አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.87K photos
25 videos
1.87K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
አዲሱ_የሒሳብ_መዝገብ_አያያዝ_መመሪያ.pdf
1.1 MB
#እንድታውቁት #አለ_ህግ #Ale_Hig

የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ኦዲት የቅሬታ ምንጭ ሆኖ የቆየው

" የሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 152/2011 " ን በአዲስ መመሪያ እንዲተካ ማድረጉን አሳውቋል።

መመሪያውን ማሻሻል ያስፈለገበት ዋነኛ ምክንያት የታክስ አስተዳደሩን ቀልጣፋ ለማድረግ እና ግልጽነት የጎደላቸውን አሰራሮች ግልጽ ለማድረግ ነው ብሏል ሚኒስቴሩ።

አዲሱ መመሪያ ቁጥር 176/2014 በሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 152/2011 ላይ የነበረውን አሰራር ያሻሽላል ተብሏል።

አዲሱ ወይም የተሻሻለው የሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 176/2014 ከላይ በPDF ተያይዟል።

tikvah ethiopia

#አለ_ህግ #Ale_Hig
👍3
Forwarded from Lawyer Mike 🔊የህግ ባለሙያ
#እንድታውቁት

" ነገ እና እሁድ ከጥዋት እስከ ምሽት መታወቂያ ማሳደስ ትችላላችሁ "

#መታወቂያ_ለማሳደስ እየተጠባበቁ ያሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ነገ #ቅዳሜ እና #እሁድ ከጥዋት እስከ ምሽት አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ ተገልጿል።

የመታወቂያ እድሳት አገልግሎት ነገ ቅዳሜ እና እሁድ ማለትም ህዳር 3 እና 4 ቀን 2015 ዓ/ም ከጠዋት እስከ ምሽት ድረስ በየአካባቢው ባሉ የወረዳ ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ  ፅ/ቤቶች ይሰጣል።

ነዋሪዎች በተጠቀሱት ቀናት በየአቅራቢያቸው ባሉ ፅ/ቤቶች ተገኝተው መስተናገድ እንደሚችሉ የአዲስ አበባ ከተማ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ አሳውቋል።
#tikvahethiopia
👍1
#እንድታውቁት

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ማንኛውም የቋሚ ንብረት ሥም ዝውውር አገልግሎት፤ ከትናንት ኀዳር 29 ቀን 2015 ጀምሮ በጊዜያዊነት መታገዱ ተገልጿል።

አገልግሎቱ የታገደው በከተማዋ ህገ ወጥነትን ለመከላከል እየተደረገ ያለውን ሒደት ውጤታማ ለማድረግ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አሳውቋል።

ለሁሉም ክፍለ ከተሞች እና ለሚመለከታቸው አካላትም የተላለፋው ውሳኔ ተፈጻሚ እንዲሆን ትዕዛዝ መሰጠቱንም የከተማ አስተዳደሩን ዋቢ አድርጎ ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
#tikvahethiopia
https://t.me/lawsocieties
👍2
#እንድታውቁት

ከተሻሻለው የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክን ለመቆጣጠር የወጣው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ

ከፖሊስ በተሽከርካሪ ላይ የደረሰውን የጉዳት አይነት የሚገልጽ የፅሁፍ ማስረጃ ሳይቀበሉ ጥገና የሚያከናውኑ ጋራዦች / የጋራዥ ባለቤቶች / በወንጀል ህግ የሚጠየቁት እንዳለ ሆኑ የ20 ሺህ ብር ቅጣት ይጣልባቸዋል።

አመታዊ የተሽከርካሪ ምርመራ ያላደረገ የተሽከርካሪ ባለንብረት 3,000 ብር ይቀጣል።

የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ሳይኖረው ተሽከርካሪ ያሽከረከረ ማንኛውም ሰው 5,000 ብር ይቀጣል።

  የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ሳይኖረው ተሽከርካሪ በማሽከርከር በንብረት ላይ ጉዳት ያደረሰ ማንኛውም ሰው 7000 ብር ይቀጣል።

