አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.87K photos
25 videos
1.87K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ኔሞ የሽናሻ_ታምሩ ዳኘው.pdf
305.2 KB
#4
#እኔም_የዕርቅ_ሀሳብ_አለኝ

''ኔሞ'' የሽናሻ ብሔረሰብ ባህላዊ የዳኝነት ስርዓት

አዘጋጅ: ታምሩ ዳኘው

" ኔሞ " ሽናሾች የሚመሩበት፣ የሚተዳደሩበት፣ እና ፍትህ የሚያገኙበት የህይወታቸው አንድ አካል ነው። የሺናሻ ብሄረሰብ በውስጡ ከ16 በላይ ንዑሳን ጎሳዎች ሲኖሩት እነዚህ ጎሳዎች ለኔሞ ስርዓት እንዲያመች ሆነው በሶስት ይከፈላሉ።

እነዚህም ጎሳዎች በብሄረሰቡ ባህል መሰረት “ሦስት ጉልቻ” ተብለው ይጠራሉ። ሦስቱ ጎሳዎች ዶዎ፣ ኢኖሮ፣ እና ኢንዲዎ ይባላሉ። ከእነዚህ ሶስቱ ጉልቻዎች አንዱ እንኳን ቢጎድል የኔሞ ስርዓትአይከወንም።

የቦሮ-ሽናሻ ብሄረሰብ ባህላዊ የፍርድ አሰጣጥ ሂደቶች አራት ደረጃዎች አሉት። እነዚህም፦

#ቡራ፦ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ የሚሰጥበት “ቡራ”በመባል ይታወቃል:: ቡራ አንድ ሽማግሌ ብቻውን ሆኖ የሚፈርድበት የቤተሰብ ባህላዊ ችሎት ነው።

#ኔማ፦ ሁለተኛ ደረጃ ፍርድ የሚሰጥበት የዳኝነት ክፍል”ኔማ” ይሰኛል። በዚህኛው ደረጃ ሦስት ሽማግሌዎች ግራናቀኝ አይተው ፍርድ ወይም ፍትህ ይሰጣሉ ተብሎ ይታመናል።

#ፄራ፦ ሶስተኛው የዳኝነት ክፍል ወይም ችሎት “ፄራ” ይባላል::ይህ ባህላዊ ችሎት የሚመራው በአንድ ባህላዊ ሹም ዳኛ ነው። በዚህ ክፍል ኔማ ችሎት መፍታት ያልቻለው ጉዳይ በጥልቀት ይታያል።

#ፋላ፦ ይህ በሺናሻ የመጨረሻ ወይም ከፍተኛ የዳኝነት አካል ነው፡፡

የሽናሾች ባህላዊ የኔሞ ስርዓት ዘመናዊውን ዳኝነት እጅጉን የማገዝ አቅም አለው። በአመክንዮአዊነቱ (ምክንያታዊነቱ) ዘመናዊ አስተሳሰብንና ፍትህን በሚዛናዊነት አስተናግዶህብረተሰቡ በሰላም ተሳስቦ መኖር እንዲችል አስተዋፅኦውወደር የሌለው በመሆኑ ትልቅ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ባህላዊ እሴት ነው።
ሙሉ ጹሑፉን ከላይ ተያይዟል
#tikvahethiopia
#አለ_ህግ
https://t.me/lawsocieties
👍4
#የዩኒቨርሲቲ_መምህራን !

በዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበራት በኩል የቀረቡ ጥያቄዎች ፦

• መንግሥትን የደመወዝ ጭማሪ እና የዕርከን ዕድገት እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

• ለዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ እና ቴክኒካል ረዳቶች የተሰራውን አዲሱን የስራ ደረጃ ማሻሻያ JEG በተመለከተ ቅሬታ አላቸው።

• የመምህራን የቤት አበልን በተመለከተ በፍጥነት አሁን ያለው የቤት ኪራይ ዋጋ ከግምት አስገብቶ ተሻሽሎ ተግባራዊ እንዲደረገ ጠይቀዋል።

• በመንግስት የተደረገው የደረጃ ማሻሻያ ረጅም ጊዜ በዩንቨርሲቲ ያስተማሩ መምህራንን ልምድ ያላገናዘበ በመሆኑና በመምህራን መካከል በቀጣይ ፍትሀዊ የደምወዝ ልዩነት እንዲኖር ስለማያስችል የደረጃ ማሻሻየው የመምህራንን ልምድ እና ማዕረግ ያገናዘበ እንዲሆን ጠይቀዋል።

• የረዳት ፕሮፌሰር የአካዳሚክ ማዕረግ ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታ የ3ኛ ዲግሪ መደረጉን በተመለከተ ያለን ቅሬታ አላቸው።

• የአካዳሚክ ቴክኒክ ረዳቶች ዝቅተኛው ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ የመጀመሪያ ዲግሪ መሆኑ ላይ አቤቱታ አላቸው።

• የቺፍ ቴክኒካል ረዳት II የትምህርት ደረጃን ፒ ኤችዲ ዲግሪ መሆኑም ላይ አቤቱታ አላቸው።

ጥያቄዎቻችን መልስ ይሰጣቸው እያሉ የሚገኙት መምህራኑ ይህ ካልሆነ እስከ ስራ የማቆም አድማ መምታት ድረስ ዕርምጃ እንደሚወስዱ ገልፀዋል።

👉 ትምህርት ሚኒስቴር ለሪፖርተር ፥ " ጥያቄ እንዳለ እናውቃለን። ነገር ግን አሁን ላይ ለውጦች ለማምጣት ጥናት እየተካሄደ ነው። ከዚህ ባለፈ የምንለው ነገር የለም። የደመወዝ ጉዳይ የትምህርት ሚኒስቴር ብቻ አይደለም የሲቪል ሰርቪስ ጉዳይም ነው "

ያንብቡ : telegra.ph/ETH-08-07-2
via #tikvahethiopia
👍10👏1
" የፈተና ስርቆት እና ኩረጃ ከፍተኛ የደንብ ጥሰትና #ወንጀል " መሆኑ እና በህግ እንደሚያስጠይቅ፣

