አዲስ ለተወለደ ህፃን ልጅ ስም የማውጣት መብት፤ የእናት ወይስ የአባት?
የሕግ ባለሙያዎች ወግ
በአቤል ልዑልሰገድ አበበ
ከሰሞኑ በአንድ ጠበቆች፣ ዳኞች፣ ዓቃቢያነ ሕግች፣ የሕግ ምሁራን እና የሴቶች መብት አቀንቃኞች የተገኙበት የሴቶች እኩልነት እና ሰብዓዊ መብቶች በሚል ርእስ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ ተገኝቼ ሳለሁ፤ አንዲት ተሳታፊ ጠበቂት ሃሳቧን ስታጋራ ለህፃን ስያሜ የመስጠት መብት የወላጆች የጋራ መብት ነው ብላ በደፈናው ተናግራ ስትጨርስ የውይይቱ መሪ ይህን ሀሳብ በሕግ የተደነገገ መብት ነው ብላ ስትደግም ከተሳታፊዎች ጉርምምታ ሲበዛ ለምን አላጠራውም በሚል፤ ይህንን ንግግሯን የሚደግፍ የሕግ ማዕቀፍ ካለ በሚል ጥያቄ አቅርቤላት ነበር፡፡ አወያዪዋም የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ እና ሕገ-መንግሥቱ ይደነግጋል በማለት ምላሽ ስትሰጥ፤ በዚህ ነጥብ ላይ የጦፈ ክርክር ይነሳል፡፡
በአንድ ወገን ይህንን ስያሜ የመስጠት ቅድሚያ መብት የሚደነግገው የፍትሐብሔር ሕጉ ነው እንዲሁም በቤተሰብ ሕጉ በግልፅ የተደነገገ አንቀጽ የለም በሚል ሲቃወሙ፤ በሌላ ፀንፍ አወያዩዋን ጨምሮ ሌሎች ተሳታፊዎች ደግሞ የሴቶች እኩልነት በሕገ-መንግሥቱ ስለተደነገገ እና በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ ስር ቤተሰብን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት በጋራ መሆን አለበት በሚለው አንቀጽ ስር ይወድቃል በማለት ተከራከሩ፡፡ በመጨረሻም ከስምምነት መድረስ ሲያቅተን ጭብጥ ቀይረን ውይይቱን ቀጠልን፤ ነገር ግን እንደ አንድ የሕግ ባለሙያ ጉዳዩን የበለጠ ልመረምር ይገባል ብዬ ይህንን ዕልባት ያላገኘ ነጥብ ወደ ማውቃቸው የሕግ ምሁራን ወስጄ ሀሳባቸውን ስጠይቅ እዚህም ሁለት ጎራ የያዘ ምላሽ አገኘሁ፡፡ በዚህም የተነሳ ይህንን ነጥብ የበለጠ ለማጥራት ከሕግ ማዕቀፎቹ፣ ከመሰረታዊ የሕግ ፍልስፍና መርሆች እና ከፆታ እኩልነት አንጻር ለመመርመር ወደድኩ፡፡ ምንም እንኳ በውይይቱ አንዱን ጎራ ይዤ ስከራከር የነበረ ቢሆንም ለዚህ ፅሁፍ አላማ ሲባል ገለልተኛ ሆኜ የሁለቱንም ገራ ክርክር አካትቼ እንደሚከተለው አቀርባለሁ፡፡
https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/2033-choice-of-first-name-in-ethiopia
#አለ_ህግ #AleHig
@Lawsocieties
@AleHig
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
የሕግ ባለሙያዎች ወግ
በአቤል ልዑልሰገድ አበበ
ከሰሞኑ በአንድ ጠበቆች፣ ዳኞች፣ ዓቃቢያነ ሕግች፣ የሕግ ምሁራን እና የሴቶች መብት አቀንቃኞች የተገኙበት የሴቶች እኩልነት እና ሰብዓዊ መብቶች በሚል ርእስ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ ተገኝቼ ሳለሁ፤ አንዲት ተሳታፊ ጠበቂት ሃሳቧን ስታጋራ ለህፃን ስያሜ የመስጠት መብት የወላጆች የጋራ መብት ነው ብላ በደፈናው ተናግራ ስትጨርስ የውይይቱ መሪ ይህን ሀሳብ በሕግ የተደነገገ መብት ነው ብላ ስትደግም ከተሳታፊዎች ጉርምምታ ሲበዛ ለምን አላጠራውም በሚል፤ ይህንን ንግግሯን የሚደግፍ የሕግ ማዕቀፍ ካለ በሚል ጥያቄ አቅርቤላት ነበር፡፡ አወያዪዋም የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ እና ሕገ-መንግሥቱ ይደነግጋል በማለት ምላሽ ስትሰጥ፤ በዚህ ነጥብ ላይ የጦፈ ክርክር ይነሳል፡፡
በአንድ ወገን ይህንን ስያሜ የመስጠት ቅድሚያ መብት የሚደነግገው የፍትሐብሔር ሕጉ ነው እንዲሁም በቤተሰብ ሕጉ በግልፅ የተደነገገ አንቀጽ የለም በሚል ሲቃወሙ፤ በሌላ ፀንፍ አወያዩዋን ጨምሮ ሌሎች ተሳታፊዎች ደግሞ የሴቶች እኩልነት በሕገ-መንግሥቱ ስለተደነገገ እና በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ ስር ቤተሰብን በጋራ የማስተዳደር ኃላፊነት በጋራ መሆን አለበት በሚለው አንቀጽ ስር ይወድቃል በማለት ተከራከሩ፡፡ በመጨረሻም ከስምምነት መድረስ ሲያቅተን ጭብጥ ቀይረን ውይይቱን ቀጠልን፤ ነገር ግን እንደ አንድ የሕግ ባለሙያ ጉዳዩን የበለጠ ልመረምር ይገባል ብዬ ይህንን ዕልባት ያላገኘ ነጥብ ወደ ማውቃቸው የሕግ ምሁራን ወስጄ ሀሳባቸውን ስጠይቅ እዚህም ሁለት ጎራ የያዘ ምላሽ አገኘሁ፡፡ በዚህም የተነሳ ይህንን ነጥብ የበለጠ ለማጥራት ከሕግ ማዕቀፎቹ፣ ከመሰረታዊ የሕግ ፍልስፍና መርሆች እና ከፆታ እኩልነት አንጻር ለመመርመር ወደድኩ፡፡ ምንም እንኳ በውይይቱ አንዱን ጎራ ይዤ ስከራከር የነበረ ቢሆንም ለዚህ ፅሁፍ አላማ ሲባል ገለልተኛ ሆኜ የሁለቱንም ገራ ክርክር አካትቼ እንደሚከተለው አቀርባለሁ፡፡
https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/2033-choice-of-first-name-in-ethiopia
#አለ_ህግ #AleHig
@Lawsocieties
@AleHig
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
#Daily_Tip
የአላማ ሰው መሆን!
'ምንም ነገር መጀመር ያለብህ ቀድመህ በአይምሮህ ስትጨርሰው ነው' የሚባል ሀሳብ አለ።
ብዙ ነገር ጀምረህ ያቆምከው ወይ መሀል ላይ ግራ የሚገባህ አቅም አንሶህ ወይ ሰነፍ ስለሆንክ አይደለም አላማህን ስለማታውቀው ነው! ወይ ደግሞ አላማህን ብታውቀውም እቅድ የለህም።
ሰውነትክን ከማሰራትክ በፊት አእምሮክ መጨረሻውን መዳረሻውን ማየት አለበት እንዴት ወዴት ከማን ጋር የሚለውብ በሀሳብክ ጨርስ።
Via - Social media
#Ethiopian Business Daily
የአላማ ሰው መሆን!
