👉National champion Team/የውድድሩ አሸናፊ ቡድን ባህርዳር ዩኒቨርስቲ ሁኖል
የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ህግ ትምህርት ቤት ከፌደራል ፍትህ እና ህግ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ከአርብ ግንቦት 8 ቀን 2017 ጀምሮ እስከ ዛሬ እሁድ ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ ሲካሄድ የቆየው 9ኛው ዙር ሀገር አቀፍ የህግ ትም/ት ቤቶች የምስለ ችሎት ውድድር ፍጻሜውን አግኝቶል ።
በውድድሩ ላይ 12 ዪኒቨርሲቲይዎች የተሳተፉ ሲሆን።የውድድሩ የመጨረሻ ውጤትም የሚከተለው ነው።
👉National champion Team/የውድድሩ አሸናፊ ቡድን ባህርዳር ዩኒቨርስቲ ሁኖል
1.ቤተልሔም ገበየሁ ጸጋነህ
2.ዮናስ ሙጨ ዳኘ
3.እዮብ ይመች
👉Best Runner Up Team (2ኛ ደረጃን) የያዙት ሰላሌ ዩኒቨረሲቲ ናቸው
1.ሄርሜላ መስፍን
2 ሀዴሳ መረከቡ
3.አብዲ ረታ
👉Second runner up team(3ኛ ደረጃን የያዙት) ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ሰሆን
1.ፋሲል ዘለቀ ዘውደ
2.ወርቁ ማስሬ አበበ
3. ፈቲያ ኑረድን መሃመድ
👉Best Memorial Applicant
ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ
👉Best Memorial Respondet winner
ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ
👉Best orator of the preliminary round competition
እዮብ ይመች ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ
👉Best Femal orator of the preliminary round Competition
ቤተልሔም ገበየሁ ጸጋነህ ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ
👉Best orator of the final round competition competition
እዮብ ይመች ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ
via:- Law Students Union
ጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#የዳኞችስነምግባር #አለሕግ #ህግ
የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ህግ ትምህርት ቤት ከፌደራል ፍትህ እና ህግ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ከአርብ ግንቦት 8 ቀን 2017 ጀምሮ እስከ ዛሬ እሁድ ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ ሲካሄድ የቆየው 9ኛው ዙር ሀገር አቀፍ የህግ ትም/ት ቤቶች የምስለ ችሎት ውድድር ፍጻሜውን አግኝቶል ።
በውድድሩ ላይ 12 ዪኒቨርሲቲይዎች የተሳተፉ ሲሆን።የውድድሩ የመጨረሻ ውጤትም የሚከተለው ነው።
👉National champion Team/የውድድሩ አሸናፊ ቡድን ባህርዳር ዩኒቨርስቲ ሁኖል
1.ቤተልሔም ገበየሁ ጸጋነህ
2.ዮናስ ሙጨ ዳኘ
3.እዮብ ይመች
👉Best Runner Up Team (2ኛ ደረጃን) የያዙት ሰላሌ ዩኒቨረሲቲ ናቸው
1.ሄርሜላ መስፍን
2 ሀዴሳ መረከቡ
3.አብዲ ረታ
👉Second runner up team(3ኛ ደረጃን የያዙት) ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ሰሆን
1.ፋሲል ዘለቀ ዘውደ
2.ወርቁ ማስሬ አበበ
3. ፈቲያ ኑረድን መሃመድ
👉Best Memorial Applicant
ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ
👉Best Memorial Respondet winner
ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ
👉Best orator of the preliminary round competition
እዮብ ይመች ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ
👉Best Femal orator of the preliminary round Competition
ቤተልሔም ገበየሁ ጸጋነህ ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ
👉Best orator of the final round competition competition
እዮብ ይመች ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ
via:- Law Students Union
ጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#የዳኞችስነምግባር #አለሕግ #ህግ
👍20❤4🥰1👏1
በህዝብ ተቀባይነት ያለው እና በኢኮኖሚው ላይ የተመሰረተ የግብር ስርዓት ለመፍጠር ጠለቅ ያለ የገቢ ግብር ማሻሻያ አስፈላጊነት፣
መግቢያ
የኢትዮጵያ የገቢ ግብር ሕግ (ቁ. 979/2008) ከ15 ዓመታት በፊት ተቀባይነት ቢኖረውም፣ በአሁኑ ወቅት የኢኮኖሚ ሁኔታ፣ የዋጋ ንረት፣ የዶላር ዋጋ መጨመር እና የብር ዋጋው በማሽቆልቆሉ ምክንያት ለሰራተኛው ህይወት አስቸጋሪ ሆኗል። በተለይ፣ ከ10,000 ብር በላይ የሚያገኙ ሰራተኞች 35% ግብር ሲከፍሉ፣ ይህ ደረጃ በአሁኑ የኑሮ ውድነት ከባድ ጫና እና ማማረር ፈጥሯል። ይህ ጽሁፍ የአሁኑን የግብር ስርዓት ጉድለቶች፣ ተጽዕኖው በህዝብ ላይ እንዳለው እና አስፈላጊ የሆኑ ማሻሻያዎችን ይጠቁማል ያብራራል።
የአሁኑ የገቢ ግብር ያስከተለው ችግር እና ተግዳሮቶች፣⚠️
1. የገንዘብ ዋጋ ቀንሷል
- በ2008 ዓ.ም. 10,000 ብር ≈ 500 ዶላር ነበር፤ ዛሬ?ከ80 ዶላር ያነሰ ነው!
- አንድ ሰራተኛ 35% ግብር ከከፈለው በ65% ቀሪ ብር በዋጋ ንረት የትኛውን መሠረታዊ ፍላጎት ሊሸፍን ይችላል?
2. የግብር ደረጃዎች ከአሁኑ ኢኮኖሚ ጋር አይጣጣሙም
- 600 ብር (የግብር ነፃ ዝቅተኛ ደረጃ) በ2025 አንድ ሰውን ለ1 ቀናት ብቻ ሊያቆየው ይችላል።
- 10,900 ብር ለአንድ ሰራተኛ ለአንድ ወር መቆየት አይችለም፣ ግን 35% ግብር ይከፈላል!
3. ዋጋ ንረት እና የዶላር ዋጋ መጨመር ግምት ውስጥ አላስገባም፣
- ግብር በየዓመቱ እንደ የዋጋ ንረት አይሻሻልም።
- ሌሎች፣ መምህራን፣ ዶክተሮች እና አብዛኞቹ ሰራተኞች በከፍተኛ ግብር የተጫነባቸው በመሆኑ ሰራተኞች እየተቸገሩ እና እየተማረሩ ነው።
ለውጥ የሚያስፈልግበት ጥቆማ እና ግላዊ እይታ
✔ የግብር ነፃ ዝቅተኛ ደረጃ ከ600 ብር ቢያንስ ወደ 4,000 ብር ማሳደግ፣
✔ 35% ግብር ለበለጠ ከፍተኛ ገቢዎች ብቻ መተግበር (ለምሳሌ፡ ከ50,000 ብር በላይ)
✔ የግብር ደረጃዎችን በየዓመቱ ከዋጋ ንረት ጋር በማጣጣም ማዘመን
✔ የግብር ስርዓቱን በአለም አቀፍ ደረጃ ያለው የደመወዝ እርከኖችን አይቶ ማሻሻል።
ማጠቃለያ:
ህዝቡ መንግስት ነው፣ መንግስቱም ህዝቡን ሊረዳው እና ሊደግፈው ይገባል!
የአሁኑ የገቢ ግብር ሕግ ከአለም አቀፍ የደመወዝ እና የኑሮ ወጪ ስታንዳርድ በጣም ወደ ኋላ የቀረ ነው።
የኢኮኖሚው ማሻሻያ እንዳለ ሁኖ ህጎችም ከኢኮኖሚያዊ ማሻሻያ ጋር አብሮ በማሻሸል የዜጎችን ገቢ ታሳቢ ያደረገ እና ዘመኑን የዋጀ ማስተካከያ ያስፈልገናል።
እንዲህ አይነት ማሻሻያ እና ማስተካከያዎችን ህዝቡ ተቸግሮ እና ተስፋ ቆርጦ ወደ ጥያቄ፣ አመፅ እና መሰል እንቅስቃሴዎች ሳይገባ ቀድሞ የህብረተሰቡን ችግር ነቅሶ በማውጣት ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ተግባራዊ ማድረግ መንግሥት እና ህዝብን በማቀራረብ ዘላቂ መተማመን እና መደማመጥ እንዲኖር ያደርጋል።
ስለዚህ፣ አስቸኳይ የግብር ማሻሻያ በማድረግ፡
- የሰራተኞች ገቢ በመጠኑም ቢሆን ይጨምራል
- የኑሮ ደረጃ ይሻሻላል
- የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ይጨምራል
- የጤናና የትምህርት ባለሙያዎች ተነሳሽነት ይጨምራል
የህዝብ ጤና የሀገር ጤና ነው!
ለሰራተኛ ፍቅር፣ ለትክክለኛ ግብር ስርዓት ይጠቅማል!
ህዝብ ከተረጋጋ መንግስት የተረጋጋ ልማት ለማምጣት ጊዜ አለው።
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
ሚኪያስ መላክ ተዘጋጅቶ በአለሕግ አማራጭ የሕግ እውቀት እና አገልግሎት ቀረበ
የዚህ የፅሑፍ የቅጅ መብቱ ለጠበቃ እና ሕግ አማካሪ ሚኪያስ መላክ የተጠበቀ ነው።
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#ሰራተኛ #የገቢግብር #አለሕግ #ህግ #979/2008
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Linktree
AleHig | Instagram, Facebook, TikTok | Linktree
AleHig attorney & Legal consult present across multiple social media platforms..
