አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.87K photos
25 videos
1.87K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
👍125
የእሽሙር ማህበር (JOINT VENTURE)


የእሽሙር ማህበር ምንነት

የእሸሙር ማህበር በአዲሱ የንግድ ህግ ከተካተቱ ሰባት የንግድ ማህበር አይነቶች አንዱ ሲሆን ማህበሩ ሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች በመካከላቸው በሚያደርጉት ስምምነት መሠረት የሚያቋቁሙት በሦስተኛ ወገኖች የማይታወቅና የሕግ ሰውነት የሌለው የንግድ ማህበር እንደሆነ በንግድ ህጉ አንቀፅ 234 ስር ተደንግጓል፡፡ ይሁንና የማህበሩ መኖር በሦስተኛ ወገኖች ከታወቀ ጊዜ አንስቶ ማህበሩ ከእነዚህ ወገኖች ጋር በሚኖረው ግንኙነት እንደ ህብረት ሽርክና ማህበር ይቆጠራል፡፡ የእሽሙር ማህበር ከሌሎች የንግድ ማህበራት ከሚለዩት ባህርያት የንግድ ማህበሮች የማስመዝገብ ሥርዓቶች በዚህ ማህበር ላይ ተፈጻሚ የማይሆን መሆኑ ነው፡፡

የእሽሙር ማህበር ባህርያት
የእሽሙር ማህበር መመስረት አንደኛ ሸሪክ ያለው ነገር ግን ሌላኛው ሸሪክ የሌለውን ጠንካራ ጎን ለመጋራት ያስችላል፡፡ ለምሳሌ እውቅና እና መልካም ስም ያለው የንግድ ስም (Brand Name ) ካለው የንግድ ማህበር ጋር ሽርክና የገባ ካንፓኒ ከመልካም ስሙ ተጠቃሚ ይሆናል ማለት ነው፡፡ ይህ ማለት ሁለት ሸሪኮች ያሏቸውን ጠንካራ ሀብት (የገንዘብ፣ የእውቀት፣ የቴክኖሎጂ እና የመሳሰሉትን) በማቀናጀት የተሻለ ውጤታማ የሆነ ማህበር ይመሰርታሉ፡፡ የሚከተሉት የእሽሙር ማኅበር ልዩ ባህሪያት ተብለው ሊወሰዱ ይችላሉ፡-

1. ህጋዊ ሰዉነት የሌለዉ ስለመሆኑ
የእሽሙር የሽርክና ማኅበር ህጋዊ ሰዉነት የለዉም ሲባል በሸሪኮች መካከል ያለዉ ግንኙነት ተራ ዉል ግንኙነት ነዉ ማለት ነዉ፡፡ በመሆኑም ሸሪኮቹ የአንድ ተቋም አባላት ሳይሆኑ ተራ ዉል ተዋዋይ ወገኖች ናቸዉ፡፡ ይልቁን ህጋዊ ሰዉነት ስለሌለዉ የንግዱ ስራ የሚሰራዉ በሸሪኮቹ ስም ነዉ፡፡ ስለሆነም እያንዳንዱ ሸሪክ ከሶስተኛ ወገኖች ጋር ሲዋዋል፣ ዉሉን ሲፈጽም ወዘተ… በራሱ ስም ነዉ፡፡ ይህም የሚሆነዉ የሽርክና ማኅበሩ ለሶስተኛ ወገኖች ስውር ስለሆነ ነዉ፡፡ የእሽሙር ማኅብር ህጋዊ ሰዉነት ስለሌለዉ ሸሪኮቹ የሚያዋጡት ገንዘብ እና ሀብት የማኅበሩ ሊሆን አይችልም፡፡ በመሆኑም በንግድ ህጉ ቁጥር 236/2 ስር እንደተደነገገው ተቃራኒ ስምምነት ከሌለ በስተቀር እያንዳንዱ ሸሪክ ያዋጣው ንብረት ባለቤት ነዉ፡፡

2. ለሶስተኛ ወገኖች የማይታወቅ መሆኑ
ለሶስተኛ ወገኖች አለመታወቁ (ድብቅ መሆኑ) ያለመመዝገቡ ውጤት ነዉ፡፡ የሕግ ሰዉነት ስለማይኖረዉ እንዲመዘገብ አይደረግም፡፡ ካልተመዘገበ ደግሞ ለህዝብ የሚታወቅበት መንገድ አይኖርም ማለት ነዉ፡፡ እዚህ ላይ የእሽሙር ሽርክና ማኅበር ድብቅነት የመመዝገብ ግዴታ ካለመኖሩ ብቻ የመነጨ ሳይሆን ይልቁንም በህጉ ታዉቆ እና ታስቦበት የተደነገገ ነዉ፡፡ አሰራሩም ያልተለመደ እና ግራ አጋቢ ቢመስልም በሌሎችም አገሮች የተለመደ እንጂ ኢትዮጵያ ዉስጥ ብቻ ያለ አይደለም፡፡

3. ቅንጅት መፍጠር (Creates Synergy)
የእሽሙር ማህበር በሁለት ወይም ከሁለት በላይ በሆኑ ማህበራት መካከል ሲመሰረት አንደኛው ሸሪክ የሌላኛውን ባህርይ ለመጠቀም ያስችለዋል (extract the qualities of each other)፡፡ እንዲሁም አንዳቸው ያንዳቸውን ጥቅም ለመጋራት ይችላሉ፡፡ በመሆኑም ከፍተኛ ጥንካሬ ያለው ቅንጅት መፍጠር ይችላሉ ማለት ነው( a joint venture to generate synergies between them for a greater good)፡፡ይህም በተዘዋዋሪ ትልቅ ካፒታልን ለመፍጠር የሚያስችላቸው ሲሆን ወጪያቸውንም እንዲቀንሱ ይረዳቸዋል፡፡

4. ስጋት/አደጋን መጋራት (Risk and Rewards can be Shared)
የእሽሙር ማህበር በአንድ ሀገር ውስጥ ባሉ ድርጅቶች ወይም በተለያዩ ሀገሮች ባሉ ድርጅቶች መካከል ሊደረግ የሚችል ሽርክና በመሆኑ በእነዚህ ሀገሮች ሊኖሩ የሚችሉ የባህል ልዩነቶች (diversifications in culture)፣ የቴክኖሊጂ፣ የመልከዓ መድር አቀማመጥ ጥቅምና ጉዳት (geographical advantage and disadvantage)፣ የተደራሽ ደንበኝ (target audience) ሁኔታዎች በማህበሩ ላይ ሊፈጥር የሚችለው ተፅዕኖ ትኩረት የሚሻ ነው፡፡ በመሆኑም በሸሪኮች መካከል የሚደረግ ስምምነት የአደጋ ስጋቶችን እና ጥቅሞች ለመጋራት ያስችላቸዋል፡፡

5. የተለየ ህግ አለመኖር (No Separate Laws)
የእሽሙር ማህበር የሕግ ሰውነት የሌለው የንግድ ማህበር በመሆኑ ማህበሩን የሚያስተዳድር የተለየ ሕግ አይኖርም፡፡ እንዲሁም ይህን ማህበር በተለየ ሁኔታ የሚያስተዳድር አካልም የለም(no separate governing body which regulates the activities of the joint venture.)፡፡

የእሽሙር ማህበር ጥቅሞች (advantages of a Joint Venture)
1. የምጣኔ ሀብትን ማሳደግ (Economies of Scale)
የእሽሙር ማህበር ሸሪኮች ወይም ድርጅቶች ሀብታቸውን ወይም ካፒታላቸውን በማጣመር ስለሚቋቋሙ ህብረት መመስረታቸው ውስን አቅማቸውን ለማሳደግ ይረዳቸዋል፡፡
2. አዲስ ገበያ መድረስ እና የአውታረ መረቦችን ስርጭት (Access to New Markets and Distribution Networks)
አንድ ድርጅት ከሌላ ድርጅት ጋር የእሽሙር ማህበር ስምምነት ሲያደርግ አንደኛው የሌላኛውን የገበያ እድል የመጠቀም እና የማሳደግ አጋጣሚን ይፈጥርለታል፡፡ ለምሳሌ አንድ የአሜሪካ ካንፓኒ ከህንድ ካንፓኒ ጋር የእሽሙር ማህበር ስምምነት ቢያደርግ በህንድ ውስጥ የሚኖርን ሰፊ፣ የተለያየ የመግዛት ፍላጎት እና አቀም ያለውን ገበያ የመድረስ ጥቅም ያገኛል ማለት ነው፡፡ በተመሳሳይ መልኩ የህንድ ካንፓኒም በአሜሪካ ውስጥ የሚገኝን ጥሩ የመክፈል አቅም ያለውን ገበያ መቀላቀል ይችላል ማለት ነው፡፡
3. ፈጠራን ማሳደግ (Innovation)
የእሽሙር ማህበር ምርቶችን እና አገልግሎቶችን ከቴክኖሎጂ አንጻር ለማሻሻል እድልን ይፈጥራል፡፡ በመሆኑም የቴክኖሎጂ መሻሻል እና የፈጠራ ስራዎች ማደግ የተሻሉ ምርቶችን እና አገልግሎቶችን ውጤታማ በሆነ ዋጋ( efficient cost) ለማቅረብ ያስችላል፡፡ አለም አቀፍ ድርጅቶች አዳዲስ ምርቶችን በቅናሽ ዋጋ በተሻለ ጥራት እንዲያቀርቡ ያደርጋል ማለት ነው፡፡
4. የማምረቻ ወጪን ማሳነስ (Low Cost of Production)
ሁለት እና ከሁለት በላይ ሸሪኮች ሲጣመሩ ውጤታማ በሆነ ዋጋ ምርትን ለደንበኞች ማድረስ አንዱ አላማቸው ነው፡፡ ይህም የሚሆነው የማምረቻ ዋጋን መቀነስ ሲቻል ነው፡፡ በመሆኑም የማምረቻ ዋጋን በጋራ በመቀነስ የተሻለ ምርት እና አገልግሎትን ለደንበኞች ያቀርባሉ፡፡

የእሽሙር ማህበር ጉዳት (Disadvantages of a Joint Venture)
1. ግልፅ ያለሆነ አላማ፡- ሸሪኮች በእሽሙር ማኅበር ሲጣመሩ አላማቸውን በጣም ግልፅ በሆነ ሁኔታ የማያስቀምጡበት አጋጣሚ በርካታ ነው፡፡ እንዲሁም የማህበሩ አላማ ለሁሉም የማህበሩ አባላት በአግባቡ ላይገለፅላቸው ይችላል፡፡
በመምሪያው ህ/ማ/ማ/ስ/ሂ crt to Amin
Alternative legal enlightenment (ALE)አለ Provided by Legal Experts.
አማራጭ የሕግ እውቀት፣
ነፃ የሕግ ምክርና ድጋፍ
#አለሕግ #Alehig
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Lawsocieties
👍212
ከሳሽ የሚቀርብን የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አስቀድመህ ገምተህ ከክሱ ጋር በመቃወሚያው ላይ የሚኖርህን ማስረጃ ማቅረብ ነበረብህ ሊባል አይገባም።

(ከየተጠቃለሉ የሰበር ውሳኔዎች ከቅጽ 1-23 እና ያልታተሙ ከ2006-2015 መጽሃፍ የተወሰደ) coming soon!
========%%%%%%%===============
ሰ/መ/ቁ.224265፡- ከሳሽ የሆነ ወገን ለክሱ ተከሳሽ የሚያቀርበውን የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አስቀድሞ ገምቶ ለዚህ የሚረዳው ማስረጃ ከክሱ ጋር አያይዞ እንዲያቀርብ አይጠበቅም። ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 245 ድንጋጌ መገንዘብ እንደሚቻለውም መቃወሚያ ሲቀርብ ፍርድ ቤቱ ሌላው ተከራካሪ ወገን በመቃወሚያው ላይ የሚያቀርበውን ክርክር ከሰማ በኋላ መቃወሚያውን ለመወሰን ተገቢ መስሎ የሚገምተው ማስረጃ እንዲቀርብለት ትዕዛዝ እንደሚሰጥና በመጨረሻም የቀረበው መቃወሚያ ከማስረጃው አንፃር መርምሮ ተገቢው ብይን መስጠት ይኖርበታል። ስለሆነም ከሳሽ ላቀረቡት ክስ ከተከሳሽ የቀረበውን የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ተመልክተው መቃወሚያውን ውድቅ ለማስደረግ የበኩላቸውን ክርክር በማቅረብ ክርክራቸውንም በማስረጃ ለማስደገፍ የሚያቀርቡትን ጥያቄ የማስረጃ አቀራረብ ስርዓቱን የተከተለ አይደለም በማለት ማስረጃውን ተቀብሎ ከቀረበው መቃወሚያና ከክሱ ይዘት አንጻር ሳይመረምር ብይን መስጠት ህጉን የተከተለ አይደለም። ህዳር 30 ቀን 2015 ዓ/ም
ከመላከ ጥላሁን ገጽ ተወሰደ
Alternative legal enlightenment (ALE)አለ Provided by Legal Experts.
አማራጭ የሕግ እውቀት፣
ነፃ የሕግ ምክርና ድጋፍ
#አለሕግ #Alehig
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Lawsocieties
👍12😁1
ድለላ በተግባር እና በሕግ ዓይን
******************

አለቃ ኪዳነወልድ ክፍሌ በ1948 ዓ.ም በታተመው ‘መጽሐፈ ሰዋሰው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ወሀዲስ’ መጽሐፋቸው ‘ደላላ’ የሚለውን ቃል ‘‘በቁሙ መደለል፣ ማታለል፣ መሸንገል” ይሉታል።

ዶ/ር ዕሌኒ ገብረ መድህን ደግሞ በ1991 ዓ.ም ስለኢትዮጵያ የእህል ደላሎች ሚና ባቀረቡት የጥናት ጽሁፍ ላይ ‘ደላላ’ የሚለው ቃል ምንጩ አረብኛ መሆኑንን እና በሐገራችን ብቻ ሳይሆን በናይጄሪያ ‘ዲላላ’ በህንድ ‘ዳላል’ የሚለው ተመሳሳይ ስያሜ እንዳለው ጠቅሰዋል።

ደላሎች ቤት ፤መሬት፣ መኪና፤ ማሻሻጥና ማከራየት ብቻ ሳይሆን ከምንመገበው እህል አንስቶ ሌሎች ቁሳቁሶችን፣ አሠሪና ሠራተኛ፣ የቤት ሠራተኛም ያገናኛሉ። በአምራቹ እና በጅምላ ወይም በችርቻሮ ሻጩ፣ በአጓጓዡ፣ በገዢና በሻጭ መሀከልም አይጠፉም። ሕገ ወጥ ደላሎች ከሕገ ወጥ ተግባራትና ከዋጋ መናር ጋር ብዙ ጊዜ አብረው ሲነሱም ይሰማል። በዛሬው የሕግ ጉዳይ ስለደላሎች ሕጋችን ምን እንደሚል እንመለከታለን።

ከተወሰኑት ልዩ ቁጥጥር ከሚደረግባቸው የመድህን ድለላን የመሰሉ የውስን ግብይቶች ደላላነት በስተቀር በአብዛኛው የተለመደው የድለላ ተግባር እንደሌሎች ሥራዎች የተለየ የትምህርት ማስረጃ፣ ልምድ፣ የመነሻ እርሾ (ካፒታል)፣ ከስነ ምግባር እና ከብቃት አንጻር ማረጋገጫ ፈተና ስለማይጠይቅ እዚያው አካባቢያቸው ካለ መረጃ ተነስተው ወደ ድለላው የሚገቡ ብዙዎች ናቸው።

በየአካባቢያችን እንደምናስተውለው ከገዢ እና ከሻጭ የተሻለ መረጃ ባይኖራቸውም የቤት ኪራይም ሆነ ሽያጭ ዋጋ ወይም የሌሎች አገልግሎቶች ዋጋ የሚወሰነው በገበያው ወይም በሻጩ ሳይሆን በአካባቢው ደላሎች ነው። ይህን የገበያውን ሚና ደላሎች የሚወስኑት የሚያገኙትን አበል ለመጨመር ስለሚመቻቸው እና ዋጋ በጨመረ ቁጥር በመቶኛ የሚያገኙት ክፍያ ስለሚጨምር ነው። በአሁን ጊዜ ደግሞ ማህበራዊ ሚዲያውን በመጠቀም ከሞባይል ስልክ እስከ ቤት እንደልላለን የሚሉ ደላሎችን እያየን ነው። እግር እስኪነቃ ከመዞር ለደላሎችም ለተጠቃሚውም ይህኛው የተሻለ አማራጭ ይመስላል።

በ2013 ዓ.ም ተሻሽሎ የወጣው የንግድ ሕግ አንቀጽ 54 ስለ ደላሎች እንዲህ ይላል:-

1. ደላሎች ውል ተዋዋዮችን (እንደ ሽያጭ፣ ኪራይ፣ ኢንሹራንስ፣ የማመላለሻ ውል የመሳሰሉትን) የሚዋዋሉ ሰዎችን ፈልገው የሚያገናኙ እና የሚያዋውሉ፣ ድለላን ራሱን የቻለ የሙያ ተግባራቸው አድርገው ጥቅም ለማግኘት የሚሠሩ ሰዎች ወይም ይህንኑ የድለላ ሥራ የሚሠሩ የንግድ ማህበራት ናቸው። ብዙውን ጊዜ እንደምንታዘበው ግን ደላሎች ፈልገውን አያውቁም፤ ገዥ ወይም ሻጭ ነው ፈልጎ የሚያገኛቸው።