'ምንም ነገር መጀመር ያለብህ ቀድመህ በአይምሮህ ስትጨርሰው ነው' የሚባል ሀሳብ አለ።
ብዙ ነገር ጀምረህ ያቆምከው ወይ መሀል ላይ ግራ የሚገባህ አቅም አንሶህ ወይ ሰነፍ ስለሆንክ አይደለም አላማህን ስለማታውቀው ነው! ወይ ደግሞ አላማህን ብታውቀውም እቅድ የለህም።
ሰውነትክን ከማሰራትክ በፊት አእምሮክ መጨረሻውን መዳረሻውን ማየት አለበት እንዴት ወዴት ከማን ጋር የሚለውብ በሀሳብክ ጨርስ።
Via - Social media
#Ethiopian Business Daily
#ህጉ ምን ይላል?
#የዉል ስምምነት የሚጸናባቸዉ ነጥቦች
በእዉቁ የህግ መዝገበ ቃላት ብላክስ ሎዉ ላይ “ዉል ማለት በሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች በመካከላቸዉ አንድን ድርጊት ለማድረግ ወይንም ላለማድርግ በመስማማት ግዴታ የሚፈጥሩበት መንገድ ነዉ” ሲል ትርጉም ይሰጠዋል፡፡ እንዲሁም በፍትሐ ብሔር ህጋችን አንቀፅ 1675 ላይ “ዉል ማለት ንብረታቸዉን የሚመለከቱ ግዴታዎችን ለማቋቋም ወይም ለመለወጥ ወይም ለማስቀረት ባላቸዉ ተወዳዳሪ ግንኙነት በሁለት ወይም በብዙ ሰዎች መሀል የሚደረግ ስምምነት ነዉ” በማለት ትርጉም ሰጥቶታል፡፡
የዉል ስምምነት ከሌሎች ስምምነቶች የሚለየዉ ለአፈፀሙ ከበስተጀርባዉ የሕግ ድጋፍ ያለዉ ስምምነት መሆኑ ነዉ፡፡ ይህም ማለት ተዋዋይ ወገኖች የተስማሙበትን ነገር እንደ ስምምነታቸዉ ባይፈፅሙ ያልፈፀሙትን ነገር በህግ ተገደዉ እንዲፈፅሙ ይደረጋሉ፡፡ ይህም የሚያሳየን ዉል በተስማሚዎቹ አካላት መካከል እንደ ህግ ሆኖ የሚያገለግል መሆኑን ነዉ፡፡
#የዉል ስምምነት የሚጸናባቸዉ ነጥቦች
በእዉቁ የህግ መዝገበ ቃላት ብላክስ ሎዉ ላይ “ዉል ማለት በሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች በመካከላቸዉ አንድን ድርጊት ለማድረግ ወይንም ላለማድርግ በመስማማት ግዴታ የሚፈጥሩበት መንገድ ነዉ” ሲል ትርጉም ይሰጠዋል፡፡ እንዲሁም በፍትሐ ብሔር ህጋችን አንቀፅ 1675 ላይ “ዉል ማለት ንብረታቸዉን የሚመለከቱ ግዴታዎችን ለማቋቋም ወይም ለመለወጥ ወይም ለማስቀረት ባላቸዉ ተወዳዳሪ ግንኙነት በሁለት ወይም በብዙ ሰዎች መሀል የሚደረግ ስምምነት ነዉ” በማለት ትርጉም ሰጥቶታል፡፡
የዉል ስምምነት ከሌሎች ስምምነቶች የሚለየዉ ለአፈፀሙ ከበስተጀርባዉ የሕግ ድጋፍ ያለዉ ስምምነት መሆኑ ነዉ፡፡ ይህም ማለት ተዋዋይ ወገኖች የተስማሙበትን ነገር እንደ ስምምነታቸዉ ባይፈፅሙ ያልፈፀሙትን ነገር በህግ ተገደዉ እንዲፈፅሙ ይደረጋሉ፡፡ ይህም የሚያሳየን ዉል በተስማሚዎቹ አካላት መካከል እንደ ህግ ሆኖ የሚያገለግል መሆኑን ነዉ፡፡
👇👇👇👇👇የቀጠለ👇👇👇👇
ዉል በተወያይ ወገኖች መካከል ህጋዊ ዉጤት እንዲኖረዉ አስቀድሞ የዉል አመሰራረቱ ህጋዊ መስፈርቱን ማሟላት አለበት፡፡ በፍትሐብሔር ህጋችን አንቀፅ 1678 ላይ በግልፅ እንደተቀመጠዉ የሚፀና ዉል ነዉ ለማለት መሟላት ያለባቸዉን ሁኔታዎች አስቀምጧል እነሱም፡-
1ኛ. ዉል የሚፈፀመዉ ተዋዋዮቹ ለመዋዋል በሕግ 'ችሎታ ባላቸዉ ሰዎች መካከል መሆኑ ሲሆን ይህም የተዋዋዮች ዕድሜ ከ18 ዓመት በላይ መሆን እና የአእምሮ ጤንነት ነዉ።
2ኛ• ፈቃድ (Consent) ፡- ተዋዋዩ ፈቃዱን የሰጠው ወዶና ፈቅዶ በማያሻማ ሁኔታ መሆን ይኖርበታል። ይህ ማለትም በመታለል/በማታለል የተፈጸመ ውል ዋጋ አይሰጠውም።
3ኛ• የውሉ ዋና ጉዳይ በሕግ የሚፈጸም መሆን አለበት፡- ይህም ማለት እንድን ውል ለመዋዋል ከህግና ከሞራል የሚቃረን መሆን የለበትም፡፡ ለምሳሌ ከህግ አንፃር ባዶ መሬት መሸጥ አይቻልም ስለዚህ የባዶ መሬት ሽያጭ ውል ቢደረግም በፍርድ ቤት ውድቅ ነው።
4ኛ• የውል አቀራረጽ ወይም ፎርም ነው፡- ይህም ማለት ለምሳሌ ለማይንቀሳቀስ ንብረት ሽያጭ ሁለት ምስክሮች መኖራቸው፣ በውል አዋዋይ ፊት ዉሉ መረጋገጡ ነዉ።
via DARA
#አለ_ህግ #AleHig
@Lawsocieties
@AleHig
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
ዉል በተወያይ ወገኖች መካከል ህጋዊ ዉጤት እንዲኖረዉ አስቀድሞ የዉል አመሰራረቱ ህጋዊ መስፈርቱን ማሟላት አለበት፡፡ በፍትሐብሔር ህጋችን አንቀፅ 1678 ላይ በግልፅ እንደተቀመጠዉ የሚፀና ዉል ነዉ ለማለት መሟላት ያለባቸዉን ሁኔታዎች አስቀምጧል እነሱም፡-
1ኛ. ዉል የሚፈፀመዉ ተዋዋዮቹ ለመዋዋል በሕግ 'ችሎታ ባላቸዉ ሰዎች መካከል መሆኑ ሲሆን ይህም የተዋዋዮች ዕድሜ ከ18 ዓመት በላይ መሆን እና የአእምሮ ጤንነት ነዉ።
2ኛ• ፈቃድ (Consent) ፡- ተዋዋዩ ፈቃዱን የሰጠው ወዶና ፈቅዶ በማያሻማ ሁኔታ መሆን ይኖርበታል። ይህ ማለትም በመታለል/በማታለል የተፈጸመ ውል ዋጋ አይሰጠውም።
3ኛ• የውሉ ዋና ጉዳይ በሕግ የሚፈጸም መሆን አለበት፡- ይህም ማለት እንድን ውል ለመዋዋል ከህግና ከሞራል የሚቃረን መሆን የለበትም፡፡ ለምሳሌ ከህግ አንፃር ባዶ መሬት መሸጥ አይቻልም ስለዚህ የባዶ መሬት ሽያጭ ውል ቢደረግም በፍርድ ቤት ውድቅ ነው።
