አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
አቢሲኒያ ባንክ በሚከተሉት የስራ መደቦች ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
👩 position:-
1 - Legal Officer
2 - District IFB Business Manager
3 - Cameraman & Video Editor
📚 ትምህርት ዓይነት እና ደረጃ፡-
LLB Degree in Law,MA/BA Degree in Accounting, Management, Marketing, Banking and Finance, Economics or other business related fields,Diploma in Cinematography, Photography, or other related fields.
🇪🇹 የስራ ቦታ : አዲስ አበባ , ሀዋሳ
🧭የምዝገባ ጊዜ /Deadline/: እስከ መጋቢት 15 /2014 ዓ.ም
🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ !
https://jobs.amazonethiopia.com/job/bank-of-abyssinia-11/

Position 1 – Legal Officer

Education – LLB Degree in Law.
Experience-Minimum of 6 years banking
Experience, of which 3 years in the area of Law.
Place of Work – Addis Ababa
Deadline – march 24/22
proclamation-no-881-2015-corruption-crimes-proclamation.pdf
4.7 MB
ATTORNEY
Nyala Insurance Share Company (NISCO)

Addis Ababa

Full–time

LLB Degree Minimum of 1 year experience as attorney, preferably in financial industry, Age: Not more than 35 Place of Work: Addis Ababa Deadline Date March 27, 2022
HOW TO APPLY
Interested applicants who fulfill the above requirements are invited to submit their application with non-returnable copy of CV and credentials to the under mentioned postal address or in person at our HO (Protection House) 3rd floor Room No. 307 located around 22 Mazoria Mickey Leland Road.

• N.B. Only short listed applicants will be contacted and invited for interview. • NYALA INSURANCE S.C. (NISCO) • PROTECTION HOUSE P O. Box 12753 Addis Ababa

#አለ_ህግ #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_ስራ
#አለ_ልዩልዩ
#አለ_ችሎት
#አለ_ዜና
#አለ_መዝናኛ
#አለ_ጤና
#አለ_መረጃ
#አለ_ትምህርት
#አለ_ሁሉም
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
መመሪያ ቁጥር 14-2010 ዓ.ም.docx
74.8 KB
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፍትሕ ቢሮ የተሻሻለው የዐቃብያነ-ሕግ የደረጃ እድገት መመሪያ መመሪያቁጥር 14-2010 ዓ.ም
የኢትዮጵያና የውጭ ሀገር ገንዘቦች መያዝ ላይ ያለው ገደብ እና የወንጀል ተጠያቂነት🔴
ገንዘብ እንደ ሀብት መለኪያ ሆኖ ከማገልገሉ ባለፈ የመገበያያ መሳሪያ ሆኖ ያገለግላል፡፡ ለዚህ እዲረዳ ሀገራት የየራሳቸው የሆነ ሕጋዊ ገንዘብ አላቸው፡፡ ይህን የራሳቸውንም ሆነ የሌላ ሀገር ገንዘብ ስለአያያዝና አጠቃቀሙ ምንዛሬን ጨምሮ የሚያስተዳድሩበት ሥርዓት ይዘረጋሉ፡፡ በዚህ አጭር ፅሑፍ የኢትዮጵያና የውጭ ሀገር ገንዘቦችን አያያዝ በተመለከተ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ያወጣው መመሪያን ማዕከል አድርገን ያሉት ገደቦች ምን እንደሚመስሉ ለመዳሰስ እንሞክራለን፡፡

1. የገንዝብና የውጭ ሀገር ገንዘብ ምንነት

ቀደም ባሉት ጊዜያት ግብይቶች ሁሉ ቁስን በመለዋወጥ ወይም ዕቃን በዕቃ በቀጥታ መለዋወጥን (Barter System) መሰረት ያደረጉ ነበሩ፡፡ በዚህ ስርዓት ውስጥ ግብይት እጅግ ከባድ ስለሆነ ቀስ በቀስ ሌላ የግብይት ስርዓቱን የሚያቀላጥፍ በማስፈለጉ ምክንያት በራሳቸው ዋጋ ያላቸው ቁሶች ጉልህ ሚናቸውን መጫወት ጀመሩ፡፡ ለአብነት ወርቅ፣ ብር እና የመሳሰሉት ቁሶች በተፈጥሯቸው ከገንዘብነት ባለፈ ለሌላ ጉዳይ አገልግሎት ላይ መዋል የሚችሉ ናቸው፡፡ በሂደት ግን ይህም አሰራር ተቀይሮ ለብቻው በራሱ ገንዘብ ሆኖ ከማገልገል ውጭ ዋጋው ኢምንት የሆነ፤ መንግስታት አትመው ወይም አሳትመው ስርጭቱን እንዲሁም ተመኑን የሚያስቀምጡለት ስርዓት የተፈጠረ ሲሆን እነዚህም አሁን የምንገለገልባቸው የወረቀት ገንዘብና ሳንቲሞች ናቸው፡፡

የውጭ ሀገር ገንዘብ ምንነትን አስመልክቶ በብሔራዊ ባንክ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 591/2000 በአንቀፅ 2(5) ሥር እንደሚከተለው ተተርጉሟል፡- “የውጭ ሀገር ገንዘብ ማለት ከኢትዮጵያ ገንዘብ በስተቀር ከኢትዮጵያ ውጭ በማናቸውም ሀገር ሕጋዊ ገንዘብ የሆነና በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚደረግ ክፍያ ተቀባይነት እንዳለው ብሔራዊ ባንክ ያሳወቀው ማናቸውም ገንዘብ ነው” ይላል፡፡ በዚህ ትርጉም መሰረት አንድ የውጭ አገር ገንዘብ በኢትዮጵያ ተቀባይነት እንዲያገኝ ሁለት መሰረታዊ ነገሮች ሟሟላት እንደሚጠበቅበት ይገልፃል፡፡ 1ኛ በሌላ ሃገር ህጋዊ የሆነ ገንዘብ መሆን አለበት፣ 2ኛ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ በኢትዮጵያ ውስጥ ለክፍያ ያሳወቀው መሆን አለበት የሚሉ መስፈርቶች ተቀምጠዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ተቀባይነት እንዳላቸው ያሳወቃቸው ማለትም በቋሚነት በሕግ ተለይተው የታወቁ የውጭ ሀገር ገንዘቦች ባይኖሩም በየጊዜው ዋጋ እየተመነ የሚያወጣቸውና የተለመዱ የውጭ ሀገር ገንዘቦች አሉ፡፡ ለምሳሌ በቅርቡ ከብሔራዊ ባንክ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው የሚከተሉት ገንዘቦች በወቅቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ለክፍያ እውቅና የተሰጣቸው ገንዘቦች ናቸው፡፡ እነዚህም የጃፓን የን፣ የኖርዌይ ክሮን፣ የስዊድን ክሮነር፣ የቻይና ይዋን፣ የዴንማርክ ክሮነር፣ የሳውዲ ሪያል፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ድርሀም፣ የአውስትራሊያ ዶላር፣ የካናዳ ዶላር፣ የአሜሪካ ዶላር፣ የሲውዘርላንድ ፍራንክ፣ የእንግሊዝ ፓውንድ እና የአውሮፓ ዩሮ ናቸው፡፡ ከነዚህ የገንዘብ ዓይነቶች ውጪ የሌላ ሀገር ገንዘብ ይዞ የተገኘ ማንኛውም ግለሰብ ተጠያቂነት የለበትም ማለት ነው፡፡