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፤ " የፈተና ስርቆት እና ኩረጃ ከፍተኛ የደንብ ጥሰትና #ወንጀል " መሆኑን የሚገልፅ ሲሆን እንዲህ ያለው ድርጊት በህግ እንደሚያስጠይቅ ያስገነዝባል።

የማህበረሰብ የጋራ ሀብት በሆነው ፈተና ላይ ሚፈጸም ማንኛውንም አይነት ወንጀል በጋራ መከላከል ይገባል ይላል አገልግሎቱ።

የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የብሔራዊ ፈተና ከማክሰኞ ጥቅምት 8 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ እስከ አርብ ጥቅምት 11 ቀን 2015 ዓ/ም ድረስ ይሰጣል።
#tikvahethiopia
https://t.me/lawsocieties
👍7👏3
"ዳኞች በወንጀል ሲጠረጠሩ ምክንያቱ ታምኖበት ያለመከሰስ መብታቸዉ ከተነሳ በኋላ መሆን ይገባዋል "
- ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ


በኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምሥራቅ ምድብ ችሎት የወንጀል ችሎት ዳኛ የሆኑት ፦
1ኛ ዳኛ ደሳለኝ ለሚ፣
2ኛ ዳኛ ሙሀመድ ጅማ
3ኛ ዳኛ አብዲሳ ዋቅጅራ ጥቅምት 25 ቀን 2015 ዓ.ም. ከሚሠሩበት ፍርድ ቤት በአዳማ ከተማ ኦሮሚያ ፖሊስ ተወስደው ታስረዋል።

ይህን ተከትሎ የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ እስራቱ ፈጽሞ ሕገወጥ እና በዳኝነት ነጻነት ላይ የተፈጸመ ጥቃት በመሆኑ በአስቸኳይ ከእስር ሊለቀቁና ድርጊቱ ተጣርቶ ተገቢው እርምጃ ሊወሰድ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

ኢሰመኮ ስለጉዳዩ ባደረገው ማጣራት ዳኞቹ በሕግ የተሰጣቸው ልዩ ጥበቃ መብት በሕጋዊ መንገድ ሳይነሳ እና ዳኞች መሆናቸው ሳይገለጽ ከወረዳ ፍርድ ቤት ተሰጥቷል በተባለ የእስር ትእዛዝ ከሥራ ገበታቸው ላይ ተነስተው የታሰሩ መሆኑን ገልጿል።

የእስር ትእዛዙን የሰጠው የወረዳ ፍርድ ቤት ታሳሪዎቹ ዳኞች መሆናቸውን እንደተረዳ የእስር ትእዛዙን የሻረ መሆኑን አሳውቋል፡፡

ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ፥ ዳኞቹ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈቱ አጥብቀው አሳስበዋል።

ትላንት አርብ ኢሰመኮ እስሩን በተመለከተ መግለጫ እስካወጣበት አመሻሽ ድረስ ዳኞቹ በእስር ላይ ነበሩ ፤ ዛሬም ስለመፈታታቸው የተባለ ነገር የለም።

ዛሬ የጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዜዳንት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ የዳኞቹ መታሰር " በጣም አሳሳቢ ነው " ብለዋል።

" በትላንትናው ዕለት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት ሥስት የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች በአዳማ ከተማ መታሠራቸው በጣም አሳሳቢ ነው " ያሉት ወ/ሮ መአዛ ፥ " ዳኞች የሕግ የበላይነት እንዲረጋገጥ ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ " ብለዋል።

ወ/ሮ መአዛ ፤ ዳኞች በወንጀል ሲጠረጠሩ ምክንያቱ ታምኖበት ያለመከሰስ መብታቸዉ ከተነሳ በኋላ መሆን እንደሚገባው አስገንዝበው " ስለተከሰተዉ ሁኔታ የበለጠ ለመረዳት እየሞከርን ነዉ። " ሲሉ ገልፀዋል።

" ከዚህ ቀደም እንደዚህ ያሉ ተመሳሳይ ድርጊቶች በአንዳንድ ክልሎች በዳኞች ላይ ሲፈጸሙ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤትና የክልል ፍርድ ቤቶች ፕሌነም አውግዘው ውሳኔ አስተላልፈው ነበር ። " ሲሉ ወ/ሮ መአዛ አስታውሰዋል።
#tikvahethiopia
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
👍8👎1
Forwarded from Lawyer Mike 🔊የህግ ባለሙያ
#እንድታውቁት

" ነገ እና እሁድ ከጥዋት እስከ ምሽት መታወቂያ ማሳደስ ትችላላችሁ "

#መታወቂያ_ለማሳደስ እየተጠባበቁ ያሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ነገ #ቅዳሜ እና #እሁድ ከጥዋት እስከ ምሽት አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ ተገልጿል።

የመታወቂያ እድሳት አገልግሎት ነገ ቅዳሜ እና እሁድ ማለትም ህዳር 3 እና 4 ቀን 2015 ዓ/ም ከጠዋት እስከ ምሽት ድረስ በየአካባቢው ባሉ የወረዳ ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ  ፅ/ቤቶች ይሰጣል።

ነዋሪዎች በተጠቀሱት ቀናት በየአቅራቢያቸው ባሉ ፅ/ቤቶች ተገኝተው መስተናገድ እንደሚችሉ የአዲስ አበባ ከተማ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ አሳውቋል።
#tikvahethiopia
👍1
#እንድታውቁት

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ማንኛውም የቋሚ ንብረት ሥም ዝውውር አገልግሎት፤ ከትናንት ኀዳር 29 ቀን 2015 ጀምሮ በጊዜያዊነት መታገዱ ተገልጿል።

አገልግሎቱ የታገደው በከተማዋ ህገ ወጥነትን ለመከላከል እየተደረገ ያለውን ሒደት ውጤታማ ለማድረግ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አሳውቋል።

ለሁሉም ክፍለ ከተሞች እና ለሚመለከታቸው አካላትም የተላለፋው ውሳኔ ተፈጻሚ እንዲሆን ትዕዛዝ መሰጠቱንም የከተማ አስተዳደሩን ዋቢ አድርጎ ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
#tikvahethiopia
https://t.me/lawsocieties
👍2
#Update