👍20❤7🔥1
ቲክቶክን ጨምሮ በመሰል የማህበራዊ ሚዲያ መተግበሪያዎች ላይ የሙያውን ክብር እና ስነምግባርን የሚያጎድፉ ተግባራት ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎችን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር የተሰጠ ጥብቅ ማሳሰቢያ፤የፌደራል ጠበቆች ማህበር ቲክቶክን ጨምሮ በመሰል የማህበራዊ ሚዲያ መተግበሪያዎች የሚሠሩ የህግ ቪዲዮችን ይዘትና አቀራረብ በቅርበት ሲከታተል ቆይቷል:: በተመሳሳይ ጥቆማዎችንም ሲያሰባስብ ቆይቷል::
ሆኖም የሚሰሩ ተንቀሳቃሽ ምስሎች (Video) ዓላማ ለህዝብ ንቃተ- ህግ እና ግንዛቤን ለመፍጠር የሚያግዙ ይሆናሉ በሚል እና በተለይም ከሌሎች አቻ ሀገራት አንፃር በታሪክ አጋጣሚ ወደ ኃላ የቀረውን እና በቅርብ አመታት ከፍ ያለ መነቃቃት እያሳየ ያለውን የህግ አገልግሎት ዘርፍ ለማበረታታት ሲባል ጉዳዩን በትእግስት ለመከታተል ሞክሯል::
ይህ በእንዲህ እንዳለ ጉዳዩ እየተሻሻለ ከመምጣት ይልቅ የህግን ሙያ ክብር እና ጥብቅ ስነ-ምግባር በሚያጎድፍ መልኩ የቀጠለ ሆኖ ተገኝቷል::
ክትትል ሲደረግባቸው ቆይቶ በጥናት ከተለዩ ነጥቦች ውስጥ የሚከተሉት በማሳያነት ሊጠቀሱ የሚችሉ ናቸው::
👍4
ከክስ በፊት እግድ ትዕዛዝ እንዲሰጥልን በሚል የሚቀርብ አቤቱታ ተከሳሽ የሆነ ወገን ላይ ያልተገባ የመብት ገደብ እንዳይደረግበት ጊዚያዊ እግድ የሚጠይቀው ወገን ክስ ለማቅረብ ዝግጅት ላይ እንደሆነና ለክስ ዝግጅቱም ተጨማሪ ጊዜ የሚያስፈልግበትን ምክንያት ማስረዳት የሚጠበቅበት ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም ክሱ እስኪቀርብ ድረስ የዕግድ ትዕዛዙ ባይሰጥ ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት ማሳየትና ማረጋገጥ የሚጠበቅበት ሲሆን ፍርድ ቤቱም ክሱን ለማቅረብ የሚያስፈልገውን ምክንያታዊ ጊዜ ብቻ በመወሰን የእግድ ትዕዛዝ ሊሰጥ የሚገባ ስለመሆኑ በሰ/መ/ቁ.191402 ቅፅ 25 ላይ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ተሰጥቶበታል።
💎💎💎💎💎💎✏️✏️✏️
አመልካች በሠበር አቤቱታው ለግልግል ጉባዔ የሚገቡንን ክፍያዎች በተመለከተ ክስ እስከምናቀርብ ድረስ ዋስትናዎች እንዳይከፈሉ ታግዶ እንዲቆይ ሊደረግ ይገባል ያለ በመሆኑ ለክርክሩ አወሳሰን ዋናው ጭብጥ ክስ ባልቀረበበት ሁኔታ የእግድ ጥያቄ ሊቀርብ ይችላልን? ዋስትናዎቹ ያለቅድመ ሁኔታ የሚከፈሉ መሆናቸው ሲታይ እግድ ሊሰጥባቸው ይችላል ወይስ አይችልም? የሚለውን መመርመር ያስፈልጋል፡፡ በዚህ ረገድ 1ኛ ተጠሪ የሚከራከረው የእግድ ጥያቄ የሚቀርበው ዋና ክርክር ወይም ክስ ኖሮ ክርክሩ በፍርድ ቤት እስኪወሰን ድረስ ለጊዜው የሚሰጥ ትዕዛዝ ነው፡፡ ዋና ክርክር በሌለበት ገና ለገና ጉዳዩ በግልግል እስኪታይ ድረስ እግድ ይሰጥልኝ ብሎ ዳኝነት መጠየቅ በሕግ ያልተፈቀደ ነው በማለት ነው፡፡
የእግድ ትዕዛዝ በመርሕ ደረጃ የቀረበ ክስን መሠረት ያደረገ እና በሥነ-ሥርዓት ሕጉ አግባብ በተመለከቱት መስፈርቶች የሚሰጥ ነው፡፡ ዓላማው ደግሞ ክሱ ያለ ውጤት እንዳይቀርና ፍርድ በሚሰጥበት ጊዜም የሚፈጸምበት ንብረት እንዲኖርና ዜጎች መብታቸውን ማስከበር የሚችሉበትን ዕድል የሚፈጥርና በሂደቱም ፍርድ ቤቶች ላይ ያላቸውን እምነት የሚጨምር ነው፡፡ በመሆኑም ሠዎች ክስ ከማቅረባቸው በፊት ነገር ግን በክስ ዝግጅት ላይ እያሉ ተከሳሽ የሚሆነው ወገን ጉዳዩን በመረዳት ክስ ሲቀርብ ክሱ ውጤት እንዳይኖረው በፍብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 154(ለ) እንደተመለከተው ተግባሮችን እየፈጸመ ከሆነ፤ ተግባሩን አለመከላከል ሥነ-ሥርዓት ሕጉ የተቀረጸበትን ዓላማ እንዳይሳካ ያደርገዋል፡፡ ነገር ግን እግዱ እንዲሰጥ የተጠየቀው ክስ ሳይቀርብ ከሆነ ተከሳሽ የሚሆነው ወገን ላይ ያልተገባ የመብት ገደብ እንዳይደረግበት፤ ጊዜያዊ እግድ የሚጠይቀው ወገን ክስ ለማቅረብ ዝግጅት ላይ እንዳለ፣ የክስ ዝግጅቱ ተጨማሪ ጊዜ ያስፈለገበትን ምክንያት፣ ክሱ እስኪቀርብ ድረስ የእግድ ትዕዛዙ ባይሰጥ የሚያስከትለው ጉዳት ማሳየት ያለበት ሲሆን ፍርድ ቤቱም ክሱን ለማቅረብ የሚያስፈልገውን ምክንያታዊ ጊዜ ድረስ ብቻ በጊዜ ገደብ የተገደበ የእግድ ትዕዛዝ ሊሰጥ ይችላል፡፡
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#አለሕግ #ህግ #ሰበርመዝገብ #ቁጥር #191402 #የሕግ_መረጃ #እግድ
💎💎💎💎💎💎✏️✏️✏️
አመልካች በሠበር አቤቱታው ለግልግል ጉባዔ የሚገቡንን ክፍያዎች በተመለከተ ክስ እስከምናቀርብ ድረስ ዋስትናዎች እንዳይከፈሉ ታግዶ እንዲቆይ ሊደረግ ይገባል ያለ በመሆኑ ለክርክሩ አወሳሰን ዋናው ጭብጥ ክስ ባልቀረበበት ሁኔታ የእግድ ጥያቄ ሊቀርብ ይችላልን? ዋስትናዎቹ ያለቅድመ ሁኔታ የሚከፈሉ መሆናቸው ሲታይ እግድ ሊሰጥባቸው ይችላል ወይስ አይችልም? የሚለውን መመርመር ያስፈልጋል፡፡ በዚህ ረገድ 1ኛ ተጠሪ የሚከራከረው የእግድ ጥያቄ የሚቀርበው ዋና ክርክር ወይም ክስ ኖሮ ክርክሩ በፍርድ ቤት እስኪወሰን ድረስ ለጊዜው የሚሰጥ ትዕዛዝ ነው፡፡ ዋና ክርክር በሌለበት ገና ለገና ጉዳዩ በግልግል እስኪታይ ድረስ እግድ ይሰጥልኝ ብሎ ዳኝነት መጠየቅ በሕግ ያልተፈቀደ ነው በማለት ነው፡፡
እግድ በሠው የንብረት መብት አጠቃቀም ላይ ገደብ የሚፈጥር ነው፡፡ በኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 40(1) ላይ ጥበቃ የተደረገለት ንብረት መብት ላይ ገደብ ለማድረግ ደግሞ በሕግ በግልጽ በተመለከተ፣ ውስን ጉዳይና አፈጻጸሙም መብቱን መልሶ የመውሰድ ያህል ውጤት በማይፈጥር ሁኔታ ውስጥ ብቻ ሊሆን ይገባል የሚለው ስለሠብዓዊ መብት ጥበቃ የተደረጉ የሥምምነት ድንጋጌዎች ሆነ በሕገ-መንግሥቱ ውስጥ የተቀረጸ የሕግ መርሕ ነው፡፡ በፍብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 151 መሠረት ከፍርድ በፊት ንብረት ተከብሮ እንዲቆይ (attachment) የሚደረግበትን ሥርዓትና ሁኔታ የሚመለከተው ሆነ በፍብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 154 መሠረት ነገሩ በፍርድ እስኪወሰን ወይም ሌላ ትዕዛዝ እስኪሰጥ ድረስ ንብረቱ እንዳለ እንዲቆይ፣ ከመጥፋት እንዲድን ወይም እንዳይበላሽ፣ ለሌላ ሰዉ ተላልፎ እንዳይሰጥ፣ ወደ ሌላ ስፍራ እንዳይዛወር ወይም እንዳይባክን የእግድ ትዕዛዝ የተጠየቀው ለጥያቄው መሠረት የሆነው ክስ ቀርቦ ከሆነ እግድ መሰጠቱ የተከሳሹ ወገን የንብረት መበት አጠቃቀም ላይ የሚያስከትለውን ውጤት በመረዳት በጥንቃቄ መታየት ያለበት ነው፡፡
የእግድ ትዕዛዝ በመርሕ ደረጃ የቀረበ ክስን መሠረት ያደረገ እና በሥነ-ሥርዓት ሕጉ አግባብ በተመለከቱት መስፈርቶች የሚሰጥ ነው፡፡ ዓላማው ደግሞ ክሱ ያለ ውጤት እንዳይቀርና ፍርድ በሚሰጥበት ጊዜም የሚፈጸምበት ንብረት እንዲኖርና ዜጎች መብታቸውን ማስከበር የሚችሉበትን ዕድል የሚፈጥርና በሂደቱም ፍርድ ቤቶች ላይ ያላቸውን እምነት የሚጨምር ነው፡፡ በመሆኑም ሠዎች ክስ ከማቅረባቸው በፊት ነገር ግን በክስ ዝግጅት ላይ እያሉ ተከሳሽ የሚሆነው ወገን ጉዳዩን በመረዳት ክስ ሲቀርብ ክሱ ውጤት እንዳይኖረው በፍብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 154(ለ) እንደተመለከተው ተግባሮችን እየፈጸመ ከሆነ፤ ተግባሩን አለመከላከል ሥነ-ሥርዓት ሕጉ የተቀረጸበትን ዓላማ እንዳይሳካ ያደርገዋል፡፡ ነገር ግን እግዱ እንዲሰጥ የተጠየቀው ክስ ሳይቀርብ ከሆነ ተከሳሽ የሚሆነው ወገን ላይ ያልተገባ የመብት ገደብ እንዳይደረግበት፤ ጊዜያዊ እግድ የሚጠይቀው ወገን ክስ ለማቅረብ ዝግጅት ላይ እንዳለ፣ የክስ ዝግጅቱ ተጨማሪ ጊዜ ያስፈለገበትን ምክንያት፣ ክሱ እስኪቀርብ ድረስ የእግድ ትዕዛዙ ባይሰጥ የሚያስከትለው ጉዳት ማሳየት ያለበት ሲሆን ፍርድ ቤቱም ክሱን ለማቅረብ የሚያስፈልገውን ምክንያታዊ ጊዜ ድረስ ብቻ በጊዜ ገደብ የተገደበ የእግድ ትዕዛዝ ሊሰጥ ይችላል፡፡
በሰ/መ/ቁ.191402 ቅፅ 25 ላይ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ተሰጥቶበታል።
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#አለሕግ #ህግ #ሰበርመዝገብ #ቁጥር #191402 #የሕግ_መረጃ #እግድ
👍18❤8
❤6
1. በቂ የወንጀል ጥርጣሬ መኖሩ ተጣርቶ በፓሊስ የወንጀል ምርመራ ይጀመርበታል ፣
2. የምርመራ መዝገቡ ለአቃቤሕግ ከተላከ በሁላ ፣ ለመክሰስ የሚያስችል ማስረጃና የሕግ መሰረት መኖሩ ሲረጋግጥ ክስ የመስረትበታል ፣ ካልሆነ መዝገቡ ይዘጋል ፣
3. ፍ/ቤት ክሱ እንዲደረሰው ትእዛዝ ከስጠ በሁላ ይሄው ደርሶት እራሱን ለመከላከል እድል ይስጠዋል
4. አቃቤሕግ መጀመሪያ ማስረጃውን ያሰማል ፣
5. ፍ/ቤቱ የአቃቤ ሕግን ማስረጃ ከሰማ በሁዋላ ፣ ተከላከል ይለዋል ፣ ወይም መከላከል ሳያስፈልገው በነጻ ያሰናብተዋል ፣
6. ተከላከል ከተባለ ፣ አለኝ የሚለውን መከላከያ አቅርቦ ያሰማል ፣ ይከራከራል ። መከላከል መስረታዊ መብት ነው ፣
7. ተከላከል ከተባለ በሁዋላ ፍ/ቤቱ ጥፋተኛ ሊለው ወይም በነጻ ሊያሰናብተው ይችላል ፣
አንድ ሰው ወንጀል ፈጽሞ ጥፋተኛ ተባለ የሚባለው በዚህ ሂደት ውስጥ አልፎ ነው ። ክስ ከተመሰረተበት በሁዋላ እንኩዋን በሁለት የስነ ስርአት ደረጃዎች ነጻ የመባል እድል አለው ። ማንኛችንም ነገ በሆነ አጋጣሚ በሰውየው ቦታ ልንሆን እንችላለን ። ሕግ የስጠውን መብት እናክብርለት ፣ ቀድሞ ፈራጅ አንሁን ፣ ውጤቱን እንጠብቅ ።
፣ ከማስታወሻዬ ፣ በአንድ ወቅት ...
