውዝፍ ክፍያ ካለ ከፍሎ ደረሰኝ ሲያቀርብ ይሆናል፡፡
3) በሊዝ ውሉ መሰረት አውራሹ በህይወት እያለ ለግንበታ መጀመሪያ የተሰጠው የጊዜ ገደብ ካለፈና ግንባታ ካልጀመረ ውሉ ተቋርጦ ቦታው ለከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት ተመላሽ ይሆናል፡፡
አውራሽ በይዞታው ላይ ግንባታ ያልጀመረው ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት መሆኑ ከተረጋጠ አውራሽ በህይወት ቢኖር ኖሮ በመመሪያው መሰረት ሊፈቀድለት የሚችለው የግንባታ መጀመሪያ የማራዘሚያ ጊዜ ለወራሽ ሊፈቀድለት ይችላል፡፡
🛑 1.4. በባንክ ሃራጅ የሚሸጥ እና የሚወረስ ቤት የባለቤትነት ስም ዝውውር
1) በባንክ የተሸጠ ቤት የባለቤትነት ስም ዝውውር ለመፈፀም በሐራጅ ጨረታው አሸናፊ የሆነው ሰው ያሸነፈበትን ዋጋና ለዝውውሩ በውል የገባቸው ግዴታዎች ተገልፀው ከባንኩ የተፃፈ ህጋዊ ደብዳቤና ውል ሲቀርብ፣
2) በባንክ ዋስትና ተይዞ የነበረው ይዞታ የባለቤትነት ማረጃ/ካርታ በማህደሩ ውስጥ ካለው ሰነድ ጋር ተገናዝቦ ትክክለኛነቱ ሲረጋገጥ፣
3) ይዞታው በሌላ ባንክ ብድርና ዋስትና ያልተያዘ ወይም እገዳ የሌለበት መሆኑ ሲረጋገጥ፣
4) በሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃ ዋስትና የተመዘገበ ዋስትና ያለው ባንክ መኖሩ ከተረጋገጠ ባንኩ ስለ ይዞታው መሸጥ ሲፈቅድ፣
5) በባንክ ሃራጅ ሽያጭ እንዲዞር የተጠየቀው ቤትና ይዞታ የተሟላ ሰነድ የሌለው/ሰነድ አልባ ከሆነ በቅድሚያ በሥራ ላይ ባለው የሰነድ አልባ መመሪያ መሰረት ሰነድ ተሰጥቶት ሲቀርብ፣
6) ባንኩ ንብረቱን ባለበት ሁኔታ የሚረከብ ከሆነ የቤቱና ይዞታው ግምት እንደማንኛውም ቋሚ ንብረት ግምት ተሰልቶ ተገቢውን የአገልግሎትና የገቢ ክፍያ ሲፈጸም፣
7) ቤቱና ይዞታው ባንኩ በሚያወጣው ጨረታ የሚሸጥ ከሆነ ባንኩ ያቀረበው የጨረታ መነሻ ዋጋ በከተማው በኩል ተገቢ መሆኑ ተረጋግጦ በጨረታ ሲሸጥ እና የስም ማዛወሪያ ክፍያዎችን ስለመፈጸሙ የክፍያ ደረሰኝ ማስረጃ ሲያቀርብ የሥመ-ንብረት ዝውውሩ የሚፈጸም ይሆናል፣
በሳሙኤል ግርማ
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
በስመ ንብረት ዝውውር ወቅት መሟላት ያለባቸው መረጃዎች የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀፅ 33 ንዑስ አንቀፅ 2 አንፃር ሲታይ
🛑 1.1. የከተማ ቤትና ይዞታ ስመ-ንብረት ዝውውር ስለመፈጸም የሚከተሉት ማስረጃዎች/ሰነዶች ሲሟሉ የስመ ንብረት ዝውውር የሚፈጸም ይሆናል፤ 👇
1) ህጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት/ካርታ፣
2) ጸድቆ የተሰጠ የግንባታ ፕላን፣ የስራ ዝርዝር ግምት ወይም የጸደቀ የነባር ግንባታ ፕላን፣
3) ጸድቆ በተሰጠው የግንባታ ፕላን መሰረት ስለመገንባቱ እና ግንባታው ያለበት ደረጃ የተረጋገጠበት ማስረጃ/50% እና በላይ/፤