ወይዘሮ አበባ እምቢአለ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ተሹመዋል።

ምክር ቤቱ የወይዘሮ አበባ እምቢአለን ሹመት በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

ወ/ሮ አበባ በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዳኛነት ፣ የፌደራል ስነምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አቃቤ ህግነት፣ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዳኛነት አገልግለዋል።

አቶ ቴዎድሮስ ምህረት (ፕሬዜዳንት) እና ወ/ሮ አበባ እምቢአለ (ምክትል ፕሬዜዳንት) በጉባኤው ፊት ቀርበው ቃለ-መሐላ ፈጽመዋል።
#tikvahethiopia
👍11
1287_2015_የኤክሳይዝ_ታክስ_አዋጅ_ማሻሻያ_.pdf
7.6 MB
#ETHIOPIA

የኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ ላይ ማሻሻያ መደረጉን የገቢዎች ሚኒስቴር አሳውቋል።

የኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ ቁጥር 1186/2012 ከየካቲት 5/2012 ዓ.ም ጀምሮ ስራ ላይ የዋለ ሲሆን ይህ አዋጅ የታክሱን መሰረት በማስፋት እና የታክሱን አስተዳደር ስርዓት በመቀየር ከፍተኛ ጠቀሜታን ማስገኘቱን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ሚያዚያ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ባካሄደው 15ኛ መደበኛ ጉባኤው በአዋጁ ላይ የቀረቡ ማሻሻያዎችን ታሳቢ በማድረግ የአዋጁ ማሻሻያ ተደርጓል ሲል አስታውሷል።

የአዋጁ ማሻሻያ ታሰቢ ያደረገው ፦

- #ተደራራቢ የኤክሳይዝ ታክስ የተጣለባቸው ምርቶች ላይ ማሻሻያ ለማድረግ፣

- ቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት ላይ የኤክሳይዝ ታክስ እንዲከፈል ለማድረግ፣

- የኤክሳይዝ ታክስ ተጥሎባቸው የነበሩት አንዳንድ ምርቶች ላይ ታክሱን ለማንሳት መሆኑ ተመላክቷል።

ምክር ቤቱ በአስተዳደር ምክንያት የተደረጉ ማስተካከያዎችን እና የማሻሻያውን ዋና ዋና ምክንያቶችን ከመረመረ በኋላ የኤክሳይዝ ታክስ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1287/2015 እንዲጸድቅ አድርጓል፡፡

በመሆኑም ገቢዎች ሚኒስቴር የአዋጁ ማሻሻያ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፀደቀበት ጊዜ ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል እንዲደረግ እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት ፣ የንግዱ ማህበረሰብ ሁሉ እንዲያውቁት መመሪያ ሰጥቷል።

(የአዋጁ ማሻሻያ ከላይ በ #PDF ተያይዟል)

#የገቢዎች_ሚኒስቴር
#tikvahethiopia
#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
👍2
አሜሪካ የDV-2025 አመልካቾችን መቀበል ጀመረች።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አመታዊውን የዲይቨርሲቲ ቪዛ (#ዲቪ) ፕሮግራም / " ግሪን ካርድ ሎተሪ " በመባል የሚታወቀውን በአሜሪካ ለመኖር እና ለመስራት ለሚፈልጉ አመልካቾች ዛሬ ክፍት አድርጓል።

እንደ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ መግለጫ መርሃ ግብሩ ዛሬ ሩቡዕ ጥቅምት 4 ተጀምሮ ማክሰኞ ህዳር 7 ቀን 2023 ይጠናቀቃል።

አሜሪካ አሁን ባለው ፕሮግራም 55000 ለሚደርሱ የውጭ ዜጎች የግሪን ካርድ እድል ትሰጣለች።

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለዲቪ ፕሮግራም ለመመዝገብ / ለማመልከት ምንም አይነት ክፍያ እንደሌለው አሳውቋል።

ነገር ግን ወደፊት ለቃለ መጠይቅ ቀጠሮ የተያዙ ተመራጮች መደበኛ የቪዛ ማመልከቻ ከማቅረባቸው በፊት የቪዛ ማመልከቻ ክፍያ እንዲከፍሉ ይገደዳሉ። እነዚህ ተመራጮች በቆንስላ ኦፊሰር አማካኝነት ለቪዛ ብቁ መሆን አለመሆናቸውን የሚወሰንላቸው ናቸው።

በአጠቃላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ዲቪ ለመሙላት ብቁ ከሆኑ በርካታ ሀገራት 55,000 አመልካቾች በዘፈቀደ በውስጥ ስርዓት ይመረጣሉ።

አስፈላጊ #መመሪያዎችን ፣ መስፈርቶችን እንዲሁም ለማመልከት ይህን ትክክለኛ ድረገፅ ይከተሉ፦ https://dvprogram.state.gov/

አመልካቾች ዲቪ ለማመልከት #ክፍያ_የማያስፈልግ ስለሆነ ከአጨባርባሪዎች እንዲጠነቀቁ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳስቧል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
👍9
የኢንቨስትመንት ባንክ ምንድነው ? ከሌሎች ባንኮች በምን ይለያል ?

የንግድ ባንኮች የሚባሉት ፦ በብሔራዊ ባንክ ስር የሚተዳደሩ ፤ ከብሔራዊ ባንክ ፍቃድ ተሰጥቷቸው የሚተዳደሩ ናቸው።

ኢንቨስትመንት ባንክ ፦ በካፒታል ገበያ አዋጅ መሰረት የሚቋቋም፣ በካፒታል ገበያ ባለስልጣን ፍቃድ የሚሰጠው ነው። ከግለሰቦች ተቀማጭ የሚወስድ ከሆነ የኢንቨስትመንት ባንክ መሆን አይችልም።

የኢንቨስትመንት ባንኪግ ስራ ምንድነው ?

