ከሰራተኝነት ወደ አምራችነት!
ቀኑን ሙሉ በስራ ሲባክኑ መዋልና ምርታማነት ሁለት የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡ አንዳንድ ሰዎች ቀኑን ሙሉ ወዲህና ወዲያ ስላሉ ብቻ ስኬታማ የሆኑ ይመስላቸዋል፡፡ ነገር ግን ቀኑን ሙሉ ስራ መስራት ማለት ውጤታማና ምርታማ መሆን ማለት አይደለም፡፡
ለምሳሌ፣ በአንዳንድ መስሪያ ቤቶች ውስጥ ሰራተኞች ብዙ ናቸው፣ አምራቾች ግን ጥቂት ናቸው፡፡ በግል ሕይወታችንም ቢሆን ተመሳሳይ ሁኔታ ሊከሰት ይችላል፡፡ ከጠዋት እስከማታ፣ ሳምንቱን ሙሉ ስነባክንና ስንሯሯጥ ውለንና ከርመን መጨረሻ ላይ ያመረትነው (ያከናወንነው) ነገር ከሌለ ጊዜያችንን በከንቱ አባክነናል፡፡
በጣም እየሰራን ወራትና አመታት አስቆጥረን ብዙም ለውጥ ካላየን ምናልባት ምክንያቱ የምንሰራው ስራ ምርታማ የመሆኑን ጉዳይ ስላላሰብንበት ይሆናል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ በሚገባ ማሰብ ማለት ሁሉን ነገር ከዋናው ዓላማችንና ከግባችን አንጻር መቃኘት ማለት ነው፡፡
ከሰራተኝነት ወደ አምራችነት ለመዘዋወር አንዱ መንገድ በየቀኑ የምንሰራቸውን ስራዎች ቅደም ተከተል ማውጣት ነው፡፡ ይህንን ተግባር ለምንድን ነው የምተገብረው? ሌላ ሊቀድም የሚገባው ስራ ይኖር ይሆን? እዚህ ቦታ ዛሬ የምሄደው ለምንድነው? ሌላ ቀን ብሄድ ምን ችግር አለበት? ይህ የማደርገው ነገር ማከናወን ከምፈልገው ከዋናው አላማዬ ጋር ምን ግንኙነት አለው? . . . እና የመሳሰሉትን ጥያቄዎች መጠየቅ እጅግ ወሳኝ ጉዳይ ነው፡፡
ሰራተኝነት ማለት የተገኘውንና ፊታችን የመጣውን ነገር ሁሉ ሲሰሩ መዋል ማለት ነው፣ አምራችነት ማለት ከአላማ አንጻር መስራት ማለት ነው፡፡ ሰራተኝነት ቢዚ ያደርገናል፣ አምራችነት ውጤታማ ያደርገናል፡፡ ሰራተኛ ሆነን አምራች ላንሆን እንችላለን፣ አምራች ሆነን ግን ሰራተኛ ላለመሆን አንችልም፡፡
ብዙ አጠናለሁ (ስራ) ውጤቴ (ምርት) ግን ጥሩ አይደለም . . . ብዙ አይነት ተግባሮች አከናውናለሁ (ስራ)፣ ነገር ግን የገቢዬ ምንጭ (ምርት) ግን አይጨምርም . . . ይኸው ብዙ ስደክም (ስራ) አመታት ሆነኝ፣ ሕይወቴ ግን ምንም ለውጥ የለውም (ምርት) . . . ብዙ ጓደኞች አሉኝ (ስራ)፣ ነገር ግን ከማንም ጋር የጠለቀና ውጤታማ ወዳጅነት እንደለኝ አይሰማኝም (ምርት) . . . ፡፡
ከላይ የተጠቀሱት አይነትና መሰል ስሜቶች ካሉብህ በሁኔታው በሚገባ አስብበት፡፡ ከሰራህ አይቀር ለምርታማነት ስራ፡፡ ከሮጥክ አይቀር ለማሸነፍ ሩጥ፡፡ ከለፋህ አይቀር ውጤት ለማግኘጥት ልፋ፡፡
Dr-Eyob-Mamo
ቀኑን ሙሉ በስራ ሲባክኑ መዋልና ምርታማነት ሁለት የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡ አንዳንድ ሰዎች ቀኑን ሙሉ ወዲህና ወዲያ ስላሉ ብቻ ስኬታማ የሆኑ ይመስላቸዋል፡፡ ነገር ግን ቀኑን ሙሉ ስራ መስራት ማለት ውጤታማና ምርታማ መሆን ማለት አይደለም፡፡
ለምሳሌ፣ በአንዳንድ መስሪያ ቤቶች ውስጥ ሰራተኞች ብዙ ናቸው፣ አምራቾች ግን ጥቂት ናቸው፡፡ በግል ሕይወታችንም ቢሆን ተመሳሳይ ሁኔታ ሊከሰት ይችላል፡፡ ከጠዋት እስከማታ፣ ሳምንቱን ሙሉ ስነባክንና ስንሯሯጥ ውለንና ከርመን መጨረሻ ላይ ያመረትነው (ያከናወንነው) ነገር ከሌለ ጊዜያችንን በከንቱ አባክነናል፡፡
በጣም እየሰራን ወራትና አመታት አስቆጥረን ብዙም ለውጥ ካላየን ምናልባት ምክንያቱ የምንሰራው ስራ ምርታማ የመሆኑን ጉዳይ ስላላሰብንበት ይሆናል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ በሚገባ ማሰብ ማለት ሁሉን ነገር ከዋናው ዓላማችንና ከግባችን አንጻር መቃኘት ማለት ነው፡፡
ከሰራተኝነት ወደ አምራችነት ለመዘዋወር አንዱ መንገድ በየቀኑ የምንሰራቸውን ስራዎች ቅደም ተከተል ማውጣት ነው፡፡ ይህንን ተግባር ለምንድን ነው የምተገብረው? ሌላ ሊቀድም የሚገባው ስራ ይኖር ይሆን? እዚህ ቦታ ዛሬ የምሄደው ለምንድነው? ሌላ ቀን ብሄድ ምን ችግር አለበት? ይህ የማደርገው ነገር ማከናወን ከምፈልገው ከዋናው አላማዬ ጋር ምን ግንኙነት አለው? . . . እና የመሳሰሉትን ጥያቄዎች መጠየቅ እጅግ ወሳኝ ጉዳይ ነው፡፡
ሰራተኝነት ማለት የተገኘውንና ፊታችን የመጣውን ነገር ሁሉ ሲሰሩ መዋል ማለት ነው፣ አምራችነት ማለት ከአላማ አንጻር መስራት ማለት ነው፡፡ ሰራተኝነት ቢዚ ያደርገናል፣ አምራችነት ውጤታማ ያደርገናል፡፡ ሰራተኛ ሆነን አምራች ላንሆን እንችላለን፣ አምራች ሆነን ግን ሰራተኛ ላለመሆን አንችልም፡፡
ብዙ አጠናለሁ (ስራ) ውጤቴ (ምርት) ግን ጥሩ አይደለም . . . ብዙ አይነት ተግባሮች አከናውናለሁ (ስራ)፣ ነገር ግን የገቢዬ ምንጭ (ምርት) ግን አይጨምርም . . . ይኸው ብዙ ስደክም (ስራ) አመታት ሆነኝ፣ ሕይወቴ ግን ምንም ለውጥ የለውም (ምርት) . . . ብዙ ጓደኞች አሉኝ (ስራ)፣ ነገር ግን ከማንም ጋር የጠለቀና ውጤታማ ወዳጅነት እንደለኝ አይሰማኝም (ምርት) . . . ፡፡
ከላይ የተጠቀሱት አይነትና መሰል ስሜቶች ካሉብህ በሁኔታው በሚገባ አስብበት፡፡ ከሰራህ አይቀር ለምርታማነት ስራ፡፡ ከሮጥክ አይቀር ለማሸነፍ ሩጥ፡፡ ከለፋህ አይቀር ውጤት ለማግኘጥት ልፋ፡፡
Dr-Eyob-Mamo
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Alemwaza)
Where are the lawyers, the natural leaders in Ethiopia!?
Most of the greatest leaders and change agents in the world are Lawyers. The notable ones being Abraham Lincoln, Gandhi, Mandella, Barack Obama, even the President-Elect Joe-all Lawyers.
What about in Ethiopia? Lawyers are busy with rhetorics and opportunism while others play the game (of course, very badly). So, Comrades, it is time to live up to what the discipline is all about-leadership! Come out from your temporary refuge and lead the nation to leave some legacy behind. Or else, you will remain playing Low-year!
By Moges Zewdu Teshome
@lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
Most of the greatest leaders and change agents in the world are Lawyers. The notable ones being Abraham Lincoln, Gandhi, Mandella, Barack Obama, even the President-Elect Joe-all Lawyers.
What about in Ethiopia? Lawyers are busy with rhetorics and opportunism while others play the game (of course, very badly). So, Comrades, it is time to live up to what the discipline is all about-leadership! Come out from your temporary refuge and lead the nation to leave some legacy behind. Or else, you will remain playing Low-year!
By Moges Zewdu Teshome
@lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
Forwarded from 🇪🇹የሕግ ጉዳይ
የሕገ_መንግሥት_ጉዳዮች_አጣሪ_ጉባዔ_የጉዳዮች_አቀራረብና_አወሳሰን_መመሪያ.pdf
366.3 KB
Share 'የሕገ_መንግሥት_ጉዳዮች_አጣሪ_ጉባዔ_የጉዳዮች_አቀራረብና_አወሳሰን_መመሪያ.pdf'
የሰበር ችሎት በ2014 ዓ/ም /የቀበሌ ቤቶችን አስመልክቶ ከሰጣቸው ውሳኔዎች በሰ/መ/ቁ 228002 የቀድሞ አቋሙነሰ /በግልፅ ባይጠቀስም/ የሚቀይር ነው። በዚህ መዝገብ በተሰጠው የህግ ትርጉም ቤቱ የቀበሌ መሆኑን የሚያሳይ ቅፅ 003 እና 004 በሌሉበት ለረጅም ጊዜ በመንግስት አካል ተይዞ መቆየቱ ብቻ በመንግስት /በቀበሌ/ የተወረሰ ነው ሊያስብለው አይችልም።
https://youtu.be/Aj5YQCNrynI?feature=shared
https://youtu.be/Aj5YQCNrynI?feature=shared
YouTube
የመንግስት /ቀበሌ/ ቤቶች 5 መሰረታዊ የሰበር ውሳኔዎች
ልዩነታቸው አደናጋሪ የሆኑ 5 የህግ ቃላት
የጊዜ ገደብ እና ይርጋ፥ በጽሑድ መደረግና በጽሑፍ መረጋገጥ ያለበት ውል፥ የልዩነት ሀሳብ እና የመስማሚያ ሀሳብ፥ የውል መሰረዝ እና የውል መፍረስ፥ ሐራጅ እና ጨረታ
https://youtu.be/2KXflpkGQ6g
የጊዜ ገደብ እና ይርጋ፥ በጽሑድ መደረግና በጽሑፍ መረጋገጥ ያለበት ውል፥ የልዩነት ሀሳብ እና የመስማሚያ ሀሳብ፥ የውል መሰረዝ እና የውል መፍረስ፥ ሐራጅ እና ጨረታ
https://youtu.be/2KXflpkGQ6g
YouTube
ልዩነታቸው አደናጋሪ የሆኑ 5 የህግ ቃላት
የጊዜ ገደብ እና ይርጋ፥ በጽሑድ መደረግና በጽሑፍ መረጋገጥ ያለበት ውል፥ የልዩነት ሀሳብ እና የመስማሚያ ሀሳብ፥ የውል መሰረዝ እና የውል መፍረስ፥ ሐራጅ እና ጨረታ
ሰ.መ.ቁ 226490 ጥቅምት 29 ቀን 2015 ዓ.ም
የወራሽነት ማስረጃ ከፍርድ ቤት የተሰጠው ሰው የመብት ጥያቄ ሲያቀርብ ሌላኛው ወራሽ የመውረስ መብት እንደሌለው ክርክር ለማቅረብ በቅድሚያ የወራሽነት ማስረጃውን ማሰረዝ አስፈላጊ አይደለም። ስለሆነም የወራሽነት ማስረጃ የተሰጠው ሰው የውርስ ድርሻውን ለማግኘት ባቀረበው ክስ ላይ የሟች ልጅ አይደለም ብሎ ለመቃወም በቅድሚያ የወራሽነት ማስረጃው እንዲሰረዝ አቤቱታ አቅርቦ ማሰረዝ አይጠበቅበትም። ወራሽነትን በማረጋግጥ የሚሰጥ የወራሽነት ማስረጃ በአመልካች ብቻ የቀረበውን የአንድ ወገን ማስረጃ በመቀበል የሚሰጥ ማስረጃ (Declaratory judgment) ለመክሰስ መብትና ጥቅም ያለው መሆኑን አሳይቶ የድርሻ ክፍፍል ጥያቄ ለማቅረብ በማስረጃነት የሚቀርብ፤ በማንኛውም ተዓማኒነት እና ክብደት ባለው ማስረጃ ሊስተባበል የሚችል ማስረጃ በመሆኑ ማስረጃው በተሰጠበት መዝገብ ላይ መብት ወይንም ጥቅሜን ይነካል በማለት በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 358 መሠረት የፍርድ መቃወሚያ የሚቀርብበት አይደለም።
Via
#ethiolawtips
የወራሽነት ማስረጃ ከፍርድ ቤት የተሰጠው ሰው የመብት ጥያቄ ሲያቀርብ ሌላኛው ወራሽ የመውረስ መብት እንደሌለው ክርክር ለማቅረብ በቅድሚያ የወራሽነት ማስረጃውን ማሰረዝ አስፈላጊ አይደለም። ስለሆነም የወራሽነት ማስረጃ የተሰጠው ሰው የውርስ ድርሻውን ለማግኘት ባቀረበው ክስ ላይ የሟች ልጅ አይደለም ብሎ ለመቃወም በቅድሚያ የወራሽነት ማስረጃው እንዲሰረዝ አቤቱታ አቅርቦ ማሰረዝ አይጠበቅበትም። ወራሽነትን በማረጋግጥ የሚሰጥ የወራሽነት ማስረጃ በአመልካች ብቻ የቀረበውን የአንድ ወገን ማስረጃ በመቀበል የሚሰጥ ማስረጃ (Declaratory judgment) ለመክሰስ መብትና ጥቅም ያለው መሆኑን አሳይቶ የድርሻ ክፍፍል ጥያቄ ለማቅረብ በማስረጃነት የሚቀርብ፤ በማንኛውም ተዓማኒነት እና ክብደት ባለው ማስረጃ ሊስተባበል የሚችል ማስረጃ በመሆኑ ማስረጃው በተሰጠበት መዝገብ ላይ መብት ወይንም ጥቅሜን ይነካል በማለት በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 358 መሠረት የፍርድ መቃወሚያ የሚቀርብበት አይደለም።
Via
#ethiolawtips
የሥራ ቦታ ዝውውርን ሠራተኛን ለማሰናበት በእጅአዙር መጠቀም /Constructive dismissal/
በአሠሪ እና ሠራተኛ ሕጉ መሠረት አሠሪው ሠራተኛውን ከቦታ ቦታ አዘዋውሮ የማሠራት ሥልጣኑ እስከ ምን ድረስ ነው? አሠሪ በቂ ምክንያት ሳይኖረው ሠራተኛውን ከአንድ ቦታ ወደሌላ ቦታ ማዘዋወር ይችላል? ሠራተኛው በአዲሱ የሥራ ቦታ ለመገኘት የማይችልበት በቂ ምክንያት ቢኖረው እና በ5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ሪፖርት ሳያደርግ ቢቀር የሚኖረው ሕጋዊ ውጤት ምንድን ነው? በጉዳዩ የሰበር ችሎት አቋምስ ምን ይመስላል?
በኢትዮጵያ አሠሪና ሠራተኛ ሕግ እንዲሁም በሰበር ችሎት የተሰጡ አስገዳጅ ውሳኔዎች ለቀጣሪዎች የተለጠጠ ሠራተኛን የማስተዳደር ሥልጣን (Managerial prerogative) ይሰጣሉ፡፡ በመሆኑም አንዳንድ አሠሪዎች የሥራ ቦታ ዝውውርን እንደሁነኛ ሠራተኛን የመቅጫ መንገድ ሲጠቀሙበት ይስተዋላል፡፡ አሠሪ የዓይንህ ቀለም አላማረኝም በማለት ሠራተኛውን ከአንድ ክልል ወደ ሌላ ክልል ሲያዘዋውር ሠራተኛው ቅሬታ ቢኖረው እንኳን ወደተዘዋወረበት ቦታ ሔዶ ሥራ ከጀመረ በኋላ ክስ ማቅረብ ከመቻሉ በቀር ባለበት ቦታ ቅሬታውንም ይሁን ክሱን ማቅረብ አይችልም፡፡ የሰበር ችሎት በመዝገብ ቁጥር 37778፣ 38189 እና በሌሎች መዝገቦች በሰጠው ውሳኔ አንድ ሠራተኛ የዝውውርን ትእዛዝ ባለመቀበል ለአምስት ተከታታይ ቀናት አዲስ ወደተመደበበት የሥራ ቦታ ላይ ሪፖርት ካላደረገ እና ሥራውን ካልጀመረ በአሠሪና ሠራተኛ ሕጉ አንቀጽ 27 መሠረት ለሥራ ስንብት ምክንያት እንደሚሆን ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
የሰበር ችሎት በመ/ቁ 37778 (ቅጽ 8 ኅዳር 4 ቀን 2001) በአሠሪ በተደረገ የሥራ ዝውውር ቅሬታ አድሮብኛል በሚል ምክንያት ከሥራ መቅረት የሕግ ድጋፍ እንደሌለው ሲገልጽ በሰ/መ/ቁ 41623 (ቅጽ 8 መጋቢት 8 ቀን 2001) ላይ ደግሞ በአሠሪው ወደሌላ ቦታ ተዘዋውሮ እንዲሠራ የተደረገ ሠራተኛ ዝውውሩን በወቅቱ ሳይቃወም የተዘዋወረበት የሥራ ገበታ ላይ ለ 5 ተከታታይ ቀናት የቀረ እንደሆነ የሥራ ውሉን ለማቋረጥ በቂ ምክንያት እንደሆነ ያትታል፡፡
በሌላ በኩል ሠራተኛው ወደ ተዘዋወረበት ቦታ ተገኝቶ ሥራ መጀመር ሲገባው ይህን አለማድረጉ አሠሪው እርምጃ ከመውሰዱ በፊት የነገሩን ነባራዊ ሁኔታ ማየት ያለበት ስለመሆኑ ሰበር ችሎት በመ/ቁ 125004 ቅጽ 20 ላይ ውሳኔ ሰጥቶበታል፡፡ ችሎቱ ሠራተኛው በተዘዋወረበት ቅርንጫፍ ለመገኘት የሚፈጅበትን ጊዜ ግምት ውስጥ በማስገባት በተባለው ቀን መድረስ እንደማይችል ግምት በመውሰድ ስንብቱ ሕገወጥ ነው ብሏል፡፡
በዝውውር ምክንያት የሥራ ውል የመቋረጥ አግባብነት ጭብጥ ሆኖ በተያዘበት የሰ/መ/ቁ 238246 (አመልካች ወጋገን ባንክ አክሲዮን ማህበር እና ተጠሪ አቶ መንግሥቱ ካሣ መጋቢት 27 ቀን 2015 ዓ.ም ያልታተመ) ችሎቱ በሰጠው ትንታኔ የሥራ ውሉ የተቋረጠበት አግባብ እና ሕጋዊ ውጤቱ እንደውሉ፣ የሥራው ዓይነት እና የሥራ ውሉ የተቋረጠበት ምክንያት የሚለያይ መሆኑን ያስረዳል፡፡
ስለሆነም በሥራ ውሉ የሥራ ቦታው አዲስ አበባ መሆኑ ከተገለጸ አሠሪ ከአዲስ አበባ ውጪ ወደ ሌላ ቦታ አዘዋውሮ ማሠራት አይችልም፡፡ (በአሠሪና ሠራተኛ ሕግ አንቀጽ 4/3 ማንኛውም የሥራ ውል የሥራውን ዓይነትና ቦታ መያዝ እንዳለበት ይገልጻል፡፡ ቦታው በውሉ አለመገለጹ የሚኖረው ውጤት አጠያያቂ ነው)
በሌላ በኩል በጥበቃነት የተቀጠረ አንድ ሠራተኛ ይሠራበት ከነበረው አዲስ አበባ አንስቶ ደሴ ላይ ማዘዋወር ሥራው ካለው ባህሪ አንጻር አዲስ በተመደበበት ቦታ በቀላሉ ሊተካ የሚችል በመሆኑ እና ሠራተኛውን ከማዘዋወር ይልቅ ሌላ ሠራተኛ መቅጠር የሚቀል በመሆኑ ዝውውሩ አግባብ አይሆንም፡፡
በሰ/መ/ቁ 238246 ላይ አሠሪው ሠራተኛውን አዘዋውሮ የማሠራት መብት ያለው መሆኑን ቢያስረዳም ሠራተኛው ወደተመደበበት ቦታ ለመሄድ የማይችልበትን ምክንያት በበቂ ሁኔታ ካስረዳ ስንብቱ ሕገወጥ እንደሚሆን ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ በመሆኑም በዚህ ውሳኔ መሠረት ሠራተኛው ወደተመደበበት ቦታ መሄድ ያልቻለበትን በቂ ምክንያት በማስረጃ የማስረዳት ሸክም /burden of proof/ ያለበት ሲሆን ፍርድ ቤቱ ምክንያቱ በቂ ነው ብሎ ካመነ ዝውውሩን ሊያግድ ይችላል፡፡
በአብዛኛው የሥራ ቦታ ዝውውር የሚደረገው እንደ ጥበቃ ባሉ የሥራ ዘርፎች ሲሆን ሠራተኛውን ከሥራ ለማሰናበት እንደ legal loop hole በመሆን ሲያገለግል ይታያል፡፡ በአገራችን ያለው ዝቅተኛ የደመወዝ ምጣኔ እና በየዕለቱ የሚጨምረው ኑሮ ውድነት Stagflation የሚያስከትለው ጫና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ላሉ ወገኖች የራስ ምታት መሆኑ ቀጥሏል፡፡ ይባስ ብሎ በሥራ ቦታ ዝውውር ስም የሠራተኞቹ job security ጥያቄ ውስጥ መግባቱ አሳሳቢ ነው፡፡ አንድ ሠራተኛ ዝውውሩ ሕገወጥ ነው በማለት እየተከራከረ እያለ በተዘዋወርክበት ቦታ ሔደህ ክሰስ ማለት የሠራተኛውን ፍትሕ የማግኘት መብት በጥብቅ የሚጋፋ ነው፡፡ በመሆኑም የሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ 238246 የሰጠው ውሳኔ ተገቢ እና ቅጥ አጥቶ የነበረውን የአሠሪዎች የማስተዳደር ሥልጣን (Managerial prerogative) ልክ ያበጀለት ሆኖ አግኝቼዋለሁ፡፡
#solomon Baye
በአሠሪ እና ሠራተኛ ሕጉ መሠረት አሠሪው ሠራተኛውን ከቦታ ቦታ አዘዋውሮ የማሠራት ሥልጣኑ እስከ ምን ድረስ ነው? አሠሪ በቂ ምክንያት ሳይኖረው ሠራተኛውን ከአንድ ቦታ ወደሌላ ቦታ ማዘዋወር ይችላል? ሠራተኛው በአዲሱ የሥራ ቦታ ለመገኘት የማይችልበት በቂ ምክንያት ቢኖረው እና በ5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ሪፖርት ሳያደርግ ቢቀር የሚኖረው ሕጋዊ ውጤት ምንድን ነው? በጉዳዩ የሰበር ችሎት አቋምስ ምን ይመስላል?
በኢትዮጵያ አሠሪና ሠራተኛ ሕግ እንዲሁም በሰበር ችሎት የተሰጡ አስገዳጅ ውሳኔዎች ለቀጣሪዎች የተለጠጠ ሠራተኛን የማስተዳደር ሥልጣን (Managerial prerogative) ይሰጣሉ፡፡ በመሆኑም አንዳንድ አሠሪዎች የሥራ ቦታ ዝውውርን እንደሁነኛ ሠራተኛን የመቅጫ መንገድ ሲጠቀሙበት ይስተዋላል፡፡ አሠሪ የዓይንህ ቀለም አላማረኝም በማለት ሠራተኛውን ከአንድ ክልል ወደ ሌላ ክልል ሲያዘዋውር ሠራተኛው ቅሬታ ቢኖረው እንኳን ወደተዘዋወረበት ቦታ ሔዶ ሥራ ከጀመረ በኋላ ክስ ማቅረብ ከመቻሉ በቀር ባለበት ቦታ ቅሬታውንም ይሁን ክሱን ማቅረብ አይችልም፡፡ የሰበር ችሎት በመዝገብ ቁጥር 37778፣ 38189 እና በሌሎች መዝገቦች በሰጠው ውሳኔ አንድ ሠራተኛ የዝውውርን ትእዛዝ ባለመቀበል ለአምስት ተከታታይ ቀናት አዲስ ወደተመደበበት የሥራ ቦታ ላይ ሪፖርት ካላደረገ እና ሥራውን ካልጀመረ በአሠሪና ሠራተኛ ሕጉ አንቀጽ 27 መሠረት ለሥራ ስንብት ምክንያት እንደሚሆን ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
የሰበር ችሎት በመ/ቁ 37778 (ቅጽ 8 ኅዳር 4 ቀን 2001) በአሠሪ በተደረገ የሥራ ዝውውር ቅሬታ አድሮብኛል በሚል ምክንያት ከሥራ መቅረት የሕግ ድጋፍ እንደሌለው ሲገልጽ በሰ/መ/ቁ 41623 (ቅጽ 8 መጋቢት 8 ቀን 2001) ላይ ደግሞ በአሠሪው ወደሌላ ቦታ ተዘዋውሮ እንዲሠራ የተደረገ ሠራተኛ ዝውውሩን በወቅቱ ሳይቃወም የተዘዋወረበት የሥራ ገበታ ላይ ለ 5 ተከታታይ ቀናት የቀረ እንደሆነ የሥራ ውሉን ለማቋረጥ በቂ ምክንያት እንደሆነ ያትታል፡፡
በሌላ በኩል ሠራተኛው ወደ ተዘዋወረበት ቦታ ተገኝቶ ሥራ መጀመር ሲገባው ይህን አለማድረጉ አሠሪው እርምጃ ከመውሰዱ በፊት የነገሩን ነባራዊ ሁኔታ ማየት ያለበት ስለመሆኑ ሰበር ችሎት በመ/ቁ 125004 ቅጽ 20 ላይ ውሳኔ ሰጥቶበታል፡፡ ችሎቱ ሠራተኛው በተዘዋወረበት ቅርንጫፍ ለመገኘት የሚፈጅበትን ጊዜ ግምት ውስጥ በማስገባት በተባለው ቀን መድረስ እንደማይችል ግምት በመውሰድ ስንብቱ ሕገወጥ ነው ብሏል፡፡
በዝውውር ምክንያት የሥራ ውል የመቋረጥ አግባብነት ጭብጥ ሆኖ በተያዘበት የሰ/መ/ቁ 238246 (አመልካች ወጋገን ባንክ አክሲዮን ማህበር እና ተጠሪ አቶ መንግሥቱ ካሣ መጋቢት 27 ቀን 2015 ዓ.ም ያልታተመ) ችሎቱ በሰጠው ትንታኔ የሥራ ውሉ የተቋረጠበት አግባብ እና ሕጋዊ ውጤቱ እንደውሉ፣ የሥራው ዓይነት እና የሥራ ውሉ የተቋረጠበት ምክንያት የሚለያይ መሆኑን ያስረዳል፡፡
ስለሆነም በሥራ ውሉ የሥራ ቦታው አዲስ አበባ መሆኑ ከተገለጸ አሠሪ ከአዲስ አበባ ውጪ ወደ ሌላ ቦታ አዘዋውሮ ማሠራት አይችልም፡፡ (በአሠሪና ሠራተኛ ሕግ አንቀጽ 4/3 ማንኛውም የሥራ ውል የሥራውን ዓይነትና ቦታ መያዝ እንዳለበት ይገልጻል፡፡ ቦታው በውሉ አለመገለጹ የሚኖረው ውጤት አጠያያቂ ነው)
በሌላ በኩል በጥበቃነት የተቀጠረ አንድ ሠራተኛ ይሠራበት ከነበረው አዲስ አበባ አንስቶ ደሴ ላይ ማዘዋወር ሥራው ካለው ባህሪ አንጻር አዲስ በተመደበበት ቦታ በቀላሉ ሊተካ የሚችል በመሆኑ እና ሠራተኛውን ከማዘዋወር ይልቅ ሌላ ሠራተኛ መቅጠር የሚቀል በመሆኑ ዝውውሩ አግባብ አይሆንም፡፡
በሰ/መ/ቁ 238246 ላይ አሠሪው ሠራተኛውን አዘዋውሮ የማሠራት መብት ያለው መሆኑን ቢያስረዳም ሠራተኛው ወደተመደበበት ቦታ ለመሄድ የማይችልበትን ምክንያት በበቂ ሁኔታ ካስረዳ ስንብቱ ሕገወጥ እንደሚሆን ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ በመሆኑም በዚህ ውሳኔ መሠረት ሠራተኛው ወደተመደበበት ቦታ መሄድ ያልቻለበትን በቂ ምክንያት በማስረጃ የማስረዳት ሸክም /burden of proof/ ያለበት ሲሆን ፍርድ ቤቱ ምክንያቱ በቂ ነው ብሎ ካመነ ዝውውሩን ሊያግድ ይችላል፡፡
በአብዛኛው የሥራ ቦታ ዝውውር የሚደረገው እንደ ጥበቃ ባሉ የሥራ ዘርፎች ሲሆን ሠራተኛውን ከሥራ ለማሰናበት እንደ legal loop hole በመሆን ሲያገለግል ይታያል፡፡ በአገራችን ያለው ዝቅተኛ የደመወዝ ምጣኔ እና በየዕለቱ የሚጨምረው ኑሮ ውድነት Stagflation የሚያስከትለው ጫና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ላሉ ወገኖች የራስ ምታት መሆኑ ቀጥሏል፡፡ ይባስ ብሎ በሥራ ቦታ ዝውውር ስም የሠራተኞቹ job security ጥያቄ ውስጥ መግባቱ አሳሳቢ ነው፡፡ አንድ ሠራተኛ ዝውውሩ ሕገወጥ ነው በማለት እየተከራከረ እያለ በተዘዋወርክበት ቦታ ሔደህ ክሰስ ማለት የሠራተኛውን ፍትሕ የማግኘት መብት በጥብቅ የሚጋፋ ነው፡፡ በመሆኑም የሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ 238246 የሰጠው ውሳኔ ተገቢ እና ቅጥ አጥቶ የነበረውን የአሠሪዎች የማስተዳደር ሥልጣን (Managerial prerogative) ልክ ያበጀለት ሆኖ አግኝቼዋለሁ፡፡
#solomon Baye
#ጋብቻ
አሳስቢውን የጋብቻ ፍቺ ለመግታት ወደ ጋብቻ ከማምራት በፊት የጋብቻን መርህ ፣ ዓላማ ምንነት ጠንቅቆ ማወቅ ይገባል ሲሉ የጋብቻ እና ቤተሰብ አማካሪ ባለሞያው ተናገሩ።
የጋብቻ እና ቤተሰብ አማካሪ አቶ ይመስገን ሞላ ትዳራቸውን ለማትረፍ ምክር ፈልገው የሚመጡ ቤተሰቦች ከጊዜ ወደ ጊዜ ቁጥራቸው እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል።
የጋብቻ እና ቤተሰብ አማካሪው ምን አሉ ?
" የችግሩ አይነት እየበዛ እየጨመረ መጥቷል። በዚህም ቢሯችን የምናስተናግደው እንኳን አብዛኛው ችግር ሲገጥማቸው ለምክር የሚመጡ ናቸው ለመገንባት ከሚመጡ ይልቅ።
በሀገራችን ምክንያት ተብለው የሚሰጡ አሉ፦
- የመጀመሪያው በወሲብ አለመጣጣም ይባለል ፣
- በገንዘብ እጥረት ይባለል አብዛኛው የሚፋታው ግን ገንዘብ ሲያገኝ ነው፣
- የቤተሰብ ጣልቃ ገብነት / የጓደኛ ጠልቃ ገብነት ይባለል ይህም ቢሆን የግንኙነቱን ስስ መሆን ያሳያል፣
- የኮሚኒኬሽን ችግር ይባላል ፣
- አሁን እየጨመረ የመጣው የእምነት ጉዳይ ይነሳል በሁለቱ መካከል አለመተማመን አለ ምክንያት የሚባሉት እነዚህ ናቸው።
ለእኔ ግን ከዚህም በላይ ተጨማሪ ምክንያቶች አሉ ፦
- ያለን መንፈሳዊ እሴት መበላሸት አንድ ነገር ነው ፤
- በጾታዊ አክራሪነት የመጣው የወንድ እና የሴት ፆታ መገፋፋት ፣ አለመቀባበል በሁለቱ መካከል ያለው መተባበር ሳይሆን መፎካከር ስላለ፣ እንደ ባል እና ሚስት ሚናቸውን አለማወቃቸው ምክንያት ናቸው።
መጋባት ይፈልጋሉ ተዋደን ይሆናል ብለው መዋደድ ግን የጋብቻ መሰረት አይደለም ወይም ፍቅር ስላለ ጋብቻ መሰረት አያገኝም ውጤታማም አይሆንም። የጋብቻ መርህ አላማ፣ የጋብቻን ምንነት መረዳት ይጠይቃል። የነዚህ ሁሉ ድምር ውጤቶች ጋብቻ እንዳይፀና ቤተሰብ እንዲፈርስ ያደርጋል።
ወደ ጋብቻም ወደ ቤተሰብም የገቡ ሰዎች አስበው አይገቡበትም፤ ገብተው ምን እንደሚያደርጉ፣ ከመግባታቸው በፊት ምን መዘጋጀት እንዳለባቸው ስለማያውቁ ጋብቻው እንዳይዘልቅ ቤተሰብም እንዲፈርስ ዋነኛ ምክንያት ይሆናሉ። "
ባለሞያው ከቅርብ ጊዚያት ወዲህ ወደ ትዳር የሚገቡ #ወጣቶች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ገልጸው ከጋብቻ በፊት ስልጠና የመውሰድ ልምድም እያደገ ነው ብለዋል። ይህ ፍቺን ለመቀነስ ሚና እንዳለው ጠቁመው ከምንም በላይ ግን ቤተሰብ ልጆችን ሲያሳድግ አርያ መሆን አለበት ብለዋል።
ባለሞያው ፦
" ጋብቻ ብዙ ጊዜ እኛም ሀገር አይተን እንደሆነ ስመረቅ፣ ቤት ስገዛ ፣ስራ ስይዝ ብለው condition ያስቀምጣሉ ጋብቻ ግን Condition ሳይሆን Qualification ነው የሚጠይቀው። የበቃች ሚስት የበቃ ባል ለመሆን እራሱን አስቀድሞ ማዘጋጀት አለበት።
ለምሳሌ ፦ ባልነት ለበሰለ ወንድ ነው ኃላፊነት ለመሸከም ለበቃ ወንድ ነው ሚስትነትም እንደዛው ስለዚህ ከመዋደድ ያለፈ የመጋባት ምክንያትና ኃላፊነት የመወጣት አቅም ይጠይቃል። አንድ ወንድ ባል የሚሆነው ብስለቱና ብቃቱ ነው ወንድነቱ ብቻ ባል አያደርገውም። ስለዚህ ይህን ለማድረግ በግል እራስን መገንባት አለበት።
ወላጆች ልጆቻቸውን ለራሳቸው ጥሩ ልጅ፣ ለዛ ቤት ደግሞ ጥሩ ባልና ሚስት እንዲሆኑ፤ ሲወልዱ ጥሩ አባት እና እናት እንዲሆኑ ሞዴል መሆን አለባቸው።
አሁን የሚታየው የጋብቻ መፍረስ፣ የፍቺው ብዛት፣ የልጆች መጎዳት ትላንት ያልተሰራው ስራ መዘዝ ነው። ነገም እንደዚያ ይቀጥል ከተባለ ዛሬ እያንዳንዳችን የራሳችንን ቤት ጠብቀን ልጆቻችንን ለጋብቻ ማብቃት (የራሳችንን ጋብቻ በመጠበቅ)፣ ልጆቻችን እንዲሰለጥኑ ማድረግ ጋብቻን አውቀው እንዲኖሩ ማድረግ መፍትሄ ነው " ብለዋል።
ፁሁፍ በቲክቫህ ቤተሰብ አባላት።
Credit፦ ቪኦኤ (አስማማው አየነው)
@tikvahethiopia
አሳስቢውን የጋብቻ ፍቺ ለመግታት ወደ ጋብቻ ከማምራት በፊት የጋብቻን መርህ ፣ ዓላማ ምንነት ጠንቅቆ ማወቅ ይገባል ሲሉ የጋብቻ እና ቤተሰብ አማካሪ ባለሞያው ተናገሩ።
የጋብቻ እና ቤተሰብ አማካሪ አቶ ይመስገን ሞላ ትዳራቸውን ለማትረፍ ምክር ፈልገው የሚመጡ ቤተሰቦች ከጊዜ ወደ ጊዜ ቁጥራቸው እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል።
የጋብቻ እና ቤተሰብ አማካሪው ምን አሉ ?
" የችግሩ አይነት እየበዛ እየጨመረ መጥቷል። በዚህም ቢሯችን የምናስተናግደው እንኳን አብዛኛው ችግር ሲገጥማቸው ለምክር የሚመጡ ናቸው ለመገንባት ከሚመጡ ይልቅ።
በሀገራችን ምክንያት ተብለው የሚሰጡ አሉ፦
- የመጀመሪያው በወሲብ አለመጣጣም ይባለል ፣
- በገንዘብ እጥረት ይባለል አብዛኛው የሚፋታው ግን ገንዘብ ሲያገኝ ነው፣
- የቤተሰብ ጣልቃ ገብነት / የጓደኛ ጠልቃ ገብነት ይባለል ይህም ቢሆን የግንኙነቱን ስስ መሆን ያሳያል፣
- የኮሚኒኬሽን ችግር ይባላል ፣
- አሁን እየጨመረ የመጣው የእምነት ጉዳይ ይነሳል በሁለቱ መካከል አለመተማመን አለ ምክንያት የሚባሉት እነዚህ ናቸው።
ለእኔ ግን ከዚህም በላይ ተጨማሪ ምክንያቶች አሉ ፦
- ያለን መንፈሳዊ እሴት መበላሸት አንድ ነገር ነው ፤
- በጾታዊ አክራሪነት የመጣው የወንድ እና የሴት ፆታ መገፋፋት ፣ አለመቀባበል በሁለቱ መካከል ያለው መተባበር ሳይሆን መፎካከር ስላለ፣ እንደ ባል እና ሚስት ሚናቸውን አለማወቃቸው ምክንያት ናቸው።
መጋባት ይፈልጋሉ ተዋደን ይሆናል ብለው መዋደድ ግን የጋብቻ መሰረት አይደለም ወይም ፍቅር ስላለ ጋብቻ መሰረት አያገኝም ውጤታማም አይሆንም። የጋብቻ መርህ አላማ፣ የጋብቻን ምንነት መረዳት ይጠይቃል። የነዚህ ሁሉ ድምር ውጤቶች ጋብቻ እንዳይፀና ቤተሰብ እንዲፈርስ ያደርጋል።
ወደ ጋብቻም ወደ ቤተሰብም የገቡ ሰዎች አስበው አይገቡበትም፤ ገብተው ምን እንደሚያደርጉ፣ ከመግባታቸው በፊት ምን መዘጋጀት እንዳለባቸው ስለማያውቁ ጋብቻው እንዳይዘልቅ ቤተሰብም እንዲፈርስ ዋነኛ ምክንያት ይሆናሉ። "
ባለሞያው ከቅርብ ጊዚያት ወዲህ ወደ ትዳር የሚገቡ #ወጣቶች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ገልጸው ከጋብቻ በፊት ስልጠና የመውሰድ ልምድም እያደገ ነው ብለዋል። ይህ ፍቺን ለመቀነስ ሚና እንዳለው ጠቁመው ከምንም በላይ ግን ቤተሰብ ልጆችን ሲያሳድግ አርያ መሆን አለበት ብለዋል።
ባለሞያው ፦
" ጋብቻ ብዙ ጊዜ እኛም ሀገር አይተን እንደሆነ ስመረቅ፣ ቤት ስገዛ ፣ስራ ስይዝ ብለው condition ያስቀምጣሉ ጋብቻ ግን Condition ሳይሆን Qualification ነው የሚጠይቀው። የበቃች ሚስት የበቃ ባል ለመሆን እራሱን አስቀድሞ ማዘጋጀት አለበት።
ለምሳሌ ፦ ባልነት ለበሰለ ወንድ ነው ኃላፊነት ለመሸከም ለበቃ ወንድ ነው ሚስትነትም እንደዛው ስለዚህ ከመዋደድ ያለፈ የመጋባት ምክንያትና ኃላፊነት የመወጣት አቅም ይጠይቃል። አንድ ወንድ ባል የሚሆነው ብስለቱና ብቃቱ ነው ወንድነቱ ብቻ ባል አያደርገውም። ስለዚህ ይህን ለማድረግ በግል እራስን መገንባት አለበት።
ወላጆች ልጆቻቸውን ለራሳቸው ጥሩ ልጅ፣ ለዛ ቤት ደግሞ ጥሩ ባልና ሚስት እንዲሆኑ፤ ሲወልዱ ጥሩ አባት እና እናት እንዲሆኑ ሞዴል መሆን አለባቸው።
አሁን የሚታየው የጋብቻ መፍረስ፣ የፍቺው ብዛት፣ የልጆች መጎዳት ትላንት ያልተሰራው ስራ መዘዝ ነው። ነገም እንደዚያ ይቀጥል ከተባለ ዛሬ እያንዳንዳችን የራሳችንን ቤት ጠብቀን ልጆቻችንን ለጋብቻ ማብቃት (የራሳችንን ጋብቻ በመጠበቅ)፣ ልጆቻችን እንዲሰለጥኑ ማድረግ ጋብቻን አውቀው እንዲኖሩ ማድረግ መፍትሄ ነው " ብለዋል።
ፁሁፍ በቲክቫህ ቤተሰብ አባላት።
Credit፦ ቪኦኤ (አስማማው አየነው)
@tikvahethiopia
Public Information Noble (PIN) is an NGO/CSO that works to promote the right to access information.
They have a website at [pinngo.org](https://www.pinngo.org) where you can find more information about their work. In addition, they have a presence on various social media platforms such as Facebook, Twitter, Telegram, YouTube, LinkedIn, and TikTok.
You can find their official Facebook page at
[facebook.com/PublicInformationNoble](https://www.facebook.com/PublicInformationNoble?mibextid=ZbWKwL),
their Twitter handle at
[@PINNGO_org](https://twitter.com/PINNGO_org?t=xKZd2ejDdUIKvS4bkrdZ5A&s=09),
their Telegram channel at
[t.me/PublicInformationNoble](https://t.me/PublicInformationNoble),
their YouTube channel at
[youtube.com/@PublicinformationNoblePIN](https://youtube.com/@PublicinformationNoblePIN?si=xVQQAoiVF-nqw1dN),
and their TikTok account at
[vm.tiktok.com/ZMjNEvekB/](https://vm.tiktok.com/ZMjNEvekB/).
You can also reach out to them via email at support@pinngo.org or info@pinngo.org.
They have a website at [pinngo.org](https://www.pinngo.org) where you can find more information about their work. In addition, they have a presence on various social media platforms such as Facebook, Twitter, Telegram, YouTube, LinkedIn, and TikTok.
You can find their official Facebook page at
[facebook.com/PublicInformationNoble](https://www.facebook.com/PublicInformationNoble?mibextid=ZbWKwL),
their Twitter handle at
[@PINNGO_org](https://twitter.com/PINNGO_org?t=xKZd2ejDdUIKvS4bkrdZ5A&s=09),
their Telegram channel at
[t.me/PublicInformationNoble](https://t.me/PublicInformationNoble),
their YouTube channel at
[youtube.com/@PublicinformationNoblePIN](https://youtube.com/@PublicinformationNoblePIN?si=xVQQAoiVF-nqw1dN),
and their TikTok account at
[vm.tiktok.com/ZMjNEvekB/](https://vm.tiktok.com/ZMjNEvekB/).
You can also reach out to them via email at support@pinngo.org or info@pinngo.org.
Facebook
Log in to Facebook
Log in to Facebook to start sharing and connecting with your friends, family and people you know.
ከወጪ መጋራት ጋር ተያይዞ የአሰሪዎች ግዴታ
ማንኛውም አሰሪ፡-
1. የቀጠራቸውን ተጠቃሚዎች ዝርዝር ለባለሥልጣኑ ወይም ለሚመወክለው የማስታወቅ
2. በገንዘብ ለመክፈል ግዴታ ከገቡ ተጠቃሚዎች የሚፈለግባቸውን እዳ የሚያሳይ ማስረጃ ከተጠቃሚዎቹ በመቀበልና ስለ ትክክለኛነቱ ከሚኒስቴሩ በማረጋገጥ በየወሩ ከጥቅል ደመወዛቸው ቢያንስ 10% እየቀነሰ ከእያንዳንዱ ወር መጨረሻ አንስቶ ባሉት ሰላሳ ቀናት ውስጥ ለሚኒስቴሩ ወይም ለሚወክለው የመክፈል
3. ተጠቃሚዎች ከተቋሙ የተሰጣቸውንና የሚፈለግባቸውን እዳ የሚያሳየውን ማስረጃ ለመስጠት ፍቃደኛ ካልሆኑ የጥቅል ደመወዛቸው አንድ ሶስተኛ እየቀነሰ ለሚኒስቴሩ ወይም ለሚወክለው ገቢ የማድረግ፣
4. ገንዘብ በመክፈልም ሆነ አገልግሎት በመስጠት እዳቸውን ከፍለው ያጠናቀቁ ተጠቃሚዎችን ዝርዝር ክፍያው በተጠናቀቀበት ወር ለሚኒስቴሩ ወይም ለሚወክለው የማሳወቅ
5. አገልግሎት በመስጠት እንደሚከፍሉ ተገልጾ የተመደቡለትን ተጠቃሚዎች ተገቢውን ክትትል በማድረግ ማሰራትና አገልግሎት ካቋረጡ ሙሉ ለሙሉ ማቋረጣቸውን በማረጋገጥ ወዲያውኑ ለሚኒስቴሩ፣ ለትምህርት ሚኒስቴር እንዲሁም ለመደባቸው ሚኒስቴር መስሪያ ቤት የማሳወቅ ግዴታ አለበት ፡፡
ማንኛውም አሰሪ፡-
1. የቀጠራቸውን ተጠቃሚዎች ዝርዝር ለባለሥልጣኑ ወይም ለሚመወክለው የማስታወቅ
2. በገንዘብ ለመክፈል ግዴታ ከገቡ ተጠቃሚዎች የሚፈለግባቸውን እዳ የሚያሳይ ማስረጃ ከተጠቃሚዎቹ በመቀበልና ስለ ትክክለኛነቱ ከሚኒስቴሩ በማረጋገጥ በየወሩ ከጥቅል ደመወዛቸው ቢያንስ 10% እየቀነሰ ከእያንዳንዱ ወር መጨረሻ አንስቶ ባሉት ሰላሳ ቀናት ውስጥ ለሚኒስቴሩ ወይም ለሚወክለው የመክፈል
3. ተጠቃሚዎች ከተቋሙ የተሰጣቸውንና የሚፈለግባቸውን እዳ የሚያሳየውን ማስረጃ ለመስጠት ፍቃደኛ ካልሆኑ የጥቅል ደመወዛቸው አንድ ሶስተኛ እየቀነሰ ለሚኒስቴሩ ወይም ለሚወክለው ገቢ የማድረግ፣
4. ገንዘብ በመክፈልም ሆነ አገልግሎት በመስጠት እዳቸውን ከፍለው ያጠናቀቁ ተጠቃሚዎችን ዝርዝር ክፍያው በተጠናቀቀበት ወር ለሚኒስቴሩ ወይም ለሚወክለው የማሳወቅ
5. አገልግሎት በመስጠት እንደሚከፍሉ ተገልጾ የተመደቡለትን ተጠቃሚዎች ተገቢውን ክትትል በማድረግ ማሰራትና አገልግሎት ካቋረጡ ሙሉ ለሙሉ ማቋረጣቸውን በማረጋገጥ ወዲያውኑ ለሚኒስቴሩ፣ ለትምህርት ሚኒስቴር እንዲሁም ለመደባቸው ሚኒስቴር መስሪያ ቤት የማሳወቅ ግዴታ አለበት ፡፡