4) ውዝፍ የሊዝ/ኪራይ ዕዳ የሌለበት ስለመሆኑ የተሰጠ የማረጋገጫ ደብዳቤ ወይም ቀሪ የሊዝ ክፍያ ዕዳውን ገዥው ለመክፈል በፊርማ ያረጋገጠበት የስምምነት ደብዳቤ ፣
5) በንብረቱ ላይ የባንክ እዳ/የፍ/ቤት ዕግድ የሌለበት ስለመሆኑ ማረጋገጫ ሲቀርብ፣
6) የቤትና ይዞታ ስም ዝውውር ጥያቄው የቀረበው በህግ ባለመብት/በውርስ/በፍርድ አፈጻጸም ወይም በውክልና ከሆነ ይህንኑ የሚገልጽ ማስረጃ፤
7) በግለሰቦች ግዥና ሽያጭ ወይም ስጦታ ስምምነት ከሆነ በዉልና ማስረጃ በአካል ቀርቦ በእማኞች የተፈረመ የስምምነት የውል ማስረጃ ሲቀርብ፣
🛑 1.2. በሽያጭ/በስጦታ የሚተላለፍ ቤትና ይዞታ ስም-ዝውውር መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች፣ 👇
1) ግንባታው በዋስትና ያልተያዘ እንዲሁም እዳ የሌለበት መሆኑ ሲረጋገጥ ወይም እዳው በሚመለከተው አካል በደብዳቤ መነሳቱ ሲረጋገጥ፣
2) የቤትና ይዞታ ሽያጭ ወይም የስጦታ ውሉ በምስክሮች ሲረጋገጥና በፍትህ ወይም በመሪ ማዘጋጃ ቤት ፊት ቀርቦ ሲጸድቅ፣
3) ግንባታው ጸድቆ በተሰጠው ዲዛይን መሰረት 50 በመቶና በላይ የተሰራ መሆኑ በባለሙያ ተረጋግጦ ሲቀርብ፣
4) በይዞታው ላይ ውዝፍ የቦታ ኪራይ የሌለበት ስለመሆኑ ወይም ውዝፍ የቦታ ኪራይ ክፍያ አጠናቆ የከፈለ ስለመሆኑ የቀረበ ክፍያ ደረሰኝ ማረጃ ሲቀርብ፣
5) የአገልግሎትና የገቢዎች ክፍያ በቤቱ ግምት መሰረት ስለመከፈሉ ሲረጋገጥ፣
🛑 #ዝውውሩ የሚፈፀመው #በሊዝ በተገኘ ይዞታና ግንባታ ላይ ከሆነ
1) የሊዝ ይዞታ ባለቤትነት ኦሪጅናል ካርታና ውል ሲቀርብ፣
2) በሊዝ ውል መሰረት ክፍያው የተጠናቀቀና ሌሎች ግዴታዎቹን የተወጣ መሆኑ ሲረጋገጥ ወይም የሊዝ እዳው ያልተጠናቀቀ ከሆነ ስም የሚዞርለት ወገን እዳውን ለመክፈል እና ነባሩን የሊዝ ውል ግዴታዎች የተቀበለ ስለመሆኑ ከከተማው በጽሁፍና በፊርማ አረጋግጦ ሲያቀርብ፣
3) በሊዝ የተገዛን የመሬት ይዞታ ለሌላ ሰው ለማስተላለፍ በቅድሚያ በገባው የሊዝ ውል መሰረት በተቀመጠው የጊዜ ገደብ የሚፈለገውን የግንባታ ደረጃ ያሟላ መሆኑ ወይም የግንባታ ፈቃድ የጊዜ ገደብ ያላለፈ ወይም የግንባታ ማራዘሚያ የተፈቀደለት መሆኑ ሲረጋጥ፣
4) የከተማ ቤትና ይዞታ ሽያጭ ወይም የስጦታ ውሉ በምስክሮች ሲረጋጥና በዉልና ማስረጃ ቀርቦ ሲጸድቅ ይሆናል፡፡
🛑 1.3. በውርስ የተገኘ ይዞታና ቤት የባለቤትነት ስመ-ንብረት ዝውውር አፈፃፀም፣
(ሀ) በውርስ የተላለፈ #ነባር_ይዞታ ዝውውር ለመፈፀም መሟላት ያለባቸው፡-
1) የሚዛወረው የመሬት ይዞታ ወይም ቤት ህጋ የባለቤትነት ማስረጃ/ካርታ ሲኖረው፣
2) ወራሾች የውርስ ባለመብትነትን የሚያረጋግጥ የፍርድ ቤት ውሳኔ ማስረጃ ሲያቀርቡ፣
3) ወራሾች በውርስ ያገኙትን ይዞታ ወይም ቤት በየግላቸው የባለቤትነት ማስረጃ ለመያዝ ሲፈልጉ ለእያንዳንዳቸው ድርሻ መጠን በፍ/ቤት የፀደቀ ማስረጃ ሲያቀርቡ ወይም የሁሉም ወራሾች የጋራ ስምምነት በውል አፅዳቂ አካል ጸድቆ ሲቀርብ፣
4) የእያንዳንዱ ወራሽ የድርሻ መጠን በፍርድ ቤት ያልተረጋገጠ ከሆነ የስም ዝውውሩ በሁሉም ወራሾች ስም በጋራ የሚፈፀም ይሆናል፡፡