ዋና ስራው ወደ ካፒታል ገበያ የሚመጡትን ኩባንያዎች፣ ድርጅቶች ፣ መንግስት ፣ ከተሞች ሊሆኑ ይችላሉ ቦንድ መሸጥ ሲፈልጉ ፣ አክሲዮን መሸጥ ሲፈልጉ ፦
* አክሲዮኑ ምን ይመስላል ?
* አክሲዮኑ በምን ያህል ዋጋ ይሸጥ ?
* መቼና ለማን ይሸጥ ? የሚለውን የፋይናንስ ስትራተጂ ላይ የምክር አገልግሎት የሚሰጡና የሚያገናኙ በካፒታል ገበያ ውስጥ ትልቁን ድርሻ የሚጫወቱ ናቸው።

ለምሳሌ ፦ አንድ በግል የተያዘ ድርጅት ፤ ወደ ህዝብ ድርጅት ነው መቀየር የምፈልገው ፣ የሼር ኩባንያ ነው መሆን የምፈልገው ብሎ ሼሩን የካፒታል ማርኬት ላይ መሸጥ ቢፈልግ ድርጅቱ ምን ያህል ነው ዋጋው ? ለአብነት ወደ 2000 ሼር ቀይሬ 2 ሺህ ሼር ለገበያው ሸጣለሁ ቢል እያንዳንዱ ሼር ዋጋው ምን ያህል ነው የሚለውን አጠቃላይ ስራ የሚሰራው ኢንቨስትመንት ባንክ ነው።

በተጨማሪ ኢንቨስትመንት ባንክ ፦

* price discovery / ገበያው ላይ ኩባንያዎች ያላቸው እውነተኛ ዋጋቸው ምንድነው የሚለውን ያጣራል።
* የካፒታል ገበያ ላይ የሚሳተፉ አካላትን ያማክራል።
* የካፒታል ብክነት እንዳይኖርና ካፒታል ወደአስፈላጊው ቦታ እንዲሄድ ያደርጋል።

ኢንቨስትመንት ባንኮች እንደ ሌሎች የንግድ ባንኮች ከሰዎች ላይ ተቀማጭ ገንዘብ / deposit አይወስዱም።

የኢንቨስትመንት ባንኮች የማማከር ስራን የሚሰሩ ሲሆን አንዳንድ ኩባንያዎች የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ነዋይ ገበያ ለመግባት ሲወስኑ ኩባንያውን ማዛጋጀት፣ ሼሩ ምን ያህል ነው የሚለውን መለየት ፣ ምን ያህል ሼር ለምን ያህል ሰው የሚለውን መለየት ስራዎችን ይሰራሉ።

የካፒታል ገበያውን የሚቆጣጠረው አካል ፤ በካፒታል ገበያው ለሚሳተፉ አካላት ፍቃድ ከመስጠት እና ሂደቱን ከመቆጣጠር ባለፈ ኢንቬስተሮች በየትኛው ዘርፍ መሳተፍ አለባቸው የሚለውን አይወስንም ሃሳብም አይሰጥም ፤ ይህን የሚያደርጉት የአዋጭነት ትንተናዎችን በመስራት የኢንቨስትመንት ባንኮች ናቸው።

ማማከር፣ ኢንቬስተሮችን እና ተፈላጊ የፋይናንስ ሃብት ማገናኘት የኢንቨስትመንት ባንኮች ስራ ይሆናል። የካፒታል ገበያ ላይ የሚሳተፉ ድርጅቶችን ወክለው ከሰነደ መዋዕለ ነዋይ ገበያው ሆነ ከተቆጣጣሪ መ/ቤቱ ጋር በመሆን ብዙ ስራዎች ይሰራሉ።

ለኢንቨስትመንት ባንክ መስረታ የሚጠየቀው ካፒታል ለንግድ ባንኮች ከሚጠየቀው #ያነሰ ነው።

የንግድ ባንኮች በዚህ ላይ መሳተፍ ይችላሉ ?

አሁን በኢትዮጵያ ስራ ላይ ያሉ የንግድ ባንኮች ጎን ለጎን የኢንቨስትመንት ባንክ ተሳትፎ የሚያደርጉበት እድል አላቸው።

እንደ ኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን መረጃ ከመጪው ሰኞ ጀምሮ መስፈርቱን ለሚያሟሉ የኢንቨስትመንት ባንክ ፍቃድ መስጠት የሚጀምር ሲሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ በኢትዮጵያ ያሉና ከኢትዮጵያ ውጭ ያሉ ባንኮችም የኢንቨስትመንት ባንክ ፍቃድ ይወስዳሉ ተብሎ እንደሚጠብቅ ተስፋ ተደርጓል።

Credit ፦
#DrBirukTaye (ECMA Director)
#SirakSolomon (ECMA Senior Legal Advisor)
#YohanessArega (ECMA Senior Advisor)
#WuberstTessema (Journalist , FBC)

ዝግጅት ፦ #TikvahEthiopia

#tikvahethiopia
👍14🎉1
#AddisAbaba #ንግድ

የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ማህበረሰብ ያለወከባ በተረጋጋ መንፈስ የንግድ ተግባሩን ለማከናወን እንዲያስችል ዕድል ይፈጥርለታል የተባለ አዲስ መመሪያ ስራ ላይ መዋሉን ለማወቅ ተችሏል።

አዲሱ መመሪያ  " በመንደር ንግድ ቁጥጥር አሰራር ስርዓት መመሪያ 159/2016 " እንደሚባል ከአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

መመሪያው በየትኛው አስተዳደር እርከን የትኛው አይነት እርምጃ እንደሚወሰድ በግልጽ ያስቀመጠ ሲሆን ይህም ሲታይ የነበረውን ግልጽ እና ፍትሃዊ ያልሆነ አሰራር ያስቀራል ተብሏል።

በአዲሱ የመንደር ንግድ መመሪያ መሰረት የወረዳ የንግድ ቁጥጥር ባለሙያ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወስድ ህጉ የሚፈቅድለት በተመደበበት መንደር ላይ ፦
ያለ ንግድ ፍቃድ
ባልታደሰ ፍቃድ
በታገደ አልያም በተሰረዘ ንግድ ፈቃድ የሚነግድ የንግድ ድርጅት ላይ #ብቻ_ነው። ይህን ሲያደርግም ለቅርብ ኃላፊ ማሳወቅ አለበት።