እነ እገሌ ፣ በቢሊዮን ብር ዘረፉ ተባለ ። ተራገበ ፣ ተጋነነ ፣ ብዙ ተጮህ ። ተጠርጣሪዋቹ ፣ ቤተሰብ ፣ ወዳጅ ዘመዳቸው አፈረ ፣ አንገቱን ደፋ ። ብዙ ሰው በየቤቱ ሰምቶ አዘነባቸው ፣ እነዚህን መግደል እንጂ የምን ክስ ምናምን ነው ተባለ ፣ እኛ ጠበቆቹም ተሰደብን ፣ ሞራል የሌላችው ፣ እንዴት ለነዚህ ይቆማሉ ተባልን ።
ክስ ተመሰረተ ፣ ወሬውና ክሱ አይገናኝም ፣ ክሱና እውነታው አይገናኝም ። እናም ፣ ቆይቶ ፣ ሰዎቹ እንዲከሱ ይፈለግበት የነበረው ፓለቲካ ሲለወጥ ፣ ክሳቸው ተነሳ ።
ዝርዝሩን ሳናውቅ ለመፍረድ አንቸኩል ። ብዙ በተዋራባቸው የወንጀል ጉዳዮች ላይ በጠበቃነት ተሳትፌአለሁ ። በአብዛኛው ግነቱና እውነቱ አይገናኝም ። ሰከን ማለት ፣ ግራ ቀኙን መስማት ፣ ማገናዘብ ፣ ከስሜታዊ ፈራጅነት መቆጠብ ጥሩ ነው ... የወንጀል ምርመራውን ለፓሊስ ፣ የክሱን ጉዳይ ለአቃቤሕግ ፣ ዳኝነቱን ለፍ/ቤት እንተወው ....
መልካም ቀን ። በአበበ አስማረ
Alternative legal enlightenment & Service
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
https://t.me/AleHig
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#አለሕግ #ህግ #ሰበርመዝገብ #ሕግ_መረጃ #እግድ
2. የምርመራ መዝገቡ ለአቃቤሕግ ከተላከ በሁላ ፣ ለመክሰስ የሚያስችል ማስረጃና የሕግ መሰረት መኖሩ ሲረጋግጥ ክስ የመስረትበታል ፣ ካልሆነ መዝገቡ ይዘጋል ፣
3. ፍ/ቤት ክሱ እንዲደረሰው ትእዛዝ ከስጠ በሁላ ይሄው ደርሶት እራሱን ለመከላከል እድል ይስጠዋል
4. አቃቤሕግ መጀመሪያ ማስረጃውን ያሰማል ፣
5. ፍ/ቤቱ የአቃቤ ሕግን ማስረጃ ከሰማ በሁዋላ ፣ ተከላከል ይለዋል ፣ ወይም መከላከል ሳያስፈልገው በነጻ ያሰናብተዋል ፣
6. ተከላከል ከተባለ ፣ አለኝ የሚለውን መከላከያ አቅርቦ ያሰማል ፣ ይከራከራል ። መከላከል መስረታዊ መብት ነው ፣
7. ተከላከል ከተባለ በሁዋላ ፍ/ቤቱ ጥፋተኛ ሊለው ወይም በነጻ ሊያሰናብተው ይችላል ፣
አንድ ሰው ወንጀል ፈጽሞ ጥፋተኛ ተባለ የሚባለው በዚህ ሂደት ውስጥ አልፎ ነው ። ክስ ከተመሰረተበት በሁዋላ እንኩዋን በሁለት የስነ ስርአት ደረጃዎች ነጻ የመባል እድል አለው ። ማንኛችንም ነገ በሆነ አጋጣሚ በሰውየው ቦታ ልንሆን እንችላለን ። ሕግ የስጠውን መብት እናክብርለት ፣ ቀድሞ ፈራጅ አንሁን ፣ ውጤቱን እንጠብቅ ።
፣ ከማስታወሻዬ ፣ በአንድ ወቅት ...
እነ እገሌ ፣ በቢሊዮን ብር ዘረፉ ተባለ ። ተራገበ ፣ ተጋነነ ፣ ብዙ ተጮህ ። ተጠርጣሪዋቹ ፣ ቤተሰብ ፣ ወዳጅ ዘመዳቸው አፈረ ፣ አንገቱን ደፋ ። ብዙ ሰው በየቤቱ ሰምቶ አዘነባቸው ፣ እነዚህን መግደል እንጂ የምን ክስ ምናምን ነው ተባለ ፣ እኛ ጠበቆቹም ተሰደብን ፣ ሞራል የሌላችው ፣ እንዴት ለነዚህ ይቆማሉ ተባልን ።
ክስ ተመሰረተ ፣ ወሬውና ክሱ አይገናኝም ፣ ክሱና እውነታው አይገናኝም ። እናም ፣ ቆይቶ ፣ ሰዎቹ እንዲከሱ ይፈለግበት የነበረው ፓለቲካ ሲለወጥ ፣ ክሳቸው ተነሳ ።
ዝርዝሩን ሳናውቅ ለመፍረድ አንቸኩል ። ብዙ በተዋራባቸው የወንጀል ጉዳዮች ላይ በጠበቃነት ተሳትፌአለሁ ። በአብዛኛው ግነቱና እውነቱ አይገናኝም ። ሰከን ማለት ፣ ግራ ቀኙን መስማት ፣ ማገናዘብ ፣ ከስሜታዊ ፈራጅነት መቆጠብ ጥሩ ነው ... የወንጀል ምርመራውን ለፓሊስ ፣ የክሱን ጉዳይ ለአቃቤሕግ ፣ ዳኝነቱን ለፍ/ቤት እንተወው ....
መልካም ቀን ። በአበበ አስማረ
Alternative legal enlightenment & Service
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
https://t.me/AleHig
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#አለሕግ #ህግ #ሰበርመዝገብ #ሕግ_መረጃ #እግድ
Telegram
አለሕግAleHig ️
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
👍10❤6🙏1
በወንጀል የተገኘ ንብረት ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር አዋጅ ላይ የተደቀኑ ስጋቶች፣
ዓለም አቀፍና የሕገ-መንግስት ብርሃን ውስጥ ሲፈተሽ በኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቆ ሥራ ላይ የዋለው በወንጀል የተገኘ ንብረትን ሕጋዊ ማስመሰልን እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከል የወጣው አዋጅ፣ ከአገራዊ የሕገ-መንግስት ድንጋጌዎችና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ሕጎች አኳያ ሲታይ በርካታ ጥያቄዎችን የሚያስነሳ ሆኖ አግኝተነዋል። በተለይም "በሽፋን ስር ምርመራ የሚያደርጉ መርማሪዎች ከግድያ ውጪ በሆነ በማንኛውም ወንጀል ተጠያቂ እንደማይሆኑ" የሚያዘው ድንጋጌ፣ የሕግ የበላይነትን እና የሰብዓዊ መብቶችን መርሆዎች አደጋ ላይ የሚጥል ነው የሚሉ አስተያየቶች በስፋት እየተሰሙ ነው።
#የኢትዮጵያ_ሕገ-መንግስት እና #የአዋጁ_ተግዳሮቶች
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግስት፣ በመሰረታዊ መብቶችና ነጻነቶች ዙሪያ ሰፊ ድንጋጌዎችን አስቀምጧል። በተለይም አንቀጽ 13 የመንግስት አካላት ሁሉ በሕገ-መንግስቱ የተደነገጉትን የሰብዓዊ መብቶችና ነጻነቶች የማክበርና የማስከበር ግዴታ እንዳለባቸው ይደነግጋል። አንቀጽ 14 የሰብዓዊ ክብርን፣ አንቀጽ 15 የሕይወት መብትን፣ አንቀጽ 16 የአካል ደህንነት መብትን፣ አንቀጽ 17 የነጻነት መብትን፣ አንቀጽ 18 ደግሞ ጭካኔ የተሞላበት፣ ኢ-ሰብዓዊ ወይም አዋራጅ ቅጣት ወይም አያያዝን ይከለክላል።
አዲሱ አዋጅ "መርማሪዎች ከግድያ ውጪ በማንኛውም ወንጀል አይጠየቁም" በሚለው ድንጋጌው፣ እነዚህን የሕገ-መንግስት መርሆዎች የሚጻረር ነው የሚል ጠንካራ መከራከሪያ ይቀርባል። አንድ መርማሪ ገንዘብ በመቀበል፣ ንጹሃንን በማሰቃየት ወይም ሌላ የመብት ጥሰት በመፈጸም ተጠያቂነትን የሚያመልጥ ከሆነ፣ የሕገ-መንግስቱ የመብቶች ጥበቃ ዋጋ የለውም የሚል ስጋት ይፈጠራል። ይህ ድንጋጌ ለሙስና፣ ለሥልጣን አላግባብ መጠቀም እና ለሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ክፍት በር ሊከፍት ይችላል።
#ዓለም_አቀፍ_ሕጎችና_ስምምነቶች
ኢትዮጵያ በርካታ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ስምምነቶችንና ኮንቬንሽኖችን አጽድቃለች።
ከእነዚህም መካከል፡-
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቻርተር (UN Charter): ይህ ቻርተር የሰብዓዊ መብቶችን ማክበር እና ማስከበር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መሰረታዊ ዓላማዎች አንዱ እንደሆነ ይገልጻል።
ዓለም አቀፍ የሲቪል እና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን (International Covenant on Civil and Political Rights - ICCPR): ኢትዮጵያ ይህን ቃል ኪዳን አጽድቃለች። ቃል ኪዳኑ በግልጽ የሕይወትን፣ የነጻነትን፣ ከማሰቃየት የመጠበቅን እና የሕግ ፊት እኩልነትን መብቶች ያስቀምጣል። የትኛውም አገር ሽብርተኝነትን ለመዋጋት በሚል ሰበብ እነዚህን መሰረታዊ መብቶች መርገጥ እንደሌለበት ዓለም አቀፍ ሕግ ያዛል።
የማሰቃየትን እና ሌሎች ጭካኔ የተሞላባቸው፣ ኢ-ሰብዓዊ ወይም አዋራጅ ቅጣቶችን ወይም አያያዞችን የሚከለክል ኮንቬንሽን (Convention Against Torture and Other Cruel, Inhuman or Degrading Treatment or Punishment - CAT): ኢትዮጵያ የዚህ ኮንቬንሽን አባል ስትሆን፣ ማሰቃየትን በማንኛውም ሁኔታ ለመከልከል እና ወንጀለኞችን ተጠያቂ ለማድረግ ግዴታ አለባት። አዲሱ አዋጅ "መርማሪው ማሰቃየት ቢፈጽም አይጠየቅም ማለት ነው?" የሚለው ስጋት፣ የዚህን ኮንቬንሽን መርሆዎች የሚጻረር ነው።