የፍርድ ቤቱ የውርሱ ውሳኔ የይዞታ ክፍፍልን የሚያስከትል ሆኖ ሲገኝ የሚፈፀመው የወቅቱን አነስተኛ የይዞታ መጠን መስፈርት የሚያሟላ ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ይህ ካልሆነም በተነፃፃሪ የመሬት ይዞታ ድርሻ ህግ ወይም በጋራ ሰነድ/ካርታ መሰረት ይስተናገዳል፡፡
ይዞታው በውሉ መሰረት ግንባታ ለመጀመር የተሰጠውን የጊዜ ገደብ ያለፈበት እና ግንባታው ያልተጀመረ ከሆነ በውርስ ሊተላለፍ አይችልም፡፡
(ለ) #በሊዝ የተያዘ ይዞታ ለህጋዊ ወራሽ የሚተላለፈውና ዝውውር የሚፈፀመው፡-
1) አውራሹ በገባው የሊዝ ውል ግዴታ መሰረት አመታዊውን የሊዝ ክፍያ የፈፀመና ሌሎች የሊዝ ግዴታችን በተገቢው መንገድ የተወጣ ሲሆን፣
2) ወራሽ አውራሽ የገባቸውን የውል ስምምነቶች(የሊዝ መብት፣ክልከላና ኃላፊነት) ሙሉ በሙሉ የተቀበለ መሆኑን በፊርማው ሲያረጋግጥና ውዝፍ ክፍያ ካለ ከፍሎ ደረሰኝ ሲያቀርብ ይሆናል፡፡
3) በሊዝ ውሉ መሰረት አውራሹ በህይወት እያለ ለግንበታ መጀመሪያ የተሰጠው የጊዜ ገደብ ካለፈና ግንባታ ካልጀመረ ውሉ ተቋርጦ ቦታው ለከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት ተመላሽ ይሆናል፡፡
አውራሽ በይዞታው ላይ ግንባታ ያልጀመረው ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት መሆኑ ከተረጋጠ አውራሽ በህይወት ቢኖር ኖሮ በመመሪያው መሰረት ሊፈቀድለት የሚችለው የግንባታ መጀመሪያ የማራዘሚያ ጊዜ ለወራሽ ሊፈቀድለት ይችላል፡፡
🛑 1.4. በባንክ ሃራጅ የሚሸጥ እና የሚወረስ ቤት የባለቤትነት ስም ዝውውር
1) በባንክ የተሸጠ ቤት የባለቤትነት ስም ዝውውር ለመፈፀም በሐራጅ ጨረታው አሸናፊ የሆነው ሰው ያሸነፈበትን ዋጋና ለዝውውሩ በውል የገባቸው ግዴታዎች ተገልፀው ከባንኩ የተፃፈ ህጋዊ ደብዳቤና ውል ሲቀርብ፣
2) በባንክ ዋስትና ተይዞ የነበረው ይዞታ የባለቤትነት ማረጃ/ካርታ በማህደሩ ውስጥ ካለው ሰነድ ጋር ተገናዝቦ ትክክለኛነቱ ሲረጋገጥ፣
3) ይዞታው በሌላ ባንክ ብድርና ዋስትና ያልተያዘ ወይም እገዳ የሌለበት መሆኑ ሲረጋገጥ፣
4) በሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃ ዋስትና የተመዘገበ ዋስትና ያለው ባንክ መኖሩ ከተረጋገጠ ባንኩ ስለ ይዞታው መሸጥ ሲፈቅድ፣
5) በባንክ ሃራጅ ሽያጭ እንዲዞር የተጠየቀው ቤትና ይዞታ የተሟላ ሰነድ የሌለው/ሰነድ አልባ ከሆነ በቅድሚያ በሥራ ላይ ባለው የሰነድ አልባ መመሪያ መሰረት ሰነድ ተሰጥቶት ሲቀርብ፣
6) ባንኩ ንብረቱን ባለበት ሁኔታ የሚረከብ ከሆነ የቤቱና ይዞታው ግምት እንደማንኛውም ቋሚ ንብረት ግምት ተሰልቶ ተገቢውን የአገልግሎትና የገቢ ክፍያ ሲፈጸም፣
7) ቤቱና ይዞታው ባንኩ በሚያወጣው ጨረታ የሚሸጥ ከሆነ ባንኩ ያቀረበው የጨረታ መነሻ ዋጋ በከተማው በኩል ተገቢ መሆኑ ተረጋግጦ በጨረታ ሲሸጥ እና የስም ማዛወሪያ ክፍያዎችን ስለመፈጸሙ የክፍያ ደረሰኝ ማስረጃ ሲያቀርብ የሥመ-ንብረት ዝውውሩ የሚፈጸም ይሆናል፣
በሳሙኤል ግርማ
#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