ከባለቤትነት ወይም በይዞታው የተያዘውን ተሽከርካሪ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ለሌላው ሰው አሳልፎ የሰጠ ማንኛውም የተሸከርካሪ ባለንብረት 3,000 ብር ይቀጣል።

🚨የትራፊክ ግጭት ወይም ጉዳት አድርሶ በቦታው ላይ ያልቆመ ወይም ባደረሰው የትራፊክ ጉዳት የተጎዳውን እና ሕክምና የሚያስፈልገውን ሰው ወደ ህክምና በመውሰድ እንዲታከም ያላደረገ 👉 በወንጀል ህጉ መሰረት ይጠየቃል።

ወጣት አሽከርካሪዎች፣ ጀማሪ አሽከርካሪዎች ፣ ሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎች ፣ የንግድ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች እና አደገኛ ጭነት የጫኑ አሽከርካሪዎች የአልኮል መጠን በትንፋሽ በየትኛውም መጠን ከተገኘ 2,000 ብር ቅጣት ይጠብቃቸዋል።

የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ታግዶበት ሳለ ያሽከረከረ 3,000 ብር ቅጣት ይጣልበታል።

አልኮል መጠን በትንፋሽ ውስጥ ፦
🍻 0.24 እስከ 0.6 ሚሊግራም/ሊትር 1,500 ብር ያስቀጣል።
🍻 0.61 እስከ 0.8 ሚሊግራም /ሊትር 2,000 ብር ያስቀጣል።
🍻 0.81 እስከ 1.0 ሚሊግራም/ሊትር 2,000 ብር ያስቀጣል።
🍻 1.0 ሚሊግራም/ሊትር በላይ የተገኘበት 3,000 ብር ይቀጣል።

በተሽከርካሪ ላይ ተገቢ ያልሆነ አካል የጨመረ ወይም ከተፈቀደለት ወንበር ውጭ ተጨማሪ ወንበር ወይም መቀመጫ የጨመረ የተሽከርካሪ ባለንብረት 400 ብር ይቀጣል።

የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ሞተር እየሰራና በተሽከርካሪው ውስጥ መንገደኞች እያሉ ነዳጅ መሙላት 1,500 ብር ያስቅጣል።

ቴሌቪዥን ወይም ሌሎች ምስሎችን ተሽከርካሪ ውስጥ እየተመለከተ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

የደህንነት ቀበቶ ሳያስር ወይም ተሳፋሪዎች የደህንነት ቀበቶ ማሰራቸውን ሳያረጋግጥ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

የተንቀሳቃሽ ስልክ በእጁ ይዞ እያነጋገረ፣ ወይም መልዕክት እየጻፈ እየላከ ወይም እያነበበ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

ጫት ቅሞ ወይም እየቃመ ወይም አደንዛዥ ዕፅ ወስዶ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

የተሽከርካሪ የፊት ወይም የኃላ ሰሌዳ ሳይኖረው ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

ለአውቶብስ ብቻ ተብሎ በተለየ መንገድ ላይ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

ቀይ መብራት የጣሰ 1,500 ብር ይቀጣል።

የትራፊክ ተቆጣጣሪ ትዕዛዝ ያልፈጸመ፣ ወይም የተሳሳተ መረጃ የሰጠ ወይም እንዲቆም ሲታዘዝ በእንቢተኝነት ሳይቆም የሄደ 1,000 ብር ይቀጣል።

የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ኖሮት ሳይዝ ያሽከረከረ ወይም የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃዱን ሳያሳድስ ያሽከረከረ 1,000 ብር ይቀጣል።

ከተፈቀደው ፍጥናት በታች ያሽከረከረ ወይም የቀኙን ጠርዝ ሳይዝ በዝግታ ያሽከረከረ 1,000 ብር ይቀጣል።

ከመጠን በላይ ድምጽ እያሰማ ወይም የጆሮ ማዳመጫ እያዳመጠ ያሽከረከረ 1,000 ብር ይቀጣል።

መንገድ ላይ ያለን ውሃ በተሽከርካሪው አማካኝነት እግረኛ ላይ እንዲረጭ ያደረገ 1,000 ብር ይቀጣል።

(ተጨማሪ የጥፋት ዝርዝር እና ቅጣቶቹን ከላይ ያንብቡ)
#tikvahethiopia
🔴Attorney and Legal Consultant
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ

We are delighted to connect with you! You can easily reach us through the following platforms to stay informed and access our legal services:

Website & Social Media
Linktree:📱📱📱📱📱📱📱📱  

              https://linktr.ee/alehig

📱Facebook:
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

📱Telegram Channel:⭐️
https://t.me/AleHig

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com


Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595
📱Telegram:  ✉️ @MikiasMelak


Our Commitment
alehig.com
📊አለሕግ🔽
🔠🔠🔠    🔠🔠🔠
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት


We provide expert legal advice, support, and resources on various laws, proclamations, regulations, and directives to empower and guide you.

Feel free to reach out anytime‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍243👏1🙏1
#እንድታውቁት 📣❗️🆕

የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ባለስልጣን በሽያጭ የተሽከርካሪ ስም ዝውውር ለማድረግ ሊሟሉ እሚገባቸው ጉዳዮች ብሎ የሚከተሉትን ነጥቦች አስቀምጧል።

በዚህም በሽያጭ የተሽከርካሪ ስም ዝውውር ለማድረግ፦

1. በተሽከርካሪው ላይ የተላለፈ ማንኛውም ዓይነት እዳ እና እገዳ እንዲሁም ቀረጥ ያለበት ከሆነ የስምምነት ደብዳቤ መኖሩን ማረጋገጥ፣

2. ኮድ 01 እና ኮድ 03 ከሆነ ከገቢዎች የግብር ክሊራንስ መቅረቡን

3. የዘመኑን ዓመታዊ የቴክኒክ ምርመራ/ቦሎ፤ ያደረገ መሆኑን፤

4. የጸደቀ የውልና ማስረጃ ሰነድና የስም ዝውውር 2% የከፈለበት ማስረጃ መኖሩን፣

5. የንግድ ተሽከርካሪ ከሆነ አንዱ የግምት ውጤት ለሀገር ውስጥ ገቢ ባለስልጣን ይላካል፤ ሁለተኛውን የግምት ውጤት ሁለቱ ተዋዋዮች ውል መፈፀም የሚችሉ ለመሆኑ በሸኚ ደብዳቤ ለሠነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽ/ቤት የተላከበት ሰነድ፤

6. የቤት ተሸከርካሪ ከሆነ የግምት ውጤቱን በቀጥታ ሰሠነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ የተላከበት ሰነድ፤

7 . የገዢ ሁለት ፎቶ ግራፍ

8. የስም ዝውውርና የአገልግሎት ለውጥ የሚያደርግ ከሆነ ተሸከርካሪው በድጋሚ ለቴክኒክ ምርመራ ብቃት ማረጋገጫ ሲቀርብ እገልግሎቱ ይሰጣል ሲል አስቀምጧል።

በተጨማሪም ቢሮው በዚሁ መረጃው ላይ በሰጠው ማሳሰቢያ፦

1. የሚገዙት ተሽከርካሪ የሻንሲና ምተር ቁጥር ትክክለኛነት የማረጋገጥ፣

2. የተሚገዙት ተሽከርካሪ ሊብሬና ተሽከርካሪ ስለያዙ እና ዉክልና ስለተሰጦት ብቻ ሀጋዊ ተሽከርካሪ ማለት ስላልሆነ የሚገዙት ተሽከርካሪ በተመዘገበበት ቅ/ጽ/ቤት ትክክለኛነቱ መረጋገጥ አለበት ሲል ገልጿል።
#tikvahethmagazine
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp📱 #+251920666595
Telegram📱 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍172