አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
#እርቅ በወንጀል ጉዳዮች ያለው ፋይዳ!

#አገራችን ኢትዬጲያ የበርካታ ብሄር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ፤ ቋንቋዎች ፣ ባህሎች እና ወጎች ፣ ያላት ሀገር ነች፤የሀገራችን ህዝቦች የየራሳቸውን የሆነ ባህል /ወግ፣ አለባበስ እንዲሁም አገር በቀል የሆነ የዕርቅ፣ የሰላም መጠበቂያ እና የሰላም ግንባታ ስነ-ዘዴዎችም ያሏቸው ህዝቦች ናቸው፤ሀገር በቀል የሰላም መስሪያ ፣ የሰላም መጠበቂያና የሰላም ግንባታ ዘዴ የምንለው ኢ-መደበኛ የሆነው እና ማህበረሰቡ ከአያት ቅድመ አያቶቹ የወረሰው ሰነ-ዘዴ ነው፡፡

#በመሆኑም በእንግሊዘኛው አጠራር non-state based customary institutions የሚያመላክት ሆኖ በዚህ የሰላም እና የፍትህ ስርዓት በዳኝነት የሚቀመጡት መንግስት የሾማቸው ዳኞች ሳይሆኖ ማህበረሰቡ አምኖና ተቀብሎ ለዳኝነት የሾማቸው ባለ ልዪ ተስጦኦ የሆኑ የዕድሜ ባለፀጋ ሽማግሌዎች፤ባህላዊ መሪዎች እና ሀይማኖት አባቶች ሲሆኑ በዚህ ሂደት ውስጥም ትልቅ ሚና ይጫወታሉ፡፡

ይህ መልካም የሆነ ታሪክ እና ባህል በቂ ነው ባይባልም በህጉም እውቅና ተሰጥቶት የነበረ ሲሆን በፍርድ ቤቶችም ጭምር በወንጀል አድራጊው እና ተበዳይ መካከል እርቅ ሲበረታታ ይታያል፡፡ በሁሉም የወንጀል አይነቶች እርቅ መታረቅ ያልተከለከለ ሲሆን ነገር ግን እንደወንጀሉ አይነት እና በጠቅለላዉ እርቁ ፍትህን የማያረጋግጥ በሆነ ጊዜ ከሆነ እርቁ ተፈጻሚ የማይደረግ ሲሆን ነገር ግን ከተፈፀመው ወንጀል ክብደት አንጻር ፍ/ቤቶች ፍርድ ከሰጡ በኀላ ለቅጣት ማቅለያነት ይጠቀሙታል፡፡

#በወንጀል ህጉ በእርቅ ሊያልቁ የሚችሉ ወንጀሎችን በአፈፃፀሙ እና ቅጣቱ ቀላል በመሆኑ የህብረተሰቡን ሰላም እና መልካም ግንኙነት ተጠብቆ ለማቆየት እንደሚጠቅም ተመልክተዋል፡፡
ሌላው በወንጀል ጉዳይ የመታረቅ ጥቅሙ፡ -የመዝገብ ክምችትን ይቀንሳል፣ ከእስራት ይልቅ በእርቅ ማለቁ ለሁለቱም ወገን ዘላቂ ሰላም ያመጣል፣ በወንጀል አድራጊው ላይ የባህሪ ለውጥ ሊመጣ ስለሚችል፣ እንዲሁም የፍርድ ቤቶችን የስራ ጫና እና የተከራካሪዎችን ግዜ ፣ ወጭ እና ጉልበት ያቀላል፡፡

#ከዘህም ባሻገር እርቅ ቀጣይነት ያለውን ሰላም በማስፈን፣የተጎዳን በመካስ ብሎም ሁለንተናዊ የሆነ ማህበራዊ ተግባቦትን በመመለስ ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው፡፡ ነገር ግን እርቅና የተለያዩ አማራጭ የግጭት መፍቻ ሀገር በቀል እውቀቶችና ስርዐቶች እየተረሱና እየተሸረሸሩ በመሄዳቸው በአገራችን በተለያዩ አካባቢዎች በተፈጠሩ ግጭቶችና አለመግባባቶች ምክንያት በርካታ ዜጎች ለመፈናቀል ለሞት እና ለንብረት ውድመት ሰለባ የሆኑባቸው አጋጣሚዎች ተከስተዋል፡፡

#በመሆኑም በአገር በቀል የግጭት አፈታት እና የዕርቅ ሥርዓቶች ላይ ትኩረት በማደረግ ወደ ቦታቸው መመለስ እንዲሁም በህግ ማዕቀፎቻችንም በሰፊው እንዲካተቱና እውቅና እንዲያገኙ ማድረግ ህብረተሰቡን በሰፊው የሚጠቅም ከመሆኑም በላይ በፍትህ ዘርፉ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመሠረታዊነት የሚፈታ በመሆኑ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፡፡

#ድሬዳዋ ፍትህ ፀጥታና ህግ ጉዳዬች ቢሮ
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ
#Share #ሼር
#አለ_ህግ #Alehig
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties

https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ 
ይህንን ሊንክ ተከትለው #አለ_ህግ  የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራብ እና ሼር አድርጉልን
አለ_ህግ 

https://youtube.com/@Lawsocieties

subscribe and share Ale_Hig YouTube channel.
Coming soon 🔜🔜🔜🔜🔜
https://youtube.com/@Lawsocieties
https://youtube.com/@Lawsocieties
#አለ_ህግ  የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራብ እና ሼር አድርጉልን አለ_ህግ  የተሰኘ ፕሮግራም በቅርቡ ይዘንላቸወሁ እየመጣን ነው🔜🔜🔜

https://youtube.com/@Lawsocieties

subscribe and share Ale_Hig YouTube channel.
Coming soon 🔜🔜🔜🔜🔜
https://youtube.com/@Lawsocieties
https://youtube.com/@Lawsocieties
ሰ.መ.ቁ 193295 ሐምሌ 29 ቀን 2014 ዓ.ም

የወንጀል ሕግ አንቀጽ 419(1)(ሀ)(ለ) ጋር በተያያዘ በዓቃቤሕግ እና በተከሳሹ ላይ የተጣለው የማስረዳት ሸክም ተፈጻሚነቱ በተከሳሹ ላይ የቀረበው ክስ ተከሳሹ ራሱ የሚኖርበትን የኑሮ ደረጃ፤ በተከሳሹ በራሱ ስም የተገኘውን ንብረት ወይም ገንዘብ ብቻ የሚመለከት በሆነ ጊዜ ነው፡፡

የወንጀል ሕግ አንቀጽ 419(1)(ሀ)(ለ) ድንጋጌ የመንግስት ሠራተኛ የሆነ ወይም የነበረ ማንም ሰው የኑሮ ደረጃው አሁን ባለበት ወይም አስቀድሞ በነበረበት የመንግስት ሥራ ወይም በሌላ መንገድ ከሚያገኘው ወይም ሲያገኝ ከነበረው ሕጋዊ ገቢ የበለጠ እንደሆነ ወይም ያለው ንብረት ወይም የገንዘብ ምንጭ አሁን ባለበት ወይም አስቀድሞ በነበረበት የመንግስት ሥራ ወይም በሌላ መንገድ ከሚያገኘው ወይም ሲያገኝ ከነበረው ሕጋዊ ገቢ ጋር የማይጣጣም እንደሆነ የዚህ ዓይነቱ የኑሮ ደረጃ እንዴት ሊኖረው እንደቻለ ወይም የገንዘብ ምንጩ በእጁ እንዴት ሊገባ እንደቻለ ለፍርድ ቤቱ ካላስረዳ በቀር በድንጋጌው የተመለከተውን ቅጣት ይቀጣል በማለት ይደነግጋል፡፡
ከድንጋጌው ይዘት መገንዘብ የሚቻለው ከሳሽ የሆነው ዓቃቤሕግ ማስረዳት የሚጠበቅበት ተከሳሹ የመንግስት ሠራተኛ ሆኖ ሲያገኝ የነበረውን የገቢ መጠን ማሳወቅ ሌሎች የገቢ ምንጮች ካሉ ማሳየት እና ኑሮው ወይም ሀብቱ ከገቢው ጋር ሲነጻጸር ያልተመጣጠን መሆኑን ማስረዳት ሲሆን በተቃራኒው ደግሞ ተከሳሹ አሁን ያለው የኑሮ ደረጃ እንዴት ሊኖረው እንደቻለ ወይም ያለው ንብረት ወይም የገንዘብ ምንጭ በእጁ እንዴት ሊገባ እንደቻለ የማስረዳት ሸክሙ ወደ ተከሳሹ የሚዞር መሆኑን ነው፡፡ ሆኖም ይህ በዓቃቤሕግ እና በተከሳሹ ላይ የተጣለው የማስረዳት ሸክም ተፈጻሚነቱ በተከሳሹ ላይ የቀረበው ክስ ተከሳሹ ራሱ የሚኖርበትን የኑሮ ደረጃ፤ በተከሳሹ በራሱ ስም የተገኘውን ንብረት ወይም ገንዘብ ብቻ የሚመለከት በሆነ ጊዜ ነው፡፡
BDU-JL Vol 13 No 1.pdf
3.6 MB
በሕግ አውጭው በኩል ለብዙ ዘመናት ያገለገለውን የኢትዮጵያ ከውል ውጭ ኃላፊነት ሕግ እንዲሁም የታክስ ሕግጋትን የማሻሻል ዕቅድ አለ፡፡ ለዚህም ይረዳ ዘንድ በUSAID ፍትሕ ፕሮጀክት የገንዘብ ድጋፍ ጥናት ተካሄዷል፡፡ በጥናቱ ከሕግ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ተመራማሪዎች ተሳትፈዋል ፡፡ የጥናቱ ዉጤት ከውል ውጭ ኃላፊነት ሕግን እና የታክስ ሕግጋትን ለማሻሻል ለሕግ አውጭዎች እና ለፖሊሲ አርቃቂዎች ዐብይ ግብዓት ይሆናል፡፡ የእነዚህ ጥናቶች አጭርና ጥቅል የውጤት መግለጫ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሕግ መጽሔት ቅጽ 13 ቁጥር 1 ታትሟል፡፡

የእነዚህን ጥናቶች ጥቅል የውጤት መግለጫ ከተያያዘው ፋይል ማግኘት ይችላሉ፡፡
https://t.me/lawsocieties
221476 የአደራ ውል.pdf
802.3 KB
ገንዘብ በባንክ የተላከበት የባንክ ሐዋላ ወረቀት የብድር ውል ሆነ የአደራ ውል መኖሩን ለማስረዳት በቂ አይደለም።
ሰ/መ/ቁጥር 221476 ጥቅምት 28 ቀን 2015 ዓ/ም
የባንክ ሐዋላ ወረቀት የብድር ውል መኖሩን የሚያስረዳ ማስረጃ ተደርጎ ሊወሰድ እንደሚገባ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 31737 ላይ የህግ ትርጉም መሰጠቱ ይታወቃል፡፡ ነገር ግን በመዝገብ ቁጥር 150290 በሐምሌ 23 ቀን 2010 ዓ.ም እና በሌሎች በርካታ መዝገቦች በተሰጠ ውሳኔ የባንክ የገንዘብ መላኪያ ሰነድ ገንዘብ መላኩን ከማስረዳት ውጪ በምን ምክንያት ገንዘቡ መላኩን ወይም ገንዘቡ በብድር የተሰጠ መሆኑን ሊያስረዳ እንደማይችል የህግ ትርጉም ተሰጥቷል፡፡ በመሆኑም በሰበር መዝገብ ቁጥር 31737 የተሰጠው የህግ ትርጉም በመዝገብ ቁጥር 150290 እና ሌሎች በርካታ መዝገቦች ላይ በተሰጠ ውሳኔ ተቀይሯል።
https://t.me/lawsocieties
220830.pdf
825.3 KB
ከባንክ ሂሳቤ ላይ ገንዘብ አላአግባብ ወጪ በመደረጉ ባንኩ ገንዘቡን እንዲመልስ የሚል ክስ ሲቀርብ የፎረንሲክ ምረመራውን ውጤት ብቻ መሠረት በማድረግ ባንኩን ለክሱ ኃላፊ ማድረግ መሰረታዊ ስህተት ነው።
ሰ/መ/ቁ. 220830 ጥቅምት 29 ቀን 2015 ዓ/ም
በወጪ ማዘዣው ላይ የተመለከተዉ ፊርማ በሲስተሙ ላይ ከተመለከተዉ የፊርማ ናሙና ጋር ተመሳሳይ መሆን አለመሆኑን ለማረጋገጥ የወጪ ማዘዣው ላይ የተመለከተዉ ፊርማ ከናሙና ፊርማ ጋር የሚመሳሰል መሆን አለመሆኑ ገለልተኛ በሆነ አካል ታይቶ መረጋገጥ ይኖርበታል።
በመሆኑም ክስ ከቀረበበት ባንክ ዉጪ በሌሎች ባንኮች ከወጪ ማዛዣ ክፍያ ጋር በተያያዘ ልምድ ባላቸዉ የባንክ ባለሙያዎች እንዲታይ በማድረግ ባንኩ ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ ግዴታዉን የተወጣ መሆን አለመሆኑ ማረጋገጥ ይገባል፡፡ የባለሂሳቡ ባንክ ደብተር ቀርቦ ሂሳቡ ተቀንሶ የተጻፈ መሆን አለመሆኑ ሆነ የባለሂሳቡ መታወቂያ በማየት ባንኩ ያረጋገጠ መሆን አለመሆኑ ደግሞ በሰው ማስረጃ ሆኖ የባንክ ሂሳብ ደብተሩ ካለ በማስቀረብ መረጋገጥ ይኖርበታል።
https://t.me/lawsocieties
የግብር አከፋፈል መረጃ ‼️

***

የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህ
በር የተያዘውን አመት የጠበቆችና የህግ አማካሪዎች የግብር አከፋፈል ሁኔታ ላይ እየገጠሙ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር ተከታታይ ውይይቶች ሲያደርግ መቆየቱ የሚታወስ ነው::

- በዚሁ መሰረት የደረጃ -ሐ ግብር ከፋይ የሆናችሁ ጠበቆችና የህግ አማካሪዎች ከዛሬ ጀምሮ በየቅርንጫፎቻችሁ በመገኘት ግብራችሁን በማሳወቅ እንድትከፍሉ ከመግባባት ላይ የተደረሰ መሆኑን እናሳውቃለን::

በየቅርንጫፉ በምትስተናገዱበት ወቅት ከሂሳብ መዝገብና መሰል ተጨማሪ ምክንያቶችን የሚያቀርቡ ባለሙያዎችና ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች ካሉ ማህበሩ ለመደባቸው ከዚህ ለሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች በስራ ሰአት ብቻ ወዲያውኑ ሪፖርት እንድታደጉ እናሳስባለን:: የስልክ ቁጥሮች:
              1ኛ) 0913- 66 1578 
             2ኛ) 0915- 58 1888

በሌላ በኩል የደረጃ - ለ  እና
                    የደረጃ -ሀ ግብር ከፋዮች በተመለከተ ማህበሩ እያደረገ ያለውን ያላሰለሰ ጥረት ቀጥሎ በሚቀጥለው ሳምንት አጋማሽ ከባለድርሻ አካላት ጋር በሚደረግ ቀጣይ ውይይቶች መደምደሚያ ላይ የምንደርስ ሆኖ ፤  የሚደረስበትን ውጤት በተመሳሳይ የምናሳውቅ መሆኑን እንገልፃለን::

የደረጃ - ለ  እስከ ጳግሜ 05 ቀን 2015ዓ.ም እንዲሁም የደረጃ -ሀ ግብር ከፋዮች እስከ ጥቅምት 30 2016 ዓ.ም ድረስ ግብር የሚከፈል መሆኑን እያስታወስን ቀሪ የደረጃ - ሐ ግብር ከፋዮች የግብር ግዴታችሁን በአግባቡ እንድትወጡ ማህበሩ ከአደራ ጭምር ያሳስባል::

መረጃውን #share በማድረግ ላልደረሳቸው እንድታሳውቁ እንጠይቃለን::

የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
ሀምሌ 20 ቀን 2015ዓ.ም
አዲስ አበባ ፤

https://t.me/lawsocieties
#Concept_Note _አሰራር

አንድ ጥናት ወይም ፈንድ ለማፈላለግ ከሚሰራ ፕሮጀክት (ከፕሮፖዛል በፊት) በፊት የሚዘጋጅ ሃሳባዊ መግለጫ ሲሆን ከተቻለ በአንድ ገጽ ካልተቻለ በሁለት ገጽ እንዲሆን ይመከራል (ነገር ግን እንደ ተቀባይ ድርጅት ወይም የትምህርት ተቋም የገጽ መጠኑ በጥቂቱ ከፍ ሊል ይችላል)፡፡

ርዕስ

1.የፕሮጀክት ፈንድ ፍቃድ (የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ ለመጠየቅ የሚሰራ) አልያም ለመስራት የምታስቡትን ማንኛውም የጥናት ርዕስ በተገቢው መጥቀስ::

መግቢያ (Introduction)

1.ለመስራት ያሰባችሁት ጥናት አልያም የፕሮጀክት ፈንድ ፍቃድ ጥያቄ ጭብጥ በአጭሩ ማስረዳት፤

2.የጥናቱን ወይም የፕሮጀክት ፈንድ ፍቃድ ጥያቄ አስፈላጊነት በአግባቡ ማስረዳት፤

3.የጥናቱን ወይም የፕሮጀክት ፈንድ ፍቃድ ጥያቄ ስለሚፈታቸው ችግሮች ወይም ስለሚያረጋግጠው ጉዳይ ማስረዳት፤

4.እንደ አስፈላጊነቱ ከማህበራዊ፤ ፖለቲካዊ፤ ኢኮኖሚያዊ እና አካባቢያዊ ፋይዳዎች አንጻር ምን እንደሚመስል ማስረዳት፤

ዓላማ (Objectives)

1.ዋና የጥናቱ ውጤት መግለጫ ዓላማ (General Objective) እና ትክክለኛ ገላጭ የሆኑ ዝርዝር ዓላማዎች (Specific Objectives) መግለጽ፤

የጥናት ስልት (Research Methodology)

1.የታሰበውን ጥናት ከክፍተት መነሳቱን ማረጋገጥ (Research Gaps)፤

2. የታሰበውን ጥናት ትክክለኛ ስልት (Research Design) ማቅረብ፤

3. የታሰበውን ጥናት ትክክለኛውን የናሙና አመራረጥ/ስብጥር ስልት ማቅረብ፤

4.የታሰበውን ጥናት የውጤት ትንተና ስልቶቹ (Data Analysis Methods) ትክክለኛነት ማረጋገጥ፤

5.የታሰበውን ጥናት የጥናቱን ጥራት (Validity እና Reliability) ስለሚረጋግጥበት መንገድ ማስረዳት፤


የሚጠበቅ ውጤት (Impact)

1.ከታሰበው ጥናት ይመጣሉ የሚባሉ ውጤቶች እንዴት እንደሚለኩ ማስረዳት፤

2. የሚመጣውን ጥናት ግኝት እንዴት ወደ ተጠቃሚዎች ማስተላለፍ እንደሚቻል ማስረዳት፤


የጊዜ እና የወጪ ሰሌዳ (Work Plan and Budget Schedule)

1.ትክክለኛ የጥናቱን እና የፕሮጀክቱን የጊዜ ሰሌዳ መግለጽ፤

2.ለጥናቱ ወይም ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልግ የበጀት ዝርዝር ማቅረብ፤

ዋቢ ጽሁፍ (Reference)

1. በአጭር ሰነድ ውስጥ የተጠቀማችሁት ዋቢ ካለ ትክክለኛ መንገዱን ተከትሎ መጥቀስ፤
Via #WaseAlpha

#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
በቸልተኝነት መንገድ የሚሻገር ሰውን በመኪና ገጭቶ መግደል የሚያስከትለው ውጤት በሰበር ሰሚ ችሎት የተሰጠ የህግ ትርጉም:- 👇👇🛑 Via #ethiolawtips
ኑዛዜን መቃወም የሚቻልበት የግዜ ገደብ በፍታብሔር የውርስ ሕግ ሙሉ አይታ/ጠበቃ/
👇👇👇👇👇👇👇👇
ውድ አንባቢዎች እንዴት ሰንበታችኋል!አንድ ሰው በህይወት ዘመኑ ያፈራውን ንብረት በኑዛዜ ለወራሾቹ ማስተላለፍ የሚችል ስለመሆኑ በፍታብሔር ሕጉ ተደንግጎ ይገኛል፡፡

ኑዛዜ በሚደረግበት አግባብ /ፎርማሊቲ/ መሰረት በግልጽ የሚደረግ ፤በተናዛዡ ጽሁፍ የሚደረግ እና በቃል የሚደረግ ኑዛዜ ተብሎ በሶስት ይከፈላል፡፡በግልጽ የሚደረግ ኑዛዜ ተናዛዡ እየተናገረ ማናቸውም ሌላ ሰው የሚጽፈው ሲሆን በ 4 ምስክሮች ፊት ወይንም ውል ለማዋዋል ስልጣን ባለው ተቋም ቀርቦ ከተደረገ በሁለት ምስክሮች ፊት ካልተደረገ ፈራሽ ነው፡፡
በተናዛዡ ጽሁፍ የሚደረግ ኑዛዜ ተናዛዡ ራሱ በሙሉ ካልጻፈው ፈራሽ ይሆናል፤ተናዛዡ በኮምፒዩተር የሚጽፈው እንደሆንም እያንዳንዱ ገጽ ላይ በእጅ ጽሁፍ ራሱ የጻፈው መሆኑን ካላረጋገጠ በቀር ፈራሽ ይሆናል፡፡በቃል የሚደረግ ኑዛዜ ተናዛዡ የሞቱ መቅረብ ተሰምቶት በሁለት ምስከሮች ፊት የሚያደርገው የኑዛዜ አይነት ሲሆን ግምቱ ከብር 500 ከሆነ ንብረት በላይ በቃል ኑዛዜ ማስተላለፍ አይቻልም፡፡
አንድ ሰው ከላይ ከተቀመጡት በአንዱ ፎርም ንብረቱን እና የንብረቱን አስተዳደር፤የቀብር ስነስርዓት አፈጻጸሙን፤አካለመጠን ያላደረሱ ልጆቹን አስተዳደግን እና የመሳሰሉትን አስመልክቶ በኑዛዜ ማስተላለፍ እና ግዴታዎችን ማስቀመጥ የሚችል ሲሆን ሟች ያደረጋቸው ኑዛዜዎች ተፈጻሚ እንዲሆኑ በሕጉ ላይ የተቀመጡ ፎርማሊቲዎች እና ሕጉ ግዴታ አድርጎ ያስቀመጣቸውን ድንጋጌዎች የተላለፈ እንደሆነ ኑዛዜው ፈራሽ እንዲሆን ኑዛዜው ጥቅሜን ጎድቶኛል የሚል ማንኛውም ሰው ሊጠይቅ ይችላል፡፡በውርስ ሕጉ ከተቀመጡ አስገዳጅ ሁኔታዎች መካከል ሟች ወደታች የሚቆጠር ተወላጅን ተቀባይነት ካለው ምክንያት ውጪ ከውርስ ሐብቱ ምንም እንዳያገኝ በማድረግ ከውርስ በመንቀል ወይንም በሕጉ ከሚያገኘው 1/4ኛ በታች እንዲያገኝ በማድረግ በኑዛዜ ሐብቱን ማከፋፈል አይፈቀድለትም፡፡ይህ በሆነ ግዜም ክፍፍሉ ጎድቶኛል ወይንም ከውርስ ተነቅዬያለሁ የሚለው ተወላጅ ኑዛዜው እንዲፈርስ ሊጠይቅ ይችላል፡፡
ታዲያ ሟች ያደረገው ኑዛዜ አይጸናም በሚል የሚቀርብ ክስ በማንኛውም ግዜ የሚቀርብ ሳይሆን በሕጉ በተቀመጠ የግዜ ገደብ ውስጥ ያልቀረበ እንደሆነ ጥያቄው በይርጋ ይታገዳል፡፡ይርጋ በሕግ ተለይቶ ከተቀመጠው የግዜ ገደብ በኋላ በአንድ ጉዳይ ክስ ለማቅረብ የሚከለከልበት የሕግ ጽንሰ ሀሰብ ሲሆን ይርጋ ያስፈለገበት ምክንያትም ከሳሽ በተገቢ ትጋት  መብቱን እንዲጠይቅ ለማስቻል /ለማንቃት እና ተከሳሽም ዘግይተው የሚመጡ ክሶችን ለመከላከል ማስረጃ እንዳያጣ ብሎም ዘግይተው የሚቀርቡ ክሶች ፍትህን ከማስገኘት ይልቅ ለማጥቂያ በመሳሪያነት እንዳይውሉ ለመከላከል መሆኑን የህግ ምሁራን ይገልጻሉ፡፡
በፍታብሔር ሕጉ አንቀጽ 973 አንድ ኑዛዜ ሲነበብ የነበሩ ወይም የተወከሉ ወራሾች በኑዛዜ የተነገረው ቃል አይጸናም ሲሉ ክስ የሚያቀርቡበትን የግዜ ገደብ አስቀምጧል፡፡በዚህ ድንጋጌ መሰረት ኑዛዜ ሲነበብ የነበሩ ወይንም የተወከሉ ሰወች ኑዛዜው አይጸናም የሚሉ እንደሆነ ይህንኑ ክስ የማቅረብ ሐሳባቸውን ለውርስ አጣሪው፤ለዚሁ ለተወከሉ ሽማግሌዎች ወይንም ለዳኞች ኑዛዜው በፈሰሰ / በተነበበ / በ15 ቀን ግዜ ውስጥ ማቅረብ ያለባቸው ሲሆን ይህ የግዜ ገደብ ለፍርድ ቤት ክስ የማቅረቢያ ግዜ ሳይሆን ክስ የማቅረብ ሀሳብን መግለጫ የሚሰጥበት ግዜ መሆኑን እና መግለጫው ከተሰጠ ወይንም በኑዛዜው ውስጥ የሰፈረው  ከታወቀበት ግዜ አንስቶ በ 3 ወር ግዜ ውስጥ ክስ ያልቀረበ እንደሆነ ኑዛዜውን አስመልክቶ የሚቀርብ ክስ በይርጋ የሚታገድ መሆኑን ድንጋጌውን አስመልክቶ የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ 82585 አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ ሰጥቶበታል፡፡
ኑዛዜው ሲነበብ ያልነበሩ እንዲሁም ስለኑዛዜው መኖር ያላወቁ ሰወች ኑዛዜው ከተነበበ ከ 5 ዓመት በኋላ ስለ ኑዛዜው መጽናትም ሆነ ስለ ክፍያ አመዳደብ መቃወሚያ ማቅረብ አይችሉም፡፡በሌላ በኩል ሟች ያደረገው ኑዛዜ ተወላጅን ከውርስ የመንቀል ውጤት ያለው በመሆኑ እና ማግኘት ከሚገባው ከ1/4ኛ በታች እንዲያገኝ ያደረገ በመሆኑ እንዲፈርስ በሚል የሚቀርብ የዳኝነት ጥያቄ የሚታየው በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1123 መሰረት መሆኑን እና በ2 ዓመት ግዜ ውስጥ ጥያቄው ያልቀረበ እንደሆነ በይርጋ የሚታገድ ስለመሆኑ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ 152134 አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ ሰጥቶበታል፡፡
በስተመጨረሻም ሟች ያደረገው ኑዛዜ በተናዛዡ ንብረት ላይ ሳይሆን  በሌላ ሰው ንብረት ላይ መሆኑን ወይንም የሌላ ሰው ንብረት በኑዛዜው ላይ የተካተተ መሆኑን በመጥቀስ በባለንብረቱ የሚቀርብ የኑዛዜ ይፍረስልኝ ክስ ከላይ በተጠቀሱት ድንጋጌዎች መሰረት በይርጋ የማይታገድ ስለመሆኑ የሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ 53223 አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ ሰጥቶበታል፡፡
ውድ አንባቢዎች ከዚህ በላይ የተጠቀሱት ኑዛዜ አይጸናም በሚል ክስ የሚቀርብበት የግዜ ገደብን አስመልክቶ በፍታብሔር ሕጉ ውስጥ የተጠቀሱ የይርጋ ድንጋጌዎች የሰበር ሰሚ ችሎት ድንጋጌዎቹን አስመልክቶ ከሰጠው አስገዳጅ የህግ ትርጓሜ ጋር በማገናዘብ የቀረበ ሲሆን በሸሪአ ሕጉ የውርስ መብትን መጠየቅ የሚያበቃበት የግዜ ገደብ /የይርጋ ጽንሰ ሐሳብ መኖሩን፤ስለ ይርጋ መርህ ፍትሀዊነት እና ሌሎችም  ተመሳሳይ ጉዳዮችን አስመልክቶ በሸረአ ሕግ ምሁር በሆኑት ኡስታዝ ሙስጠፋ ሐሚድ ሳምንት የሚቀርብ ይሆናል፡፡መልካም ሳምንት!


#አለ_ህግ #Ale_Hig #Lawsocieties
#ሼር #Share
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
ውልና ማስረጃ ምን አለ
በየትኛውም ቦታ ሁነው ሰነዶች ማረጋገጫ(ውልና ማስረጃ) ጉዳይ አላችሁ
👉ውክልና
👉 ብድር ውል
👉 የሺያጭ ውል
👉ቃለ ጉባዔ
👉ሼር መግዛት /መሸጥ..........

ሌሎችንም አገልግሎት በአካል መገኘት ሳይጠበቅብዎች በአሉበት ቦታ ሁነው መረጃውን ይሰጡና በባለሙያ ተፅፎ በቴሌግራም፣ ዋትስአፕ ወይም በኢሜል ይላክላችኋል።
ከእናንተ የሚጠበቀው ፕሪንት አድርጎ ወደ ሰነዶች ማረጋገጫ በመሄድ ምን ጊዜ ሳያባክኑ አገልግሎት ማግኘት ብቻ።
ስለ አስፈላጊ ሰነድ መረጃ በነፃ ይገኛሉ።
ይደውሉ:- 0909039999
የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት (ውልና ማስረጃ) ሲፈልጉ
Emails:-
admin@entrustconsult.com
info@entrustconsult.com
consultantentrust@gmail.com
1. Power of attorney/ውክልና
2. Any contracts/ውል
3. Sales agreement/የሺያጭ ውል
4. Loan agreement/የብድር ውል
5. Share transfer or sales/ሼር ማስተላለፍና መሸጥ
6. Car and house sales agreement/ቤትና መኪና የመሸጥ እና የመግዛት ውል

- Do you need a power of attorney to act on your behalf in legal matters?
Don't worry, we have you covered. Just provide us with the information and we will write a professional power of attorney for you and send it to you via Telegram, WhatsApp or email.
You can print it and go to document authentication and registration service (DARS) within 15 days to get it validated. Call us at 0909039999 for more details.

- Whether you are starting a new business, hiring an employee, renting a property, or buying a car, you need a contract to protect your rights and obligations. But writing a contract can be time-consuming and complicated. That's why we offer you a convenient and affordable service to write any contract for you online.

Just provide us with the information and we will write a customized contract for you and send it to you via Telegram, WhatsApp or email. You can print it and go to document authentication and registration service (DARS) within 15 days to get it signed. Call us at 0909039999 for more information.

- Are you looking for a sales agreement to sell or buy goods or services? We can help you with that. Just provide us with the information and we will write a clear and concise sales agreement for you and send it to you via Telegram, WhatsApp or email. You can print it and go to document authentication and registration service (DARS) within 15 days to get it finalized. Call us at 0909039999 for more assistance.

- Do you need a loan agreement to borrow or lend money? We can help you with that too. Just provide us with the information and we will write a secure and fair loan agreement for you and send it to you via Telegram, WhatsApp or email. You can print it and go to document authentication and registration service (DARS) within 15 days to get it approved. Call us at 0909039999 for more support.

- Do you want to transfer or sell your shares in a company?
We can help you with that as well. Just provide us with the information and we will write a valid and legal share transfer or sales agreement for you and send it to you via Telegram, WhatsApp or email. You can print it and go to document authentication and registration service (DARS) within 15 days to get it executed.
Call us at 0909039999 for more guidance.

- Do you want to sell or buy a car or a house?
We can help you with that also. Just provide us with the information and we will write a comprehensive and accurate car or house sales agreement for you and send it to you via Telegram, WhatsApp or email. You can print it and go to document authentication and registration service (DARS) within 15 days to get it completed.
Call us at 0909039999 for more advice.

- Do you want to make a testament to distribute your assets after your death?
We can help you with that too. Just provide us with the information and we will write a lawful and effective testament for you and send it to you via Telegram, WhatsApp or email. You can print it and go to document authentication and registration service (DARS) within 15 days to get it witnessed.
Call us at 0909039999 for more consultation.

We also offer free information about important documents on our website https://t.me/EntrustConsultant
. Don't hesitate to contact us if you need document verification and registration service.
We are here to serve you online anytime, anywhere! 😊
Forwarded from PIN NGO
Public Information Noble(PIN) ፐብሊክ ኢንፎርሜሽን ኖብል #ፒን is an NGO/CSO, Public Information Noble (PIN) is an NGO/CSO https://www.pinngo.org
working on the right to access information.
"Information is a key_let's promote access to all"
The NGO is looking for 22 volunteers from all professional background to work on Access to Information in Ethiopia.
The NGO aims to promote the right of all persons to seek, obtain and communicate any information held by public bodies.
The government has the responsibility to share information on request, except for a few information, namely third-party information, information that endangers the country's defense, security and international relations, and some information that is required by law to be kept secret. The volunteers will be engaged in the access to information in all government service providers and other sectors.
Although there is no salary, all volunteers will be certified.......

Follow us vis the following social medias:
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

Website:👇👇👇👇👇
https://www.pinngo.org

Telegram: 👇👇👇👇
https://t.me/PublicInformationNoble

Twitter :👇👇👇👇👇
https://twitter.com/PINNGO_et?t=xKZd2ejDdUIKvS4bkrdZ5A&s=09

Facebook: 👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/PublicInformationNoble?mibextid=ZbWKwL

Emails:
support@pinngo.org


publicinformationnoble@gmail.com
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
የመኪና ሽያጭ፡ የመኪና ሽያጭን በተመለከተ ሻጭ ከመኪናው ጋር በተገናኘ ከመኪናው ጋር የተያያዙ አስፈላጊ ሰነዶችን ለገዥ አሟልቶ ያስረከበ መሆኑ ከተረጋገጠ ገዥ ስመ ኃብቱ በስሜ አልተዘዋወረም በሚል ምክንያት ብቻ ውሉ እንዲፈርስ የሚያቀርበው አቤቱታ ተቀባይነት የሌለው ሲሆን ስመ ሀብቱን ለማዞር አስፈለጊ ሁኔታዎችን አሟልቶ ስም እንዲዘዋወርለት ለሚመለከተው የአስተዳደር አካል ጥያቄ አቅርቦ መብቱ ሊረጋገጥለት ያልቻለ ሰው መብቱን የሚያስጠብቀው በሚመለከተው አከል ላይ በፍርድ ቤት ክስ በመመስረት እንጂ ውሉ እንዲፍርስለት በመጠየቅ አይደለም::
ቅጽ 12; ሰ/መ/ቁ 56569
በሠራተኛ ቅጥር ሂደት ስለሚፈፀም የኋላ ታሪክ ፍተሻ፣ አስፈላጊነት እና ሕጋዊነት
By: ኃይለማርያም ይርጋ

ይህ ጽሑፍ በቅጠር ወቅት የኋላ ታሪክ ፍተሻ አስፈላጊነት፣ በሃገራችን ተግባሩን የሚፈቅድ ወይም የሚከለክል ሕግ ስለመኖሩ፣ የሕግ ወሰን ወይም ቅድመ ሁኔታ ከኖረ ይህንኑ አክብሮ የኋላ ታሪክ ፍተሻ ስለሚደረግበት ሁኔታ አግባብነት ካላቸው የሃገራችን ሕጎችን አንፃር ይመለከታል።

https://www.abyssinialaw.com/blog/the-need-to-background-check-on-recruiting-employees