2. ድለላ ጥቅም ለማግኘት የሚሰራ ራሱን የቻለ የሙያ ተግባር ሲሆን ደላላው ምንም ያገናኝ ምን በንግድ ሕጉ መሰረት ነጋዴ ነው፤ በመሆኑም የንግድ ፍቃድ ማውጣት አለበት።
የንግድ ፍቃድ ለማግኘት ደግሞ የድለላ ሙያ የሚጠይቀው ልምድ፣ የትምህርት ዝግጅት፣ አስፈላጊ ካፒታል፣ ቋሚ አድራሻ ያስፈልጋል። የንግድ ፍቃዱ በግል ንግድ ወይም በንግድ ማህበርነት የተመዘገበ መሆን አለበት። ስለዚህ እንደማንኛውም የንግድ ስራ ድለላ ከሚያስገኘው ገቢ ላይ ግብር ለማስገበር ያስገኘው ገቢና የሚከፍለው ግብር መታወቅ አለበት።
ተገቢው አካልም ትክክለኛውን አገልግሎት መስጠታቸውንና የግብር ግዴታቸውን መወጣታቸውን ለማረጋገጥ አሠራራቸውን ቁጥጥር ሊያደርግበት ይገባል። በተግባርስ? ሌላ ነው።ጥቂት የድለላ መስኮች ብቻ ናቸው በሕጋዊ መልኩ እየሠሩ ያሉት። የመድህን ዋስትና ደላሎች በብሔራዊ ባንክ ፈቃድ የሚሰጣቸው እና ቁጥጥር የሚደረግባቸው ናቸው።
ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶች ቡና፣ ሰሊጥ እና ነጭ ቦለቄ የሚያገበያዩ ደላሎች በኢትዮጵያ ምርት ገበያ ፍቃድ አውጥተው አባል በመሆን ቁጥጥር እየተደረገባቸው ይሠራሉ።
ለዚህ አይነቶቹ የድለላ ሥራዎች ከፍተኛው የአገልግሎት ክፍያ በሚመለከተው ሕግ ተደንግጓል። ከአምራቹ እስከ ነጋዴው ያለው ረጅም የደላላ ቅብብሎሽ ሰንሰለት በማጠሩና ተገቢ ቁጥጥር የሚደረግበት ውድድር በመሀላቸው በመኖሩ የምርት ገበያው ደላሎች ኮሚሽን የሚያስከፍሉት በሕግ በተገደበ የመቶኛ ስሌት ነው ።
የቁም ከብት ግብይት ላይም በግብይቱ የመሐል ደላሎችን የሚቆጣጠር ተመሳሳይ አዋጅ ወጥቷል። ከእነዚህ ውጪ በተለይ በየሰፈራችን ያሉት የቤት ኪራይ እና ሽያጭ እና ሌሎችም ደላሎች ግን የተወሰኑት ካልሆኑ በስተቀር የንግድ ፈቃድ ያላቸውና ግብር የሚገብሩ አይደሉም።
አብዛኞቹ ሌሎች የተለመዱ የድለላ ሥራዎች ላይ ግን ፈቃዱን ለማግኘት ሙያው የሚያስፈልገውን መስፈርት የሚጠይቃቸው አካል ባለመኖሩ ልምድና ትምህርቱ እንዲሁም ስነ ምግባሩ የሌላቸው ደላሎችም ሲደልሉ ይታያል። በዚህም የተነሳ በተመጣጣኝ ዋጋ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ አገልግሎታቸውን እንዳናገኝ ሆነናል።

3. የደላላ አበልን በተመለከተ የንግድ ሕጋችን "በደላላው አስማሚነት ውሉን ካስጨረሰ ወይም ካዋዋለ በኋላ የውሉ ግዴታ ቢፈፀምም ባይፈፀምም ደላላው አበሉ ይከፈለዋል" ይላል። በተግባር ግን የሚታየው ደላላው ዋጋ ይናገራል ቤቱን ወይም እቃውን ያሳያል ተከራክረው የሚያስማማቸው ዋጋ ላይ የሚደርሱት ግን ገዥና ሻጭ ወይም አከራይና ተከራይ ናቸው።

4. ሕጉ እንደሚለው በልማድ የታወቀ ካልሆነ ወይም ሌላ ስምምነት ከሌለ ለደላላው አበል የሚከፍለው አገልግሎቱን የጠየቀው ሰው ብቻ ነው። በተግባር እንደምንታዘበው ግን ለአንድ አገልግሎት ደላላው ወይም ደላሎቹ ከሁለቱም ተዋዋዮች አበል ይቀበላሉ። ‘የሚከራይ ቤት አለኝ’ ብሎ አከራዩ ለደላላው ይናገራል። ደላላው ይህን መረጃ ይዞ ተከራይ አያፈላልግም ምን በወጣው! ተከራይ ራሱ ነው ‘ቤት እፈልጋለሁ’ ብሎ የሚመጣው። ሕጉ እንደሚለው ተዋዋዮችን ደላላው ስለማያፈላልግና አገልግሎቱን የሚጠይቁት ተዋዋዮች ስለሆኑ ደላላው ከሁለቱም አበል ይቀበላል።በተጨማሪም በአንድ ግብይት ውስጥ ከሁለቱም ተዋዋዮች በኩል ብዙ ደላሎች ስለሚኖሩ የግብይቱን ዋጋ እና የአበሉን መጠን በማናገር ገዢ ወይም ተከራይ ላይ ጫና ያሳድራል።

5. የአበሉ መጠን በቅድሚያ በስምምነት መወሰን አለበት። ተዋዋዩ እና ደላላው የደለለበትን አበል ይህን ያህል እከፍላለው ብለው ቅድሚያ መስማማት አለባቸው ። በተግባር ግን ይህ ስምምነት በቅድሚያ ስለማይደረግ አብዛኛውን ጊዜ ደላላው ኪራይ ከሆነ የመጀመሪያውን ክፍያ 10 በመቶ ሽያጭ ከሆነ 2 በመቶ ይቀበላል።

6. በንግድ ሕጉ መሰረት የድለላው አበል ላይ በቅድሚያ ስምምነት ካልተደረገ ሕጉ "የደላላው አበል በልማድ መሰረት ይቆረጣል" ይላል። በዚህ ምክንያት ይመስላል በአብዛኛው ደላሎች ቀድመው የአበላቸውን መጠን የማይጠይቁት። አበላቸውም በመቶኛ እንጂ በቁርጥ እንዲሆንም አይፈልጉም። ስለዚህ ለአንድ ቀን ቤቱን አሳይቶ ዋጋ ለተናገረበት ከላይ የጠቀስኩትን የልማድ ዋጋ የመቶኛ ስሌት በሁለቱም ተዋዋዮች በኩል ያሉት ደላሎች ያስከፍላሉ። ይህ የልማድ ዋጋ ለደላሎች ቢመችም ለተዋዋዮች እና ለሻጮች ግን በአብዛኛው ፍትሐዊ ወይም ከተሰጠው አገልግሎት ጋር ተመጣጣኝ አይደለም።

7. ተዋዋዮ እና ደላላው የአበሉን መጠን ቢስማሙም እንኳን የተስማሙበት አበል ከባድ መስሎ ከታየው ወይም ደላላው ከሰጠው አገልግሎት ጋር ተመጣጣኝ አለመሆኑ ሲታየው የንግድ ሕጋችን በአንቀፅ 57 (3) ላይ ለፍ/ቤት የአበሉን መጠን የመቀነስ ስልጣን ሰጥቷል ። በተግባር ግን ደላሎች በዚህም በዚያም ብለው ተመጣጣኝ ሆነ አልሆነ የጠየቁትን ያስከፍላሉ።
👍6
8. የንግድ ሕጉ አንቀፅ 57(4) ደላላው ኃላፊነት አለበት ይላል። ደላላው ለደንበኛው ወይም አገልግሎቱን ለጠየቀው ወገን ያሉበትን ግዴታዎች ተላልፎ የደንበኛውን ጥቅም በሚጎዳ አኳኀን ለሌላ 3ኛ ወገን ጥቅም የሠራ እንደሆነ ወይም ደንበኛው ሳያውቅ ከ3ኛ ወገን ክፍያ ከተቀበለ አበል የማግኘት መብቱ ቀሪ ይሆናል። በተግባር ግን ብዙዎች ደላላ ቢጎዳቸውም ከመበሳጨት በስተቀር በፍርድ ቤት ከሰው በኃላፊነት ካሳ ሲጠይቁ አይታይም።

ለማንኛውም ደላላ ስትጠቀሙ በተለይ አበሉን በተመለከተ በቁርጥ በቅድሚያ ተስማሙ። በመቶኛ ከሆነ አበላቸውን ለመጨመር ዋጋውን ከፍ ሊያደርጉት ስለሚችሉ በቁርጥ አድርጉት። አበሉን ተስማምታችሁም ቢሆን ከሰጡት አገልግሎት ጋር የክፍያው መጠን ከተጋነነ ይገባል ከምትሉት በላይ አልከፍልም በሉ። ጉዳዩ ፍ/ቤት ከደረሰ ሊቀነስላችሁ ይችላል። ቢቻል የንግድ ፍቃድ ባላቸው ደላሎች ተጠቀሙ። ደላላው የሚጠራውን ዋጋ ከማመናችሁ በፊትም በተለያየ ዘዴ የገበያውን ዋጋም ለማጣራት ሞክሩ።
EBC
Alternative legal enlightenment (ALE)አለ Provided by Legal Experts.
አማራጭ የሕግ እውቀት፣
ነፃ የሕግ ምክርና ድጋፍ
#አለሕግ #Alehig
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Lawsocieties
👍94🔥1
👍31
ሰ/መ/ቁ 235844 የማይንቀሳቀስ ንብረት በባልና ሚስት ስም ተመዝግቦ የሚገኝ ቢሆንም ከጋብቻ በፊት መፈራቱ ወይም መገዛቱን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ካለ የአንደኛው ተጋቢ የግል ንብረት ነው።
Abrham yohanes
👍23😁1
የሆቴሎች የአለባበስ ሥርዓት ረቂቅ ደንብ ይፋ ሆነ
*
(ኢ ፕ ድ)

በሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ የሚሰሩ ባለሙያዎች የሚደርስባቸውን አካላዊና ስነ ልቦናዊ ጫናን ያስቀራል የተባለለት ረቂቅ ደንብ ይፋ ተደረገ፡፡

አዲስ አበባ ባህል፣ ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ በሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ባለሙያዎች የደንብ ልብስ አለባበስ፣ የገፅታና የውበት አጠባበቅ እንዲሁም የጌጣጌጥ አጠቃቀም ሥነ-ሥርዓት ያወጣውን የደንብ ረቂቅ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አድርጓል።

በቢሮው የቱሪዝም ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኃፍታይ ገ/እግዚአብሔር በወቅቱ እንደገለጹት፤ በባለሙያዎች የሚደርስን ጥቃት የሚያስቀር የአለባበስ ሥርዓት ረቂቅ ደንብ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ የደንብ ረቂቁ ዓለም አቀፋዊ ተሞክሮዎችም የተካተቱበት ነው፡፡

በሂደቱም የቢሮው የቱሪዝም ባለሙያዎች፣ የኢትዮጵያ መስተንግዶ ማህበር፣ የአዲስ አበባ ሆቴሎችና ቱሪዝም ባለሙያዎች ማህበር፣ የቱሪዝም ማሰልጠኛ ተቋም እና የአዲስ አበባ ሆቴሎች ሥራ አስኪያጅ ማህበር እንደተሳተፉበት ገልጸዋል።

እንደ አቶ ሃፍታይ ገለጻ፤ ደንቡ በአዲስ አበባ ያሉ ሆቴሎችና መሰል ተቋማት ወጥ የሆነ ሥርዓት እንዲኖራቸው....

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=115367
Alternative legal enlightenment (ALE)አለ Provided by Legal Experts.
አማራጭ የሕግ እውቀት፣
ነፃ የሕግ ምክርና ድጋፍ
#አለሕግ #Alehig
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Lawsocieties
👍5👏2😱1
Alternative legal enlightenment (ALE)አለ Provided by Legal Experts.
አማራጭ የሕግ እውቀት፣
ነፃ የሕግ ምክርና ድጋፍ
#አለሕግ #Alehig
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Lawsocieties
👍4
Alternative legal enlightenment (ALE)አለ Provided by Legal Experts.
አማራጭ የሕግ እውቀት፣
ነፃ የሕግ ምክርና ድጋፍ
#አለሕግ #Alehig
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Lawsocieties
6👍5
Exit Exam
👍5
የፌዴራል_የመጀመሪያ_ደረጃ_ፍርድ_ቤት_የንግድ_ችሎቶች_ሥርዓተ_ችሎት.pdf
3.7 MB
የንግድ ችሎቶች ሥርዓተ ችሎት

Alternative legal enlightenment (ALE)አለ Provided by Legal Experts.
አማራጭ የሕግ እውቀት፣
ነፃ የሕግ ምክርና ድጋፍ
#አለሕግ #Alehig
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Lawsocieties
👍1
Directives_for_Licensing_and_Supervision_of_CMSPs_in_Ethiopia_Public.pdf
1.1 MB
የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን Ethiopian Capital Market Authority

Capital Market Service Providers Licensing and Supervision Directive

This draft is furnished to seek public comments as per the requirements of the Federal Administrative Procedure Proclamation No. 1183/2020.

All comments on the draft should be forwarded to ecmadirective@gmail.com within 15 working days or by March 6, 2023.


DRAFT FOR PUBLIC CONSULTATION

Alternative legal enlightenment (ALE)አለ Provided by Legal Experts.
አማራጭ የሕግ እውቀት፣
ነፃ የሕግ ምክርና ድጋፍ
#አለሕግ #Alehig
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Lawsocieties
👍6
#የዳኝነት_ሳይከፈል_በነፃ_ስለሚቀርብ_ክስ

ማንኛውም የፍትሐብሔር ክስ ሲከፈት በፍርድ ቤት ለሚሰጠው የዳኝነት አገልግሎት የዳኝነት እንዲከፈል ይጠበቃል፡፡ ክስ ለማቅረብ የፈለገ ወገን ለሚያገኘው የዳኝነት አገልግሎት መክፈል የሚገባውን የዳኝነት ገንዘብ ለመክፈል የሚያስችል የገንዘብ አቅም የሌለው ከሆነ ለግዜው የዳኝነት መክፈል ባለመቻሉ ብቻ መብቶቹን እንዳያጣ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርአት ህጉ መፍትሄ አስቀምጧል፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ የዳኝነት ሳይከፈል በነፃ ስለሚቀርብ ክስ ምንነት እና ስለሚቀርብበት ሥነ ሥርዓት እንመለከታለን፡፡
የዳኝነት ሳይከፈል በነፃ የሚቀርብ ክስ ምንነት
በ1958 ዓ.ም በወጣው የፍትሐብሔር ሥነ ሥርአት ህግ ቁጥር 467 መሰረት የዳኝነት ሳይከፈል በነፃ የሚቀርብ ክስ ማለት ገንዘብ የሌለው እና ገንዘብ ለማግኘት የማይችል ማንኛውም ደሀ ሰው የዳኝነት ሳይከፍል በነፃ ፋይል ክፍቶ ክስ የሚያቀርብበት ሂደት ነው፡፡
የዳኝነት ሳይከፈል በነፃ የሚቀርብ ክስ ሥነ-ሥርዓት
በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር 467 መሰረት ዳኝነት መክፈል የማይችል ደሀ ሰው የዳኝነት ገንዘብ በሙሉ ወይም በከፊል ሳይከፍል የነፃ ፋይል ማስከፈት የሚችለው ከክሱ አቤቱታ ጋር የነፃ ዳኝነት ማመልከቻ በቃለ መሀላ አስግፎ ዋናውን ጉዳይ ለሚያየው ፍርድ ቤት ሲያቀርብ ነው (ቁ.468)፡፡ ፍርድ ቤቱም ማመልከቻውን ተመልክቶ ስለአመልካች የሀብት ሁኔታ እና ስለማመልከቻው ተገቢነት አስፈላጊ ማስረጃ ለማግኘት አመልካችን ወይም ወኪሉን አስቀርቦ ሊጠይቀው ይችላል፡፡
ፍርድ ቤቱ የቀረበው ማመልከቻ ሲመረምር የሚነቀፍበት ምክንያት ካላገኘ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር 471 መሰረት አመልካች ድሀ ስለመሆኑ እንዲያስረዳ እና በአንፃሩም አመልካቹ ሀብት አለው የሚሉ ሰዎች እንዳሉ እንዲያስረዱ ቀጠሮ በመስጠት ከቀጠሮ አስር ቀን በፊት ለባለጋራው ማስታወቂ እንዲደርሰው ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡ ማስረጃው ተሰምቶ ከተመረመረ በኋላ ፍርድ ቤቱ ማመልከቻውን ሊቀበል ወይም ውድቅ ሊያደርግ ይችላል፡፡ ማመልከቻው ተቀባይነት ካገኘ አመልካቹ ዳኝነት ሳይከፍል ያቀረበው ክስ ዳኝነት እንደተከፈለበት እንደማንኛውም ክስ ተቆጥሮ በመደበኛ ሥነ ሥርአት ይመራል፡፡
ይህም ውሳኔ በነፃ ዳኝነት የቀረበው ክስ ቀጥሎ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ የሚያገለግል እና ማስረጃነቱ የሚቀጥል ሲሆን ይህ ማስረጃ ግን ለሌሎች ክርክሮች እንደ ማስረጃ ሊሆን አይችልም፡፡ በይግባኝ ደረጃ የሚሄድ ክርክር አመልካች ይግባኝ ባይ ከሆነ በነፃ ይግባኝ መዝገብ እንደ አዲስ ይከፈትልኝ እስካላለ ድረስ በነፃ እንዲከራከር በስር ፍርድ ቤት የተሰጠው የድህነት ማስረጃ አያገለግለውም፡፡ ነገር ግን በይግባኝ ክርክሩ መልስ ሰጪ ከሆነ የድህነት ማስረጃው ያገለግለዋል (ቁ.474)፡፡
በሌላ በኩል ዳኝነት ሳይከፈል በነፃ እንዲታይ የሚቀርብ ማመልከቻ ተቀባይነት ላያገኝ ይችላል፡፡ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር 470 መሰረት ማመልከቻው ተቀባይነትን ላያገኝ የሚችለው፡-
 አመልካቹ ድሀ አለመሆኑ ከተረጋገጠ፣
 በነፃ ለመክሰስ ያቀረበው ነገር የማያስከስስ የሆነ እንደሆነ፣
 ክስ ከማቅረቡ ከሁለት ወር በፊት የነበረውን ንብረት ለሌላ ሰው አስተላልፎ እንደሆነ ወይም በማጭበርበር መንገድ ንብረቱን አዛውሮ ከሆነ ወይም ዳኝነት ከመክፈል ለመዳን ዘዴ ፈጥሮ ከሆነ፣
 ክርክር በሚያቀርብበት ንብረት ወይም መብት ውስጥ ሌላ ሶስተኛ ሰው እንዲጠቀም ወይም ማናቸውንም መብት እንዲያገኝ ተዋውሎ ወይም ተስማምቶ እንደሆነ ነው፡፡
የዳኝነት ሳይከፍል ልከራከር የሚለው ማመልከቻ ውድቅ ከተደረገ በዚሁ ጉዳይ ድጋሚ መቅረብ የማይችል ሲሆን ክስ ማቅረብ የሚችለው የዳኝነት ክፍያ እንዲሁም የነፃ ዳኝነት እንዲፈቀድለት ባቀረበ ጊዜ ባለጋራው ለመቃወም ያወጣውን ወጪና ኪሳራ ከፍሎ እንደሆነ ከፍሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር 477 መረዳት ይቻላል፡፡
በነፃ ለመከራከር የተፈቀደለት ሰው በነፃ የመከራከር መብቱን ሊያጣ የሚችልባቸው ሁኔታዎች
በፍሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር 475 መሰረት የዳኝነት ሳይከፈል በነፃ መከራከር ማስረጃ ዋጋ ሊያጣ የሚችል ሲሆን ይኸውም
 ክርክሩ እንዲሰማ በተቀጠረው ቀነ ቀጠሮ የዳኝነት ሳይከፈል በነፃ ልከራከር ባይ ሳይቀርብ የቀረ እንደሆነ ወይም የማወክ፣ የማስቸገርና የተንኮለኛነት ጠባይ ያሳየ እንደሆነ፣
 ክርክሩ በሚቀጥልበት ጊዜ ሀብት ያለው መሆኑ የተገለፀበት እንደሆነና በነጻ ዳኝነት መጠቀም ወይም በዚህ መቀጠል የማይገባው መሆኑን ፍርድ ቤቱ የተረዳ እንደሆነ፤
 ለክርክሩ መነሻ በሆነው ሀብት ላይ ሌላ ሶስተኛ ወገን ጥቅም እንዲያገኝ ስምምነት አድርጎ የተገኘ እንደሆነ ነው፡፡
ሀብት ያለው መሆኑ ተገልፆበት ወይም ለክርክሩ መነሻ በሆነው ሀብት ላይ ሌላ ሶስተኛ ወገን ጥቅም እንዲያገኝ ስምምነት አድርጎ በመገኘቱ በነፃ መከራከር መብቱ የተሰረዘበት ሰው ተገቢውን የዳኝነትና ማናቸውንም ለፍርድ ቤት የሚከፈለውን ገንዘብ እንዲከፍል ይታዘዛል፡፡
በነፃ እንዲከራከር የተፈቀደለት ድሀ በክርክሩ የመርታት ወይም ሀብት የማግኘት ውጤት
በነፃ እንዲከራከር የተፈቀደለት ሰው የዳኝነት ሳይከፍል የሚከራከርበትን ጉዳይ ራሱ በፍርድ አፈፃፀም የረታ እንደሆነ ፍርድ አስፈፃሚው በፍሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር 476 መሰረት ለመንግስት የሚገባውን የዳኝነት ገንዘብና ማናቸውንም ወጪ ከረታው ሀብት ላይ ተቀናሽ በማድረግ ገቢ ካደረገ በኋላ ቀሪው ሀብት ረቺው እንደ ፍርዱ እንዲረከብ ማድረግ እንዳለበት ተደንግጎአል፡፡ ሌሎች በነፃ ለመዳኘት የሚቀርቡ ማመልከቻዎችና ይህንን ለመመርመር የሚያስፈልጉ ማናቸውም ወጭዎች ሁሉ ለዳኝነት ከሚከፈል ገንዘብ ጋር የሚታሰቡ እንደሆኑ ከፍሐብሔር ሥነ ሥርአት ህግ ቁጥር 479 መረዳት ይቻላል፡፡
በተጨማሪም የዳኝነት ሳይከፍል የሚከራከር ወገን ማስረጃው በተሰጠው በአስር አመት ግዜ ውስጥ ወይም ክርክሩ በሚቀጥልበት ጊዜ ሀብት ካገኘ ይህንኑ አስታውቆ ዳኝነቱን መክፈል እንዳለበት በፍሐብሔር ሥነ ሥርአት ህግ ቁጥር 478 ስር ተደንግጎ ይገኛል፡፡ ገንዘብ አግኝቶ እያለ ይህንን የማያስታወቅ ወይም የመክፈል ግዴታውን ባይወጣ በአታላይነት ወንጀል እንደሚጠየቅ በድንጋጌው ተመልክቷል፡፡
ዳኝነት ሳይከፈልበት በነፃ የሚቀርብ ክስ የዳኝነት ለመክፈል አቅም ያጡ ሰዎች ገንዘብ በማጣት መብቶቻቸውን እንዳያጡ ለማድረግ በህጉ የተቀመጠ መፍትሄ ሲሆን በዚሁ መልኩ የተከራከረ ሰው ሀብት ሲያገኝ በአግባቡ አስታውቆ የዳኝነት መክፈል ይጠበቅበታል፡፡ ስለሆነም ገንዘብ ሲያገኙ መክፍል እንደተጠበቀ ሆኖ የዳኝነት ለመክፈል አቅም የሌላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ገንዘብ ማጣታቸው ዳኝነት እንዳያገኙ እንደማይከለክላቸው አውቀው ተገቢውን ማስረጃ በማቅረብ በህጉ በተቀመጠው መልኩ መስተናገድ ይችላሉ፡፡
መረጃው፡- ከፍትሕ ሚኒስቴር የተገኘ ነው!
Federal Justice and Law Institute
Alternative legal enlightenment (ALE)አለ Provided by Legal Experts.
አማራጭ የሕግ እውቀት፣
ነፃ የሕግ ምክርና ድጋፍ
#አለሕግ #Alehig
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Lawsocieties
👍111
#የዳኝነት_ሳይከፈል_በነፃ_ስለሚቀርብ_ክስ

ማንኛውም የፍትሐብሔር ክስ ሲከፈት በፍርድ ቤት ለሚሰጠው የዳኝነት አገልግሎት የዳኝነት እንዲከፈል ይጠበቃል፡፡ ክስ ለማቅረብ የፈለገ ወገን ለሚያገኘው የዳኝነት አገልግሎት መክፈል የሚገባውን የዳኝነት ገንዘብ ለመክፈል የሚያስችል የገንዘብ አቅም የሌለው ከሆነ ለግዜው የዳኝነት መክፈል ባለመቻሉ ብቻ መብቶቹን እንዳያጣ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርአት ህጉ መፍትሄ አስቀምጧል፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ የዳኝነት ሳይከፈል በነፃ ስለሚቀርብ ክስ ምንነት እና ስለሚቀርብበት ሥነ ሥርዓት እንመለከታለን፡፡
የዳኝነት ሳይከፈል በነፃ የሚቀርብ ክስ ምንነት
በ1958 ዓ.ም በወጣው የፍትሐብሔር ሥነ ሥርአት ህግ ቁጥር 467 መሰረት የዳኝነት ሳይከፈል በነፃ የሚቀርብ ክስ ማለት ገንዘብ የሌለው እና ገንዘብ ለማግኘት የማይችል ማንኛውም ደሀ ሰው የዳኝነት ሳይከፍል በነፃ ፋይል ክፍቶ ክስ የሚያቀርብበት ሂደት ነው፡፡
የዳኝነት ሳይከፈል በነፃ የሚቀርብ ክስ ሥነ-ሥርዓት
በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር 467 መሰረት ዳኝነት መክፈል የማይችል ደሀ ሰው የዳኝነት ገንዘብ በሙሉ ወይም በከፊል ሳይከፍል የነፃ ፋይል ማስከፈት የሚችለው ከክሱ አቤቱታ ጋር የነፃ ዳኝነት ማመልከቻ በቃለ መሀላ አስግፎ ዋናውን ጉዳይ ለሚያየው ፍርድ ቤት ሲያቀርብ ነው (ቁ.468)፡፡ ፍርድ ቤቱም ማመልከቻውን ተመልክቶ ስለአመልካች የሀብት ሁኔታ እና ስለማመልከቻው ተገቢነት አስፈላጊ ማስረጃ ለማግኘት አመልካችን ወይም ወኪሉን አስቀርቦ ሊጠይቀው ይችላል፡፡
ፍርድ ቤቱ የቀረበው ማመልከቻ ሲመረምር የሚነቀፍበት ምክንያት ካላገኘ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር 471 መሰረት አመልካች ድሀ ስለመሆኑ እንዲያስረዳ እና በአንፃሩም አመልካቹ ሀብት አለው የሚሉ ሰዎች እንዳሉ እንዲያስረዱ ቀጠሮ በመስጠት ከቀጠሮ አስር ቀን በፊት ለባለጋራው ማስታወቂ እንዲደርሰው ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡ ማስረጃው ተሰምቶ ከተመረመረ በኋላ ፍርድ ቤቱ ማመልከቻውን ሊቀበል ወይም ውድቅ ሊያደርግ ይችላል፡፡ ማመልከቻው ተቀባይነት ካገኘ አመልካቹ ዳኝነት ሳይከፍል ያቀረበው ክስ ዳኝነት እንደተከፈለበት እንደማንኛውም ክስ ተቆጥሮ በመደበኛ ሥነ ሥርአት ይመራል፡፡
ይህም ውሳኔ በነፃ ዳኝነት የቀረበው ክስ ቀጥሎ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ የሚያገለግል እና ማስረጃነቱ የሚቀጥል ሲሆን ይህ ማስረጃ ግን ለሌሎች ክርክሮች እንደ ማስረጃ ሊሆን አይችልም፡፡ በይግባኝ ደረጃ የሚሄድ ክርክር አመልካች ይግባኝ ባይ ከሆነ በነፃ ይግባኝ መዝገብ እንደ አዲስ ይከፈትልኝ እስካላለ ድረስ በነፃ እንዲከራከር በስር ፍርድ ቤት የተሰጠው የድህነት ማስረጃ አያገለግለውም፡፡ ነገር ግን በይግባኝ ክርክሩ መልስ ሰጪ ከሆነ የድህነት ማስረጃው ያገለግለዋል (ቁ.474)፡፡
በሌላ በኩል ዳኝነት ሳይከፈል በነፃ እንዲታይ የሚቀርብ ማመልከቻ ተቀባይነት ላያገኝ ይችላል፡፡ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር 470 መሰረት ማመልከቻው ተቀባይነትን ላያገኝ የሚችለው፡-
 አመልካቹ ድሀ አለመሆኑ ከተረጋገጠ፣
 በነፃ ለመክሰስ ያቀረበው ነገር የማያስከስስ የሆነ እንደሆነ፣
 ክስ ከማቅረቡ ከሁለት ወር በፊት የነበረውን ንብረት ለሌላ ሰው አስተላልፎ እንደሆነ ወይም በማጭበርበር መንገድ ንብረቱን አዛውሮ ከሆነ ወይም ዳኝነት ከመክፈል ለመዳን ዘዴ ፈጥሮ ከሆነ፣
 ክርክር በሚያቀርብበት ንብረት ወይም መብት ውስጥ ሌላ ሶስተኛ ሰው እንዲጠቀም ወይም ማናቸውንም መብት እንዲያገኝ ተዋውሎ ወይም ተስማምቶ እንደሆነ ነው፡፡
የዳኝነት ሳይከፍል ልከራከር የሚለው ማመልከቻ ውድቅ ከተደረገ በዚሁ ጉዳይ ድጋሚ መቅረብ የማይችል ሲሆን ክስ ማቅረብ የሚችለው የዳኝነት ክፍያ እንዲሁም የነፃ ዳኝነት እንዲፈቀድለት ባቀረበ ጊዜ ባለጋራው ለመቃወም ያወጣውን ወጪና ኪሳራ ከፍሎ እንደሆነ ከፍሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር 477 መረዳት ይቻላል፡፡
በነፃ ለመከራከር የተፈቀደለት ሰው በነፃ የመከራከር መብቱን ሊያጣ የሚችልባቸው ሁኔታዎች
በፍሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር 475 መሰረት የዳኝነት ሳይከፈል በነፃ መከራከር ማስረጃ ዋጋ ሊያጣ የሚችል ሲሆን ይኸውም
 ክርክሩ እንዲሰማ በተቀጠረው ቀነ ቀጠሮ የዳኝነት ሳይከፈል በነፃ ልከራከር ባይ ሳይቀርብ የቀረ እንደሆነ ወይም የማወክ፣ የማስቸገርና የተንኮለኛነት ጠባይ ያሳየ እንደሆነ፣
 ክርክሩ በሚቀጥልበት ጊዜ ሀብት ያለው መሆኑ የተገለፀበት እንደሆነና በነጻ ዳኝነት መጠቀም ወይም በዚህ መቀጠል የማይገባው መሆኑን ፍርድ ቤቱ የተረዳ እንደሆነ፤
 ለክርክሩ መነሻ በሆነው ሀብት ላይ ሌላ ሶስተኛ ወገን ጥቅም እንዲያገኝ ስምምነት አድርጎ የተገኘ እንደሆነ ነው፡፡
ሀብት ያለው መሆኑ ተገልፆበት ወይም ለክርክሩ መነሻ በሆነው ሀብት ላይ ሌላ ሶስተኛ ወገን ጥቅም እንዲያገኝ ስምምነት አድርጎ በመገኘቱ በነፃ መከራከር መብቱ የተሰረዘበት ሰው ተገቢውን የዳኝነትና ማናቸውንም ለፍርድ ቤት የሚከፈለውን ገንዘብ እንዲከፍል ይታዘዛል፡፡
በነፃ እንዲከራከር የተፈቀደለት ድሀ በክርክሩ የመርታት ወይም ሀብት የማግኘት ውጤት
በነፃ እንዲከራከር የተፈቀደለት ሰው የዳኝነት ሳይከፍል የሚከራከርበትን ጉዳይ ራሱ በፍርድ አፈፃፀም የረታ እንደሆነ ፍርድ አስፈፃሚው በፍሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር 476 መሰረት ለመንግስት የሚገባውን የዳኝነት ገንዘብና ማናቸውንም ወጪ ከረታው ሀብት ላይ ተቀናሽ በማድረግ ገቢ ካደረገ በኋላ ቀሪው ሀብት ረቺው እንደ ፍርዱ እንዲረከብ ማድረግ እንዳለበት ተደንግጎአል፡፡ ሌሎች በነፃ ለመዳኘት የሚቀርቡ ማመልከቻዎችና ይህንን ለመመርመር የሚያስፈልጉ ማናቸውም ወጭዎች ሁሉ ለዳኝነት ከሚከፈል ገንዘብ ጋር የሚታሰቡ እንደሆኑ ከፍሐብሔር ሥነ ሥርአት ህግ ቁጥር 479 መረዳት ይቻላል፡፡
በተጨማሪም የዳኝነት ሳይከፍል የሚከራከር ወገን ማስረጃው በተሰጠው በአስር አመት ግዜ ውስጥ ወይም ክርክሩ በሚቀጥልበት ጊዜ ሀብት ካገኘ ይህንኑ አስታውቆ ዳኝነቱን መክፈል እንዳለበት በፍሐብሔር ሥነ ሥርአት ህግ ቁጥር 478 ስር ተደንግጎ ይገኛል፡፡ ገንዘብ አግኝቶ እያለ ይህንን የማያስታወቅ ወይም የመክፈል ግዴታውን ባይወጣ በአታላይነት ወንጀል እንደሚጠየቅ በድንጋጌው ተመልክቷል፡፡
ዳኝነት ሳይከፈልበት በነፃ የሚቀርብ ክስ የዳኝነት ለመክፈል አቅም ያጡ ሰዎች ገንዘብ በማጣት መብቶቻቸውን እንዳያጡ ለማድረግ በህጉ የተቀመጠ መፍትሄ ሲሆን በዚሁ መልኩ የተከራከረ ሰው ሀብት ሲያገኝ በአግባቡ አስታውቆ የዳኝነት መክፈል ይጠበቅበታል፡፡ ስለሆነም ገንዘብ ሲያገኙ መክፍል እንደተጠበቀ ሆኖ የዳኝነት ለመክፈል አቅም የሌላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ገንዘብ ማጣታቸው ዳኝነት እንዳያገኙ እንደማይከለክላቸው አውቀው ተገቢውን ማስረጃ በማቅረብ በህጉ በተቀመጠው መልኩ መስተናገድ ይችላሉ፡፡
መረጃው፡- ከፍትሕ ሚኒስቴር የተገኘ ነው!
Federal Justice and Law Institute
Alternative legal enlightenment (ALE)አለ Provided by Legal Experts.
አማራጭ የሕግ እውቀት፣
ነፃ የሕግ ምክርና ድጋፍ
#አለሕግ #Alehig
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Lawsocieties
👍182🔥1
ሰ/መ/ቁ. 158292 የካቲት 25 ቀን 2011 ዓ.ም

ባልና ሚስት በጋብቻ ዉስጥ እያሉ በመካከላቸዉ የሚያደርጉት ዉል ፍ/ቤት ካላጸደቀዉ በሕግ ፊት ዉጤት ሊኖረዉ እንደማይችል ያመልክታል። 
በጋብቻ እያሉ ባል እና ሚስት በመካከላቸዉ የሚያደርጉት የስጦታ ዉልን በተመለከተ አግባብነት ያለዉ ሕግ የተሻሻለዉ የቤተሰብ ሕግ ድንጋጌ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።
በመሆኑም ባል በአዋጅ ቁጥር 334/1995 አንቀጽ 27 መሰረት የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽ/ቤት ፊት ቀርበዉ ያደረጉት እና የተመዘገበ መሆኑ የተረጋገጠ ባል ለሚስት በስጦታ ዉል ንብረታቸዉን ሲሰጧቸዉ በጋብቻ ዉስጥ በመሆኑ የስጦታ ዉሉ በፍርድ ቤት የጸደቀ ካልሆነ የስጦታ ዉሉ በፍ/ቤት እስካልጸደቀ ድረስ በሕግ ፊት ዉጤት ሊኖረዉ አይችልም።
Abrham Yones
ALE)አለ Provided by Legal Experts.
አማራጭ የሕግ እውቀት፣
ነፃ የሕግ ምክርና ድጋፍ
#አለሕግ #Alehig
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Lawsocieties
👍10
2016 VOL -3 BY DANIEL FIKADU LAW OFFICE.pdf
13.8 MB
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በ2016 ዓ.ም. የተሰጡ ያልታተሙ አስገዳጅ የህግ ትርጉሞች
የ2016 3ተኛ ስብስብ ቅጽ - 3 በዳንኤል ፍቃዱ /ጠበቃ/
https://t.me/lawsocieties
👍9
የቀረጥና ታክስ ነጻ መብት አሰጣጥን በተመለከተ

በጉምሩክ አዋጅ 1160/2011 መሰረት

1.  በገቢና ወጪ እቃዎች ላይ የቀረጥ ነጻ መብት የሚሰጠው የገንዘብ ሚኒስቴር ብቻ ይሆናል
2.  ከዲፕሎማሲ ግንኙነት ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ በፈረመችባቸው እና ተቀብላ ባፀደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች መሰረት የሚሰጡ የቀረጥና ታክስ ነጻ መብቶች በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እየተረጋገጠ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡  
3.  የቀረጥና ታክስ ነጻ መብት እንዲፈቅዱ በሕግ ለተለየዩ የመንግስት አካላት የተሰጠው ስልጣን ለገንዘብ ሚኒስቴር ተላልፏል፡፡
4.  ማንኛውም የመንግስት አካል በሚዋዋለው የፕሮጀክት ስምምነት መሰረት የሚፈቀድ የቀረጥና ታክስ ነጻ መብት ተፈጻሚ የሚሆነው በገንዘብ ሚኒስቴር ሲጸድቅ ብቻ ይሆናል፡፡
5.  የጉምሩክ ኮሚሽን ከቀረጥና ታክስ ነጻ ሆነው ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ ወይም ከአገር የሚወጡ እቃዎች ለታለመላቸው ዓላማ ስለመዋላቸው መረጃ ይይዛል፤ ይከታተላል፤ እርምጃ ይወስዳል፡፡
6.  የቀረጥና ታክስ ነጻ መብት ስለሚፈቀድበት ሁኔታ እና ስለአፈጻጸሙ ሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚያወጣው ደንብ ይወሰናል፡፡
ገቢዎች ቢሮ
Alternative legal enlightenment (ALE)አለ Provided by Legal Experts.
አማራጭ የሕግ እውቀት፣
ነፃ የሕግ ምክርና ድጋፍ
#አለሕግ #Alehig
https://t.me/lawsocieties
👉Facebook Page 👈
https://www.facebook.com/lawsocieties/

👉YouTube 👈
https://youtube.com/@Lawsocieties
👍13
#በብር_ኖት_ወይም_በገንዘቦች_ላይ_የሚፈፀሙ_ወንጀሎች_ምንነት
ገንዘብ በአንድ ሀገር ውስጥ ህጋዊ መገበያያ ሰነድ ነው፡፡ ሀገራት የገንዘብ ኖታቸውን የመወሰን ሉአላዊ ስልጣን ያላቸው በመሆኑ አገራችንን ጨምሮ ሀገራት የመገበያያ ገንዘባቸውን ይወስናሉ፡፡ በሀገራችን ብር ህጋዊ ገንዘብ ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ ስለሀገራችን ህጋዊ ገንዘብ እና በገንዘብ ላይ ስለሚፈፀሙ ወንጀሎች እንመለከታለን፡፡
ህጋዊ የገንዘብ ኖት
ህጋዊ የገንዘብ ኖትን በተመለከተ በብሔራዊ ባንክ ማቋቋሚያ አዋጅ አዋጅ ቁጥር 591/2000 አንቀጽ 17(1) መሰረት የኢትዮጵያ ህጋዊ የገንዘብ መደብ ብር እንደሆነ እና ይኸውም የሀገሪቱ ህጋዊ ገንዘብ እንደሆነ ድንግጎ ይገኛል፡፡ የዚህ ህጋዊ መገበያያ ኖት ስም በአገር አቀፍ ደረጃ “ብር” ተብሎ የተሰየመ ሲሆን በአለምአቀፍ ደረጃ ዒቲቢ(ETB) ተብሎ በዚሁ አዋጅ ተሰይሟል፡፡ ህጉ ከብር ውጪ ሳንቲሞችንም እንዲሁ እውቅና ሰጥቷል፡፡                       ብሄራዊ ባንክ በተለየ ሁኔታ በፈቀደው አግባብ ካልሆነ በስተቀር በአገራችን ውስጥ የሚደረግ ማናቸውም የገንዘብ ስምምነቶች እና ውሎች በብር እንደተፈጸሙ ይቀቆጠራል፡፡ ይህ ማለት ገንዘብን በተመለከተ የሚደረግ ስምምነት በአገር ውስጥ ሲደረግ የግዴታ በብር መደረግ አለበት ማለት ነው፡፡ ከዚህ ውጨ በሌላ አገር ምንዛሬ ለማከናወን የግድ ብሄራዊ ባንክ ሊፈቅድ ይገባል ማለት ነው፡፡ ይህ ፍቃድም በልዩ ሁኔታ በጥብቅ መስፈርት የሚሰጥ መሆኑን ከህጉ ንባብ እና አንድምታ መረዳት ይቻላል፡፡

ነገር ግን አገራችን ተቀብላ ባፀደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች እና በሌላ የአገራችን ህግ ከዚህ በተለየ ሁኔታ ግንኙቶች በሌላ የገንዘብ ኖት እንዲደረጉ በግልጽ በተደነገገ ጊዜ ገንዘብ ነክ ውሎች ወይም ግንኘነቶች በአለም አቀፍ ህጉ ወይም በግልፅ በደነገገው ህግ ወይም ብሄራዊ ባንክ ባዘዘው መሰረት በሚፈቀድ የገንዘብ ኖት ሊመዘገብ ይችላል፡፡                                                          ህጋዊ ገንዘብን የመወሰን እና የማሳተም ስልጣን
በኢ.ፌ.ድ.ሪ ህገመንግስት አንቀጽ 51 ንኡስ አንቀጽ 7 መሰረት ብሄራዊ ባንክን የማስተዳደር፣ ገንዘብ ማተም፣ መበደር እና የውጭ ምንዛሬን መቆጣጠር የፌደራል መንግስት ስልጣን እና ሀላፊነት እንደሆነ ተደንጓል፡፡ በፌደራል መንግስት ደረጃ ስልጣን እና አወቃቀር መሰረት እነዚህን ብሮች እና ሳንቲሞች የመቅረጽ፣ የማተም፣ የማስቀረጽ፣ የማሳተም፣ የማሰራጨት፣ የማስወገድ እና እንዲወገዱ የማድረግ ብቸኛ ስልጣን ያለው ብሄራዊ ባንክ እንደሆን በብሔራዊ ባንክ ማቋቋሚያ አዋጅ አዋጅ ቁጥር 591/2000 አንቀጽ 5 ንኡስ አንቀጽ 1 እና 2 መረዳት ይቻላል፡፡ በእነዚህ ህጋዊ ገንዘቦች ላይ የሚጻፈውን ፅሁፍ፣ የኖቶቹ ስፋት፣ ቅርጽ እና መደባቸው እንዲሁም ሌሎች ልዩ ልዩ ጉዳየች በብሄራዊ ባንክ እንደሚወሰን የአዋጁ አንቀጽ 18 ያመለክታል፡፡
የወንጀል ተጠያቂነት የሚስከትሉ የወንጀሎች ድርጊቶች
ህጋዊ የገንዘብ ኖቶችን በተመለከተ የኢ.ፌ.ድ.ሪ የወንጀል ህግ ከአንቀጽ 356 ጀምሮ እስከ አንቀጽ 362 አስቀጪ የሆኑ የወንጀል ድርጊቶች እና የሚያስቀጠቱን የቅጣት መጠን ደንግጎ ይገኛል፡፡ በዚሁም መሰረት በህጉ አንቀጽ 356 መሰረት ህጋዊ መገበያያ የሆኑትን ገንዘቦች ያለ ፍቃድ መስራት ወይም አስመስሎ መስራት ከ5 አመት በማያንስ ጽኑ እስራት የሚያስቀጣ የወንጀል ድርጊት ነው፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ በአንቀጽ 357 መሰረት ህጋዊ ገንዘቦችን ከትክክለኛ ዋጋቸው በላይ እንዲዘዋወሩ ለማድረግ በማሰሰብ መልካቸውን መለወጥ፣ እውነተኛ መልካቸው ላይ ሌላ ነገርን መጨመር፣ ቀለማቸውን መለወጥ ወይም በሌላ ማናቸውም አይነት ዘዴን በመጠቀም በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር ወደሀሰተኛነት መለወጥ ከ15 አመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ያስቀጣል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በአንቀጽ 358 መሰረት በኬሚካል፣ በፊዚካል፣ መካኒካል ወይም ማናቸውንም ዘዴ ተጠቅሞ ህጋዊ የሆኑትን ገንዘቦች ዋጋቸውን ዝቅ እንዲል ማድረግ ከ10 አመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ያስቀጣል፡፡ ይህ ወንጀል በአገራች ውስጥም ሆነ በውጪ አገር ቢፈፀም የሚያስቀጣ ነው፡፡
ወደ አገር ከማስገባት ጋር ተያይዞ ሀሰተኛ የሆኑ ወይም ዋጋቸው ዝቅ እንዲል የተደረጉ ገንዘቦችን እውነተኛ እንደሆኑ ወይም ሙሉ ዋጋቸውን እንደያዙ አስመስሎ ራሱ እንዲገበያይባቸው ወይም እንዲዘዋወሩ ለማድረግ በማሰብ ወደ አገር ውስጥ ማስገባትም ሆነ ከአገር ማስወጣት እንዲሁም ይዞ መገኘት፣ ማስቀመጥና ማቅረብም ጭምር ከ15 አመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ያስቀጣል፡፡ እነዚህ በገንዘብ ኖቶች ላይ የሚፈጸሙ የወንጀል ድርጊቶች ከተፈጸሙ ህጉ ድርጊቱ የተፈጸመው ገንዘቦቹን ለማዘዋወር እንደሆነ ግምት ይወስዳል፡፡
ማዘዋወርንም በተመለከተ በአንቀጽ 361 ላይ እንደተደነገገው ሀሰተኛ የሆኑትን ወይም ወደ ሀሰት የተለወጡትን ገንዘቦች እውነተኛ አስመስሎ ወይም ከተወሰነው በላይ ዋጋ እንዳላቸው አስመስሎ በኢትዮጵያ ውስጥ ወይም ከአገር ውጭ ማዘዋወር ከ10 አመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ያስቀጣል፡፡ በዚሁ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 2 እንደተገለጸው ዋጋቸው የተቀነሰውን ገንዘቦች ሙሉ ዋጋ እንደያዙ አስመስሎ ማዘዋወር ከ5 አመት በማይበልጥ ቀላል እስራት ወይም በገንዘብ መቀጮ የሚያስቀጣ ወንጀል ነው፡፡ ወንጀል አድራጊው ገንዘቡን እውነተኛ ነው በሚል እምነት ወይም በትክክለኛ ዋጋው ከተቀበለ በኋላ ሀሰተኛ መሆኑን ወይም ዋጋው መቀነሱን እያወቀ ከኪሳራ ለመዳን ሀሰተኛውን ወይም ወደ ሀሰት የተለወጠውን ገንዘብ ያዘዋወረ እንደሆነ በቀላል አስራት ይቀጣል፡፡ በተጨማሪም ዋጋው የተቀነሰውን ገንዘብ ሙሉ ዋጋው እንዳለ በማስመሰል ያዘዋወረ እንደሆነ በመቀጮ የሚቀጣ ይሆናል።
በወንጀል ህጉ አንቀጽ 362 መሰረት ከላይ የተገለጹት ወንጀሎች የተፈጸሙበት የገንዘብ መጠን ማነሱ ከወንጀል ተጠያቂነት ያስመልጥም፡፡ ይልቁንም ህጉ ባስቀመጠው መሰረት የገንዘቡ መጠን ትንሽ ከሆነ ቅጣቱ ቀላል እስራት ይሆናል፡፡
ገንዘቦችን አስመስሎ መስራትን ስናይ ወንጀል ፈፃሚው የማታለል ሀሳብ ባይኖረውም ገንዘቦችን በማስመሰል መስራት፣ በሚያሳሳት መልኩ አምሳያ ሆነው እንዲዘዋወሩ በማስታወቂያነት አስመስሎ ማወጣት ድርጊቱ የማሳሳት አደጋ የሚፈጥር ወይም ለመፍጠር የሚችል ከሆነ እንዲሁም እነዚህኑ መስለው የተሰሩትን ገንዘቦች ወደ አገር ማስገባት፣ ከአገር ማስወጣት፣ በአደራ በቀበል፣ ለሽያጭ ወይም በስጦታ ማቅረብ ወይም እንዲዘዋወሩ ማድረግ በህጉ አንቀጽ 369 መሰረት በመቀጮ ወይም ከሶስት ወር በማይበልጥ ቀላል እስራት ያስቀጣል፡፡ እነዚህን የሀሰት ገንዘቦች ከመስራት ጋር በተገናኘ ሌላው መታወቅ ያለበት ነገር ማንም ሰው አግባብ ያለው ባለስልጣን በግልፅ ሳያዘው ለገንዘብ ማተሚያ ወይም መስሪያነት የሚያገለግሉትን መሳሪያዎች ፎርሞች፣ ከውሮች ወረቀቶች፣ ሞዴሎች እና መሰል እቃዎች የሰራ፣ በእጁ ያስገባ፣ ወደ አገር ያስገባ ወይም ያስወጣ፣ ለሌላ ሰው ያቀረበ ወይም አሳልፎ የሰጠ እንደሆነ እንዲሁም እነዚህ ገንዘቦች እንዲሰሩ የሚሰጡ ትእዛዞችን የተቀበል፣ የፈጸመ፣ ያስፈጸመ፣ ለሌላ ሰው ያስረከበ እንደሆነ በህጉ አንቀጽ 370 መሰረት በቀላል እስራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል፡፡
👍84