በተጨማሪም፣ ገንዘብ ሕገወጥ የማድረግ (Money Laundering) እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት (Terrorist Financing) ወንጀሎችን ለመዋጋት የወጡ ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ቢኖሩም፣ እነዚህ ስምምነቶች ወንጀልን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት የሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩ አበክረው ያሳስባሉ። የፋይናንስ ተግባር ግብረ ኃይል (Financial Action Task Force - FATF) ያሉ ድርጅቶችም ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመዋጋት የሚረዱ ደረጃዎችን ሲያወጡ፣ የሕግ የበላይነትን እና የመብቶችን ጥበቃ ግምት ውስጥ ያስገባሉ።
#የሞራል_ሕግ_እና_የሕግ_የበላይነት
ከሕግ በላይ የሆነ የሞራል ሕግ አለ የሚለው መርህ በበርካታ ፍልስፍናዎች እና የሕግ አስተምህሮዎች ዘንድ ተቀባይነት አለው። ይህ ማለት አንድ ሕግ በጽሑፍ ቢቀመጥም፣ ዓለም አቀፍ የሞራል እና የፍትህ መርሆዎችን የሚጻረር ከሆነ ተቀባይነት የለውም። "ከግድያ ውጪ በሌላ ወንጀል አይጠየቅም" የሚለው ድንጋጌ፣ የሕግ የበላይነትን እና የፍትህን መሰረታዊ መርሆዎች የሚዳፈር በመሆኑ፣ በብዙዎች ዘንድ የሞራል ብቁነት የለውም የሚል ትችት ይቀርብበታል። የሕግ የበላይነት ሁሉም ሰው ከሕግ በታች እኩል ነው የሚለውን መርህ ያመለክታል፤ የመርማሪዎችን ተጠያቂነት ማስቀረት ይህን መርህ ይጥሳል።
#የመናገር_እና_የመሰብሰብ_ነጻነት
አዋጁ በተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በጋዜጠኞች እና በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ላይ ጫና ይፈጥራል የሚለው ስጋትም ትልቅ ቦታ አለው። የኢትዮጵያ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 29 የመናገር እና የመግለጽ ነጻነትን፣ አንቀጽ 30 የመሰብሰብ፣ የመመደብ እና ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትን ያረጋግጣል። አዋጁ ከእነዚህ መብቶች ጋር እንዴት እንደሚጣጣም ግልጽ የሆነ ማብራሪያ ያስፈልገዋል። የመንግስት ተቃዋሚዎችን ወይም ሕጋዊ በሆነ መንገድ የፖሊሲ ትችት የሚያቀርቡ አካላትን "ሽብርተኝነትን መርዳት" በሚል ሰበብ ኢላማ ለማድረግ የሚያስችል ክፍተት እንዳለው የሚሰጋ ከሆነ፣ ለዴሞክራሲያዊ ምህዳር መስፋፋት እንቅፋት ይሆናል።
መደምደሚያ
ሽብርተኝነትን እና ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውርን መዋጋት የማንኛውም ሉዓላዊ መንግስት ሕጋዊ ግዴታ እና የዜጎች ደህንነት ጉዳይ ነው። ይሁን እንጂ፣ ይህ ትግል የዜጎችን መሰረታዊ መብቶች እና የሕግ የበላይነት መርሆዎችን ሳያጓድል መከናወን ይኖርበታል። አዲሱ አዋጅ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ሕጎችን እና የኢትዮጵያን ሕገ-መንግስት መሰረታዊ ድንጋጌዎችን የሚያከብር መሆኑን ለማረጋገጥ፣ ሰፊ ውይይት እና ምናልባትም ክለሳ ሊደረግበት ይገባል። አለበለዚያ፣ ሕግን ለማስከበር በሚል የሚወጡ ሕጎች ራሳቸው ለሕገ-ወጥነት በር ከፍተው የሞራል እና የሕግ ቀውስ ሊፈጥሩ ይችላሉ።
እናንተስ፣ አዲሱ አዋጅ የሀገራችንን ሕገ-መንግስት እና ዓለም አቀፍ ሕጎችን ያከብራል ብላችሁ ታስባላችሁ?
የህዝብ ጤና የሀገር ጤና ነው!
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
ሚኪያስ መላክ ተዘጋጅቶ በአለሕግ አማራጭ የሕግ እውቀት እና አገልግሎት ቀረበ ነው።
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
ዓለም አቀፍና የሕገ-መንግስት ብርሃን ውስጥ ሲፈተሽ በኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቆ ሥራ ላይ የዋለው በወንጀል የተገኘ ንብረትን ሕጋዊ ማስመሰልን እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከል የወጣው አዋጅ፣ ከአገራዊ የሕገ-መንግስት ድንጋጌዎችና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ሕጎች አኳያ ሲታይ በርካታ ጥያቄዎችን የሚያስነሳ ሆኖ አግኝተነዋል። በተለይም "በሽፋን ስር ምርመራ የሚያደርጉ መርማሪዎች ከግድያ ውጪ በሆነ በማንኛውም ወንጀል ተጠያቂ እንደማይሆኑ" የሚያዘው ድንጋጌ፣ የሕግ የበላይነትን እና የሰብዓዊ መብቶችን መርሆዎች አደጋ ላይ የሚጥል ነው የሚሉ አስተያየቶች በስፋት እየተሰሙ ነው።
#የኢትዮጵያ_ሕገ-መንግስት እና #የአዋጁ_ተግዳሮቶች
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግስት፣ በመሰረታዊ መብቶችና ነጻነቶች ዙሪያ ሰፊ ድንጋጌዎችን አስቀምጧል። በተለይም አንቀጽ 13 የመንግስት አካላት ሁሉ በሕገ-መንግስቱ የተደነገጉትን የሰብዓዊ መብቶችና ነጻነቶች የማክበርና የማስከበር ግዴታ እንዳለባቸው ይደነግጋል። አንቀጽ 14 የሰብዓዊ ክብርን፣ አንቀጽ 15 የሕይወት መብትን፣ አንቀጽ 16 የአካል ደህንነት መብትን፣ አንቀጽ 17 የነጻነት መብትን፣ አንቀጽ 18 ደግሞ ጭካኔ የተሞላበት፣ ኢ-ሰብዓዊ ወይም አዋራጅ ቅጣት ወይም አያያዝን ይከለክላል።
አዲሱ አዋጅ "መርማሪዎች ከግድያ ውጪ በማንኛውም ወንጀል አይጠየቁም" በሚለው ድንጋጌው፣ እነዚህን የሕገ-መንግስት መርሆዎች የሚጻረር ነው የሚል ጠንካራ መከራከሪያ ይቀርባል። አንድ መርማሪ ገንዘብ በመቀበል፣ ንጹሃንን በማሰቃየት ወይም ሌላ የመብት ጥሰት በመፈጸም ተጠያቂነትን የሚያመልጥ ከሆነ፣ የሕገ-መንግስቱ የመብቶች ጥበቃ ዋጋ የለውም የሚል ስጋት ይፈጠራል። ይህ ድንጋጌ ለሙስና፣ ለሥልጣን አላግባብ መጠቀም እና ለሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ክፍት በር ሊከፍት ይችላል።
#ዓለም_አቀፍ_ሕጎችና_ስምምነቶች
ኢትዮጵያ በርካታ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ስምምነቶችንና ኮንቬንሽኖችን አጽድቃለች።
ከእነዚህም መካከል፡-
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቻርተር (UN Charter): ይህ ቻርተር የሰብዓዊ መብቶችን ማክበር እና ማስከበር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መሰረታዊ ዓላማዎች አንዱ እንደሆነ ይገልጻል።
ዓለም አቀፍ የሲቪል እና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን (International Covenant on Civil and Political Rights - ICCPR): ኢትዮጵያ ይህን ቃል ኪዳን አጽድቃለች። ቃል ኪዳኑ በግልጽ የሕይወትን፣ የነጻነትን፣ ከማሰቃየት የመጠበቅን እና የሕግ ፊት እኩልነትን መብቶች ያስቀምጣል። የትኛውም አገር ሽብርተኝነትን ለመዋጋት በሚል ሰበብ እነዚህን መሰረታዊ መብቶች መርገጥ እንደሌለበት ዓለም አቀፍ ሕግ ያዛል።
የማሰቃየትን እና ሌሎች ጭካኔ የተሞላባቸው፣ ኢ-ሰብዓዊ ወይም አዋራጅ ቅጣቶችን ወይም አያያዞችን የሚከለክል ኮንቬንሽን (Convention Against Torture and Other Cruel, Inhuman or Degrading Treatment or Punishment - CAT): ኢትዮጵያ የዚህ ኮንቬንሽን አባል ስትሆን፣ ማሰቃየትን በማንኛውም ሁኔታ ለመከልከል እና ወንጀለኞችን ተጠያቂ ለማድረግ ግዴታ አለባት። አዲሱ አዋጅ "መርማሪው ማሰቃየት ቢፈጽም አይጠየቅም ማለት ነው?" የሚለው ስጋት፣ የዚህን ኮንቬንሽን መርሆዎች የሚጻረር ነው።
