#ሰሌዳ
በኢትዮጵያ የተሽከርካሪ ሰሌዳ (ታርጋ) ለውጥ ለማድረግ የሚያስችል መመሪያ ጸድቋል።
መመሪያው የተሸከርካሪ የመለያ ቁጥር ሰሌዳ ዓይነቶችና ምልክቶች መወሰኛ እና የአገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 1050/2017 ነው።
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አማካሪ ከድልማግስት ኢብራሂም፤ " የሰሌዳ ለውጡ ዋና ምክንያት ኢትዮጵያ የተቀበለቻቸውን ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ታሳቢ ያደረገ ሰሌዳ እንዲኖር ለማስቻል ነው " ብለዋል።
ከዚህ ቀደም በነበረው የተሽከርካሪ መለያ ቁጥር ሰሌዳ ፦
- የአመራረት እና አሰረጫጨት ችግር፣
- የአወጋገድ ችግር፣
- የአሰራር ክፍተት፣
- የሀብት ብክነት፣
- በሲስተም የተደገፈ ስራ አለመኖር ችግር እንደነበር ጠቁመዋል።
ከዚህ በፊት ከነበረው አሰራር ጋር ተያይዞ የዕለት የተላላፊ እና የቋሚ መለያ ቁጥር ሰሌዳ አገልግሎት አሰጣጥ ለፎርጅሪ ለብልሹ አሰራር ለበርከታ ወንጀሎች የተጋለጠ በመሆኑ ይህ መመሪያ ችግሩን ይቀርፋል ሲሉ አስረድተዋል።
" መመሪያው በመላ ሀገሪቱ ተግባራዊ የሚደረግ ሲሆን፤ በተመዘገቡና ለምዝገባ በሚቀርቡ ተሽከርካሪዎች፣ በተሽከርካሪ አምራች /አስመጪ/ገጣጣሚ ድርጅቶች፣ በተሽከርካሪ መዝጋቢ አካላት እንዲሁም በኢትዮጵያ በሚገኙ እና አህጉር አቀፍ ተቋማት እና በግለሰቦች ላይ ተፈጻሚ ይሆናል " ብለዋል።
የተሽከርካሪ መለያ ቁጥር ሰሌዳ ዓይነቶች እና ምልክቶች ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን መሰረት በማድረግ፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ የመለያ ቁጥር ሰሌዳ አገልግሎት ይዘት በዓይነት እና በመጠን ወጥ እንዲሆን ለማድረግ፣ የመለያ ቁጥር ሰሌዳ ምርት ስርጭት አወጋገድ የተሸከርካሪ መረጃ አያያዝ ቁጥጥሩ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድርግ የመመሪያው ዓላማ መሆኑ ተብራርቷል፡፡
@tikvahethiopia
በኢትዮጵያ የተሽከርካሪ ሰሌዳ (ታርጋ) ለውጥ ለማድረግ የሚያስችል መመሪያ ጸድቋል።
መመሪያው የተሸከርካሪ የመለያ ቁጥር ሰሌዳ ዓይነቶችና ምልክቶች መወሰኛ እና የአገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 1050/2017 ነው።
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አማካሪ ከድልማግስት ኢብራሂም፤ " የሰሌዳ ለውጡ ዋና ምክንያት ኢትዮጵያ የተቀበለቻቸውን ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ታሳቢ ያደረገ ሰሌዳ እንዲኖር ለማስቻል ነው " ብለዋል።
ከዚህ ቀደም በነበረው የተሽከርካሪ መለያ ቁጥር ሰሌዳ ፦
- የአመራረት እና አሰረጫጨት ችግር፣
- የአወጋገድ ችግር፣
- የአሰራር ክፍተት፣
- የሀብት ብክነት፣
- በሲስተም የተደገፈ ስራ አለመኖር ችግር እንደነበር ጠቁመዋል።
ከዚህ በፊት ከነበረው አሰራር ጋር ተያይዞ የዕለት የተላላፊ እና የቋሚ መለያ ቁጥር ሰሌዳ አገልግሎት አሰጣጥ ለፎርጅሪ ለብልሹ አሰራር ለበርከታ ወንጀሎች የተጋለጠ በመሆኑ ይህ መመሪያ ችግሩን ይቀርፋል ሲሉ አስረድተዋል።
" መመሪያው በመላ ሀገሪቱ ተግባራዊ የሚደረግ ሲሆን፤ በተመዘገቡና ለምዝገባ በሚቀርቡ ተሽከርካሪዎች፣ በተሽከርካሪ አምራች /አስመጪ/ገጣጣሚ ድርጅቶች፣ በተሽከርካሪ መዝጋቢ አካላት እንዲሁም በኢትዮጵያ በሚገኙ እና አህጉር አቀፍ ተቋማት እና በግለሰቦች ላይ ተፈጻሚ ይሆናል " ብለዋል።
የተሽከርካሪ መለያ ቁጥር ሰሌዳ ዓይነቶች እና ምልክቶች ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን መሰረት በማድረግ፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ የመለያ ቁጥር ሰሌዳ አገልግሎት ይዘት በዓይነት እና በመጠን ወጥ እንዲሆን ለማድረግ፣ የመለያ ቁጥር ሰሌዳ ምርት ስርጭት አወጋገድ የተሸከርካሪ መረጃ አያያዝ ቁጥጥሩ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድርግ የመመሪያው ዓላማ መሆኑ ተብራርቷል፡፡
@tikvahethiopia