4ኛ• የውል አቀራረጽ ወይም ፎርም ነው፡- ይህም ማለት ለምሳሌ ለማይንቀሳቀስ ንብረት ሽያጭ ሁለት ምስክሮች መኖራቸው፣ በውል አዋዋይ ፊት ዉሉ መረጋገጡ ነዉ።
via DARA
#አለ_ህግ #AleHig
@Lawsocieties
@AleHig
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
የከፍተኛ_ባለሙያዎች_ምዘናና_ማረጋገጫ_አፈፃፀም_ረቂቅ_መመሪያ.pdf
1 MB
በኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ግንቦት 2014 ዓ.ም በኮንስትራክሽን ዘርፍ የከፍተኛ ባለሙያዎች ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ አፈፃፀም ላይ የወጣ ረቂቅ መመሪያ
ደንብ መተላለፍ በኢትዮጵያ የወንጀል ህግ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
#መግቢያ
በኢትዮጵያ ህግ ቅጣት ሊያስከትሉ የሚችሉ ድርጊቶችን ከክብደታቸው እና ከሚያስከትሉት ሀላፊነት አንፃር በወንጀል ህግ የሚያስቀጡ እና በደንብ መተላለፍ ህግ የሚያስቀጡ ብለን ልንከፍል እንችላለን፡፡ በደንብ መተላለፍ የሚያስቀጡ ድርጊቶች በኢ.ፌ.ድ.ሪ የወንጀል ህግ ሰባተኛ መፅሀፍ እና ስምንተኛ የተደነገጉ ሲሆን ቅጣትን የሚመለከቱ ደንቦች እና የህጉ ተፈጻሚነት ወሰን በወንጀል ህጉ ተካቶ ይገኛል፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ የደንብ መተላለፍ ምንነት እና ከወንጀል ሀላፊት በምን እንደሚለይ ፣ የደንብ መተላለፎች የሚያስከትሉት ቅጣት እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ይዳሰሳሉ፡፡
✅የደንብ መተላለፍ ምንነት
አንድ ሰው ደንብ ተላልፏል የሚባለው ሥልጣን ያለው አካል ባወጣው ህግ የተመለከተውንና አንድ ነገር እንዳይፈፀም የሚያዘውን ወይም የሚከለክለውን ድንጋጌ የተላለፈ ወይም በወንጀል የማያስቀጣ ቀላል ጥፋት የፈፀመ ሲሆንና የዚህ ዓይነቱ ህግ መጣስ ወይም ቀላል ጥፋት በወንጀል ህጉ ከአንቀፅ 746 እስከ 775 በተመለከቱት ድንጋጌዎች የሚያስቀጣ ሲሆን ነው፡፡ በዚሁ መሰረት በወንጀል ህጉ የደንብ መተላለፍ ህግ ላይ በተለየ ሁኔታ ካልተደነገገ በቀር የነገሩን ዓይነት እንዲሁም የህጉን መንፈስና ግብ በመመልከት የወንጀል ህጉ ጠቅላላ ክፍል መሰረታዊ መርሆችና ደንቦች በደንብ መተላለፍ ላይ ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡
✅የደንብ መተላለፍ አይነቶች
የደንብ መተላለፍ ህጉ በውስጡ የተለያዩ አይነት የደንብ መተላለፎችን የያዘ ሲሆን እነዚህ መተላለፎች በስራቸው ዝርዝር የጥፋት አይነቶችን ከሚያስከትሉት ቅጣት ጋር አካተው ይገኛሉ፡፡ የደንብ መተላለፍ አይነቶቹም በመንግስትና ህዝብ ጥቅም ላይ የሚፈፀሙ የደንብ መተላለፍ ተግባሮች( ለምሳሌ ህጋዊ ገንዘብን አለመቀበል)፤ ወታደራዊ ግዴታዎችን መጣስ እና በመከላከያ ሠራዊት እንዲሁም በፖሊስ ላይ የሚፈፀሙ የደንብ መተላለፍ ጥፋቶች፤ በመንግስት የስራ ግዴታዎች እና በመንግስት መስሪያ ቤት/ባለስልጣን/ ላይ የሚፈፀሙ የደንብ መተላለፍ ጥፋቶች(ለምሳሌ ሀቀኝነትን ማጓደል)፤ በሕዝብ ደኅንነት፣ሰላምና ተረጋግቶ መኖር ላይ የሚፈፀሙ የደንብ መተላለፍ ጥፋቶች(ለምሳሌ ሐሰተኛ የአደጋ ምልክት መስጠት)፤ በሕዝብ ጤና እና በፅዳት ጥበቃ ላይ የሚፈፀሙ የደንብ መተላለፍ ጥፋቶች( ለምሳሌ መርዛማና አደንዛዥ ንጥረ ነገሮችና መድሀኒቶች ለመቆጣጠር የወጣ ደንብ) እና በሰዎችና በንብረቶች ላይ የሚፈፀሙ የደንብ መተላለፍ ጥፋቶች ናቸው፡፡
✅ ደንብ መተላለፍ ተፈፃሚ የሚሆንባቸው ጥፋቶች
በህጋዊነት መርህ እንደተመለከተው በደንብ መተላለፍ ህግ ወይም በሌላ ህግ የተደነገጉ ጥፋቶች ብቻ የሚያስቀጡ ሲሆን የሚያስቀጡትም በህጉ የተቀመጡትን ቅጣቶች ብቻ ይሆናል፡፡ በተጨማሪም የደንብ መተላለፍ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ የሚሆኑት ለተፈፀመው ድርጊት የበለጠ ቅጣት የሚደነግጉ አንቀፆች በሌሉ ጊዜ ብቻ ነው፡፡ ስለሆነም አንድ ድርጊት የሚያስቀጣው በወንጀል ህግ ወይም በደንብ መተላለፍ ህግ በአንደኛው እንጂ በሁለቱም ሊሆን አይችልም፡፡ እንዲሁም የወንጀል ህግ ወደ ኋላ ተመልሶ የማይሰራ መሆኑ መርህ በተመሳሳይ ለደንብ መተላለፍ ይሰራል፡፡ በመሆኑም የደንብ መተላለፍ ተግባሮች የሚያስቀጡት በተፈፀመበት ጊዜ ፀንተው ባሉት ድንገጌዎች መሰረት እንጂ ከድርጊቱ በኋላ የወጣን ህግ ወደ ኋላ ተመልሶ እንዲፈፀም በማድረግ አይሆንም፡፡