በተጨማሪም፣ ገንዘብ ሕገወጥ የማድረግ (Money Laundering) እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት (Terrorist Financing) ወንጀሎችን ለመዋጋት የወጡ ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ቢኖሩም፣ እነዚህ ስምምነቶች ወንጀልን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት የሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩ አበክረው ያሳስባሉ። የፋይናንስ ተግባር ግብረ ኃይል (Financial Action Task Force - FATF) ያሉ ድርጅቶችም ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመዋጋት የሚረዱ ደረጃዎችን ሲያወጡ፣ የሕግ የበላይነትን እና የመብቶችን ጥበቃ ግምት ውስጥ ያስገባሉ።
#የሞራል_ሕግ_እና_የሕግ_የበላይነት
ከሕግ በላይ የሆነ የሞራል ሕግ አለ የሚለው መርህ በበርካታ ፍልስፍናዎች እና የሕግ አስተምህሮዎች ዘንድ ተቀባይነት አለው። ይህ ማለት አንድ ሕግ በጽሑፍ ቢቀመጥም፣ ዓለም አቀፍ የሞራል እና የፍትህ መርሆዎችን የሚጻረር ከሆነ ተቀባይነት የለውም። "ከግድያ ውጪ በሌላ ወንጀል አይጠየቅም" የሚለው ድንጋጌ፣ የሕግ የበላይነትን እና የፍትህን መሰረታዊ መርሆዎች የሚዳፈር በመሆኑ፣ በብዙዎች ዘንድ የሞራል ብቁነት የለውም የሚል ትችት ይቀርብበታል። የሕግ የበላይነት ሁሉም ሰው ከሕግ በታች እኩል ነው የሚለውን መርህ ያመለክታል፤ የመርማሪዎችን ተጠያቂነት ማስቀረት ይህን መርህ ይጥሳል።
#የመናገር_እና_የመሰብሰብ_ነጻነት
አዋጁ በተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በጋዜጠኞች እና በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ላይ ጫና ይፈጥራል የሚለው ስጋትም ትልቅ ቦታ አለው። የኢትዮጵያ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 29 የመናገር እና የመግለጽ ነጻነትን፣ አንቀጽ 30 የመሰብሰብ፣ የመመደብ እና ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትን ያረጋግጣል። አዋጁ ከእነዚህ መብቶች ጋር እንዴት እንደሚጣጣም ግልጽ የሆነ ማብራሪያ ያስፈልገዋል። የመንግስት ተቃዋሚዎችን ወይም ሕጋዊ በሆነ መንገድ የፖሊሲ ትችት የሚያቀርቡ አካላትን "ሽብርተኝነትን መርዳት" በሚል ሰበብ ኢላማ ለማድረግ የሚያስችል ክፍተት እንዳለው የሚሰጋ ከሆነ፣ ለዴሞክራሲያዊ ምህዳር መስፋፋት እንቅፋት ይሆናል።
መደምደሚያ
ሽብርተኝነትን እና ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውርን መዋጋት የማንኛውም ሉዓላዊ መንግስት ሕጋዊ ግዴታ እና የዜጎች ደህንነት ጉዳይ ነው። ይሁን እንጂ፣ ይህ ትግል የዜጎችን መሰረታዊ መብቶች እና የሕግ የበላይነት መርሆዎችን ሳያጓድል መከናወን ይኖርበታል። አዲሱ አዋጅ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ሕጎችን እና የኢትዮጵያን ሕገ-መንግስት መሰረታዊ ድንጋጌዎችን የሚያከብር መሆኑን ለማረጋገጥ፣ ሰፊ ውይይት እና ምናልባትም ክለሳ ሊደረግበት ይገባል። አለበለዚያ፣ ሕግን ለማስከበር በሚል የሚወጡ ሕጎች ራሳቸው ለሕገ-ወጥነት በር ከፍተው የሞራል እና የሕግ ቀውስ ሊፈጥሩ ይችላሉ።
እናንተስ፣ አዲሱ አዋጅ የሀገራችንን ሕገ-መንግስት እና ዓለም አቀፍ ሕጎችን ያከብራል ብላችሁ ታስባላችሁ?
የህዝብ ጤና የሀገር ጤና ነው!
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
ሚኪያስ መላክ ተዘጋጅቶ በአለሕግ አማራጭ የሕግ እውቀት እና አገልግሎት ቀረበ ነው።
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
Linktree
AleHig | Instagram, Facebook, TikTok | Linktree
AleHig attorney & Legal consult present across multiple social media platforms..
❤10
#የአዋጁ_አስፈላጊነትና_የሕግ_ከለላ_ስጋቶች፣
የፍትህ ሚኒስቴር የአዋጅ ቁጥር 1387/2017ን በተመለከተ ማብራሪያ ቢሰጥም፣ የሕጉ አተገባበር በዜጎች መሠረታዊ ሰብዓዊ መብቶች እና የሕግ የበላይነት ላይ ሊያስከትል የሚችለው ተጽእኖ አሁንም አሳሳቢ ሆኖ ቀጥሏል። "አላምንም" የሚለው ምላሽዎም፣ በዚህ አዋጅ ዙሪያ ያለውን ሰፊ አለመተማመን የሚያንፀባርቅ ነው።
#እስቲ_ይህንን_ስጋት በዝርዝር እንመልከት።
#የአዋጁ_አስፈላጊነትና_የሕግ_ከለላ_ስጋቶች
አዋጅ ቁጥር 1387/2017 የወንጀል ድርጊት ማትረፍ እንደማይቻል ለማረጋገጥ፣ የገንዘብ ሕገወጥነትንና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከል ያለመ መሆኑን የፍትህ ሚኒስቴር ያብራራል። አዋጁ ከቀድሞው አዋጅ ቁጥር 780/2005 በተሻለ መልኩ 21 አመንጪ ወንጀሎችን በዝርዝር ማካተቱ፣ ጠንካራ የአሰራር ስርዓት ማበጀቱ እና የዋና ተጠቃሚዎችን ማንነት የመለየት ሥርዓት መዘርጋቱ፣ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመከላከል ከዓለም አቀፍ መስፈርቶች ጋር ለመጣጣም ጠቃሚ እርምጃዎች ናቸው።
ሆኖም፣ የአዋጁ ዋነኛ አወዛጋቢ ነጥብ "በሽፋን ስር ምርመራ" ለሚያካሂዱ መርማሪዎች የሚሰጠው የሕግ ከለላ (Immunity) ነው። ሚኒስቴሩ ይህ ከለላ የሚሰጠው መርማሪው "በራሱ ፈቃድ አስቦና ፈቅዶ ሳይሆን ያለፈቃዱ፣ ተገዶ፣ በተጽእኖ፣ ወይም ከአቅሙ በላይ በሆነ ማንኛውንም ምክንያት ሌላ ከባድ ጉዳትን ለማስቀረት ወይም የተሰጠውን ሕጋዊ ተልእኮ ለማሳካት ሲል" ለሚፈጽመው ወንጀል መሆኑን ቢያብራራም፣ ይህ ትርጓሜ በተግባር አደገኛ ስጋቶችን ይዞ ይመጣል።
#የግዳጅ" ትርጓሜ ብዥታ እና የተጠያቂነት ክፍተቶች
የ"ግዳጅ" የሚለው ቃል አተረጓጎም እና አተገባበር አሁንም ግልጽ አይደለም። መርማሪው በእርግጥ ተገዶ ነው ወይስ በፈቃደኝነት ወንጀል የፈጸመው? ይህንን ለመወሰን የሚያስችል ግልጽ፣ ተጨባጭ እና ገለልተኛ የክትትልና የቁጥጥር ሥርዓት ከሌለ፣ የሕግ ከለላው ለሥልጣን አላግባብ መጠቀም ምቹ ሽፋን ሊሆን ይችላል። ሕግን አስከባሪ አካላት ራሳቸው ለሕግ ተገዢ መሆናቸውን ማረጋገጥ እጅግ አስፈላጊ ነው።
በተጨማሪም፣ አዋጁ "ከግድያ ውጪ" የሚል ገደብ ቢያስቀምጥም፣ እንደ ማሰቃየት፣ ሕገወጥ እስር፣ ከሕግ ውጪ የሆነ የገንዘብ ዝውውር እና ሌሎች የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በመርማሪዎች ቢፈጸሙ፣ ተጠያቂነትን የሚያረጋግጥበት መንገድ ምን ያህል ጠንካራ ነው የሚለው ጥያቄ መልስ አላገኘም። የኢትዮጵያ ሕገ-መንግስት (አንቀጽ 18) ከጭካኔ የተሞላበት፣ ኢ-ሰብዓዊ ወይም አዋራጅ ቅጣት የመጠበቅ መብትን ይደነግጋል። ኢትዮጵያ የፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ሕጎች፣ በተለይም የማሰቃየትን የሚከለክል ኮንቬንሽን (CAT)፣ ማሰቃየትን ጨምሮ ማንኛውንም ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት ይከለክላሉ።
"በግዳጅ ተደረገ" በሚል ሽፋን እነዚህ ወንጀሎች ያለ ቅጣት እንዲያልፉ ከተደረገ፣ የአገር ውስጥም ሆነ ዓለም አቀፍ የሕግ ግዴታዎች ይጣሳሉ። ይህ ደግሞ እርስዎ የገለጹትን "ሕጋዊ ህገወጥ" ተግባራት መራባት ያስከትላል።
#ዲሞክራሲያዊ ምህዳር እና #የሕግ_የበላይነት_ስጋት
አዋጁ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት ያለመ ቢሆንም፣ የፖለቲካ ተቃዋሚዎችን፣ ጋዜጠኞችን እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን ኢላማ ለማድረግ የሚያስችል ክፍተት እንዳለው የሚሰነዘረው ስጋት ተገቢ ነው። የኢትዮጵያ ሕገ-መንግስት (አንቀጽ 29 እና 30) የመናገር፣ የመሰብሰብና የመደራጀት መብቶችን በግልጽ ያረጋግጣል። ማንኛውም ሕግ እነዚህን መብቶች ምክንያታዊ በሆነ መልኩ ብቻ ሊገድብ ይገባል እንጂ ሊያጠፋ አይገባም። የመንግስት ተቃዋሚዎችን ወይም ሕጋዊ በሆነ መንገድ የፖሊሲ ትችት የሚያቀርቡ አካላትን "ሽብርተኝነትን መርዳት" በሚል ሰበብ ኢላማ ለማድረግ የሚያስችል ክፍተት እንዳለው የሚሰጋ ከሆነ፣ የሀገሪቱ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት በእጅጉ ይጎዳል።