#የከተማ #መሬት #የሊዝ ህግ በኢትዮጵያ
የሊዝ ምንነት
የመሬት ሊዝ ማለት የመሬቱ ባለቤት የሆነ አካል በተጻፈ ውል መሰረት የተወሰነ ብር በማስከፈል ለተወሰነ ጊዜ መሬቱን ሌላ ሰው እንዲጠቀምበት ማከራየት ነው በማለት በመዝገበ ቃላት ተተርጉሟል፡፡ በሀገራችንም አዋጅ ቁጥር 721/2004 በአንቀፅ 2(1) ላይ ሊዝ ማለት በጊዜ በተገደበ ውል መሰረት የከተማ ቦታ የመጠቀም መብት በውል የሚተላለፍበት ወይም የሚያዝበት የመሬት ይዞታ ስሪት ነው በማለት ደንግጓል፡፡ መሬቱን የተከራየው ሰው የመሬቱ ባለይዞታ ስለሆነ በውሉ ላይ በተቀመጠው ስምምነት መሰረት የኪራይ ጊዜው እስከሚያልቅ ድረስ ሙሉ መብት አለው፡፡ ማንኛውም የሊዝ ስምምነት መገኛ ምንጭ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መሬትን በነጻ ከያዘው አካል ሲሆን ይህ አካል የመሬቱ ባለቤትና ወሰን ለሌለው ጊዜ በመሬቱ ላይ መብት ያለው ነው፡፡ የከተማ መሬትን በሊዝ መያዝ አሁን አሁን በብዛት እየተተገበረ ያለ የመሬት አያያዝ መንገድ ነው፡፡
የከተማ መሬትን በሊዝ የመያዝ አላማ/አስፈላጊነት
የከተማ መሬትን በሚመለከት የሚዘረጋ የሊዝ ስርአት የሚከተሉት ጠቀሜታዎች ይኖሩታል
መሬትን በአግባቡ ለመጠቀም፡- የመሬትን ልማት ለማቀድና ለመቆጣጠር መሬትን ሙሉ ለሙሉ በግለሰቦች ቁጥጥር ስር ከማድረግ ይልቅ በህግ አግባብ በሊዝ እንዲተዳደር ማድረግ ይመከራል፡፡ የከተማ መሬት በግለሰቦች ባለቤትነት ስር በሆነበት ሀገር መሬቱ እንዲለማ ለማድረግ የሁሉንም ስምምነት ለማግኘት ብዙ ጊዜንና ገንዘብን ይጠይቃል፡፡
ኢንቨስትመንትንና ኢንቨስተሮችን ያበረታታል፡- ሌላው ጠቀሜታው ለኢንቨስትመንት ሲሆን ይኸውም የመሬቱ ዋጋ በሊዝ የሚከፈል በሆነ ጊዜ የመነሻ የመዋእለ ነዋይ ፍሰቱ አነስተኛ የሚሆን ሲሆን ይህም ለኢንቬስተሩ ተጨማሪ ካፒታል ለሌሎች ስራወች እንዲኖረው ያደርገዋል፡፡ በአንጻሩ ግን መሬቱን ለመግዛት የሚገደድ ከሆነ ሁሉንም ዋጋ መክፈል የሚኖርበት በመሆኑ ለዋናው ስራ የሚቀረው ገንዘብ አነስተኛ ወይም ምንም ሊሆን ይችላል፡፡ ይህም የሚገባውን ያህል ኢንቨስት እንዳያደርግ እንቅፋት ይሆንበታል፡፡
መልሶ የመጠየቅ እድል፡- መሬት ለሌላ አላማ በሚፈለግበት ጊዜ መሬቱ በነጻ ከያዘው ሰው ይልቅ በሊዝ መሬትን ከያዘ ሰው መልሶ መጠየቅ የተሻለ እድል አለው፡፡ በሊዝ ስርአት የተያዘን መሬት እንደገና ለመውሰድ የሚጠይቀው ዋጋ አነስተኛ ነው፡፡
የከተማ መሬት የሊዝ ህግ
1. የኢፌዴሪ ህገመንግስት
ብዙ ሀገራት ዘንድ የመሬት ባለቤትነት ህገመንግስታዊ ጉዳይ አይደለም፤ ነገር ግን በኢትዮጵያ መሬት ባለው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ምክንያት የመሬት ባለቤትነት የፖሊሲ ጉዳይ ከመሆን በላይ በህገመንግስቱ ውስጥ ተካቶ ዘላቂ ውሳኔን ያገኘ ጉዳይ ሆኗል።
