አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.83K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
#ፓስፖርት : ፖስፖርት ለማውጣት ፋይዳ መታወቂያ መያዝ የግዴታ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።

ከሰኔ 1/2017 ጀምሮ የፋይዳ መታወቂያ ለፓስፖርት አገልግሎት ከሚስፈልጉ ዋና ሰነዶች ውስጥ አንዱ ይሆናል።

ከሰኔ 1 በኃላ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የፓስፖርት አገልግሎት ጥያቄ አቅርበው በመጠባበቅ ላይ ያሉ ግለሰቦች ፓስፖርት ለመውሰድ ሲመጡ የፋይዳ መታወቂያ ፦
- ልዩ ቁጥር መያዝ፣
- QR ኮዱን በወረቀት አትመው መያዝ፣
- ዲጂታል ኮፒውን በ "Fayda ID" application በኩል መያዝ ወይም ትክክለኛውን QR የያዘ ሌላ አማራጭ ተጠቅመው ይዘው ሲመጡ ብቻ ነው አገልግሎት የሚያገኙት ተብሏል።

@tikvahethiopia
አዋጆች በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፀደቁ በኋላ ደንብ እስከሚወጣ ድረስ ረዥም ጊዜ እየወሰደ በመሆኑ አዋጆቹ እየተጣሱ እንደሚገኙ ተገለጸ።

በተለይም በቅርቡ የፀደቀው የሪል እስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ አዋጅ ቁጥር 1357/2017 ደንብ ሳይወጣለት በመዘግየቱ ምክንያት በአዋጁ የተከለከሉ ተግባራት እየተፈጸሙ መሆኑን ምክር ቤቱ የከተማና መሰረተ ልማት የ9 ወራት ሪፖርት ባደመጠበት ወቅት አንስቷል።

ምክር ቤቱ እንደ ምሳሌ የጠቀሰው ይኸው አዋጅ 80 በመቶ የሪል እስቴት ግንባታ ሳይጠናቀቅ መሸጥን የሚከለክል ቢሆንም፣ ደንብ ባለመውጣቱ በአሁኑ ወቅት ግንባታ ያልተጀመረባቸው መሬቶች ሳይቀሩ እየተሸጡ እንዲሁም የተለያዩ ድርድሮች እየተካሄዱ መሆኑን አመልክቷል።

አዋጆች በቶሎ ደንብ ሳይወጣላቸው በመዘግየታቸው ክፍተቶች በመፈጠር አዋጁን የሚጥሱ አካላት እየተበራከቱ መምጣታቸው ስጋት እንደፈጠረም ካፒታል ሰምቷል።

በመሆኑም የሚመለከታቸው አካላት ደንቦችን በማፋጠን የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ ጥሪ ቀርቧል።

ይሁን እንጂ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር በበኩላቸው የሪል እስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ አዋጅ ተዘጋጅቶ እንዲጸድቅ መደረጉንና አዋጁን ተከትሎ የማስፈጸሚያ ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ ረቂቅ ደንቡን የማዳበር ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ በሪፖርታቸው አስታውቀዋል።

አዋጁ በመጽደቁ በሪል እስቴት አልሚዎች እና በቤት ገዥዎች መካከል ለዘመናት ሳይፈቱ የቆዩ ችግሮችን እየተፈቱ መምጣታቸው እና በቀጣይም አዋጁ ሲተገበር ችግሮችን መሰረታዊ በሆነ መልኩ አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወት ተገልጿል።

Source: capitalethiopia
#Ethiopianbusinessdaily
አንዱ ተጋቢ ከጋብቻ በፊት ባለው ንብረት ላይ ተጨማሪ ግንባታ በጋብቻ ውስጥ ከተደረገ የጋራ ንብረት ሳይሆን ያወጣውን ወጭ ይካፈላል/የፌደሬሽን ም/ቤት ውሳኔ❗️‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የደረጃ ሀ እና ለ ግብር ከፋዮች በሙሉ የሒሳብ መዝገብ ካላቀረቡ እንዳይስተናገዱ ተወሰነ