በሌላ በኩል የደንብ መተላለፍ ተግባርን ለመፈፀም የሚደረጉ የመዘጋጀትና የሙከራ ድርጊቶች የማያስቀጡ ሲሆን ለደንብ መተላለፍ የሚደረግ ማነሳሳት፣አባሪነት እና ወንጀል ከፈፀመ በኋላ ወንጀል አድራጊውን መርዳት አያስቀጣም፡፡ ይህ ማለት የሚቀጣው ደንብ ተላላፊው ብቻ ነው ማለት ነው፡፡ እንዲሁም የህግ ሰውነት የተሰጠውን ሰው በአነሳሽነት ወይም በአባሪነት የማይቀጣ ሲሆን የድርጅቱ ሀላፊ ወይም ሰራተኛ የሚቀጣው በወንጀል ህጉ መሰረት በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን ደንብን ወይም መመሪያን በዋና ደንብ ተላላፊነት በሚጥስበት ጊዜ ብቻ ነው፡፡
በተጨማሪም በወንጀል ህጉ አንቀጽ 743 እንደተደነገገው የማያስቀጡና ይቅርታ የሚሰጡ ሁኔታዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡ እነዚህም በህግ የታዘዙ ወይም የተፈቀዱ ድርጊቶች፣ የሞያ ስራ ግዴታ፣ የተጎጂው ፍቃድ ፣ ፍፁም የሆነ መገደድ፣አስፈላጊ ሁኔታ እና ህጋዊ መከላከልን የሚመለከቱ የወንጀል ህግ ድንጋጌዎች ለደንብ መተላለፍም ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡ ይሁንና ደንብ የተላለፈ ማንም ሰው ህግ አለማወቅን ወይም የማድረግ መብት አለ ብሎ መሳሳትን እንደመከላከያ ምክንያት አድርጎ ሊያቀርብ አይችልም፡፡
✅ለደንብ መተላለፍ ተፈፃሚነት ያላቸው ቅጣቶችና የጥንቃቄ እርምጃዎች
ለደንብ መተላለፍ መደበኛ የሆኑ የወንጀል ቅጣቶች ተፈፃሚ የማይሆኑ ስለሆነ ምንጊዜም ቢሆን ለወንጀሎቹ በተወሰኑት ፅኑ እስራት ወይም በቀላል እስራት አይቀጡም፡፡ ይህም የሚያመለክተው ደንብ መተላለፍ ከወንጀል የሚለየው በሚያስከትለው የተለየ ቅጣት እንደሆነ ነው፡፡ ስለሆነም የደንብ መተላለፍ ድርጊቶች በተፈፀሙ ጊዜ የሚወሰነው ነፃነትን የሚያሳጣ ቅጣት የማረፊያ ቤት እስራት እንጂ የማረሚያ ቤት እስራት አይሆንም፡፡ መደበኛ የማረፊያ ቤት እስራት የሚፈፀመው ከፍርድ ቤቶች ወይም ከፖሊስ ጣቢያዎች ጋር በተያያዙ ልዩ የመቆያ ቦታዎች ይሆናል ማለት ነው፡፡ እንዲሁም በማረፊያ ቤት እስራት ፈንታ የግዴታ ስራን ፍርድ ቤት ሊወስን የሚችልባቸውን ሁኔታዎች የደንብ መተላለፍ ህጉ ደንግጎ ይገኛል፡፡ በተጨማሪም በማናቸውም ጊዜ ቢሆን በማረፊያ ቤት እስራት እንዲቀጣ የተፈረደበት ሰው ወደ ጠባይ ማሻሻያ ወይም ማረሚያ ቤት እንዲላክ ፣በወንጀል ምክንያት ከተቀጡት እስረኞች ጋርም እንዲቀላቀል ማድረግ አይቻልም፡፡
በወንጀል ህጉ አንቀጽ 747 እና 768 እንደተደነገገው የደንብ መተላለፍ ድርጊቶች በተፈፀሙ ጊዜ የሚወሰነው ቅጣት እና የህጉ ልዩ ድንጋጌዎች የሚያስቀምጡት ከፍተኛ ቅጣት የማረፊያ ቤት እስራቱ የሚቆይበት ጊዜ ከአንድ ቀን እስከ ሶስት ወር ይሆናል( በደጋጋሚነት እና በመደራረብ ጊዜ ከሁለት ዓመት የማረፊያ ቤት እስራት አይበልጥም) ፡፡ በተጨማሪም ደንብ ተላላፊዎች ወታደሮች ወይም ወጣት ጥፋተኞች ሲሆኑ የሚፈፀመው የተለየ ቅጣት እንደተጠበቀ ሆኖ በደንብ መተላለፍ ረገድ የሚፈፀሙ ቅጣቶች በደንብ መተላለፍ ህግ በተደነገገው መሰረት ይሆናል፡፡ እንዲሁም ለህብረተሰቡ ሲባል የጥበቃ ወይም የሕክምና እርምጃዎች መወሰድ ሲኖርባቸው በተለየ ኃላፊ ሊሆኑ የማይችሉ ሰዎችን በሚመለከት ፍርድ ቤት አግባብነት ላለው የአስተዳደር ባለስልጣን ያሳውቃል፡፡
ሌላው በደንብ መተላለፍ ህጉ ለደንብ መተላለፍ ጥፋት የተቀመጠው ቅጣት የገንዘብ መቀጮ ቅጣት ነው፡፡ ይኸውም ጥፋተኛው ደጋጋሚ ካልሆነ ወይም የህጉ ልዩ ድንጋጌ የበለጠ ካልወሰነ በቀር በደንብ ተላላፊ ላይ የሚጣል መቀጮ ከአንድ ብር እስከ ሶስት መቶ ብር ለመድረስ የሚችል ሲሆን ጥፋቱ በተደጋገመ ጊዜ የሚደረገው የቅጣት ማክበጃ እንደተጠበቀ ሆኖ ተላላፊው ጣፋቱን የፈፀመው በአፍቅሮ ንዋይ እንደሆነ መቀጮው እስከ አምስት መቶ ብር ሊደርስ ይችላል፡፡ እንዲሁም ለተፈረደበት ሰው ቢያስፈልግም ከፋፍሎ በየጊዜው ዕዳውን እንዲከፍል በመፍቀድ ፍርድ ቤቱ እስከ ሶስት ወር ለመድረስ በሚችል የመክፈያ ጊዜ ሊወስንለት የሚችል ሲሆን ሁኔታዎች በቂ ምክንያት ያስገኙ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ የመከፈያ ጊዜውን እስከ አንድ አመት ሊያራዝመው ይችላል፡፡...👇ይቀጥላል👇👇
#መግቢያ
በኢትዮጵያ ህግ ቅጣት ሊያስከትሉ የሚችሉ ድርጊቶችን ከክብደታቸው እና ከሚያስከትሉት ሀላፊነት አንፃር በወንጀል ህግ የሚያስቀጡ እና በደንብ መተላለፍ ህግ የሚያስቀጡ ብለን ልንከፍል እንችላለን፡፡ በደንብ መተላለፍ የሚያስቀጡ ድርጊቶች በኢ.ፌ.ድ.ሪ የወንጀል ህግ ሰባተኛ መፅሀፍ እና ስምንተኛ የተደነገጉ ሲሆን ቅጣትን የሚመለከቱ ደንቦች እና የህጉ ተፈጻሚነት ወሰን በወንጀል ህጉ ተካቶ ይገኛል፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ የደንብ መተላለፍ ምንነት እና ከወንጀል ሀላፊት በምን እንደሚለይ ፣ የደንብ መተላለፎች የሚያስከትሉት ቅጣት እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ይዳሰሳሉ፡፡