ከዚህ ወጪ ያሉት ጥፋቶች #በሙሉ እርምጃ ሳይወስድ ለቅርብ ኃላፊው በፅሁፍ በማሳወቅ ለውሳኔ ወደ ንግድ ቢሮ መላክ ይጠበቅበታል ፤ የተወሰነውን ውሳኔ የማስፈፀም ኃላፊነትም አለበት።

መመሪያው ፦ https://t.me/tikvahethiopia/87886

#TikvahEthiopiaFamilyAA
#tikvahethiopia
አማራጭ የሕግ እውቀት
👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties

👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/

👉 LinkedIn 👈
https://www.linkedin.com/company/lawsocieties/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Ale_Hig
👍7
159_በመንደር_የንግድ_ቁጥጥር_የአሠራር_ሥርዓት_መመሪያ_ቁጥር_159_2016.pdf
436.8 KB
#AddisAbaba

አዲሱን " በመንደር ንግድ ቁጥጥር አሰራር ስርዓት መመሪያ 159/2016 " የተያያዘውን ፋይል ከፍተው በዝርዝር ያንብቡ።

#አዲስ_አበባ_ንግድ_ቢሮ
#tikvahethiopia
አማራጭ የሕግ እውቀት
👉Telegram👈
https://t.me/lawsocieties

👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/

👉 LinkedIn 👈
https://www.linkedin.com/company/lawsocieties/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Ale_Hig
👍51
#ኢትዮጵያ

በሀገሪቱ ውስጥ ያለ ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም የፋይናንስ ኦዲት ሪፖርቱን ለሰላም ሚኒስቴር ማቅረብ እንደሚኖርበት ፤ ከውጭ አገር የሚመጣ የገንዘብ ዕርዳታ በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ እንደሚኖርበት የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ መዘጋጀቱን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

" የሃይማኖት ጉዳዮች አዋጅ " የተሰኘው ረቂቅ አዋጁ የሃይማኖት ተቋማቱ ተቀባይነት ያለው የሒሳብ አያያዝና የኦዲት ሥርዓት መዘርጋት እንደሚኖርባቸው፣ የኦዲት ሪፖርታቸውን ለሰላም ሚኒስቴር ማቀረብ እንዳለባቸው ይደነግጋል፡፡ 

ረቂቅ አዋጁ ምን ይዟል ?

- የሃይማኖት ተቋማት የሚጠቀሙት የሒሳብ አያያዝ ሥርዓት የገቢ፣ የወጪና አጠቃላይ የንብረት ዝርዝር የያዘ መሆን አለበት።

- የገቢ አሰባሰብና የወጪ አስተዳደር በሕጋዊ መንገድ ማከናወን አለባቸው።

- የሃይማኖት ተቋም በራሱ #የገቢ_ማስገኛ ሥራዎችን በሚያከናውንበት ጊዜ ለዚሁ ሥራ ሲባል የተለየ የባንክ ሒሳብ መክፈትና የተለየ መዝገብ መያዝ አለበት።

- ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም ከውጭ የሚላክለትን የገንዘብ ዕርዳታ፣ ስጦታ ወይም ሌሎች የገንዘብ ድጋፎችን በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ አለበት። ሲያሳውቅም ፦
° የለጋሹን ድርጅት ወይም ግለሰብ ስም እና አድራሻ፣
° የተለገሰው የገንዘብ፣ ስጦታ ዓይነት እና መጠን ፣
° ስጦታው / ድጋፉ የተሰጠበት ልዩ ዓላማ መካተት አለበት።

- ማንኛውም  የሃይማኖት ተቋም  የበጀት ዓመቱ ባለቀ በ3 ወር ውስጥ የፋይናንስ እንቅስቃሴውን በገለልተኛ ኦዲተር ማስመርመር አለበት። የኦዲተሩን አቋም እና የውሳኔ ሐሳብም መያዝ ይኖርበታል።

- የሰላም ሚኒስቴር የደረሰውን የኦዲት ሪፖርት አመቺ በሆነ መንገድ ለሕዝብ ይፋ ማድረግ ይኖርበታል።

#ሪፖርተርጋዜጣ
#tikvahethiopia
👍113🤔3
#DV2026

የ2026 የአሜሪካ ዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) ማመልከቻ ከዛሬ ጀምሮ ክፍት ተደርጓል።

ለ2026 DV ለማመልከት https://dvprogram.state.gov/ ይጠቀሙ።

ለማመልከት ምንም አይነት ክፍያ አያስፈልግም።

ማመልከቻው እስከ ህዳር 5 /2024 ድረስ ክፍት ሆኖ ይቆያል።

ከፍተኛ የመሙላት ፍላጎቶች ድረገጹ ላይ መዘግየቶችን ሊያስከትል ስለሚችል ለመሙላት እስከ የምዝገባው ጊዜ የመጨረሻ ሳምንት ድረስ ባይጠብቁ ይመከራል።

ዘግይተው የሚገቡ ማመልከቻዎች ተቀባይነት አይኖራቸውም።

ህጉ ለአንድ ሰው አንድ ጊዜ ብቻ እንዲያመለክት ነው የሚፈቅደው። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የሚጠቀመው የተራቀቀ ቴክኖሎጂ ደጋግሞ የሚገቡ ማመልከቻዎችን የሚለይ ነው። ከአንድ ጊዜ በላይ አንድ ሰው ካመለከተ ሁሉንም የዛን ሰዎች ማመልከቻዎች ይሰርዛል።

ያልተሟላ ማመልከቻም ተቀባይነት የለውም።

ዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) ከቪዛ አማካሪዎች ፣ ' እንሞላለን ' ከሚሉ ወኪሎችና ከሌሎች አካላት እገዛ ሳይጠይቁ ራስዎ እንዲሞሉ ይመከራል።

ማመልከቻውን እንዲሞላሎት የሰው እርዳታ ካስፈለገ ጥያቄዎችን በትክክል ለመመለስ በሚሞላበት ስፍራ መገኘት ያስፈልጋል። ከዚህ በተጨማሪም የ ' ልዩ ማረጋገጫ ቁጥሩ ' ን ለመያዝ በስፍራው መገኝት ያስፈልጋል።

አንዳንድ የሚሞሉ ሰዎች ይህን ቁጥር ይዘው በመቀየር ተጨማሪ ብር የሚጠይቁ ስላሉ እንዳይታለሉ መጠንቀቅ ያስፈልጋል።

የማረጋገጫ ቁጥሩ እጅግ ወሳኝ በመሆኑ በጥንቃቄ መያዝ አለበት።

ለ2026 የፊስካል ዓመት እስከ 55,000 የሚደርስ የዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) ተዘጋጅቷል። ይህ ቁጥር ብቁ የሆኑ ሀገራት ሁሉ የሚጠቃልል ነው።

ኢትዮጵያውያንም ለማመልከት ብቁ ናቸው።

አሜሪካ በየዓመቱ ከኢትዮጵያ ጨምሮ ከተለያዩ ሀገራት በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) አማካኝነት እንደምትቀበል ይታወቃል።

🇺🇸 ለአሜሪካ ዳይቨርሲቲ ቪዛ 2026 ለማመልከት ይህንን dvprogram.state.gov ሊንክ ይጠቀሙ !🇺🇸

(ተጨማሪ ማብራሪያ እና እንዴት መሙላት እንደሚቻል የሚገልጽ መመሪያ በቀጣይ እናያይዛለን)

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
👍198👏2
የኢፌዲሪ ህገ መንግስት ስለ ሪፐብሊኩ ፕሬዝዳንት ስልጣንና ተግባር ምን ይላል ?

(የኢፌዴሪ ህገ መንግስት)

ምዕራፍ ሰባት
ስለ ሪፐብሊኩ ኘሬዚዳንት
አንቀጽ 69
ስለ ኘሬዚዳንቱ

ኘሬዚዳንቱ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ርዕሰ ብሔር ነው፡፡


አንቀጽ 70
የፕሬዜዳንቱ አሰያየም
1. ለፕሬዜዳንትነት ዕጩ የማቅረብ ሥልጣን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው።
2. የቀረበው ዕጩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብሰባ በሁለት ሦስተኛ ድምጽ ከተደገፈ ፕሬዜዳንት ይሆናል።
3. የምክር ቤት አባል ፕሬዜዳንት ሆኖ ከተመረጠ የተወከለበትን ምክር ቤት ወንበር ይለቃል።
4. የፕሬዜዳንቱ የሥራ ዘመን 6 ዓመት ነው። አንድ ሰው ከሁለት ጊዜ በላይ ለፕሬዜዳንትነት ሊመረጥ አይችልም።

አንቀጽ 71
የኘሬዚዳንቱ ሥልጣንና ተግባር
1. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽኑን ምክር ቤት ዓመታዊ የጋራ ስብሰበባ ይከፍታል፡፡
2. በዚህ ሕገ መንግሥት መሰረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያጸደቃቸው ሕጐችና ዓለምአቀፍ ስምምነቶች በነጋሪት ጋዜጣ ያውጀል፡፡
3. ሀገሪቷን በውጭ ሀገሮች የሚወክሉትን አምባሳደሮችና ሌሎች መልክተኞች በጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅራቢነት ይሾማል፡፡
4. የውጭ ሀገር አምሳደሮችንና የልዩ መልዕክተኞችን የሹመት ደብዳቤ ይቀበላል፡፡
5. በሕግ መሰረት ኒሻኖች እና ሽልማቶችን ይሰጣል፡፡
6. በጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅራቢነት በሕግ በተወሰነው መሰረት ከፍተኛ የውትድርና ማዕረጐችን ይሰጣል፡፡
7. በሕግ መሰረት ይቅርታ ያደርጋል፡፡
#TikvahEthiopia
Telegram
https://t.me/AleHig

Telegram_Group
https://t.me/AleHig_Group

Facebook Page
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

LinkedIn
https://www.linkedin.com/company/alehig/

YouTube
https://www.youtube.com/@Ale_Hig

TikTok
https://www.tiktok.com/@alehigofficial

Instagram https://www.instagram.com/alehigofficial

Twitter /X
https://x.com/AlehigOfficial?t=yFRauAZ7v70Je2MEPIGGsQ&s=09

official website
https://www.alehig.com

#LegalAwareness #AleHig #LegalUpdates #AccessToJustice
👍22🥰32
የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅ .pdf
498.2 KB
#ፋይል: አጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅ።
#tikvahethiopia
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ

አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ https://t.me/AleHig
የሕግ እውቀት alehig.com
👍6
ኢንትረስት ሜዲካል IVF
ፀደቀ‼️በኢትዮጵያ የወንድ የዘር ፈሳሽ ልገሳ፣ የሰውነት አካል መለገስ እና በህክምና የታገዘ ሞት እንዲጀመር የሚፈቅደው ህግ ጸደቀ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና አገልግሎት እና አስተዳድር ረቂቅ አዋጅን አጽድቋል። አዋጁ ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ ተጀምረው የማያውቁ እና አዳዲስ አገልግሎቶችን መስጠት የሚያስችሉ የጤና አገልግሎቶች እንዲጀመሩ የሚያደርግ ነው። ለአብነትም መዳን በማይችል እና በስቃይ ውስጥ…
➡️ የዘር ፍሬ በመለገስ ልጅ መውለድ እንዲቻል ለመፍቀድ ቀርቦ የነበረው የአዋጅ ድንጋጌ የለበትም።
የጤና አገልግሎት አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ " ለ3 ወር ያህል ውይይት ሲደረግበት ቆይቶ ከቀናት በፊት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ9 ድመጸ ተአቅቦ ፣ 1 ተቃውሞ በአብላጫ ድምጽ ፀድቋል።

የዘር ፍሬን በመለገስ በቴክኖሎጂ በመታገዝ ልጅ መውለድ እንዲቻል እንዲፈቅድ በረቂቅ ሕጉ ተካቶ የነበረው አንቀጽ እንዲወጣ ተደርጓል።

ለጤና፣ ማኅበራዊና ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተመርቶ ውይይት ሲደረግበት በነበረው ረቂቅ አዋጅ በቴክኖሎጂ የታገዘ የሥነ ተዋልዶ ሕክምና አገልግሎት የሚፈቅደው ድንጋጌ እንዲወጣ ተጠይቆ ነበር።

ድንጋጌው እንዲወጣ ያደረገው " ልጅ እንዲኖረው የፈለገ ምን ይሁን ? " ለሚለው ጥያቄ፣ የጉዲፈቻ ልጅ በበቂ ሁኔታ የሚገኝ መሆኑን ቋሚ ኮሚቴው ተነጋግሮበት በመወሰኑ ነው።

የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ታደለ ቡራቃ (ዶ/ር) ምን አሉ ?