2. የውጭ ሀገር ገንዘብ የመያዝ ገደብ

ገደብና ክልከላው የተቀመጠው በመመሪያ ቀጥር FXD/49/2017 ሲሆን በውጭ ሀገር ገንዘቦች ላይ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያ ብርም ላይ ጭምር ነው፡፡ በዚህ መመሪያ መሰረት ክልክላና ገደቡ በሁለት ተከፍሎ ተቀምጧል፡፡ ይኸውም ዜግነትን መሰረት ሳያደርግ የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነና የኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆነ በሚል የተከፈለ ነው፡፡ በዜግነት እና በነዋሪነት መካከል ያለው ልዩነት ሰፋ ያለ ማብራሪያ የሚፈልግ ቢሆንም ባጭሩ ለመግለፅ ዜግነት በትውልድ ወይም በሕግ የሚገኝና በአንድ ሀገር እራሱን የቻለ ዜጋ ያልሆነ ሰው የማያገኘው መበትና ግዴታን የሚያሰጥ ግለሰብን ከሀገር ጋር የሚያስተሳስር (የሚያዛምድ) ሥርዓት ሲሆን ነዋሪነት ማለት ደግሞ ዜግነት ያለውም የሌለውም ሰው ሊሆን ይችላል፡፡ ነገር ግን በአዋጅ ቁጥር 354/95 አንቀፅ 13-15 እና በደንብ ቁጥር 144/95 አንቀፅ 26-31 ባሉት ድንጋጌዎች መሰረት ነዋሪ ማለት ቋሚ ወይም ጊዜያዊ ፈቃድ አግኝቶ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖር ሰው ማለት ነው፡፡

ክልከላውን በተመለከተ በኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው በውጪ ሀገር በነበረው ጉዞ ምክንያት መጠኑ ከ1,000 (አንድ ሺ) የአሜሪካን ዶላር በላይ ወይም ለዚሁ ተመጣጣኝ የሆነ የውጭ ሀገር ገንዘብ በእጁ የያዘ ሰው ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀ ቅፅ አማካኝነት በአቅራቢያ ለሚገኝ የጉምሩክ መቆጣጠሪያ ጣቢያ ማሳወቅ ወይም ዲክሌር ማድረግ እንዳለበት እና በ30 ቀናት ውስጥ ባንክ በመሄድ ወደ ኢትዮጵያ ብር መመንዘር እንዳለበት በመመሪያው አንቀፅ 4.1(a) እና 4.2 ሥር ተደንግጓል፡፡ መጠኑ ከ1,000 (አንድ ሺ) የአሜሪካን ዶላር ያነሰ ወይም ለዚሁ ተመጣጣኝ የሆነ የውጭ ሀገር ገንዘብ ይዞ ወደ ሀገር የገባ ሰው ምንም እንኳን በሕጉ የማሳወቅ ግዴታ ባይጣልበትም በ30 ቀናት ውስጥ ወደ ሕጋዊ ባንኮች ሄዶ ወደ ኢትዮጵያ ብር የመመንዘር ግዴታ አለበት፡፡

ከውጪ ሀገር የገባም ባይሆን በሆነ አጋጣሚ ማንኛውንም ያክል መጠን ያለው የውጪ ሀገር ገንዘብ ያለው ሰው ገንዘቡ በእጁ ከገባበት ወይም ለጉምሩክ ኮሚሽን ካሳወቀበት ቀን ጀምሮ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ ወደ ኢትዮጵያ ብር መመንዘር እንዳለበት በመመሪያው አንቀፅ 3 እና 4.2 (a) ላይ ተደንግጓል፡፡ የውጭ ሀገር ገንዘብ ያለው ሰው በባንክ ወደ ኢትዮጵያ ብር መመንዘር አለበት ብቻም ሳይሆን ከቀነ ገደቡ በላይ መያዝ እንደማይችል ወይም ክልክል እንደሆነ በመመሪያው ላይ ተደንግጓል፡፡

በኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ ያልሆነ ሰውም ቢሆን ወደ ሀገር በሚገባበት ጊዜ ከ3,000 የአመሪካን ዶላር በላይ ወይም ለዚሁ ተመጣጣኝ የሆነ የሌላ ሀገር ገንዘብ የያዘ እንደሆነ በአየር ማረፊያዎች ወይም በሌሎች የመግቢያ በሮች ላይ ለሚገኝ የጉምሩክ ኮሚሽን ለዚህ አገልግሎት በተዘጋጀው ቅፅ ላይ ሞልቶ የማሳወቅ ወይም Diclare የማድረግ ግዴታ እንዳለበት በመመሪያው አንቀፅ 4.1 (b) ሥር ተደንግጓል፡፡

በመመሪያው አንቀፅ 4.2 (c) መሰረት በኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ ያልሆነ ሰው ዲክሌር ያደረገውን የውጭ ሀገር ገንዘብ ካሳወቀበት ቀን ጀምሮ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ ባንክ ሄዶ ወደ ኢትዮጵያ ብር የመመንዘር ግዴታ አለበት፡፡ ቢሆንም እስከ የቪዛው (ቪዛ ማለት በኢትዮጵያ ነዋሪ ላልሆነ ሰው ለተወሰነ ጊዜ የሚሰጥ የመኖሪያ ፈቃድ ነው) ማለቂያ ጊዜ ድረስ ማቆየት እንደሚችል በአንቀፅ 4.2 (c) ተደንግጓል፡፡

3. የኢትዮጵያ ብር ላይ የተጣለ ገደብ

ከላይ በተጠቀሰው መመሪያ ላይ በግልፅ እንደተቀመጠው ከውጪ ወደ ኢትዮጵያ የሚገባ እና ከኢትዮጵያ ውጪ የሚሄድ ሰው ላይ እንጂ ማንኛውም ሰው ላይ የተጣለ ገደብ እንዳሆነ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ ወደ ኢትዮጵያ የሚገባ ወይም ከኢትዮጵያ የሚወጣ ማንኛውም ሰው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከተወሰነው ወይም ከተፈቀደው መጠን በላይ የኢትዮጵያን ገንዘብ ይዞ ወደ ሀገር ውስጥ ለመግባት ወይም ለመውጣት እንደማይችል በአዋጅ ቁጥር 591/2000 አንቀፅ 18(6) ሥር ተደንግጓል፡፡ የተፈቀደው የገንዘብ መጠንን አስመልክቶ የመመሪያ ቁጥር FXD/49/2017 አንቀፅ 2.1 መሰረት ከውጪ ሀገር ወደ ኢትዮጵያ የሚገባ ሰውም ሆነ ከኢትዮጵያ ወደ ውጪ ሀገር የሚሄድ ሰው 1,000 (አንድ ሺ) በላይ ብር መያዝ እንደማይችል ተደንግጓል
በልዩ ሁኔታ ግን ወደ ጅቡቲ የሚጓዝ ሰው እስከ 4,000 ብር ድረስ ይዞ መጓዝ እንደሚፈቀድለት በመመሪያው አንቀፅ
2.2 ላይ ተደንግጓል፡፡

4. የገደቡ አስፈላጊነት

የመመሪያው መግቢያ “ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡና ከኢትዮጵያ የሚወጡ ሰዎች ላይ ብር የመያዝ መጠናቸው ላይ ገደብ ማድረግ በማስፈለጉ” እንዲሁም “የውጪ ሀገር ገንዘቦች አያያዝና አጠቃቃም ላይ ገደብና ቁጥጥር ማድረግ በማስፈለጉ…” መመሪያው እንደተዘጋጀ ከመገልፅ አልፎ የገደቡን አስፈላጊነት በግልፅ አላስቀመጠም፡፡ ሆኖም ካለው ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታ በመነሳት የገደቡን አስፈላጊነት መገመት ይቻላል፡፡

አንደኛውና የመጀመሪያው ምክንያት ሀገሪቱ እየገጠማት ያለውን የውጭ ምንዛሬ እጥረት ለመቅረፍ ገደቡ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ስለሚኖረው ነው፡፡ ምክንያቱም ተመዝግቦ የገባ የውጭ ሀገር ገንዘብ (ያልተመዘገበም ቢሆን) በገደቡ ምንክንያት ከ30 ቀናት በላይ በግለሰቡ እጅ ሊቆይ ስለማይችል ወደ ፋይናንስ ሥርዓቱ ገብቶ የውጭ ምንዛሬ ዕጥረቱን የማቃለል ሚናው ቀላል አይደለም፡፡

ሌላኛው ምክንያት ደግሞ ገደቡ ሕገ-ወጥነትን ለመከላከል ሁነኛ መሳሪያ ሆኖ ማገልገል መቻሉ ነው፡፡ ሰዎች በህገ-ወጥ መንገድ ለምሳሌ በሙስና፣ ግብር በመደበቅ፣ በማታለል፣ በሥርቆት፣ በአራጣ ወዘተ ያገኙትን ገንዘብ ማስረጃ ለማጥፋትና ሕጋዊ ለማስመሰል የኢትዮጵያን ሕጋዊ መተላለፊያ ኬላዎችን ተገን አድርገው ሊገቡ ወይም ሊወጡ ይችላሉ፡፡ በዚህ ጊዜ ማን፣ መቼ፣ የትና ምን ይዞ እንደተጓዘ ሥርዓት ያለው ገደብና ቁጥጥር የማይደረግ ከሆነ በሕገ-ወጥ መንገድ የተገኘ ገንዘብ ሕጋዊነት እንዲላበስና ሕገ-ወጥነት እንዲስፋፋ ያደርጋል፡፡

5. የወንጀል ተጠያቂነት

ለአንድ ሕግ ተፈፃሚ መሆን ክልከላና ገደብ ማድረግ ብቻውን በቂ የማይሆንበት ሁኔታ ሊኖር ይችላል፡፡ በመሆኑም በሕጉ የተቀመጡትን ክልከላና ገደቦች ተላልፎ የሚገኝን ሰው ተመጣጣኝና ፍትሐዊ ቅጣት ሊኖር የግድ ይላል፡፡ የመመሪያውን ድንጋጌዎች የሚጥሱ ሰዎች በአዋጅ ቁጥር 591/2000 አንቀፅ 26 መሰረት መቀጣት እንዳለባቸው በመመሪያው አንቀፅ 6 ላይ ተደንግጓል፡፡ ይህ ድንጋጌ ደግሞ በወንጀል ሕግ መሰረት ያስቀጣል ስለሚል በኢፌድሪ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 346 እና 354 መሰረት ወንጀሉ የተፈፀመበት ሀብት (ገንዘቡ) መወረሱ እንደተጠበቀ ሆኖ ከ10 እስከ 15 ዓመት ፅኑ እስራት እና ከ50 እስከ 200 ሺ በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ያስቀጣል፡፡

ምንጭ የኢፌዴሪ ፍትህ ሚኒስቴር
#አለ_ህግ #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_ስራ
#አለ_ልዩልዩ
#አለ_ችሎት
#አለ_ዜና
#አለ_መዝናኛ
#አለ_ጤና
#አለ_መረጃ
#አለ_ትምህርት
#አለ_ሁሉም
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩🟨🟥
COMMERCIAL CODE IMPLEMENTATION TRAINING.pdf
2.2 MB
for South Region
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩🟨🟥
contract 15.docx
27.7 KB
አስተያየቶችን እንቀበላለን
We welcome comments.
#አለ_ህግ #ALE_lawsocities
Dear @Berhanuworkie Congratulations.
You are rewarded 50 birr card for your great job sharing our channel for more than 200 peoples.
Pleas, send us your phone.
Dear @Berhanuworkie Congratulations.
You are rewarded 50 birr card for your great job sharing our channel for more than 200 peoples.
ሕግን አለማወቅ ይቅርታን ሊያስገኝ አይችልም። የፍታብሔር ሕግ ቁጥር 2035(2)
እንወያይ...... 🙏
#አለ_ህግ #አለ_ስራ #አለ_ልዩልዩ #አለ_ችሎት #አለ_ዜና #አለ_መዝናኛ
#አለ_ጤና #አለ_መረጃ #አለ_ትምህርት #አለ_ሁሉም #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
Forwarded from BERHANU. W
አለ(ALE)law societies ለተሸለምኩት የሞባይል ካርድ ከልብ አመሠግናለሁ ።
ከ3 አመት በፊትም በውስጥ መስመር ለተሠጠኝ የህግ ትምህርት ምክር ማመስገኔ እንዳይረሳብኝ ። እግዚአብሔር ያክብርልኝ ።

Dear Customer, your prepaid account has been recharged succesfully.your Recharged balance is 50.00 Birr.your balance is 53.59 Birr.With this balance your account will expire on 19/09/2022.ethio telecom
የቤት ኪራይ ውል - አንኳር ነጥቦች
_

የውሉ ሥርዓት፡-
የቤት ኪራይ ውል ተዋዋይ ወገኖች፣ ማለትም አከራይ እና ተከራይ፣ በመረጡት ሥርዓት (በጽሑፍ ወይም በቃል) ሊደረግ ይችላል፡፡ ሕግ በጽሑፍም ሆነ በቃል ለሚደረጉ የቤት ኪራይ ውሎች እኩል ጥበቃ ይሰጣል፡፡

የኪራዩ መጠን እና የሚከፈልበት ጊዜ፡-
አከራይና ተከራይ በቤት ኪራይ ውል በስምምነት ከሚወስኗቸው ጉዳዮች መካከል የኪራዩ የዋጋ ልክ እና ኪራዩ የሚከፈልበት ጊዜ ይጠቀሳሉ፡፡ አከራይና ተከራይ በኪራይ ውሉ የኪራዩን የዋጋ መጠን እና ኪራዩ የሚከፈልበትን ጊዜ ካልወሰኑ፤ በፍትሐብሔር ሕጋችን የተቀመጡ ድንጋጌዎች ተፈጻሚ ይሆናሉ፡፡ የፍትሐብሔር ሕጋችን አንቀጽ 2950(2) አከራይና ተከራይ በውላቸው ውስጥ የኪራዩን የዋጋ መጠን ካላስቀመጡ ወይም በሚያጠራጠር ጊዜ የማዘጋጃ ቤት ባለሥልጣናት በወሰኑት ታሪፍ መሠረት ወይም የተወሰነ ታሪፍ የሌለ እንደሆነ የቦታዎቹን ልማድ በመከተል የኪራዩ የዋጋ መጠን እንደሚወሰን ይደነግጋል፡፡ በተመሳሳይ፣ አከራይና ተከራይ ኪራዩ የሚከፈልበትን ጊዜ በውላቸው ካልተወሰኑ ወይም ካልተስማሙ ተፈጻሚ የሚሆነው ደንብ በፍትሐብሔር ሕጋችን አንቀጽ 2951 ሠፍሯል፡፡ በዚሁ መሠረትም የቤት ኪራይ ውሉ ለአንድ ዓመት ወይም ለተወሰኑ ብዙ ዓመታት ተደርጎ እንደሆነ ኪራዩ በየሦስት ወር መጨረሻ የሚከፈል ይሆናል፡፡ ሆኖም የቤት ኪራይ ውሉ በጣም አጭር ለሆነ ጊዜ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ ተደርጎ እንደሆነ በየወሩ መጨረሻ የሚከፈል ይሆናል፡፡