✅የደንብ መተላለፍ ምንነት
አንድ ሰው ደንብ ተላልፏል የሚባለው ሥልጣን ያለው አካል ባወጣው ህግ የተመለከተውንና አንድ ነገር እንዳይፈፀም የሚያዘውን ወይም የሚከለክለውን ድንጋጌ የተላለፈ ወይም በወንጀል የማያስቀጣ ቀላል ጥፋት የፈፀመ ሲሆንና የዚህ ዓይነቱ ህግ መጣስ ወይም ቀላል ጥፋት በወንጀል ህጉ ከአንቀፅ 746 እስከ 775 በተመለከቱት ድንጋጌዎች የሚያስቀጣ ሲሆን ነው፡፡ በዚሁ መሰረት በወንጀል ህጉ የደንብ መተላለፍ ህግ ላይ በተለየ ሁኔታ ካልተደነገገ በቀር የነገሩን ዓይነት እንዲሁም የህጉን መንፈስና ግብ በመመልከት የወንጀል ህጉ ጠቅላላ ክፍል መሰረታዊ መርሆችና ደንቦች በደንብ መተላለፍ ላይ ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡
✅የደንብ መተላለፍ አይነቶች
የደንብ መተላለፍ ህጉ በውስጡ የተለያዩ አይነት የደንብ መተላለፎችን የያዘ ሲሆን እነዚህ መተላለፎች በስራቸው ዝርዝር የጥፋት አይነቶችን ከሚያስከትሉት ቅጣት ጋር አካተው ይገኛሉ፡፡ የደንብ መተላለፍ አይነቶቹም በመንግስትና ህዝብ ጥቅም ላይ የሚፈፀሙ የደንብ መተላለፍ ተግባሮች( ለምሳሌ ህጋዊ ገንዘብን አለመቀበል)፤ ወታደራዊ ግዴታዎችን መጣስ እና በመከላከያ ሠራዊት እንዲሁም በፖሊስ ላይ የሚፈፀሙ የደንብ መተላለፍ ጥፋቶች፤ በመንግስት የስራ ግዴታዎች እና በመንግስት መስሪያ ቤት/ባለስልጣን/ ላይ የሚፈፀሙ የደንብ መተላለፍ ጥፋቶች(ለምሳሌ ሀቀኝነትን ማጓደል)፤ በሕዝብ ደኅንነት፣ሰላምና ተረጋግቶ መኖር ላይ የሚፈፀሙ የደንብ መተላለፍ ጥፋቶች(ለምሳሌ ሐሰተኛ የአደጋ ምልክት መስጠት)፤ በሕዝብ ጤና እና በፅዳት ጥበቃ ላይ የሚፈፀሙ የደንብ መተላለፍ ጥፋቶች( ለምሳሌ መርዛማና አደንዛዥ ንጥረ ነገሮችና መድሀኒቶች ለመቆጣጠር የወጣ ደንብ) እና በሰዎችና በንብረቶች ላይ የሚፈፀሙ የደንብ መተላለፍ ጥፋቶች ናቸው፡፡
✅ ደንብ መተላለፍ ተፈፃሚ የሚሆንባቸው ጥፋቶች
በህጋዊነት መርህ እንደተመለከተው በደንብ መተላለፍ ህግ ወይም በሌላ ህግ የተደነገጉ ጥፋቶች ብቻ የሚያስቀጡ ሲሆን የሚያስቀጡትም በህጉ የተቀመጡትን ቅጣቶች ብቻ ይሆናል፡፡ በተጨማሪም የደንብ መተላለፍ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ የሚሆኑት ለተፈፀመው ድርጊት የበለጠ ቅጣት የሚደነግጉ አንቀፆች በሌሉ ጊዜ ብቻ ነው፡፡ ስለሆነም አንድ ድርጊት የሚያስቀጣው በወንጀል ህግ ወይም በደንብ መተላለፍ ህግ በአንደኛው እንጂ በሁለቱም ሊሆን አይችልም፡፡ እንዲሁም የወንጀል ህግ ወደ ኋላ ተመልሶ የማይሰራ መሆኑ መርህ በተመሳሳይ ለደንብ መተላለፍ ይሰራል፡፡ በመሆኑም የደንብ መተላለፍ ተግባሮች የሚያስቀጡት በተፈፀመበት ጊዜ ፀንተው ባሉት ድንገጌዎች መሰረት እንጂ ከድርጊቱ በኋላ የወጣን ህግ ወደ ኋላ ተመልሶ እንዲፈፀም በማድረግ አይሆንም፡፡
በሌላ በኩል የደንብ መተላለፍ ተግባርን ለመፈፀም የሚደረጉ የመዘጋጀትና የሙከራ ድርጊቶች የማያስቀጡ ሲሆን ለደንብ መተላለፍ የሚደረግ ማነሳሳት፣አባሪነት እና ወንጀል ከፈፀመ በኋላ ወንጀል አድራጊውን መርዳት አያስቀጣም፡፡ ይህ ማለት የሚቀጣው ደንብ ተላላፊው ብቻ ነው ማለት ነው፡፡ እንዲሁም የህግ ሰውነት የተሰጠውን ሰው በአነሳሽነት ወይም በአባሪነት የማይቀጣ ሲሆን የድርጅቱ ሀላፊ ወይም ሰራተኛ የሚቀጣው በወንጀል ህጉ መሰረት በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን ደንብን ወይም መመሪያን በዋና ደንብ ተላላፊነት በሚጥስበት ጊዜ ብቻ ነው፡፡
በተጨማሪም በወንጀል ህጉ አንቀጽ 743 እንደተደነገገው የማያስቀጡና ይቅርታ የሚሰጡ ሁኔታዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡ እነዚህም በህግ የታዘዙ ወይም የተፈቀዱ ድርጊቶች፣ የሞያ ስራ ግዴታ፣ የተጎጂው ፍቃድ ፣ ፍፁም የሆነ መገደድ፣አስፈላጊ ሁኔታ እና ህጋዊ መከላከልን የሚመለከቱ የወንጀል ህግ ድንጋጌዎች ለደንብ መተላለፍም ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡ ይሁንና ደንብ የተላለፈ ማንም ሰው ህግ አለማወቅን ወይም የማድረግ መብት አለ ብሎ መሳሳትን እንደመከላከያ ምክንያት አድርጎ ሊያቀርብ አይችልም፡፡
✅ለደንብ መተላለፍ ተፈፃሚነት ያላቸው ቅጣቶችና የጥንቃቄ እርምጃዎች
ለደንብ መተላለፍ መደበኛ የሆኑ የወንጀል ቅጣቶች ተፈፃሚ የማይሆኑ ስለሆነ ምንጊዜም ቢሆን ለወንጀሎቹ በተወሰኑት ፅኑ እስራት ወይም በቀላል እስራት አይቀጡም፡፡ ይህም የሚያመለክተው ደንብ መተላለፍ ከወንጀል የሚለየው በሚያስከትለው የተለየ ቅጣት እንደሆነ ነው፡፡ ስለሆነም የደንብ መተላለፍ ድርጊቶች በተፈፀሙ ጊዜ የሚወሰነው ነፃነትን የሚያሳጣ ቅጣት የማረፊያ ቤት እስራት እንጂ የማረሚያ ቤት እስራት አይሆንም፡፡ መደበኛ የማረፊያ ቤት እስራት የሚፈፀመው ከፍርድ ቤቶች ወይም ከፖሊስ ጣቢያዎች ጋር በተያያዙ ልዩ የመቆያ ቦታዎች ይሆናል ማለት ነው፡፡ እንዲሁም በማረፊያ ቤት እስራት ፈንታ የግዴታ ስራን ፍርድ ቤት ሊወስን የሚችልባቸውን ሁኔታዎች የደንብ መተላለፍ ህጉ ደንግጎ ይገኛል፡፡ በተጨማሪም በማናቸውም ጊዜ ቢሆን በማረፊያ ቤት እስራት እንዲቀጣ የተፈረደበት ሰው ወደ ጠባይ ማሻሻያ ወይም ማረሚያ ቤት እንዲላክ ፣በወንጀል ምክንያት ከተቀጡት እስረኞች ጋርም እንዲቀላቀል ማድረግ አይቻልም፡፡
በወንጀል ህጉ አንቀጽ 747 እና 768 እንደተደነገገው የደንብ መተላለፍ ድርጊቶች በተፈፀሙ ጊዜ የሚወሰነው ቅጣት እና የህጉ ልዩ ድንጋጌዎች የሚያስቀምጡት ከፍተኛ ቅጣት የማረፊያ ቤት እስራቱ የሚቆይበት ጊዜ ከአንድ ቀን እስከ ሶስት ወር ይሆናል( በደጋጋሚነት እና በመደራረብ ጊዜ ከሁለት ዓመት የማረፊያ ቤት እስራት አይበልጥም) ፡፡ በተጨማሪም ደንብ ተላላፊዎች ወታደሮች ወይም ወጣት ጥፋተኞች ሲሆኑ የሚፈፀመው የተለየ ቅጣት እንደተጠበቀ ሆኖ በደንብ መተላለፍ ረገድ የሚፈፀሙ ቅጣቶች በደንብ መተላለፍ ህግ በተደነገገው መሰረት ይሆናል፡፡ እንዲሁም ለህብረተሰቡ ሲባል የጥበቃ ወይም የሕክምና እርምጃዎች መወሰድ ሲኖርባቸው በተለየ ኃላፊ ሊሆኑ የማይችሉ ሰዎችን በሚመለከት ፍርድ ቤት አግባብነት ላለው የአስተዳደር ባለስልጣን ያሳውቃል፡፡
ሌላው በደንብ መተላለፍ ህጉ ለደንብ መተላለፍ ጥፋት የተቀመጠው ቅጣት የገንዘብ መቀጮ ቅጣት ነው፡፡ ይኸውም ጥፋተኛው ደጋጋሚ ካልሆነ ወይም የህጉ ልዩ ድንጋጌ የበለጠ ካልወሰነ በቀር በደንብ ተላላፊ ላይ የሚጣል መቀጮ ከአንድ ብር እስከ ሶስት መቶ ብር ለመድረስ የሚችል ሲሆን ጥፋቱ በተደጋገመ ጊዜ የሚደረገው የቅጣት ማክበጃ እንደተጠበቀ ሆኖ ተላላፊው ጣፋቱን የፈፀመው በአፍቅሮ ንዋይ እንደሆነ መቀጮው እስከ አምስት መቶ ብር ሊደርስ ይችላል፡፡ እንዲሁም ለተፈረደበት ሰው ቢያስፈልግም ከፋፍሎ በየጊዜው ዕዳውን እንዲከፍል በመፍቀድ ፍርድ ቤቱ እስከ ሶስት ወር ለመድረስ በሚችል የመክፈያ ጊዜ ሊወስንለት የሚችል ሲሆን ሁኔታዎች በቂ ምክንያት ያስገኙ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ የመከፈያ ጊዜውን እስከ አንድ አመት ሊያራዝመው ይችላል፡፡...👇ይቀጥላል👇👇
👆የቀጠለ.... 👆👆👆👆👆👆👆
በተያያዘ ሁኔታ በተወሰነው ጊዜ ውስጥ መቀጮው ያልተከፈለ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ሙሉውን ወይም ያልተከፈለውን ቀሪ መቀጮ ከሚያገኘው ገቢ ተቀናሽ በማድረግ ለመንግስት ገቢ ከማድረግ ጋራ ነፃነትን በሚቀንስ ወይም በማይቀንስ የግዴታ ሥራ እንዲለወጥ በማዘዝ በደንብ መተላለፍ ህጉ ጠቅላላ ድንጋጌዎች መሰረት የግዴታ ስራው የሚቆይበትን ጊዜ ይወስናል፡፡
በሌላ በኩል ከማረፊያ ቤት እስራት፣ ከግዴታ ስራ ወይም ከመቀጮ በተጨማሪ ፍርድ ቤት በቃል ወይም በፅሁፍ ጥፋተኛውን ሊያስጠነቅቀው፣ ሊወቅሰው፣ ሊገስፀው ወይም ተበዳዩን ይቅርታ እንዲጠይቅ ሊያደርገው ይችላል፡፡ እንዲሁም የጥንቃቄ እርምጃዎች ማለትም የመልካም ጠባይ ዋስትና፣ መውረስ እና ለመንግስት ገቢ ማድረግ፣ ድርጅቶችን መከልከል እና የስራ ፍቃድ ማገድ እና የግል ነፃነትን መከልከልና መቀነስ እንደ የጥንቃቄ እርምጃዎች የደንብ መተላለፍ በፈፀሙ ሰዎች ላይ ሊወሰኑ የሚችሉ እርምጃዎች ናቸው፡፡
ይሁንና ከመብት የመሻር ቅጣትን የተመለከቱ ማለትም ከህዝባዊ ወይም ከቤተዘመድ፣ የመንግሥት ሥራ ወይም የሙያ ሥራ ከመሥራት ወይም ከመሳሰሉት መብቶች መሻር እንዲሁም ወታደራዊ ማዕረግን ዝቅ ማድረግ ወይም ከመከላከያ ሰራዊት ባልደረባነት ማስወገድ በደንብ መተላለፍ ላይ ተፈፃሚ አይሆንም፡፡ እንዲሁም በአመክሮ መለቀቅን የሚመለከቱ የወንጀል ህጉ ድንጋጌዎች ለማረፊያ ቤት እስራት ተፈፃሚ የማይሆኑ ሲሆን የደንብ መተላለፍ ቅጣቶች በወንጀል ህጉ ላይ በተደነገጉት ጠቅላላ ሁኔታዎች መሰረት በይቅርታ ወይም በምህረት ቀሪ እንዲሆኑ ማድረግ ይቻላል፡፡
የይርጋ ዘመንን በተመለከተ ማናቸውም ዓይነት የደንብ መተላለፍ ድርጊት ቢሆን ክስ ሳይቀርብበት አንድ ዓመት ካለፈ የተፈረደውም ቅጣት ተፈፃሚ ሳይሆን ሁለት ዓመት ካለፈ በይርጋ ይታገዳል፡፡ በሌላ በኩል ፍርድ ቤቶች የተከሳሹን ያለፈ ታሪክ ጠንቅቀው ማወቅ ይችሉ ዘንድ በደንብ መተላለፍ ረገድ የሚሰጡት የመጨረሻ ቅጣቶች የደንብ መተላለፍ ህግን ጠቅላላ ድንጋጌዎችን በወንጀለኞች መዝገብ ላይ እንዲመዘገብ ፍርድ ቤቱ ይወስናል፡፡
በአጠቃላይ የደንብ መተላለፍ ህግ በወንጀል ህጉ ውስጥ የደንብ መተላለፎችን እና የሚያስከትሉትን ቅጣቶች ያካተተ ቢሆንም በተጨማሪ ሌሎች ባለስልጣናት የሚያወጧቸው የደንብ መተላለፎች ለምሳሌ የትራፊክ ደንብ፣ የከተማ ደንብ ማስከበር( ለምሳሌ ህገ ወጥ ንግድ እና ግንባታ) በተደነገጉት የጥፋት አይነቶች እና ቅጣቶች ኃላፊነትን ያስከትላሉ ወይም ያስቀጣሉ፡፡
በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