#የሕግ_የበላይነት ማለት ሁሉም ሰው፣ መንግስትንና ባለሥልጣናትን ጨምሮ፣ ለሕግ ተገዢ ነው ማለት ነው።
አዋጁ ለመርማሪዎች የሚሰጠው ልዩ የሕግ ከለላ፣ ይህንን መርህ የሚሸረሽር እና ከመደበኛ የፍትህ ሥርዓት በላይ የሆነ "ልዩ ሥርዓት" የሚፈጥር ሆኖ ከታየ፣ አለመተማመን መፈጠሩ አይቀሬ ነው። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ የመብቶች ጥሰት እና ተጠያቂነት አለመኖር ሲነሱ የቆዩ ስጋቶች እንደነበሩ ግምት ውስጥ ሲገባ፣ አዲሱ አዋጅ እነዚህን ስጋቶች ይበልጥ የሚያባብስ ነው የሚል ስሜት መፍጠሩ ተፈጥሯዊ ነው።
#የሕግ_ማዕቀፎች የሀገርን ደህንነት ማስጠበቅ ሲገባቸው፣ በተመሳሳይ መልኩ የዜጎችን መብት ዋስትና መስጠት እና የሕግ የበላይነትን ማክበር አለባቸው። አንዱን ለማስጠበቅ ሌላውን መስዋዕት ማድረግ ዘላቂ ሰላምንና መረጋጋትን አያመጣም። የአዋጅ ቁጥር 1387/2017 ተግባራዊነት፣ የመሠረታዊ መብቶችን እና የሕግ የበላይነትን ዋጋ እንዳይቀንስ ከፍተኛ ጥንቃቄ እና ቁርጠኝነት ይጠይቃል። ያለበለዚያ፣ አደገኛ ሁኔታዎችን በመፍጠር ወደ #"ሕጋዊ_ህገወጥ" ድርጊቶች ሊያመራ የሚችልበት ስጋት #አለ።
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
ሚኪያስ መላክ ተዘጋጅቶ በአለሕግ አማራጭ የሕግ እውቀት እና አገልግሎት ቀረበ ነው።
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
የፍትህ ሚኒስቴር የአዋጅ ቁጥር 1387/2017ን በተመለከተ ማብራሪያ ቢሰጥም፣ የሕጉ አተገባበር በዜጎች መሠረታዊ ሰብዓዊ መብቶች እና የሕግ የበላይነት ላይ ሊያስከትል የሚችለው ተጽእኖ አሁንም አሳሳቢ ሆኖ ቀጥሏል። "አላምንም" የሚለው ምላሽዎም፣ በዚህ አዋጅ ዙሪያ ያለውን ሰፊ አለመተማመን የሚያንፀባርቅ ነው።
#እስቲ_ይህንን_ስጋት በዝርዝር እንመልከት።
#የአዋጁ_አስፈላጊነትና_የሕግ_ከለላ_ስጋቶች
አዋጅ ቁጥር 1387/2017 የወንጀል ድርጊት ማትረፍ እንደማይቻል ለማረጋገጥ፣ የገንዘብ ሕገወጥነትንና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከል ያለመ መሆኑን የፍትህ ሚኒስቴር ያብራራል። አዋጁ ከቀድሞው አዋጅ ቁጥር 780/2005 በተሻለ መልኩ 21 አመንጪ ወንጀሎችን በዝርዝር ማካተቱ፣ ጠንካራ የአሰራር ስርዓት ማበጀቱ እና የዋና ተጠቃሚዎችን ማንነት የመለየት ሥርዓት መዘርጋቱ፣ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመከላከል ከዓለም አቀፍ መስፈርቶች ጋር ለመጣጣም ጠቃሚ እርምጃዎች ናቸው።
ሆኖም፣ የአዋጁ ዋነኛ አወዛጋቢ ነጥብ "በሽፋን ስር ምርመራ" ለሚያካሂዱ መርማሪዎች የሚሰጠው የሕግ ከለላ (Immunity) ነው። ሚኒስቴሩ ይህ ከለላ የሚሰጠው መርማሪው "በራሱ ፈቃድ አስቦና ፈቅዶ ሳይሆን ያለፈቃዱ፣ ተገዶ፣ በተጽእኖ፣ ወይም ከአቅሙ በላይ በሆነ ማንኛውንም ምክንያት ሌላ ከባድ ጉዳትን ለማስቀረት ወይም የተሰጠውን ሕጋዊ ተልእኮ ለማሳካት ሲል" ለሚፈጽመው ወንጀል መሆኑን ቢያብራራም፣ ይህ ትርጓሜ በተግባር አደገኛ ስጋቶችን ይዞ ይመጣል።
#የግዳጅ" ትርጓሜ ብዥታ እና የተጠያቂነት ክፍተቶች
የ"ግዳጅ" የሚለው ቃል አተረጓጎም እና አተገባበር አሁንም ግልጽ አይደለም። መርማሪው በእርግጥ ተገዶ ነው ወይስ በፈቃደኝነት ወንጀል የፈጸመው? ይህንን ለመወሰን የሚያስችል ግልጽ፣ ተጨባጭ እና ገለልተኛ የክትትልና የቁጥጥር ሥርዓት ከሌለ፣ የሕግ ከለላው ለሥልጣን አላግባብ መጠቀም ምቹ ሽፋን ሊሆን ይችላል። ሕግን አስከባሪ አካላት ራሳቸው ለሕግ ተገዢ መሆናቸውን ማረጋገጥ እጅግ አስፈላጊ ነው።
በተጨማሪም፣ አዋጁ "ከግድያ ውጪ" የሚል ገደብ ቢያስቀምጥም፣ እንደ ማሰቃየት፣ ሕገወጥ እስር፣ ከሕግ ውጪ የሆነ የገንዘብ ዝውውር እና ሌሎች የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በመርማሪዎች ቢፈጸሙ፣ ተጠያቂነትን የሚያረጋግጥበት መንገድ ምን ያህል ጠንካራ ነው የሚለው ጥያቄ መልስ አላገኘም። የኢትዮጵያ ሕገ-መንግስት (አንቀጽ 18) ከጭካኔ የተሞላበት፣ ኢ-ሰብዓዊ ወይም አዋራጅ ቅጣት የመጠበቅ መብትን ይደነግጋል። ኢትዮጵያ የፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ሕጎች፣ በተለይም የማሰቃየትን የሚከለክል ኮንቬንሽን (CAT)፣ ማሰቃየትን ጨምሮ ማንኛውንም ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት ይከለክላሉ።
"በግዳጅ ተደረገ" በሚል ሽፋን እነዚህ ወንጀሎች ያለ ቅጣት እንዲያልፉ ከተደረገ፣ የአገር ውስጥም ሆነ ዓለም አቀፍ የሕግ ግዴታዎች ይጣሳሉ። ይህ ደግሞ እርስዎ የገለጹትን "ሕጋዊ ህገወጥ" ተግባራት መራባት ያስከትላል።
#ዲሞክራሲያዊ ምህዳር እና #የሕግ_የበላይነት_ስጋት
አዋጁ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት ያለመ ቢሆንም፣ የፖለቲካ ተቃዋሚዎችን፣ ጋዜጠኞችን እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን ኢላማ ለማድረግ የሚያስችል ክፍተት እንዳለው የሚሰነዘረው ስጋት ተገቢ ነው። የኢትዮጵያ ሕገ-መንግስት (አንቀጽ 29 እና 30) የመናገር፣ የመሰብሰብና የመደራጀት መብቶችን በግልጽ ያረጋግጣል። ማንኛውም ሕግ እነዚህን መብቶች ምክንያታዊ በሆነ መልኩ ብቻ ሊገድብ ይገባል እንጂ ሊያጠፋ አይገባም። የመንግስት ተቃዋሚዎችን ወይም ሕጋዊ በሆነ መንገድ የፖሊሲ ትችት የሚያቀርቡ አካላትን "ሽብርተኝነትን መርዳት" በሚል ሰበብ ኢላማ ለማድረግ የሚያስችል ክፍተት እንዳለው የሚሰጋ ከሆነ፣ የሀገሪቱ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት በእጅጉ ይጎዳል።
#የሕግ_የበላይነት ማለት ሁሉም ሰው፣ መንግስትንና ባለሥልጣናትን ጨምሮ፣ ለሕግ ተገዢ ነው ማለት ነው።
አዋጁ ለመርማሪዎች የሚሰጠው ልዩ የሕግ ከለላ፣ ይህንን መርህ የሚሸረሽር እና ከመደበኛ የፍትህ ሥርዓት በላይ የሆነ "ልዩ ሥርዓት" የሚፈጥር ሆኖ ከታየ፣ አለመተማመን መፈጠሩ አይቀሬ ነው። ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ የመብቶች ጥሰት እና ተጠያቂነት አለመኖር ሲነሱ የቆዩ ስጋቶች እንደነበሩ ግምት ውስጥ ሲገባ፣ አዲሱ አዋጅ እነዚህን ስጋቶች ይበልጥ የሚያባብስ ነው የሚል ስሜት መፍጠሩ ተፈጥሯዊ ነው።
#የሕግ_ማዕቀፎች የሀገርን ደህንነት ማስጠበቅ ሲገባቸው፣ በተመሳሳይ መልኩ የዜጎችን መብት ዋስትና መስጠት እና የሕግ የበላይነትን ማክበር አለባቸው። አንዱን ለማስጠበቅ ሌላውን መስዋዕት ማድረግ ዘላቂ ሰላምንና መረጋጋትን አያመጣም። የአዋጅ ቁጥር 1387/2017 ተግባራዊነት፣ የመሠረታዊ መብቶችን እና የሕግ የበላይነትን ዋጋ እንዳይቀንስ ከፍተኛ ጥንቃቄ እና ቁርጠኝነት ይጠይቃል። ያለበለዚያ፣ አደገኛ ሁኔታዎችን በመፍጠር ወደ #"ሕጋዊ_ህገወጥ" ድርጊቶች ሊያመራ የሚችልበት ስጋት #አለ።
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
ሚኪያስ መላክ ተዘጋጅቶ በአለሕግ አማራጭ የሕግ እውቀት እና አገልግሎት ቀረበ ነው።
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
Linktree
AleHig | Instagram, Facebook, TikTok | Linktree
AleHig attorney & Legal consult present across multiple social media platforms..