በዘጠኝ ወራት 160.9 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡ ተገልጿል

ከመጪው በጀት ዓመት ጀምሮ የደረጃ ሀ እና ለ ግብር ከፋዮች በሙሉ የሒሳብ መዝገብ ካላቀረቡ እንዳይስተናገዱ የሚያስገድድ ውሳኔ መተላለፉን፣ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ገለጸ።
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ሁሉም የደረጃ ሀ እና ለ ግብር ከፋዮች ሥርዓት ያለው የሒሳብ መዝገብ ካላቀረቡ ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ አይስተናገዱም፡፡
የደረጃ ሀ እና ለ ግብር ከፋይ ነጋዴዎች በታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008 መሠረት የሒሳብ መዝገብ እንዲይዙ በሕግ እንደሚገደዱ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። በዚህም መሠረት የወጪ ገቢ ሰነዳቸውን ባግባቡ አዘጋጅተው የሚስተናገዱ እንዳሉም ጠቁመዋል። ሆኖም በደረሰኝ ግብይት ካለመፈጸምና በሌሎች ምክንያቶች የሒሳብ መዝገብ ይዞ ለመገኘት ችግር አለ ያሉት አቶ ሰውነት፣ ‹‹አብዛኞቹ በተለይ የደረጃ ለ ግብር ከፋዮች በግም...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/140722/
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Council of Ministers Approves Draft Law Allowing Foreign Nationals to Own Real Estate in Ethiopia.

The Council of Ministers has recently approved a draft law permitting foreign nationals to own immovable property in Ethiopia and submitted it to parliament for ratification. Once enacted, this law is expected to bring several key benefits, including:

1. Boosting Foreign Investment: The legislation aims to attract foreign capital, stimulating economic growth and development.
2. Expanding the Housing and Real Estate Market: Allowing foreign nationals to own property will increase demand in both residential and commercial real estate, encouraging further development in the sector.
3. Creating Job Opportunities: New investments in construction, real estate, and related services will generate employment opportunities.

Additionally, the Council of Ministers has made decisions on other critical matters, including:
African Finance Corporation (AFC) Membership Agreement: Ethiopia’s accession to the AFC will enhance financial support and development project funding.
African Continental Free Trade Area (AfCFTA) Implementation: The agreement includes tariff reductions to promote intra-African trade and economic integration.
Service Fee Regulations: New guidelines ensure fair and efficient pricing for services provided by transport, logistics, and civil society organizations.

Overall, these reforms are expected to strengthen Ethiopia’s economy and encourage greater foreign investment.
Mikias Melak & Associates Law Office

🔴Attorney and Legal Consultant ጠበቃና የሕግ አማካሪ

Website & Social Media

https://www.linkedin.com/in/mikias-melak-76499811a?utm_source=share&utm_campaign=share_via&utm_content=profile&utm_medium=android_app

📱Facebook:
https://www.facebook.com/share/1BXx3RSsLZ/

📱Telegram: ✉️ @MikiasMelak⭐️📱

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com

Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595

Our Commitment
alehig.com #አለሕግ
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት

We provide expert legal advice, support, and resources on various laws, proclamations, regulations, and directives to empower and guide you.

Feel free to reach out anytime‼️
" አስተማሪ ተማሪውን የመምታት መብት የለውም በተማሪዋ ላይ ያደረሰችው ቅጣት ቀላልም ቢሆን እንኳ የአካል ጉዳት በማድረስ በህግ ያስጠይቃታል " - የህግ ባለሙያ

" የቤት ስራ አልሰራሽም " በማለት የሁለተኛ ክፍል ተማሪዋን ተገቢ ያልሆነና አጸያፊ የሆነ ቅጣት የቀጣችው መምህርት ከስራ ታግዳ በህግ ቁጥጥር ስር መደረጓ መገለፁ ይታወሳል።

በመሆኑም መምህርቷ በተማሪዋ ላይ የወሰደችው እርምጃ በህገመንግስቱ አንደት ይታያል ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ጠይቋል።

የህግ አማካሪና ጠበቃ ሳሙኤል ግርማ መምህርቷ የወሰደችው እርምጃ " ቀላል የአካል ጉዳት በማድረስ በወንጀል ህጉ 5/ 35 እስከ 3 አመት ፅኑ እስራት ቅጣት " ሊጠብቃት አንደሚችል ተናግረዋል።


የህግ ባለሙያው ምን አሉ ?