የተከራዩትን ቤት ስለማደስ፡-
በቤት ኪራይ ውል ሊወሰን ወይም ስምምነት ሊደረግበት የሚችለው ሌላኛው ጉዳይ የቤቱ እድሳት ነው፡፡ በፍትሐብሔር ሕጉ አንቀጽ 1954 መሠረት ማደስ የቤቱን መዝጊያዎችን ወይም መስኮቶችን፣ የቤቱን ወለሎችን ወይም ንጣፎችን፣ የውሃ መስመሮችንና የፍሳሽ ማስወገጃዎችን ማደስ እና ቤቱን የማፅዳት እና በደንብ የመያዝ ተግባሮችን ያጠቃልላል፡፡ ተከራይ ለማደስ የተዋዋለውን የተከራየውን ቤት በራሱ ኪሳራ (ወጭ) ለማደስ እንደሚገደድ በፍትሐብሔር ሕጋችን አንቀፅ 1953 ተደንግጓል፡፡ ሆኖም ግን ቤቱ በማርጀት ወይም ካቅም በላይ በሆነ ነገር የተበላሸ ሲሆን ተከራዩ ቤቱን የማደስ ስራ መፈፀም አይጠበቅበትም፡፡ ይሁን እንጂ በቤት ኪራይ ውሉ ውስጥ በማርጀት ወይም ካቅም በላይ በሆነ ነገር የተበላሹትንም ጭምር አድሳለው በማለት ተከራዩ የተስማማ ከሆነ እንዲያድስ ይገደዳል፡፡

የተከራዩትን ስለ ማከራየት (የኪራይ ኪራይ)፡-
ተከራይ የተከራየውን ቤት መልሶ ለማከራየት ይችላል፡፡ ይሁን እንጂ ተከራዩ የተከራየውን ቤት ሊያከራይ የሚችለው አከራዩ ለዚህ የኪራይ ኪራይ ተቃውሞ ከሌለው ብቻ ነው፡፡

የቤት ኪራይ ክፍያን በጊዜው አለመክፈል፡-
ተከራይ የቤት ኪራይ ክፍያውን በጊዜው ያልከፈለ እንደሆነ የሚያስከትለው ውጤት በፍትሐብሔር ሕጋችን አንቀፅ 2952 ሰፍሯል፡፡ የቤት ኪራይ ውሉ ለአንድ ዓመት ወይም ከአንድ ዓመት ለበለጠ ጊዜ ተደርጎ እንደሆነ አከራዩ የሠላሳ ቀን ማስጠንቀቅያ በመስጠት፤ የቤት ኪራይ ውሉ ለአጭር ጊዜ ተደርጎ እንደሆነ ደግሞ አከራዩ የአስራ አምስት ቀን ማስጠንቀቅያ በመስጠት፣ በዚህ ጊዜ ውስጥ ተከራዩ ኪራዩን ያልከፈለ እንደሆነ አከራዩ ውሉን የሚያቆርጥ መሆኑን ለተከራዩ ያሳውቃል፡፡ በዚህ በተሰጠው የማስጠንቀቂያ ጊዜ ውስጥ ተከራዩ ያልከፈለ እንደ ሆነ አከራይ ውሉን ለማቋረጥ ይችላል፡፡

የቤት ኪራይ ውል የሚፈርስባቸው ምክንያቶች፡-
በአከራይና ተከራይ መካከል የተደረገ የቤት ኪራይ ውል በልዩ ልዩ ምክንያቶች ሊፈርስ ወይም ሊቋረጥ ይችላል፡፡ የቤት ኪራይ ውሉ ለተወሰነ ጊዜ ተደርጎ የውሉ ጊዜ ሲያበቃ፤ ተዋዋይ ወገኖች በስምምነት ውላቸውን ለማቋረጥ ሲስማሙ፤ ተከራይ ኪራዩን በጊዜው ባለመክፈሉ አከራዩ የማስጠንቀቂያ ጊዜ ሰጥቶት በዚህ ጊዜ ውስጥም ያልከፈለ እንደሆነ፤ አከራይ ቤቱን ፈልጎት ለተከራይ ማስጠንቀቂያ ጊዜ በመስጠት ወይም ተከራዩ ቤቱን መልቀቅ ፈልጎ ለአከራዩ ማስጠንቀቂያ ጊዜ በመስጠት የቤት ኪራይ ውል ሊቋረጥ ይችላል፡
👇#Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties