አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የኢትዮጵያ የኩባንያ ሕግ (3ኛው የተሻሻለ እትም) በቅርብ ቀን ታትሞ ይወጣል፡፡ ስለ 2ኛው እትም የተለያዩ ገንቢ ሀሳቦችን በመስጠት ላበረታታችሁኝ ሁሉ ምስጋናዬን እያቀርብኩ ስለ 3ኛው እትም ጥቂት መረጃ ልስጣችሁ፡፡

የገጽ ብዛት፡478
የመጽሐፉ መጠን፡ B5 (width 17.6 cm Height 25 cm)
ISBN 978-99944-3-573-1
አከፋፋይ፡ አንከቡት መጻሕፍት

ይህ 3ኛ እትም ከአዲሱ የንግድ ሕግ አንጻር ከእንደገና የተከለሰ ሲሆን አምስት አዳዲስ ምዕራፎችም ተካተውበታል፡፡ እነዚህም፡-

ስለ ባለ አንድ አባል ኩባንያ
ስለ ካፒታል/አክሲዮን ገበያ አሰራር
ስለ ተቧደኑ ኩባንያዎች
ስለ ኩባንያዎች ማህበራዊ ኃላፊነት
በኩባንያዎች ውስጥ ስለሚደረጉ መሠረታዊ ለውጦች (ለምሳሌ የካፒታል ለውጥ፣ ውህደት፣ የማህበር ዓይነት መለወጥ፣…)

ስለ መጽሐፉ ከመግቢያው ላይ ተቀንጮቦ የተወሰደ ጥቂት ማብራሪያ ይሄውላችሁ፡-

ይህ መጽሐፍ የሚያጠነጥነው ኩባንያ እንዴት እንደሚቋቋም፣ እንዴት እንደሚተዳደርና እንደሚፈርስ ነው፡፡ መጽሐፉ ከአዲሱ የንግድ ሕግ፣ ከተለያዩ አዋጆች፣ የፍርድ ውሳኔዎችና የሌሎች አገራት ተሞክሮዎች በመነሳት የኢትዮጵያን የኩባንያ ሕግ ይተነትናል፡፡
የኢትዮጵያ የኩባንያ ሕግ (3ኛው የተሻሻለ እትም) በቅርብ ቀን ታትሞ ይወጣል፡፡ ስለ 2ኛው እትም የተለያዩ ገንቢ ሀሳቦችን በመስጠት ላበረታታችሁኝ ሁሉ ምስጋናዬን እያቀርብኩ ስለ 3ኛው እትም ጥቂት መረጃ ልስጣችሁ፡፡

የገጽ ብዛት፡478
የመጽሐፉ መጠን፡ B5 (width 17.6 cm Height 25 cm)
ISBN 978-99944-3-573-1
አከፋፋይ፡ አንከቡት መጻሕፍት

ይህ 3ኛ እትም ከአዲሱ የንግድ ሕግ አንጻር ከእንደገና የተከለሰ ሲሆን አምስት አዳዲስ ምዕራፎችም ተካተውበታል፡፡ እነዚህም፡-

ስለ ባለ አንድ አባል ኩባንያ
ስለ ካፒታል/አክሲዮን ገበያ አሰራር
ስለ ተቧደኑ ኩባንያዎች
ስለ ኩባንያዎች ማህበራዊ ኃላፊነት
በኩባንያዎች ውስጥ ስለሚደረጉ መሠረታዊ ለውጦች (ለምሳሌ የካፒታል ለውጥ፣ ውህደት፣ የማህበር ዓይነት መለወጥ፣…)

ስለ መጽሐፉ ከመግቢያው ላይ ተቀንጮቦ የተወሰደ ጥቂት ማብራሪያ ይሄውላችሁ፡-

ይህ መጽሐፍ የሚያጠነጥነው ኩባንያ እንዴት እንደሚቋቋም፣ እንዴት እንደሚተዳደርና እንደሚፈርስ ነው፡፡ መጽሐፉ ከአዲሱ የንግድ ሕግ፣ ከተለያዩ አዋጆች፣ የፍርድ ውሳኔዎችና የሌሎች አገራት ተሞክሮዎች በመነሳት የኢትዮጵያን የኩባንያ ሕግ ይተነትናል፡፡ የኩባንያ ሕግ ዋና ትኩረት ሰዎች ኃላፊነት የተወሰነበትን አደረጃጀት (ኩባንያን) ተጠቅመው በጋራ የንግድ ስራን ሲሰሩ የሚፈጠሩ ችግሮችን መፍታት ነው፡፡ እነዚህ ችግሮች በዋናነት ሦስት ናቸው፡፡ አንደኛው የኩባንያው አስተዳዳሪዎች ባለአክሲዮኖችን እንዳይበድሉ መከላከል ነው፤ ሁለተኛው አብላጫ ድርሻ ያላቸው አነስተኛ ድርሻ ያላቸውን እንዳይበድ መከላከል ነው፡፡ ሦስተኛው ጉዳይ ሰዎች የኩባንያ አደረጃጀትን በመጠቀም በሦስተኛ ወገኖች ላይ ጉዳት እንዳያደርሱ መከላከል ነው፡፡ በመጽሐፉ ውስጥ የተካተቱት አብዛኛዎቹ ርዕሰ-ጉዳዮች (ከክፍል ሁለት እስከ ክፍል አራት ያሉት) በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ እነዚህን ጥያቄዎች የኢትዮጵያ ሕግ እንዴት እንደሚመልስ የሚተነትኑ ናቸው፡፡
መጽሀፉ በአራት ዋና ዋና ክፍሎች ተከፋፍሎ የቀረበ ነዉ፡፡ ክፍል አንድ ስለ ንግድ ማህበራት በጠቅላላው የሚዳሰስበት ሲሆን በውስጡ ሁለት ምዕራፎችን ይዟል፡፡ እነዚህም ስለ ኩባንያዎች የንግድ ምዝገባ እና ፈቃድ የሚናገረው ምዕራፍ አንድ፣ እና ስለ ንግድ ማህበራት ዓይነቶች እና ባህሪዎቻቸው የተተነተነበት ምዕራፍ ሁለት ናቸው፡፡ በምዕራፍ አንድ የሚነሱት ሀሳቦች በጥቅሉ ሁሉንም ነጋዴዎች የሚመለከቱ በመሆናቸው ለግል ንግድም (sole proprietorship) ተፈጻሚ የሆኑ ሕጎች የተዳሰሱበት ነው፡፡ ለዚህኛው ምዕራፍ ምንጭ የሆኑ ሕጎች የአዲሱ ንግድ ሕግ አንደኛ መጽሐፍ እና የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ፣ አዋጁን ለማስፈጻም የወጡ ደንቦችና መመሪያዎች ናቸው፡፡ ምዕራፍ ሁለት ሁሉንም ዓይነት የንግድ ማህበራት የሚመለከቱ የንግድ ሕጉ ሁለተኛው መጽሐፍ ጠቅላላ ድንጋጌዎች የተዳሰሱበት ክፍል ነው፡፡ የመጽሐፉ ርዕስ እንደሚያመለክተው ትኩረቱ ኩባንያዎች ላይ ስለሆነ የሽርክና ማህበራት በዚህ ምዕራፍ ብቻ ነው የተዳሰሱት፡፡ ቢሆንም እያንዳንዱ የሽርክና ማህበር ዓይነት ራሱን በቻለ ንዑስ ርዕስ ስር ቀርቧል፡፡
ክፍል ሁለት ስለ አክሲዮን ማህበር የቀረበበት ክፍል ሲሆን በውስጡ ብዙ ምዕራፎችን ይዟል፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ ስምንት ምዕራፎች አሉ፡፡ እነዚህም ከምዕራፍ ሦስት እሰከ አስር ያሉት ሲሆኑ ስለአክሲዮን ማህበር አመሰራረት፣ ስለ አክሲዮን ማህበር ካፒታልና አጠባበቁ እንዲሁም ስለ አክሲዮን፣ ስለ ኩባንያዎች መልካም አስተዳደር፣ ስለ ዳይሬክተሮች ቦርድ፣ ስለ ኩባንያ ኦዲተር፣ ስለ ጠቅላላ ጉባኤ፣ ስለ አነስተኛ ባለአክሲዮኖች ጥበቃ፣ ስለ ኩባንያዎች መግለጫ እና ስለ ካፒታል/አክሲዮን ገበያ የሚዳስሱ ክፍሎች ናቸው፡፡የመጨረሻው ስለ ካፒታል ገበያ የሚዳሰስበት ክፍል አዲሱ የካፒታል ገበያ አዋጅ ወደ ስራ ሲገባ በአብዛኛው ተፈጻሚነቱ የአክሲዮን ማህበራት ላይ ስለሚሆን በዚህ ረገድ ከአክሲዮን ማህበራት ሕግ ጋር ያለውን ዝምድና እና ተፈጻሚነት ለማብራራት ታስቦ የገባ ምዕራፍ ነው፡፡
ክፍል ሦስት በኢትዮጵያ ውስጥ በብዛት እየተሰራባቸው ስላሉት ኃላፊነታቸው የተወሰነ የግል ማህበራት የተዳሰሰበት ክፍል ነው፡፡ ክፍሉ ከምዕራፍ አስራ አንድ እሰከ ምዕራፍ አስራ አራት ያሉትን አራት ምዕራፎች ይይዛል፡፡ ምዕራፍ አስራ አንድ ስለ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር አመሠራረት ይዳስሳል፡፡ ምዕራፍ አስራ ሁለት ስለ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ካፒታል እና አክሲዮን ይቀርብበታል፡፡ እንዲሁም ምዕራፍ አስራ ሦስት ስለ ኃላፊነቱ ተወሰነ የግል ማህበር አካላት፣ ስልጣንና ኃላፊነት የተዳሰሰባቸው ክፍሎች ናቸው፡፡ በዚህ ክፍል የመጨረሻው ምዕራፍ ስለ ባለአንድ አባል ኃለፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ የሚዳሰስበት ነው፡፡ ይህ በአዲሱ የንግድ ሕግ ከተከዋወቁት የኩባንያ ዓይነቶች አንደኛው ነው፡፡ ባለአንድ አባል ኩባንያ የኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ልውጥ (variant) ስለሆነ በዚህ ክፍል ውስጥ ይቀርባል፡፡
ክፍል አራት ሌሎች ልዩ ልዩ ርዕሰ-ጉዳዮች የሚደሰሱበት ክፍል ነው፡፡ ይህም ከምዕራፍ አስራ አምስት እስከ ምዕራፍ አስራ ስምንት ያሉትን አራት ርዕሶች የሚሸፍን ሲሆን በሌሎች ክፍሎች ውስጥ ሊቀርቡ የማይችሉ ነገር ግን በጣም አስፈላጊ ርዕሶች የተዳሰሱበት ክፍል ነው፡፡ ምዕራፍ አስራ አምስት ስለ መሠረታዊ ለውጦች የቀረበበት ሲሆን ኩባንያዎች ከምስረታ ጀምሮ እስከ መፍረስ ድረስ በሚኖራቸው ዕድሜ የሚያልፉባቸው መሠረታዊ ለውጦች የሚቀርብበት ነው፡፡ የመሠረታዊ ለውጥ ዓይነቶች፣ አደራረጋቸው እና በለውጥ የማይስማሙ አባላት መብት በዚህ ምዕራፍ ይቀርባል፡፡ ምዕራፍ አስራ ስድስት ስለ ኩባንያዎች መቧደን ሲሆን የቡድን ዓይነቶች፣ የእናት ኩባንያዎች እና የተቀጥላዎች ግንኙነት፣ የተቀጥላ ኩባንያ አነስተኛ ባለአክሲዮኖችና የባለገንዘቦች መብቶችን የተመለከቱና ተያያዥ ሀሳቦች ይቀርቡበታል፡፡ ይህ በአዲሱ የንግድ ሕግ ትልቅ ትኩረት የተሰጠው ርዕስ ነው፡፡
ምዕራፍ አስራ ሰባት ስለ ኩባንያዎች ማህበራዊ ኃላፊነት ነው፡፡ ይህም ኩባንያዎች በማህበረሰብ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ተቋማት እንደመሆናቸው ያለባቸውን ማህበራዊ ኃላፊነት ትክክለኛ አረዳድና አተገባበር የሚቃኝ ምዕራፍ ነው፡፡ የመጨረሻው ምዕራፍ አስራ ስምንት ስለ ኩባንያዎች መፍረስና ሂሳብ መጣራት የሚቀርብበት ይሆናል፡፡ ይህ ምዕራፍ የአክሲዮን ማህበርን እና ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበርን የመፍረስ፣ የሂሳብ ማጣራት እና የመዝጋት ሂደት እና ሕጋዊ ውጤት የሚተነትን ክፍል ነው፡፡
#Share #Ale_Law
#አለ_ህግ #Ale_Law
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Lawyer Mike 🔊የህግ ባለሙያ)
#አለ_ህግ ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች፣ ክሶች፣ የውል ፎርሞች፤ መፅሐፍቶች 🔴ሁሉም ሕጎች በአንድ🔴 All in one, for All.
አለ_ህግ፣ መሰረታዊ የህግ መረጃ እውቀት፤ ሀብት እና ሀይል ነው። contact us: @LawsocietiesBot or email us: lawsocieties@gmail.com

https://t.me/lawsocieties
#Share
#አለ_ህግ
#አለ_ስራ
Lawyers for Human Rights (LHR) is pleased to announce the signing of a Memorandum of Understanding (MoU) with Abbay Media. Both parties have agreed to strengthened and collaborate on their own respective roles in bringing social change that is favourable to Human rights and the protection of Human Rights in general.

The joint effort will reinforce the contribution of civil societies and media engagement in the human rights space; resulting in much better cooperation and interaction for better protection and promotion of human rights values.

#Ethiopia #HumanRight #HumanRightLawyers #LawyersforHumanRights #LHR #media #abbay
አቢሲኒያ ባንክ በሚከተሉት የስራ መደቦች ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
👩 position:-
1 - Legal Officer
2 - District IFB Business Manager
3 - Cameraman & Video Editor
📚 ትምህርት ዓይነት እና ደረጃ፡-
LLB Degree in Law,MA/BA Degree in Accounting, Management, Marketing, Banking and Finance, Economics or other business related fields,Diploma in Cinematography, Photography, or other related fields.
🇪🇹 የስራ ቦታ : አዲስ አበባ , ሀዋሳ
🧭የምዝገባ ጊዜ /Deadline/: እስከ መጋቢት 15 /2014 ዓ.ም
🔔ስለ ስራው ሙሉ መረጃ ለማየት እና ለማመልከት ቀጣዩን ሊንክ ይጠቀሙ !
https://jobs.amazonethiopia.com/job/bank-of-abyssinia-11/

Position 1 – Legal Officer

Education – LLB Degree in Law.
Experience-Minimum of 6 years banking
Experience, of which 3 years in the area of Law.
Place of Work – Addis Ababa
Deadline – march 24/22
proclamation-no-881-2015-corruption-crimes-proclamation.pdf
4.7 MB
ATTORNEY
Nyala Insurance Share Company (NISCO)

Addis Ababa

Full–time

LLB Degree Minimum of 1 year experience as attorney, preferably in financial industry, Age: Not more than 35 Place of Work: Addis Ababa Deadline Date March 27, 2022
HOW TO APPLY
Interested applicants who fulfill the above requirements are invited to submit their application with non-returnable copy of CV and credentials to the under mentioned postal address or in person at our HO (Protection House) 3rd floor Room No. 307 located around 22 Mazoria Mickey Leland Road.

• N.B. Only short listed applicants will be contacted and invited for interview. • NYALA INSURANCE S.C. (NISCO) • PROTECTION HOUSE P O. Box 12753 Addis Ababa

#አለ_ህግ #Ale_Law #አለ_ጠበቃ #አለ_ህግአማካሪ #አለ_ነገረፈጅ
#አለ_ስራ
#አለ_ልዩልዩ
#አለ_ችሎት
#አለ_ዜና
#አለ_መዝናኛ
#አለ_ጤና
#አለ_መረጃ
#አለ_ትምህርት
#አለ_ሁሉም
#አለ_Share..... 👇👇👇👇👇👇
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
መመሪያ ቁጥር 14-2010 ዓ.ም.docx
74.8 KB
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፍትሕ ቢሮ የተሻሻለው የዐቃብያነ-ሕግ የደረጃ እድገት መመሪያ መመሪያቁጥር 14-2010 ዓ.ም