በህገመንግስቱ አንቀፅ 40 መሰረት ሁሉም የከተማና የገጠር መሬት ባለቤትነት የኢትዮጵያ ህዝቦችና የመንግስት እንደሆነ ተደንግጓል። በመሆኑም ግለሰብ መሬትን መሸጥ መለወጥ አይችልም ማለት ነው። መንግስት ይህን የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ንብረት የሆነን መሬት በይዞታው ስር አድርጐ በሚያስተዳድርበትና ለልማት በዋና መሳሪታነት በሚገለገልበት ጊዜ ዜጐች በከተማ ቦታ ላይ የሚያፈሯቸዉ ንብረቶች ላይ የሚኖራቸዉ ንብረቶችን በተመለከተ ህገ-መንግስታዊ ዋስትና የተሰጠዉ ሲሆን በዚሁ አንቀፅ ላይ “ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በጉልበቱ ወይም በገንዘቡ በመሬት ላይ ለሚገነባው ቋሚ ንብረት ወይም ለሚያደርገው ቋሚ መሻሻል ሙሉ መብት አለው” በማለት ደንግጓል፡፡ ይህ መብት የመሸጥ የመለወጥ፣ የማውረስ፣ የመሬት ተጠቃሚነት ሲቋረጥ ንብረቱን የማንሳት ባለቤቱን የማዛወር ወይም የካሳ ክፍያ የመጠየቅ መብትን ያካትታል፡፡
2. የሊዝ አዋጅ
የከተማ መሬትን በሊዝ የመያዝ ስርአት በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስራ ላይ የዋለው አዋጅ ቁጥር 80/1986 ከወጣ በኋላ ነው፡፡ ይህ አዋጅም በ1994 ዓ.ም በወጣው አዋጅ ቁጥር 272/94 የተሻረ ሲሆን እንደገና ይህ አዋጅ ደግሞ በአዋጅ ቁጥር 721/2004 ተሸሯል፡፡ ስለዚህ አሁን ሰአት ማንኛውም የከተማ ሊዝ ስርአት የሚስተናገደው በዚህ አዋጅ መሰረት ነው፡፡
በአዋጁ አንቀጽ 5 መሰረት የከተማ መሬትን በሊዝ የመያዝ ስርአት ከመዘርጋቱ በፊት ከተያዙ መሬቶች በስተቀር በኢትዮጵያ የከተማ መሬት መያዝ የሚቻለው በሊዝ ስርአት ብቻ ነው ከዚህ ውጭ በሌላ መንገድ መያዝ የተከለከለ ነው። ሆኖም ግን እንደልዩ ሁኔታ የተቀመጠው በክልሎች የሚገኙ የሊዝ ስርአትን ለመፈጸም የማይችሉ ትናንሽ ከተሞች አዋጁ ተፈጻሚ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ ከአምስት አመት ላልበለጠ ጊዜ የሊዝ ስርአቱ ተፈጻሚ እንዳይሆን ማድረግ ይችላሉ።
ነባር ይዞታወችን በተመለከተ ከተማው የሊዝ ስርአቱን ከመጀመሩ በፊት በህጋዊ መንገድ የተገኘ መሬት ወይም ነባሩ መሬት ተወስዶ በምትክ በካሳነት የተሰጠ መሬት በሊዝ ውል እስካልተሰጠ ድረስ ነባር ይዞታ ተብሎ ይወሰዳል። እንደመርህ ሁሉም የከተማ መሬት በዚህ አዋጅ በተደነገገው የሊዝ ስርአት መሰረት መተዳደር እንዳለባቸው አንቀጽ 5 ላይ የተደነገገ ቢሆንም ነባር ይዞታወችን በተመለከተ ወደ ሊዝ ስርአት ለመቀየር ህጉ ከሚከተሉት ሁኔታወች አንዱ እንዲሟላ ይጠይቃል፦
- በነባር ይዞታ ላይ ያለው ንብረት ከውርስ በስተቀር በሌላ ማናቸውም መንገድ ለሶስተኛ ወገን የተላለፈ እንደሆነ
- አግባብ ባልሆነ መንገድ ተይዘው የነበሩ ቦታወች አስተዳደሩ በሚያወጣው ደንብ መሰረት ወደ ሊዝ እንዲገቡ ሲደረግ
- ነባር ይዞታና በሊዝ የተያዘ ቦታ እንዲቀላቀል ተፈቅዶ ከሆነ ሁሉም ወደ ሊዝ ስርአት ይገባሉ
የተያዘ መሬት በማንኛዉም ምክንያት ወደ ሊዝ ስርአት ከተቀየረ ይዞታው የሊዝ መሬት የሚባል ሲሆን በአንቀጽ 16 መሰረት ባለይዞታው ከመንግስት ጋር የሊዝ ዘመኑንና የሊዝ ዋጋውን የሚያካትት የሊዝ ውል ይገባል። መሬትን በሊዝ እንዲይዝ የተፈቀደለት ሰው ስሙን፣ የመሬቱን ስፋት፣ አቅጣጫ፣ መሬቱ የሚውልበትን አላማ፣ የሊዝ ዋጋ፣ የሊዝ ዘመንና የመሳሰሉትን ያካተተ የሊዝ ይዞታ ምስክር ወረቀት ይሰጠዋል።
በሊዝ እንዲይዝ የተፈቀደለት ሰው በእያንዳንዱ ከተማ በሚወሰን የሊዝ መነሻ ዋጋ በቦታው ስፋት መጠን ተባዝቶ ይከፍላል። የሊዝ መነሻ ዋጋ ሲሰላ የመሰረተ ልማት መዘርጊያ ወጭን፣ ነባር ግንባታወች ያሉበት ቦታ ከሆነ ለነዚህ ንብረቶች ማስነሻ የወጣውን ወጭ እና ከቦታው ተነሽ ለሆኑ ሰወች የሚከፈል ካሳን እንዲሁም ሌሎች አግባብነት ያላቸውን ሁኔታወች ግምት ውስጥ ያስገባ መሆን አለበት። የሊዝ ይዞታ የተሰጠው ሰው የሚከፍለው ቅድሚያ ክፍያ ከ10% ማነስ የሌለበት ሲሆን ቀሪውን በውሉ መሰረት በተቀመጠ ረጅም የጊዜ ሰሌዳ መሰረት እንዲከፍል ይደረጋል።
በሊዝ አዋጁ መሰረት የከተማ ቦታ የሚገኝባቸው ስልቶች
ቀደም ሲል የነበሩት የከተማ ቦታ ማስተላለፊያ መንገዶች ያልተገቡና ለሙስና መንገድ ከፋች በመሆናቸዉ አሁን ባለው አሰራር ህጉ እውቅና የሰጣቸው ሁለት መሰረታዊ የማስተላለፊያ መንገዶች ጨረታ እና ምደባ ብቻ መሆናቸውን በአንቀጽ 7(2) ላይ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ እንደ መርህ ማንኛውም ለመኖሪያ፣ ለንግድም ሆነ ለሌላ ማንኛውም አላማ የሚፈለግ መሬት ከመንግስት የሚተላለፈው በጨረታ ነው፡፡ ተጫራቾች የሊዝ መነሻ ዋጋን መሰረት በማድረግ የራሳቸውን መግዣ ዋጋ የሚያቀርቡ ሲሆን በዚህ ዋጋና በቅድሚያ በሚከፍለው የገንዘብ መጠንን መሰረት በማድረግ አሸናፊው ይመረጣል፡፡ ..................
የሊዝ ምንነት
የመሬት ሊዝ ማለት የመሬቱ ባለቤት የሆነ አካል በተጻፈ ውል መሰረት የተወሰነ ብር በማስከፈል ለተወሰነ ጊዜ መሬቱን ሌላ ሰው እንዲጠቀምበት ማከራየት ነው በማለት በመዝገበ ቃላት ተተርጉሟል፡፡ በሀገራችንም አዋጅ ቁጥር 721/2004 በአንቀፅ 2(1) ላይ ሊዝ ማለት በጊዜ በተገደበ ውል መሰረት የከተማ ቦታ የመጠቀም መብት በውል የሚተላለፍበት ወይም የሚያዝበት የመሬት ይዞታ ስሪት ነው በማለት ደንግጓል፡፡ መሬቱን የተከራየው ሰው የመሬቱ ባለይዞታ ስለሆነ በውሉ ላይ በተቀመጠው ስምምነት መሰረት የኪራይ ጊዜው እስከሚያልቅ ድረስ ሙሉ መብት አለው፡፡ ማንኛውም የሊዝ ስምምነት መገኛ ምንጭ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መሬትን በነጻ ከያዘው አካል ሲሆን ይህ አካል የመሬቱ ባለቤትና ወሰን ለሌለው ጊዜ በመሬቱ ላይ መብት ያለው ነው፡፡ የከተማ መሬትን በሊዝ መያዝ አሁን አሁን በብዛት እየተተገበረ ያለ የመሬት አያያዝ መንገድ ነው፡፡
የከተማ መሬትን በሊዝ የመያዝ አላማ/አስፈላጊነት
የከተማ መሬትን በሚመለከት የሚዘረጋ የሊዝ ስርአት የሚከተሉት ጠቀሜታዎች ይኖሩታል
መሬትን በአግባቡ ለመጠቀም፡- የመሬትን ልማት ለማቀድና ለመቆጣጠር መሬትን ሙሉ ለሙሉ በግለሰቦች ቁጥጥር ስር ከማድረግ ይልቅ በህግ አግባብ በሊዝ እንዲተዳደር ማድረግ ይመከራል፡፡ የከተማ መሬት በግለሰቦች ባለቤትነት ስር በሆነበት ሀገር መሬቱ እንዲለማ ለማድረግ የሁሉንም ስምምነት ለማግኘት ብዙ ጊዜንና ገንዘብን ይጠይቃል፡፡
ኢንቨስትመንትንና ኢንቨስተሮችን ያበረታታል፡- ሌላው ጠቀሜታው ለኢንቨስትመንት ሲሆን ይኸውም የመሬቱ ዋጋ በሊዝ የሚከፈል በሆነ ጊዜ የመነሻ የመዋእለ ነዋይ ፍሰቱ አነስተኛ የሚሆን ሲሆን ይህም ለኢንቬስተሩ ተጨማሪ ካፒታል ለሌሎች ስራወች እንዲኖረው ያደርገዋል፡፡ በአንጻሩ ግን መሬቱን ለመግዛት የሚገደድ ከሆነ ሁሉንም ዋጋ መክፈል የሚኖርበት በመሆኑ ለዋናው ስራ የሚቀረው ገንዘብ አነስተኛ ወይም ምንም ሊሆን ይችላል፡፡ ይህም የሚገባውን ያህል ኢንቨስት እንዳያደርግ እንቅፋት ይሆንበታል፡፡
መልሶ የመጠየቅ እድል፡- መሬት ለሌላ አላማ በሚፈለግበት ጊዜ መሬቱ በነጻ ከያዘው ሰው ይልቅ በሊዝ መሬትን ከያዘ ሰው መልሶ መጠየቅ የተሻለ እድል አለው፡፡ በሊዝ ስርአት የተያዘን መሬት እንደገና ለመውሰድ የሚጠይቀው ዋጋ አነስተኛ ነው፡፡
የከተማ መሬት የሊዝ ህግ
1. የኢፌዴሪ ህገመንግስት
ብዙ ሀገራት ዘንድ የመሬት ባለቤትነት ህገመንግስታዊ ጉዳይ አይደለም፤ ነገር ግን በኢትዮጵያ መሬት ባለው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ምክንያት የመሬት ባለቤትነት የፖሊሲ ጉዳይ ከመሆን በላይ በህገመንግስቱ ውስጥ ተካቶ ዘላቂ ውሳኔን ያገኘ ጉዳይ ሆኗል።
በህገመንግስቱ አንቀፅ 40 መሰረት ሁሉም የከተማና የገጠር መሬት ባለቤትነት የኢትዮጵያ ህዝቦችና የመንግስት እንደሆነ ተደንግጓል። በመሆኑም ግለሰብ መሬትን መሸጥ መለወጥ አይችልም ማለት ነው። መንግስት ይህን የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ንብረት የሆነን መሬት በይዞታው ስር አድርጐ በሚያስተዳድርበትና ለልማት በዋና መሳሪታነት በሚገለገልበት ጊዜ ዜጐች በከተማ ቦታ ላይ የሚያፈሯቸዉ ንብረቶች ላይ የሚኖራቸዉ ንብረቶችን በተመለከተ ህገ-መንግስታዊ ዋስትና የተሰጠዉ ሲሆን በዚሁ አንቀፅ ላይ “ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በጉልበቱ ወይም በገንዘቡ በመሬት ላይ ለሚገነባው ቋሚ ንብረት ወይም ለሚያደርገው ቋሚ መሻሻል ሙሉ መብት አለው” በማለት ደንግጓል፡፡ ይህ መብት የመሸጥ የመለወጥ፣ የማውረስ፣ የመሬት ተጠቃሚነት ሲቋረጥ ንብረቱን የማንሳት ባለቤቱን የማዛወር ወይም የካሳ ክፍያ የመጠየቅ መብትን ያካትታል፡፡
2. የሊዝ አዋጅ
የከተማ መሬትን በሊዝ የመያዝ ስርአት በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስራ ላይ የዋለው አዋጅ ቁጥር 80/1986 ከወጣ በኋላ ነው፡፡ ይህ አዋጅም በ1994 ዓ.ም በወጣው አዋጅ ቁጥር 272/94 የተሻረ ሲሆን እንደገና ይህ አዋጅ ደግሞ በአዋጅ ቁጥር 721/2004 ተሸሯል፡፡ ስለዚህ አሁን ሰአት ማንኛውም የከተማ ሊዝ ስርአት የሚስተናገደው በዚህ አዋጅ መሰረት ነው፡፡
በአዋጁ አንቀጽ 5 መሰረት የከተማ መሬትን በሊዝ የመያዝ ስርአት ከመዘርጋቱ በፊት ከተያዙ መሬቶች በስተቀር በኢትዮጵያ የከተማ መሬት መያዝ የሚቻለው በሊዝ ስርአት ብቻ ነው ከዚህ ውጭ በሌላ መንገድ መያዝ የተከለከለ ነው። ሆኖም ግን እንደልዩ ሁኔታ የተቀመጠው በክልሎች የሚገኙ የሊዝ ስርአትን ለመፈጸም የማይችሉ ትናንሽ ከተሞች አዋጁ ተፈጻሚ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ ከአምስት አመት ላልበለጠ ጊዜ የሊዝ ስርአቱ ተፈጻሚ እንዳይሆን ማድረግ ይችላሉ።
ነባር ይዞታወችን በተመለከተ ከተማው የሊዝ ስርአቱን ከመጀመሩ በፊት በህጋዊ መንገድ የተገኘ መሬት ወይም ነባሩ መሬት ተወስዶ በምትክ በካሳነት የተሰጠ መሬት በሊዝ ውል እስካልተሰጠ ድረስ ነባር ይዞታ ተብሎ ይወሰዳል። እንደመርህ ሁሉም የከተማ መሬት በዚህ አዋጅ በተደነገገው የሊዝ ስርአት መሰረት መተዳደር እንዳለባቸው አንቀጽ 5 ላይ የተደነገገ ቢሆንም ነባር ይዞታወችን በተመለከተ ወደ ሊዝ ስርአት ለመቀየር ህጉ ከሚከተሉት ሁኔታወች አንዱ እንዲሟላ ይጠይቃል፦
- በነባር ይዞታ ላይ ያለው ንብረት ከውርስ በስተቀር በሌላ ማናቸውም መንገድ ለሶስተኛ ወገን የተላለፈ እንደሆነ
- አግባብ ባልሆነ መንገድ ተይዘው የነበሩ ቦታወች አስተዳደሩ በሚያወጣው ደንብ መሰረት ወደ ሊዝ እንዲገቡ ሲደረግ
- ነባር ይዞታና በሊዝ የተያዘ ቦታ እንዲቀላቀል ተፈቅዶ ከሆነ ሁሉም ወደ ሊዝ ስርአት ይገባሉ
የተያዘ መሬት በማንኛዉም ምክንያት ወደ ሊዝ ስርአት ከተቀየረ ይዞታው የሊዝ መሬት የሚባል ሲሆን በአንቀጽ 16 መሰረት ባለይዞታው ከመንግስት ጋር የሊዝ ዘመኑንና የሊዝ ዋጋውን የሚያካትት የሊዝ ውል ይገባል። መሬትን በሊዝ እንዲይዝ የተፈቀደለት ሰው ስሙን፣ የመሬቱን ስፋት፣ አቅጣጫ፣ መሬቱ የሚውልበትን አላማ፣ የሊዝ ዋጋ፣ የሊዝ ዘመንና የመሳሰሉትን ያካተተ የሊዝ ይዞታ ምስክር ወረቀት ይሰጠዋል።
በሊዝ እንዲይዝ የተፈቀደለት ሰው በእያንዳንዱ ከተማ በሚወሰን የሊዝ መነሻ ዋጋ በቦታው ስፋት መጠን ተባዝቶ ይከፍላል። የሊዝ መነሻ ዋጋ ሲሰላ የመሰረተ ልማት መዘርጊያ ወጭን፣ ነባር ግንባታወች ያሉበት ቦታ ከሆነ ለነዚህ ንብረቶች ማስነሻ የወጣውን ወጭ እና ከቦታው ተነሽ ለሆኑ ሰወች የሚከፈል ካሳን እንዲሁም ሌሎች አግባብነት ያላቸውን ሁኔታወች ግምት ውስጥ ያስገባ መሆን አለበት። የሊዝ ይዞታ የተሰጠው ሰው የሚከፍለው ቅድሚያ ክፍያ ከ10% ማነስ የሌለበት ሲሆን ቀሪውን በውሉ መሰረት በተቀመጠ ረጅም የጊዜ ሰሌዳ መሰረት እንዲከፍል ይደረጋል።
በሊዝ አዋጁ መሰረት የከተማ ቦታ የሚገኝባቸው ስልቶች
ቀደም ሲል የነበሩት የከተማ ቦታ ማስተላለፊያ መንገዶች ያልተገቡና ለሙስና መንገድ ከፋች በመሆናቸዉ አሁን ባለው አሰራር ህጉ እውቅና የሰጣቸው ሁለት መሰረታዊ የማስተላለፊያ መንገዶች ጨረታ እና ምደባ ብቻ መሆናቸውን በአንቀጽ 7(2) ላይ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ እንደ መርህ ማንኛውም ለመኖሪያ፣ ለንግድም ሆነ ለሌላ ማንኛውም አላማ የሚፈለግ መሬት ከመንግስት የሚተላለፈው በጨረታ ነው፡፡ ተጫራቾች የሊዝ መነሻ ዋጋን መሰረት በማድረግ የራሳቸውን መግዣ ዋጋ የሚያቀርቡ ሲሆን በዚህ ዋጋና በቅድሚያ በሚከፍለው የገንዘብ መጠንን መሰረት በማድረግ አሸናፊው ይመረጣል፡፡ ..................