❤13🔥1
በድብቅ የሚደረግ ምርመራ በአዲሱ አዋጅ መሰረት
የፍትሕ ሚኒስቴር በቅርቡ የጸደቀው፣ የወንጀል ንብረትን ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ፣ ከፍርድ ቤት ፈቃድ ውጪ የሚደረግ ምርመራን እንደማይፈቅድ አስታውቋል።
ይህ ማብራሪያ አዋጁን በተመለከተ በሕዝብ ዘንድ ያለውን የተሳሳተ ግንዛቤ ለመፍታት ያለመ ነው።
የፍትሕ ሚኒስቴር ማብራሪያ፦
ሚኒስቴሩ አዲሱ አዋጅ ከመደበኛው የወንጀል ምርመራ ሂደት የተለየ መንገድ እንደሚከተል አጽንኦት ሰጥቷል። እንዲህም ሲል አብራርቷል፦
ከተለመደው ምርመራ የተለየ ነው፡ እንደ ተለመደው ምርመራ፣ ተጠርጣሪዎችን በፍርድ ቤት ትእዛዝ መያዝ፣ ሰነዶችን መሰብሰብ እና ምስክሮችን መስማት የመሳሰሉትን ሂደቶች አይከተልም።
ውስብስብ ወንጀሎች ላይ ያተኩራል፡ አዋጁ ውስብስብ ወንጀሎችን ከመሰረቱ ለመለየት የሚያስችል የምርመራ ሂደትን የሚከተል ነው። ለምሳሌ፣ መርማሪ አካል፡-
እንደ ወንጀለኛ መስሎ ከወንጀለኞች ጋር ሊቀላቀል ወይም አብሮ ሊሰራ ይችላል።
እንደ ተባባሪ መስሎ አብሮ ውሎ ሊያድር ይችላል።
ወንጀለኞች ሲሸጡ ገዢ መስሎ፣ ሲገዙ ደግሞ ሻጭ መስሎ ሊሆን ይችላል።
የፍርድ ቤት ትእዛዝ ሚና፦
የፍርድ ቤት ትእዛዝ ግዴታ ነው፡ መርማሪው አካል ምርመራ ማድረግ የሚችለው የፍርድ ቤት ትእዛዝ ሲያገኝ ብቻ ነው።
የፍርድ ቤት ግልጽ መመሪያዎች፡ ፍርድ ቤት በአሳማኝ ምክንያት በሽፋን የሚደረግ ምርመራ እንዲደረግ ሲፈቅድ፣ አዋጁ በትእዛዙ ላይ የሚከተሉትን በግልጽ ማስቀመጥ እንዳለበት ደንግጓል፦
የምርመራው ዘዴ።
የአተገባበር ሁኔታ።
ምርመራው የሚከናወንበት ጊዜ።
የተሳሳቱ ግንዛቤዎች ማስተባበያ፦
ሚኒስቴሩ ስለ አዲሱ አዋጅ ያሉትን በርካታ የተሳሳቱ ግንዛቤዎችን አስተባብሏል፦
ማሰቃየት ወይም ማስገደድ የለም፡ አዋጁ ተጠርጣሪን አስሮ በማሰቃየት እንዲመረመር አይፈቅድም፣ እንዲሁም ማስረጃዎችን በማስገደድ እንዲሰበሰቡ አያደርግም።
ይህ ፈጽሞ ስህተት ነው።
ለወንጀል ድርጊት ተጠያቂነት፡ አዋጁ ወንጀል ለፈጸሙ መርማሪዎች ያለመከሰስ መብት አይሰጥም። ፍርድ ቤት በአሳማኝ ምክንያት በሽፋን ስር የሚደረግ ልዩ የምርመራ ዘዴ እንዲተገበር ሲፈቅድ፣ መርማሪው በተጠርጣሪዎች ወይም በሌላ ሦስተኛ ወገኖች ላይ ወንጀል ቢፈጽም፣ በወንጀል ይጠየቃል።
መርማሪ ከክስ ነጻ የሚሆንባቸው ሁኔታዎች፦
ሚኒስቴሩ፣ መርማሪ ከወንጀል ክስ ነጻ የሚሆንበትን ልዩ ድንጋጌ አስረድቷል፤ ይህ ግን ወንጀል ለመፈጸም አጠቃላይ ያለመከሰስ መብት አይደለም፦
ይህ ነጻ መሆን የሚመለከተው መርማሪው ከተጠርጣሪዎች ጋር የወንጀል ተካፋይ ወይም ግብረ-አበር ሲሆን፣ ይህን ያደረገው በራሱ ፈቃድ አስቦና ፈቅዶ ሳይሆን፦
ያለፈቃዱ፣
ተገዶ፣
በተጽእኖ፣
በተጠርጣሪዎች ሕገ ወጥ ትዕዛዝ፣ ወይም
ከአቅሙ በላይ በሆነ በማንኛውም ምክንያት ሌላ ከባድ ጉዳትን ለማስቀረት ወይም የተሰጠውን ሕጋዊ ተልእኮ ለማሳካት ሲል ወንጀል የሚፈጽምበት ሁኔታ ሲኖር ነው።
ይህ ድንጋጌ የሚያሳየው መርማሪ በምርመራ ወቅት ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያት (ከግድያ ውጪ) ማንኛውንም ዓይነት ወንጀል ቢፈጽም ከወንጀል ክስ ነጻ የሚደረግበትን ሁኔታ ለማመላከት የተደነገገ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።
የሕዝብ ስጋቶች፦
ይህ አዋጅ፣ መርማሪዎችን በአቅማቸው በላይ በሆነ ምክንያት (ከግድያ በስተቀር) ማንኛውንም ወንጀል ቢፈጽሙ ተጠያቂ የማያደርግ መሆኑ፣ ከምክር ቤት ትችት ሲቀርብበት ቆይቷል። ተቺዎች ይህ ድንጋጌ መርማሪዎችን ወንጀል እንዲፈጽሙ በር ይከፍታል የሚል ስጋት አላቸው።
ይህ የፍትሕ ሚኒስቴር ማብራሪያ፣ በድብቅ የሚደረጉ ምርመራዎች የሚከናወኑበትን ሁኔታዎች እና ገደቦች ግልጽ ለማድረግ ያለመ ሲሆን፣ የፍርድ ቤት ቁጥጥር ወሳኝ መሆኑን በማጉላት፣ ሊኖር በሚችል አላግባብ አጠቃቀም ዙሪያ የሚነሱ ስጋቶችን ለመፍታት ይሞክራል።
ፍትሕ ሚኒስቴር
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
የፍትሕ ሚኒስቴር በቅርቡ የጸደቀው፣ የወንጀል ንብረትን ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ፣ ከፍርድ ቤት ፈቃድ ውጪ የሚደረግ ምርመራን እንደማይፈቅድ አስታውቋል።
ይህ ማብራሪያ አዋጁን በተመለከተ በሕዝብ ዘንድ ያለውን የተሳሳተ ግንዛቤ ለመፍታት ያለመ ነው።
የፍትሕ ሚኒስቴር ማብራሪያ፦
ሚኒስቴሩ አዲሱ አዋጅ ከመደበኛው የወንጀል ምርመራ ሂደት የተለየ መንገድ እንደሚከተል አጽንኦት ሰጥቷል። እንዲህም ሲል አብራርቷል፦
ከተለመደው ምርመራ የተለየ ነው፡ እንደ ተለመደው ምርመራ፣ ተጠርጣሪዎችን በፍርድ ቤት ትእዛዝ መያዝ፣ ሰነዶችን መሰብሰብ እና ምስክሮችን መስማት የመሳሰሉትን ሂደቶች አይከተልም።
ውስብስብ ወንጀሎች ላይ ያተኩራል፡ አዋጁ ውስብስብ ወንጀሎችን ከመሰረቱ ለመለየት የሚያስችል የምርመራ ሂደትን የሚከተል ነው። ለምሳሌ፣ መርማሪ አካል፡-
እንደ ወንጀለኛ መስሎ ከወንጀለኞች ጋር ሊቀላቀል ወይም አብሮ ሊሰራ ይችላል።
እንደ ተባባሪ መስሎ አብሮ ውሎ ሊያድር ይችላል።
ወንጀለኞች ሲሸጡ ገዢ መስሎ፣ ሲገዙ ደግሞ ሻጭ መስሎ ሊሆን ይችላል።
የፍርድ ቤት ትእዛዝ ሚና፦
የፍርድ ቤት ትእዛዝ ግዴታ ነው፡ መርማሪው አካል ምርመራ ማድረግ የሚችለው የፍርድ ቤት ትእዛዝ ሲያገኝ ብቻ ነው።
የፍርድ ቤት ግልጽ መመሪያዎች፡ ፍርድ ቤት በአሳማኝ ምክንያት በሽፋን የሚደረግ ምርመራ እንዲደረግ ሲፈቅድ፣ አዋጁ በትእዛዙ ላይ የሚከተሉትን በግልጽ ማስቀመጥ እንዳለበት ደንግጓል፦
የምርመራው ዘዴ።
የአተገባበር ሁኔታ።
ምርመራው የሚከናወንበት ጊዜ።
የተሳሳቱ ግንዛቤዎች ማስተባበያ፦
ሚኒስቴሩ ስለ አዲሱ አዋጅ ያሉትን በርካታ የተሳሳቱ ግንዛቤዎችን አስተባብሏል፦
ማሰቃየት ወይም ማስገደድ የለም፡ አዋጁ ተጠርጣሪን አስሮ በማሰቃየት እንዲመረመር አይፈቅድም፣ እንዲሁም ማስረጃዎችን በማስገደድ እንዲሰበሰቡ አያደርግም።
ይህ ፈጽሞ ስህተት ነው።
ለወንጀል ድርጊት ተጠያቂነት፡ አዋጁ ወንጀል ለፈጸሙ መርማሪዎች ያለመከሰስ መብት አይሰጥም። ፍርድ ቤት በአሳማኝ ምክንያት በሽፋን ስር የሚደረግ ልዩ የምርመራ ዘዴ እንዲተገበር ሲፈቅድ፣ መርማሪው በተጠርጣሪዎች ወይም በሌላ ሦስተኛ ወገኖች ላይ ወንጀል ቢፈጽም፣ በወንጀል ይጠየቃል።
መርማሪ ከክስ ነጻ የሚሆንባቸው ሁኔታዎች፦
ሚኒስቴሩ፣ መርማሪ ከወንጀል ክስ ነጻ የሚሆንበትን ልዩ ድንጋጌ አስረድቷል፤ ይህ ግን ወንጀል ለመፈጸም አጠቃላይ ያለመከሰስ መብት አይደለም፦
ይህ ነጻ መሆን የሚመለከተው መርማሪው ከተጠርጣሪዎች ጋር የወንጀል ተካፋይ ወይም ግብረ-አበር ሲሆን፣ ይህን ያደረገው በራሱ ፈቃድ አስቦና ፈቅዶ ሳይሆን፦
ያለፈቃዱ፣
ተገዶ፣
በተጽእኖ፣
በተጠርጣሪዎች ሕገ ወጥ ትዕዛዝ፣ ወይም
ከአቅሙ በላይ በሆነ በማንኛውም ምክንያት ሌላ ከባድ ጉዳትን ለማስቀረት ወይም የተሰጠውን ሕጋዊ ተልእኮ ለማሳካት ሲል ወንጀል የሚፈጽምበት ሁኔታ ሲኖር ነው።
ይህ ድንጋጌ የሚያሳየው መርማሪ በምርመራ ወቅት ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያት (ከግድያ ውጪ) ማንኛውንም ዓይነት ወንጀል ቢፈጽም ከወንጀል ክስ ነጻ የሚደረግበትን ሁኔታ ለማመላከት የተደነገገ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።
የሕዝብ ስጋቶች፦
ይህ አዋጅ፣ መርማሪዎችን በአቅማቸው በላይ በሆነ ምክንያት (ከግድያ በስተቀር) ማንኛውንም ወንጀል ቢፈጽሙ ተጠያቂ የማያደርግ መሆኑ፣ ከምክር ቤት ትችት ሲቀርብበት ቆይቷል። ተቺዎች ይህ ድንጋጌ መርማሪዎችን ወንጀል እንዲፈጽሙ በር ይከፍታል የሚል ስጋት አላቸው።
ይህ የፍትሕ ሚኒስቴር ማብራሪያ፣ በድብቅ የሚደረጉ ምርመራዎች የሚከናወኑበትን ሁኔታዎች እና ገደቦች ግልጽ ለማድረግ ያለመ ሲሆን፣ የፍርድ ቤት ቁጥጥር ወሳኝ መሆኑን በማጉላት፣ ሊኖር በሚችል አላግባብ አጠቃቀም ዙሪያ የሚነሱ ስጋቶችን ለመፍታት ይሞክራል።
ፍትሕ ሚኒስቴር
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
❤12👏5
ሕግ ለሰው ልጅ ቀንበር ወይስ አጋዥ?
