#ጋብቻ
አሳስቢውን የጋብቻ ፍቺ ለመግታት ወደ ጋብቻ ከማምራት በፊት የጋብቻን መርህ ፣ ዓላማ ምንነት ጠንቅቆ ማወቅ ይገባል ሲሉ የጋብቻ እና ቤተሰብ አማካሪ ባለሞያው ተናገሩ።
የጋብቻ እና ቤተሰብ አማካሪ አቶ ይመስገን ሞላ ትዳራቸውን ለማትረፍ ምክር ፈልገው የሚመጡ ቤተሰቦች ከጊዜ ወደ ጊዜ ቁጥራቸው እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል።
የጋብቻ እና ቤተሰብ አማካሪው ምን አሉ ?
" የችግሩ አይነት እየበዛ እየጨመረ መጥቷል። በዚህም ቢሯችን የምናስተናግደው እንኳን አብዛኛው ችግር ሲገጥማቸው ለምክር የሚመጡ ናቸው ለመገንባት ከሚመጡ ይልቅ።
በሀገራችን ምክንያት ተብለው የሚሰጡ አሉ፦
- የመጀመሪያው በወሲብ አለመጣጣም ይባለል ፣
- በገንዘብ እጥረት ይባለል አብዛኛው የሚፋታው ግን ገንዘብ ሲያገኝ ነው፣
- የቤተሰብ ጣልቃ ገብነት / የጓደኛ ጠልቃ ገብነት ይባለል ይህም ቢሆን የግንኙነቱን ስስ መሆን ያሳያል፣
- የኮሚኒኬሽን ችግር ይባላል ፣
- አሁን እየጨመረ የመጣው የእምነት ጉዳይ ይነሳል በሁለቱ መካከል አለመተማመን አለ ምክንያት የሚባሉት እነዚህ ናቸው።
ለእኔ ግን ከዚህም በላይ ተጨማሪ ምክንያቶች አሉ ፦
- ያለን መንፈሳዊ እሴት መበላሸት አንድ ነገር ነው ፤
- በጾታዊ አክራሪነት የመጣው የወንድ እና የሴት ፆታ መገፋፋት ፣ አለመቀባበል በሁለቱ መካከል ያለው መተባበር ሳይሆን መፎካከር ስላለ፣ እንደ ባል እና ሚስት ሚናቸውን አለማወቃቸው ምክንያት ናቸው።
መጋባት ይፈልጋሉ ተዋደን ይሆናል ብለው መዋደድ ግን የጋብቻ መሰረት አይደለም ወይም ፍቅር ስላለ ጋብቻ መሰረት አያገኝም ውጤታማም አይሆንም። የጋብቻ መርህ አላማ፣ የጋብቻን ምንነት መረዳት ይጠይቃል። የነዚህ ሁሉ ድምር ውጤቶች ጋብቻ እንዳይፀና ቤተሰብ እንዲፈርስ ያደርጋል።
ወደ ጋብቻም ወደ ቤተሰብም የገቡ ሰዎች አስበው አይገቡበትም፤ ገብተው ምን እንደሚያደርጉ፣ ከመግባታቸው በፊት ምን መዘጋጀት እንዳለባቸው ስለማያውቁ ጋብቻው እንዳይዘልቅ ቤተሰብም እንዲፈርስ ዋነኛ ምክንያት ይሆናሉ። "
ባለሞያው ከቅርብ ጊዚያት ወዲህ ወደ ትዳር የሚገቡ #ወጣቶች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ገልጸው ከጋብቻ በፊት ስልጠና የመውሰድ ልምድም እያደገ ነው ብለዋል። ይህ ፍቺን ለመቀነስ ሚና እንዳለው ጠቁመው ከምንም በላይ ግን ቤተሰብ ልጆችን ሲያሳድግ አርያ መሆን አለበት ብለዋል።
ባለሞያው ፦
" ጋብቻ ብዙ ጊዜ እኛም ሀገር አይተን እንደሆነ ስመረቅ፣ ቤት ስገዛ ፣ስራ ስይዝ ብለው condition ያስቀምጣሉ ጋብቻ ግን Condition ሳይሆን Qualification ነው የሚጠይቀው። የበቃች ሚስት የበቃ ባል ለመሆን እራሱን አስቀድሞ ማዘጋጀት አለበት።
ለምሳሌ ፦ ባልነት ለበሰለ ወንድ ነው ኃላፊነት ለመሸከም ለበቃ ወንድ ነው ሚስትነትም እንደዛው ስለዚህ ከመዋደድ ያለፈ የመጋባት ምክንያትና ኃላፊነት የመወጣት አቅም ይጠይቃል። አንድ ወንድ ባል የሚሆነው ብስለቱና ብቃቱ ነው ወንድነቱ ብቻ ባል አያደርገውም። ስለዚህ ይህን ለማድረግ በግል እራስን መገንባት አለበት።
ወላጆች ልጆቻቸውን ለራሳቸው ጥሩ ልጅ፣ ለዛ ቤት ደግሞ ጥሩ ባልና ሚስት እንዲሆኑ፤ ሲወልዱ ጥሩ አባት እና እናት እንዲሆኑ ሞዴል መሆን አለባቸው።
አሁን የሚታየው የጋብቻ መፍረስ፣ የፍቺው ብዛት፣ የልጆች መጎዳት ትላንት ያልተሰራው ስራ መዘዝ ነው። ነገም እንደዚያ ይቀጥል ከተባለ ዛሬ እያንዳንዳችን የራሳችንን ቤት ጠብቀን ልጆቻችንን ለጋብቻ ማብቃት (የራሳችንን ጋብቻ በመጠበቅ)፣ ልጆቻችን እንዲሰለጥኑ ማድረግ ጋብቻን አውቀው እንዲኖሩ ማድረግ መፍትሄ ነው " ብለዋል።
ፁሁፍ በቲክቫህ ቤተሰብ አባላት።
Credit፦ ቪኦኤ (አስማማው አየነው)
@tikvahethiopia
አሳስቢውን የጋብቻ ፍቺ ለመግታት ወደ ጋብቻ ከማምራት በፊት የጋብቻን መርህ ፣ ዓላማ ምንነት ጠንቅቆ ማወቅ ይገባል ሲሉ የጋብቻ እና ቤተሰብ አማካሪ ባለሞያው ተናገሩ።
የጋብቻ እና ቤተሰብ አማካሪ አቶ ይመስገን ሞላ ትዳራቸውን ለማትረፍ ምክር ፈልገው የሚመጡ ቤተሰቦች ከጊዜ ወደ ጊዜ ቁጥራቸው እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል።
የጋብቻ እና ቤተሰብ አማካሪው ምን አሉ ?
" የችግሩ አይነት እየበዛ እየጨመረ መጥቷል። በዚህም ቢሯችን የምናስተናግደው እንኳን አብዛኛው ችግር ሲገጥማቸው ለምክር የሚመጡ ናቸው ለመገንባት ከሚመጡ ይልቅ።
በሀገራችን ምክንያት ተብለው የሚሰጡ አሉ፦
- የመጀመሪያው በወሲብ አለመጣጣም ይባለል ፣
- በገንዘብ እጥረት ይባለል አብዛኛው የሚፋታው ግን ገንዘብ ሲያገኝ ነው፣
- የቤተሰብ ጣልቃ ገብነት / የጓደኛ ጠልቃ ገብነት ይባለል ይህም ቢሆን የግንኙነቱን ስስ መሆን ያሳያል፣
- የኮሚኒኬሽን ችግር ይባላል ፣
- አሁን እየጨመረ የመጣው የእምነት ጉዳይ ይነሳል በሁለቱ መካከል አለመተማመን አለ ምክንያት የሚባሉት እነዚህ ናቸው።
ለእኔ ግን ከዚህም በላይ ተጨማሪ ምክንያቶች አሉ ፦
- ያለን መንፈሳዊ እሴት መበላሸት አንድ ነገር ነው ፤
- በጾታዊ አክራሪነት የመጣው የወንድ እና የሴት ፆታ መገፋፋት ፣ አለመቀባበል በሁለቱ መካከል ያለው መተባበር ሳይሆን መፎካከር ስላለ፣ እንደ ባል እና ሚስት ሚናቸውን አለማወቃቸው ምክንያት ናቸው።
መጋባት ይፈልጋሉ ተዋደን ይሆናል ብለው መዋደድ ግን የጋብቻ መሰረት አይደለም ወይም ፍቅር ስላለ ጋብቻ መሰረት አያገኝም ውጤታማም አይሆንም። የጋብቻ መርህ አላማ፣ የጋብቻን ምንነት መረዳት ይጠይቃል። የነዚህ ሁሉ ድምር ውጤቶች ጋብቻ እንዳይፀና ቤተሰብ እንዲፈርስ ያደርጋል።
ወደ ጋብቻም ወደ ቤተሰብም የገቡ ሰዎች አስበው አይገቡበትም፤ ገብተው ምን እንደሚያደርጉ፣ ከመግባታቸው በፊት ምን መዘጋጀት እንዳለባቸው ስለማያውቁ ጋብቻው እንዳይዘልቅ ቤተሰብም እንዲፈርስ ዋነኛ ምክንያት ይሆናሉ። "
ባለሞያው ከቅርብ ጊዚያት ወዲህ ወደ ትዳር የሚገቡ #ወጣቶች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ገልጸው ከጋብቻ በፊት ስልጠና የመውሰድ ልምድም እያደገ ነው ብለዋል። ይህ ፍቺን ለመቀነስ ሚና እንዳለው ጠቁመው ከምንም በላይ ግን ቤተሰብ ልጆችን ሲያሳድግ አርያ መሆን አለበት ብለዋል።
ባለሞያው ፦
" ጋብቻ ብዙ ጊዜ እኛም ሀገር አይተን እንደሆነ ስመረቅ፣ ቤት ስገዛ ፣ስራ ስይዝ ብለው condition ያስቀምጣሉ ጋብቻ ግን Condition ሳይሆን Qualification ነው የሚጠይቀው። የበቃች ሚስት የበቃ ባል ለመሆን እራሱን አስቀድሞ ማዘጋጀት አለበት።
ለምሳሌ ፦ ባልነት ለበሰለ ወንድ ነው ኃላፊነት ለመሸከም ለበቃ ወንድ ነው ሚስትነትም እንደዛው ስለዚህ ከመዋደድ ያለፈ የመጋባት ምክንያትና ኃላፊነት የመወጣት አቅም ይጠይቃል። አንድ ወንድ ባል የሚሆነው ብስለቱና ብቃቱ ነው ወንድነቱ ብቻ ባል አያደርገውም። ስለዚህ ይህን ለማድረግ በግል እራስን መገንባት አለበት።
ወላጆች ልጆቻቸውን ለራሳቸው ጥሩ ልጅ፣ ለዛ ቤት ደግሞ ጥሩ ባልና ሚስት እንዲሆኑ፤ ሲወልዱ ጥሩ አባት እና እናት እንዲሆኑ ሞዴል መሆን አለባቸው።
አሁን የሚታየው የጋብቻ መፍረስ፣ የፍቺው ብዛት፣ የልጆች መጎዳት ትላንት ያልተሰራው ስራ መዘዝ ነው። ነገም እንደዚያ ይቀጥል ከተባለ ዛሬ እያንዳንዳችን የራሳችንን ቤት ጠብቀን ልጆቻችንን ለጋብቻ ማብቃት (የራሳችንን ጋብቻ በመጠበቅ)፣ ልጆቻችን እንዲሰለጥኑ ማድረግ ጋብቻን አውቀው እንዲኖሩ ማድረግ መፍትሄ ነው " ብለዋል።
ፁሁፍ በቲክቫህ ቤተሰብ አባላት።
Credit፦ ቪኦኤ (አስማማው አየነው)
@tikvahethiopia