" አስተማሪ ተማሪውን የመምታት መብት የለውም በተማሪዋ ላይ ያደረሰችው ቅጣት ቀላልም ቢሆን እንኳ የአካል ጉዳት በማድረስ በህግ ያስጠይቃታል፣ በወንጀል ህጉ ደግሞ 5/ 35 እስከ 3 አመት ያሳስራል፣ ይህ ድርጊት ግን ከዚህም ባለፈ ነው የሚታየው " ብለዋል።

አክለውም " በአስተማሪ የዲስፕሊን መመሪያ በአስተዳደራዊ እርምጃ ከስራዋ ልትሰናበት የሚያስችል ወንጀል ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

የህግ ባለሙያው " መምህሯ ቅጣት ያደረሰችባት ተማሪ ከ13 አመት በታች ታዳጊ ከሆነች ይሄ ተገቢ ያልሆነ እና በወንጀል የሚያስጠይቅ ግልፅ የሆነ ጉዳይ ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

" መምህሯ ተማሪዋን የመታችበት መሳሪያ ወይም ቁስ የቅጣቱን መጠን ይወስነዋል " ያሉ ሲሆን  በእንጨት፣ በድንጋይ እና በመሳሰሉት ሆኖ በልጅቷ አካል ላይ መፋፋቅ፣ መድማት የአጥንት መሰበር አይነት ጉዳት ከሆነ ያደረሰችባት ከዚህም ከፍ ያለ ቅጣት ሊጠብቃት እንደሚችል ጠቁመዋል።

በተለይም መምህር፣ ሹፌር እና ሀኪሞች በስራ ያገኟቸውን ሰዎች የበለጠ የመጠበቅ ሃላፊነት አለባቸው። ይሄም እንደ ወንጀል ማክበጃ ይታያል ብለዋል።

የህግ ባለሙያው ሳሙኤል ይሄ ጉዳይ ይፋ መደረጉ እና በመምህርቷ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ለሌሎች አስተማሪዎች መማሪያ የሚሆን ነው ሲሉ ገልጸዋል።

" በመጨረሻም አሁን ላይ ተማሪዎችን አንደድሮው አይነት ቅጣቶች መቅጣት አይቻልም፣ ምክንያቱም  ከህፃናት መብት ጋር የሚጣረስ ነው " ሲሉ አመላክተዋል።


ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ሰሌዳ

በኢትዮጵያ የተሽከርካሪ ሰሌዳ (ታርጋ) ለውጥ ለማድረግ የሚያስችል መመሪያ ጸድቋል።

መመሪያው የተሸከርካሪ የመለያ ቁጥር ሰሌዳ ዓይነቶችና ምልክቶች መወሰኛ እና የአገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 1050/2017 ነው።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አማካሪ ከድልማግስት ኢብራሂም፤ " የሰሌዳ ለውጡ ዋና ምክንያት ኢትዮጵያ የተቀበለቻቸውን ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ታሳቢ ያደረገ ሰሌዳ እንዲኖር ለማስቻል ነው " ብለዋል።

ከዚህ ቀደም በነበረው የተሽከርካሪ መለያ ቁጥር ሰሌዳ ፦
- የአመራረት እና አሰረጫጨት ችግር፣
- የአወጋገድ ችግር፣
- የአሰራር ክፍተት፣
- የሀብት ብክነት፣
- በሲስተም የተደገፈ ስራ አለመኖር ችግር እንደነበር ጠቁመዋል።

ከዚህ በፊት ከነበረው አሰራር ጋር ተያይዞ የዕለት የተላላፊ እና የቋሚ መለያ ቁጥር ሰሌዳ አገልግሎት አሰጣጥ ለፎርጅሪ ለብልሹ አሰራር ለበርከታ ወንጀሎች የተጋለጠ በመሆኑ ይህ መመሪያ ችግሩን ይቀርፋል ሲሉ አስረድተዋል።

" መመሪያው በመላ ሀገሪቱ ተግባራዊ የሚደረግ ሲሆን፤ በተመዘገቡና ለምዝገባ በሚቀርቡ ተሽከርካሪዎች፣ በተሽከርካሪ አምራች /አስመጪ/ገጣጣሚ ድርጅቶች፣ በተሽከርካሪ መዝጋቢ አካላት እንዲሁም በኢትዮጵያ በሚገኙ እና አህጉር አቀፍ ተቋማት እና በግለሰቦች ላይ ተፈጻሚ ይሆናል " ብለዋል።

የተሽከርካሪ መለያ ቁጥር ሰሌዳ ዓይነቶች እና ምልክቶች ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን መሰረት በማድረግ፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ የመለያ ቁጥር ሰሌዳ አገልግሎት ይዘት በዓይነት እና በመጠን ወጥ እንዲሆን ለማድረግ፣ የመለያ ቁጥር ሰሌዳ ምርት ስርጭት አወጋገድ የተሸከርካሪ መረጃ አያያዝ ቁጥጥሩ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድርግ የመመሪያው ዓላማ መሆኑ ተብራርቷል፡፡

@tikvahethiopia