" ድንጋጌው ከረቂቁ እንዲወጣ የተደረገው ወላጆች ልጅ ለመውለድ ያላቸውን ፍላጎት ሳይሆን፣ ሕግ አውጪው የሚወለዱ ልጆች የማኅበረሰብ ቀውስ እዳያጋጥማቸው በማሰብ፣ ከእምነትና ከማኅበረሰብ መስተጋብር ጋር የተጣጣመ ሕግ መውጣት እንዳለበት ታስቦ ነው።

በተጨማሪም ከሕገ መንግሥቱ ጋር የሚጋጭ ድንጋጌ ማውጣት ስለማይፈቀድ ነው።

ለተጋቢ ባለትዳሮች ፍላጎት ሲባል ይህ ሕግ ወጥቶ የሚወለደውን ሕፃን መብት መጋፋት አያስፈልግም።

ይሁን እንጂ የፀደቀው ሕግ በጋብቻ የተጣመሩ ባለትዳሮች ያለ ልገሳ የራሳቸውን የዘር ፍሬ ብቻ በመውሰድ፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ የሥነ ተዋልዶ ሕክምና ማግኘት እንዲችሉ ፈቅዷል " ብለዋል።

ለፓርላማ ቀርቦ የነበረው ረቂቅ ሕግ በቴክኖሎጂ የታገዘ የሥነ ተዋልዶ ሕክምና አገልግሎት ተጠቃሚዎች፣ በሕጋዊ ጋብቻ የተጣመሩ ወይም ተፈጥሮአዊ በሆነ መንገድ ልጅ መውለድ የማይችሉ መሆናቸው በዘርፉ ባለሙያ ሲረጋገጥ እንደሆነ ይል ነበር፡፡

የምክር ቤት አባላት የዘር ፍሬን በሕጉ ከተፈቀደው ውጪ አሳልፎ የሰጠ አካል ከተገኘ በወንጀል ሕግ ተጠያቂ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።

#tikvahethiopia
🔽🚨🚨🚨
🔴Attorney and Legal Consultant
ጠበቃና የሕግ አማካሪ

We are delighted to connect with you! You can easily reach us through the following platforms to stay informed and access our legal services:

Website & Social Media
Linktree:📱📱📱📱📱📱📱📱  

              https://linktr.ee/alehig

📱Facebook:
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

📱Telegram Channel:⭐️
https://t.me/AleHig

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com


Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595
📱Telegram:  ✉️ @MikiasMelak


Our Commitment
alehig.com
📊አለሕግ🔽
🔠🔠🔠    🔠🔠🔠
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት


We provide expert legal advice, support, and resources on various laws, proclamations, regulations, and directives to empower and guide you.

Feel free to reach out anytime‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍163
#እንድታውቁት

ከተሻሻለው የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክን ለመቆጣጠር የወጣው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ

ከፖሊስ በተሽከርካሪ ላይ የደረሰውን የጉዳት አይነት የሚገልጽ የፅሁፍ ማስረጃ ሳይቀበሉ ጥገና የሚያከናውኑ ጋራዦች / የጋራዥ ባለቤቶች / በወንጀል ህግ የሚጠየቁት እንዳለ ሆኑ የ20 ሺህ ብር ቅጣት ይጣልባቸዋል።

አመታዊ የተሽከርካሪ ምርመራ ያላደረገ የተሽከርካሪ ባለንብረት 3,000 ብር ይቀጣል።

የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ሳይኖረው ተሽከርካሪ ያሽከረከረ ማንኛውም ሰው 5,000 ብር ይቀጣል።

  የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ሳይኖረው ተሽከርካሪ በማሽከርከር በንብረት ላይ ጉዳት ያደረሰ ማንኛውም ሰው 7000 ብር ይቀጣል።

ከባለቤትነት ወይም በይዞታው የተያዘውን ተሽከርካሪ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ለሌላው ሰው አሳልፎ የሰጠ ማንኛውም የተሸከርካሪ ባለንብረት 3,000 ብር ይቀጣል።

🚨የትራፊክ ግጭት ወይም ጉዳት አድርሶ በቦታው ላይ ያልቆመ ወይም ባደረሰው የትራፊክ ጉዳት የተጎዳውን እና ሕክምና የሚያስፈልገውን ሰው ወደ ህክምና በመውሰድ እንዲታከም ያላደረገ 👉 በወንጀል ህጉ መሰረት ይጠየቃል።

ወጣት አሽከርካሪዎች፣ ጀማሪ አሽከርካሪዎች ፣ ሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎች ፣ የንግድ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች እና አደገኛ ጭነት የጫኑ አሽከርካሪዎች የአልኮል መጠን በትንፋሽ በየትኛውም መጠን ከተገኘ 2,000 ብር ቅጣት ይጠብቃቸዋል።

የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ታግዶበት ሳለ ያሽከረከረ 3,000 ብር ቅጣት ይጣልበታል።

አልኮል መጠን በትንፋሽ ውስጥ ፦
🍻 0.24 እስከ 0.6 ሚሊግራም/ሊትር 1,500 ብር ያስቀጣል።
🍻 0.61 እስከ 0.8 ሚሊግራም /ሊትር 2,000 ብር ያስቀጣል።
🍻 0.81 እስከ 1.0 ሚሊግራም/ሊትር 2,000 ብር ያስቀጣል።
🍻 1.0 ሚሊግራም/ሊትር በላይ የተገኘበት 3,000 ብር ይቀጣል።