ሰው ለሕግ ሳይሆን ሕግ ነው ለሰው የተሰጠው፣
ሰው ለሕግ ሳይሆን ሕግ ነው ለሰው የተሰጠው፣
ሕግ የተሰራው ለሰው ልጅ ጥቅም እንጂ፣ ሰው ለሕግ ተገዢ እንዲሆን ብቻ አይደለም። ሕግ የሰው ልጅ ሰላማዊና ፍትሃዊ ኑሮ እንዲመራ የሚያግዝ መሳሪያ ነው። በመሆኑም፣ ሕግጋት ሲተገበሩ የሰው ልጅ ክብርና መብት ማስከበር ላይ ማተኮር አለባቸው። ሕጎች የብዙሃንን መብትና ጥቅም የሚያስጠብቁ ሲሆኑ፣ ሕዝቡ ለሕግ የሚኖረው ክብር ይጨምራል።
👍7❤5
ሕግ ማለት ሰውን የሚያንጽ፣ የተሻለ ዜጋ የሚያደርግ፣ የሚያበለጽግ እና ወደተሻለ የኢኮኖሚ ደረጃ ለመድረስ በር የሚከፍት ሥርዓት የሚዘረጋ መሆን አለበት። ሕግ ሰዎች የሚገደቡበት፣ የሚያስጨንቅ፣ የሚያደኸይ፣ የሚጎዳና የሚያንገበግብ መሆን የለበትም። በተሻለ ነፃነት የሚያኖር እና ሕጉን ለሚያከብሩ የሚያበረታታ ሲሆን፣ ለማያከብሩት ግን ደግሞ በተቃራኒው በዋናነት የሚያስተምር ሲሆን ነገር ግን መተላለፉ ሲደጋገም የሚቀጣ መሆን አለበት።
#Mikias_Melak
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
#Mikias_Melak
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
Linktree
AleHig | Instagram, Facebook, TikTok | Linktree
AleHig attorney & Legal consult present across multiple social media platforms..
❤14👍5🤔1
👉👉👉ነገረ ግራ ቀኝ👈👈👈
🔼 ✔️ ❓ 🔥 📣 💥
በወንጀል ችሎት:-
✔️ ቀኝ:- ዐቃቤ ሕግ (መርማሪ ፖሊስ)
✔️ ግራ:- ተጠርጣሪ/ተከሳሽና ጠበቃው
በፍ/ብሔር ችሎት:-
✔️ ቀኝ:- ከሳሽ (አመልካች)
✔️ ግራ:- ተከሳሽ (መልስ ሰጭ)
ግራ ቀኙ የሚወሰነው ከችሎቱ አኳያ ነው::
(ከችሎቱ በስተቀኝ በስተ ግራ)
ይህ ከችሎት ሥርዓት ድንጋጌዎች ውስጥ አንዱ ሲሆን ባለጉዳዮች ፍ/ቤት ሲቀርቡ ይህን አውቀው መቀመጥና መቆም አለባቸው::
በወንጀል ችሎት:-
በፍ/ብሔር ችሎት:-
ግራ ቀኙ የሚወሰነው ከችሎቱ አኳያ ነው::
(ከችሎቱ በስተቀኝ በስተ ግራ)
ይህ ከችሎት ሥርዓት ድንጋጌዎች ውስጥ አንዱ ሲሆን ባለጉዳዮች ፍ/ቤት ሲቀርቡ ይህን አውቀው መቀመጥና መቆም አለባቸው::
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤11👍6
የንግድ ሥራ ፍቃድ ሳይኖራቸው በሞያ ፍቃድ ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ ጠበቆች ፣የኢንሹራንስ ወኪሎች ፣ኢንሹራንስ ጉዳት ገማች ግለሰቦች በሚመለከት:-
➡️ ከግብር አመቱ አጠቃላይ እንደ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ የንግድ ሥራ ያልሆነ ገቢ ያላቸው የመኖሪያ ቤት አከራዮች ከግብር አመቱ አጠቃላይ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ በግል ኮድ 02 እና በንግድ ኮድ 03 ተሸከርካሪ የኪራይ አገልግሎት የሚሰጡ አጠቃላይ የኪራይ ገቢ ላይ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት በመረጃ የሚወሰን በመሆኑ ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ በህግ ደረሰኝ የመጠቀም ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው የከተማ ውስጥ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎች /በቴክኖሎጂ ስምሪት የሚሰጣቸውን የሜትር ታከሲዎች ጨምሮ/ የገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 ሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ መወሰኑን ይገልጻል።
(ተጨማሪውን ከተያያዘው ደብዳቤ ይመልከቱ)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
Mikias_Melak
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
➡️ ከግብር አመቱ አጠቃላይ እንደ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ የንግድ ሥራ ያልሆነ ገቢ ያላቸው የመኖሪያ ቤት አከራዮች ከግብር አመቱ አጠቃላይ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ በግል ኮድ 02 እና በንግድ ኮድ 03 ተሸከርካሪ የኪራይ አገልግሎት የሚሰጡ አጠቃላይ የኪራይ ገቢ ላይ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት በመረጃ የሚወሰን በመሆኑ ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ በህግ ደረሰኝ የመጠቀም ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው የከተማ ውስጥ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎች /በቴክኖሎጂ ስምሪት የሚሰጣቸውን የሜትር ታከሲዎች ጨምሮ/ የገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 ሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ መወሰኑን ይገልጻል።
(ተጨማሪውን ከተያያዘው ደብዳቤ ይመልከቱ)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
Mikias_Melak
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
❤8👍1
ከውርስ መንቀል (Dishersion)
ከውርስ መንቀል ማለት አንድ ተናዛዥ የውርስ ሕግ በሚደነግገው መሠረት ባደረገው ኑዛዜ ውስጥ፣ ምክንያቱን በግልጽ በመግለጽ ወይም በዝምታ፣ ከወራሾቹ አንዱን ወይም ከአንድ በላይ የሆኑትን ወራሾች በውርሱ እንዳይካፈሉ ያደረገበት ሥርዓት ነው። ይህ በውርስ ሕግ እውቅና እና ውጤት የሚሰጠው የሕግ ሂደት ነው።
* ከወራሽነት ሙሉ በሙሉ ማውጣት: ከውርስ መንቀል ማለት ከውርስ ሀብቱ ምንም ዓይነት ድርሻ አለማግኘት እንጂ አነስተኛ ድርሻ ማግኘት አይደለም።
* የሕግ ድንጋጌዎች:
* የፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 937/1/ ተናዛዡ ከወራሾቹ አንዱን ከወራሽነት የመንቀል መብት እንዳለው ይደነግጋል።
* የፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 938/1/ ደግሞ፣ ተናዛዡ ልጅን ወይም ወደታች የሚቆጠረውን ወራሽ ለመንቀል የደረሰበትን ምክንያት በኑዛዜው ውስጥ ካልገለፀ በቀር፣ ያደረገው ኑዛዜ እንደማይፀና ያስቀምጣል። ይህ የሚያሳየው ህጉ የቅርብ ወራሾችን ከውርስ የመንቀል ጉዳይ ላይ ጥብቅ መስፈርቶችን እንዳስቀመጠ ነው።
* ተፈጻሚነት: ይህ እርምጃ ሊወሰድ የሚችለው ሕጉ ወራሾች በሚያደርጋቸው ግለሰቦች ላይ ብቻ ነው። አንድ ግለሰብ የሚወረሰው በ3ኛ ወይም 4ኛ ደረጃ ወራሾች በሚሆኑ ዘመዶቹ ከሆነ፣ ለሌላ ሰው ሲናዘዝ እነዚህን ዘመዶቹን በዝምታ ከውርሱ መንቀል ይችላል።
* አላማ: ከውርስ መንቀል ወራሾችን ከውርስ ሀብት የሚያስወግድ ጠንካራ ውሳኔ ነው። ይህ ውሳኔ በሰከነ አእምሮ እና በቂ ምክንያት መወሰድ እንዳለበት ታሳቢ መሆን አለበት። ያለ በቂ ምክንያት እና በእልህ ወይም በቁጣ ተነሳስቶ የሚደረግ ውሳኔ በዘላቂነት በሰዎች መካከል የስሜት መሻከርን ሊያስከትል ይችላል።
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ሚኪያስ መላክ ተዘጋጅቶ በአለሕግ አማራጭ የሕግ እውቀት እና አገልግሎት የቀረበ ነው።
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
ከውርስ መንቀል ማለት አንድ ተናዛዥ የውርስ ሕግ በሚደነግገው መሠረት ባደረገው ኑዛዜ ውስጥ፣ ምክንያቱን በግልጽ በመግለጽ ወይም በዝምታ፣ ከወራሾቹ አንዱን ወይም ከአንድ በላይ የሆኑትን ወራሾች በውርሱ እንዳይካፈሉ ያደረገበት ሥርዓት ነው። ይህ በውርስ ሕግ እውቅና እና ውጤት የሚሰጠው የሕግ ሂደት ነው።
* ከወራሽነት ሙሉ በሙሉ ማውጣት: ከውርስ መንቀል ማለት ከውርስ ሀብቱ ምንም ዓይነት ድርሻ አለማግኘት እንጂ አነስተኛ ድርሻ ማግኘት አይደለም።
* የሕግ ድንጋጌዎች:
* የፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 937/1/ ተናዛዡ ከወራሾቹ አንዱን ከወራሽነት የመንቀል መብት እንዳለው ይደነግጋል።
* የፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 938/1/ ደግሞ፣ ተናዛዡ ልጅን ወይም ወደታች የሚቆጠረውን ወራሽ ለመንቀል የደረሰበትን ምክንያት በኑዛዜው ውስጥ ካልገለፀ በቀር፣ ያደረገው ኑዛዜ እንደማይፀና ያስቀምጣል። ይህ የሚያሳየው ህጉ የቅርብ ወራሾችን ከውርስ የመንቀል ጉዳይ ላይ ጥብቅ መስፈርቶችን እንዳስቀመጠ ነው።
* ተፈጻሚነት: ይህ እርምጃ ሊወሰድ የሚችለው ሕጉ ወራሾች በሚያደርጋቸው ግለሰቦች ላይ ብቻ ነው። አንድ ግለሰብ የሚወረሰው በ3ኛ ወይም 4ኛ ደረጃ ወራሾች በሚሆኑ ዘመዶቹ ከሆነ፣ ለሌላ ሰው ሲናዘዝ እነዚህን ዘመዶቹን በዝምታ ከውርሱ መንቀል ይችላል።
* አላማ: ከውርስ መንቀል ወራሾችን ከውርስ ሀብት የሚያስወግድ ጠንካራ ውሳኔ ነው። ይህ ውሳኔ በሰከነ አእምሮ እና በቂ ምክንያት መወሰድ እንዳለበት ታሳቢ መሆን አለበት። ያለ በቂ ምክንያት እና በእልህ ወይም በቁጣ ተነሳስቶ የሚደረግ ውሳኔ በዘላቂነት በሰዎች መካከል የስሜት መሻከርን ሊያስከትል ይችላል።
በማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ሚኪያስ መላክ ተዘጋጅቶ በአለሕግ አማራጭ የሕግ እውቀት እና አገልግሎት የቀረበ ነው።
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
#የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#AleHig #አለሕግ #አለሕግ #ህግ
Linktree
AleHig | Instagram, Facebook, TikTok | Linktree
AleHig attorney & Legal consult present across multiple social media platforms..
❤11