በተሽከርካሪ ላይ ተገቢ ያልሆነ አካል የጨመረ ወይም ከተፈቀደለት ወንበር ውጭ ተጨማሪ ወንበር ወይም መቀመጫ የጨመረ የተሽከርካሪ ባለንብረት 400 ብር ይቀጣል።

የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ሞተር እየሰራና በተሽከርካሪው ውስጥ መንገደኞች እያሉ ነዳጅ መሙላት 1,500 ብር ያስቅጣል።

ቴሌቪዥን ወይም ሌሎች ምስሎችን ተሽከርካሪ ውስጥ እየተመለከተ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

የደህንነት ቀበቶ ሳያስር ወይም ተሳፋሪዎች የደህንነት ቀበቶ ማሰራቸውን ሳያረጋግጥ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

የተንቀሳቃሽ ስልክ በእጁ ይዞ እያነጋገረ፣ ወይም መልዕክት እየጻፈ እየላከ ወይም እያነበበ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

ጫት ቅሞ ወይም እየቃመ ወይም አደንዛዥ ዕፅ ወስዶ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

የተሽከርካሪ የፊት ወይም የኃላ ሰሌዳ ሳይኖረው ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

ለአውቶብስ ብቻ ተብሎ በተለየ መንገድ ላይ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

ቀይ መብራት የጣሰ 1,500 ብር ይቀጣል።

የትራፊክ ተቆጣጣሪ ትዕዛዝ ያልፈጸመ፣ ወይም የተሳሳተ መረጃ የሰጠ ወይም እንዲቆም ሲታዘዝ በእንቢተኝነት ሳይቆም የሄደ 1,000 ብር ይቀጣል።

የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ኖሮት ሳይዝ ያሽከረከረ ወይም የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃዱን ሳያሳድስ ያሽከረከረ 1,000 ብር ይቀጣል።

ከተፈቀደው ፍጥናት በታች ያሽከረከረ ወይም የቀኙን ጠርዝ ሳይዝ በዝግታ ያሽከረከረ 1,000 ብር ይቀጣል።

ከመጠን በላይ ድምጽ እያሰማ ወይም የጆሮ ማዳመጫ እያዳመጠ ያሽከረከረ 1,000 ብር ይቀጣል።

መንገድ ላይ ያለን ውሃ በተሽከርካሪው አማካኝነት እግረኛ ላይ እንዲረጭ ያደረገ 1,000 ብር ይቀጣል።

(ተጨማሪ የጥፋት ዝርዝር እና ቅጣቶቹን ከላይ ያንብቡ)
#tikvahethiopia
🔴Attorney and Legal Consultant
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ

We are delighted to connect with you! You can easily reach us through the following platforms to stay informed and access our legal services:

Website & Social Media
Linktree:📱📱📱📱📱📱📱📱  

              https://linktr.ee/alehig

📱Facebook:
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

📱Telegram Channel:⭐️
https://t.me/AleHig

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com


Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595
📱Telegram:  ✉️ @MikiasMelak


Our Commitment
alehig.com
📊አለሕግ🔽
🔠🔠🔠    🔠🔠🔠
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት


We provide expert legal advice, support, and resources on various laws, proclamations, regulations, and directives to empower and guide you.

Feel free to reach out anytime‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍243👏1🙏1
" በስም ከተለዩት ግለሰቦች መካከል ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ዜጎችም ይገኙበታል " -የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ

የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ከ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ ዕዳ ያለባቸው 62 ግብር ከፋዮች ከሀገር እንዳይወጡ የእግድ ትዕዛዝ ማስተላለፉን ገልጿል፡፡

እግድ የተጣለባቸው 62 ግለሰቦች በተደጋጋሚ ጥሪ ቢደረግላቸውም ዕዳቸውን ለመክፈል  ፈቃደኛ ያልሆኑ ናቸው ተብሏል።

" በስም ከተለዩት ግለሰቦች መካከል ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ዜጎችም ይገኙበታል ዕዳቸውን የማይከፍሉ ከሆነም አዋጁ በሰጠን ሥልጣን መሰረትም በቀጣይ የንብረት እግድ እና ንብረታቸውን በሃራጅ የመሸጥ እርምጃዎች ይወሰዳሉ " ሲሉ የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቢሮው በታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008 አንቀፅ 44 ንዑስ አንቀፅ ከ1-3 ለተቋሙ በተሰጠ ስልጣን መሰረት ከሀገር እንዳይወጡ እግድ የተጣለባቸው ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለፌዴራል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ማስተላለፉን አሳውቋል፡፡

የ62ቱ ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለፌዴራል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የተላከው በትላንትናው ዕለት ነው።

አቶ ሰውነት " በህጉ መሰረት የተቀመጠ ቀነ ገደብ አለ በአዋጁ በተቀመጠው ቀነ ገደብ መሰረት መጥተው እስካልከፈሉ ድረስ ለእዳው ማካካሻ በሚሆን መሰረት ንብረታቸው በሃራጅ ተሽጦ እዳው ይሸፈናል " ብለዋል።

ቢሮው የግብር ዕዳቸውን ሳይወጡ የሚሰወሩ ግብር ከፋዮችን በመከታተል ግዴታቸውን እንዲወጡ ለማስቻል የዕዳ ክትትልና አስተዳደር የስራ ክፍልን በ2017 በጀት ዓመት እንደ አዲስ አዋቅሯል።

በዚህም መሰረት ባለፉት 6 ወራት ከ 6.4 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ እዳ መሰብሰቡን አቶ ሰውነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA
#tikvahethiopia
Welcome to Mikias Melak & Associates Law Office!

🔹 Facebook: AlehigOfficial
🔹 Telegram Channel: AleHig
🔹 Website: alehig.com
📧 Email: mikiasmelak.mm@gmail.com

📞 Direct Contact:
WhatsApp: +251920666595
Telegram: @MikiasMelak

For legal consultations and inquiries, feel free to reach out. We’ll get back to you as soon as possible!
👍181