በተያያዘ ሁኔታ በተወሰነው ጊዜ ውስጥ መቀጮው ያልተከፈለ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ሙሉውን ወይም ያልተከፈለውን ቀሪ መቀጮ ከሚያገኘው ገቢ ተቀናሽ በማድረግ ለመንግስት ገቢ ከማድረግ ጋራ ነፃነትን በሚቀንስ ወይም በማይቀንስ የግዴታ ሥራ እንዲለወጥ በማዘዝ በደንብ መተላለፍ ህጉ ጠቅላላ ድንጋጌዎች መሰረት የግዴታ ስራው የሚቆይበትን ጊዜ ይወስናል፡፡
በሌላ በኩል ከማረፊያ ቤት እስራት፣ ከግዴታ ስራ ወይም ከመቀጮ በተጨማሪ ፍርድ ቤት በቃል ወይም በፅሁፍ ጥፋተኛውን ሊያስጠነቅቀው፣ ሊወቅሰው፣ ሊገስፀው ወይም ተበዳዩን ይቅርታ እንዲጠይቅ ሊያደርገው ይችላል፡፡ እንዲሁም የጥንቃቄ እርምጃዎች ማለትም የመልካም ጠባይ ዋስትና፣ መውረስ እና ለመንግስት ገቢ ማድረግ፣ ድርጅቶችን መከልከል እና የስራ ፍቃድ ማገድ እና የግል ነፃነትን መከልከልና መቀነስ እንደ የጥንቃቄ እርምጃዎች የደንብ መተላለፍ በፈፀሙ ሰዎች ላይ ሊወሰኑ የሚችሉ እርምጃዎች ናቸው፡፡
ይሁንና ከመብት የመሻር ቅጣትን የተመለከቱ ማለትም ከህዝባዊ ወይም ከቤተዘመድ፣ የመንግሥት ሥራ ወይም የሙያ ሥራ ከመሥራት ወይም ከመሳሰሉት መብቶች መሻር እንዲሁም ወታደራዊ ማዕረግን ዝቅ ማድረግ ወይም ከመከላከያ ሰራዊት ባልደረባነት ማስወገድ በደንብ መተላለፍ ላይ ተፈፃሚ አይሆንም፡፡ እንዲሁም በአመክሮ መለቀቅን የሚመለከቱ የወንጀል ህጉ ድንጋጌዎች ለማረፊያ ቤት እስራት ተፈፃሚ የማይሆኑ ሲሆን የደንብ መተላለፍ ቅጣቶች በወንጀል ህጉ ላይ በተደነገጉት ጠቅላላ ሁኔታዎች መሰረት በይቅርታ ወይም በምህረት ቀሪ እንዲሆኑ ማድረግ ይቻላል፡፡
የይርጋ ዘመንን በተመለከተ ማናቸውም ዓይነት የደንብ መተላለፍ ድርጊት ቢሆን ክስ ሳይቀርብበት አንድ ዓመት ካለፈ የተፈረደውም ቅጣት ተፈፃሚ ሳይሆን ሁለት ዓመት ካለፈ በይርጋ ይታገዳል፡፡ በሌላ በኩል ፍርድ ቤቶች የተከሳሹን ያለፈ ታሪክ ጠንቅቀው ማወቅ ይችሉ ዘንድ በደንብ መተላለፍ ረገድ የሚሰጡት የመጨረሻ ቅጣቶች የደንብ መተላለፍ ህግን ጠቅላላ ድንጋጌዎችን በወንጀለኞች መዝገብ ላይ እንዲመዘገብ ፍርድ ቤቱ ይወስናል፡፡
በአጠቃላይ የደንብ መተላለፍ ህግ በወንጀል ህጉ ውስጥ የደንብ መተላለፎችን እና የሚያስከትሉትን ቅጣቶች ያካተተ ቢሆንም በተጨማሪ ሌሎች ባለስልጣናት የሚያወጧቸው የደንብ መተላለፎች ለምሳሌ የትራፊክ ደንብ፣ የከተማ ደንብ ማስከበር( ለምሳሌ ህገ ወጥ ንግድ እና ግንባታ) በተደነገጉት የጥፋት አይነቶች እና ቅጣቶች ኃላፊነትን ያስከትላሉ ወይም ያስቀጣሉ፡፡
በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
አእምሮ የሌለው ህዝብ ስርዓት የለውም፣
ስርዓት የሌለው ህዝብ የተደለደለ ኃይል የለውም‼️🔴
የኃይል ምንጭ ስርዓት ነው እንጂ፣ የሰራዊት ብዛት አይደለም‼️🔴
ስርዓት ከሌለው ሰፊ መንግስት ይልቅ *በህግ* የምትኖር ትንሽ ከተማ ሞያ ትሰራለች‼️🔴
ገብረህይወት ባይከዳኝ
Via #አለ_ህግ #Alehig
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
ስርዓት የሌለው ህዝብ የተደለደለ ኃይል የለውም‼️🔴
የኃይል ምንጭ ስርዓት ነው እንጂ፣ የሰራዊት ብዛት አይደለም‼️🔴
ስርዓት ከሌለው ሰፊ መንግስት ይልቅ *በህግ* የምትኖር ትንሽ ከተማ ሞያ ትሰራለች‼️🔴
ገብረህይወት ባይከዳኝ
Via #አለ_ህግ #Alehig
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ሰሞኑን "ፊያስ" በተባለ አድራሻው በማይታወቅ የኦላይን ማጭበርበሪያ ዘዴ ብዙዎች በየዋህነት ገንዘባቸውን ተበልተዋል። ይህ ትምህርት ሊሆነን ይገባል። አሁንም በኦላይን እያጭበረበሩ የሚገኙ ስላሉ ጥንቃቄ አድርጉ።
የአማራ ባንክ ተመርቆ እንደተከፈተ ያልተከፈተ የቴሌግራም ቻናል የለም። እነዚህ በአማራ ባንክ ስም የተከፈቱ የቴሌግራም ቻናሎች የመኖሪያ ቤት ሽልማት ይሰጣል ከዛ በፊት ግን ለ50 ወይንም ለ60 ሰው ሼር አድርጉ ይላሉ። ይህን መረጃ አምኖ ሼር የማያደርግ የለም።ለእነሱ የራሳቸውን የቴሌግራም ተከታይ ለማሳደግ የፕሮሞሽን ሥራ እየሰሩነው። አለፍ ሲልም ለሌላ ወንጀል ይጠቀሙበታል።
ለጎደኞቻችሁ ሼር የምታደርጉ ሰዎች ፍፁም ውሸት መሆኑን ልታውቁት ይገባል።
ፊደል የቆጠረ ሰው እንዲህ በአለ ነገር በቀላሉ መሸወድ የለበትም። ትክክለኛውን ገፅ ለማግኘት ይሄን ያህል የሚከብድ አይደለም። ወይንም በውስጥ መስመር መረጃውን ብትልኩ አጣርተን ትክክል መሆኑንና አለመሆኑን ማወቅ እንችላለን።
ከውጭ አገር አሜሪካ ሳይቀር ለእኔም አሰልቺ ማስታወቂያዎች በግል ደርሰውኛል።
ለማንኛውም አማራ ባንክ ምንም አይነት የቤት ሆነ የመኪና ሽልማት ማስታወቂያ አላወጣም እውነት ቢሆን እንኳን እንደሌሎቹ ባንኮች በቴሌቪዥን የምታዩት ነው የሚሆነው።
ትክክለኛው የአማራ ባንክ ቴሌግራም ይሄኛው ነው!!!
Telegram: https://t.me/Amhara_Banksc
የአማራ ባንክ የፌስቡክ ገፅ ይሄ ነው።
Facebook: www.Facebook.com/amharabanksc1
ትክክለኛ የዐማራ ባንክ የቲዊተር አድራሻ ይሄ ነው። https://twitter.com/Amharabanksc
እስካሁን በአጭበርባሪዎች ተሸውዳችሁ ለ60 ሰው ያሰራጫችሁ ሰዎች ይሄን ትክክለኛው መረጃ ለ100 ሰው ብታሳውቁ አትጎዱም። ለወደፊቱ ጥንቃቄ አድርጉ!!!
በሌሎችም የሪል እስቴት ስሞች፣ ድርጅቶች እና ታዋቂ ባለሀብቶች ስም የተከፈቱ የተለያየ አጓጊ ሽልማት አለው ሼር አድርጉ የሚሉ ብዙ የሀሰት የቴሌግራም ቻናሎች አሉ።
ጥንቃቄ ይጠብቅሃል ማስተዋል ይጋርድሀል።
እኛ ተሸውደን እና ተታለን ሰዎችን እዲታለሉና እንዲሸወዱ መንገድ አንክፈት።
#share ሼር በማድረግ እውነትን አጋልጡ
Via #አለ_ህግ #Alehig
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
የአማራ ባንክ ተመርቆ እንደተከፈተ ያልተከፈተ የቴሌግራም ቻናል የለም። እነዚህ በአማራ ባንክ ስም የተከፈቱ የቴሌግራም ቻናሎች የመኖሪያ ቤት ሽልማት ይሰጣል ከዛ በፊት ግን ለ50 ወይንም ለ60 ሰው ሼር አድርጉ ይላሉ። ይህን መረጃ አምኖ ሼር የማያደርግ የለም።ለእነሱ የራሳቸውን የቴሌግራም ተከታይ ለማሳደግ የፕሮሞሽን ሥራ እየሰሩነው። አለፍ ሲልም ለሌላ ወንጀል ይጠቀሙበታል።
ለጎደኞቻችሁ ሼር የምታደርጉ ሰዎች ፍፁም ውሸት መሆኑን ልታውቁት ይገባል።
ፊደል የቆጠረ ሰው እንዲህ በአለ ነገር በቀላሉ መሸወድ የለበትም። ትክክለኛውን ገፅ ለማግኘት ይሄን ያህል የሚከብድ አይደለም። ወይንም በውስጥ መስመር መረጃውን ብትልኩ አጣርተን ትክክል መሆኑንና አለመሆኑን ማወቅ እንችላለን።
ከውጭ አገር አሜሪካ ሳይቀር ለእኔም አሰልቺ ማስታወቂያዎች በግል ደርሰውኛል።
ለማንኛውም አማራ ባንክ ምንም አይነት የቤት ሆነ የመኪና ሽልማት ማስታወቂያ አላወጣም እውነት ቢሆን እንኳን እንደሌሎቹ ባንኮች በቴሌቪዥን የምታዩት ነው የሚሆነው።
ትክክለኛው የአማራ ባንክ ቴሌግራም ይሄኛው ነው!!!
Telegram: https://t.me/Amhara_Banksc
የአማራ ባንክ የፌስቡክ ገፅ ይሄ ነው።
Facebook: www.Facebook.com/amharabanksc1
ትክክለኛ የዐማራ ባንክ የቲዊተር አድራሻ ይሄ ነው። https://twitter.com/Amharabanksc
እስካሁን በአጭበርባሪዎች ተሸውዳችሁ ለ60 ሰው ያሰራጫችሁ ሰዎች ይሄን ትክክለኛው መረጃ ለ100 ሰው ብታሳውቁ አትጎዱም። ለወደፊቱ ጥንቃቄ አድርጉ!!!
በሌሎችም የሪል እስቴት ስሞች፣ ድርጅቶች እና ታዋቂ ባለሀብቶች ስም የተከፈቱ የተለያየ አጓጊ ሽልማት አለው ሼር አድርጉ የሚሉ ብዙ የሀሰት የቴሌግራም ቻናሎች አሉ።
ጥንቃቄ ይጠብቅሃል ማስተዋል ይጋርድሀል።
እኛ ተሸውደን እና ተታለን ሰዎችን እዲታለሉና እንዲሸወዱ መንገድ አንክፈት።
#share ሼር በማድረግ እውነትን አጋልጡ
Via #አለ_ህግ #Alehig
https://t.me/lawsocieties
https://t.me/AleHig
Telegram
Amhara Bank
አማራ ባንክ
Website https://amharabank.com.et
Facebook: www.Facebook.com/amharabanksc1
Website https://amharabank.com.et
Facebook: www.Facebook.com/amharabanksc1
ሕግን አለማወቅ ይቅርታን ሊያስገኝ አይችልም። የፍታብሔር ሕግ ቁጥር 2035(2)
Ignorance of the law is no excuse.
civil code article 2035(2)
@lawsocieties @AleHig
Ignorance of the law is no excuse.
civil code article 2035(2)
@lawsocieties @AleHig
አለሕግAleHig ️
https://t.me/lawsocieties https://t.me/AleHig
በትክክል !!!
ዳኛ ከፈጣሪ በታች ውሳኔ ሰጪ አካል ነው ፣ የዳኝነት ስራውንም በተቢው ጥንቃቄ መስራት ይጠበቅበታል ፣ ከጣፍም እሱንም ሆነ ተመልካቹን ሊያሰተምር የሚችል ህጋዊ መሰረት ያለው ቅጣት ሊቀጣ ይገበዋል ።
ነገር ነገር ግን ምክኒያት እየፈለጉ በግለሰብ ጥላቻ የፍትህ መዋቅሩን ( ሌሎችንም መልካም አጋጣሚዎች ) በመጠቅም ዳኛውን እና የዳኝነት ስርዓቱን ማወክ ህዝብን ማወክ ወይም ማስቸገር ነው የሚሆነው !!!
ሰለሆነም የህዝብን ሰላማዊና የተረጋጋ እንቅስቃሴ ለመጠበቅ ካሰፈለገ ለዳኛው ሳይሆን የዳኝነት አገልግሎቱ ለሚያስፈልገው ህዝብ ሲባል የህግ ጥበቃ እንዲደረግለት ማድረግ አንዱ መፍትሔ ነው !!!
ወርቁ መኮነን
ዳኛ ከፈጣሪ በታች ውሳኔ ሰጪ አካል ነው ፣ የዳኝነት ስራውንም በተቢው ጥንቃቄ መስራት ይጠበቅበታል ፣ ከጣፍም እሱንም ሆነ ተመልካቹን ሊያሰተምር የሚችል ህጋዊ መሰረት ያለው ቅጣት ሊቀጣ ይገበዋል ።
ነገር ነገር ግን ምክኒያት እየፈለጉ በግለሰብ ጥላቻ የፍትህ መዋቅሩን ( ሌሎችንም መልካም አጋጣሚዎች ) በመጠቅም ዳኛውን እና የዳኝነት ስርዓቱን ማወክ ህዝብን ማወክ ወይም ማስቸገር ነው የሚሆነው !!!
ሰለሆነም የህዝብን ሰላማዊና የተረጋጋ እንቅስቃሴ ለመጠበቅ ካሰፈለገ ለዳኛው ሳይሆን የዳኝነት አገልግሎቱ ለሚያስፈልገው ህዝብ ሲባል የህግ ጥበቃ እንዲደረግለት ማድረግ አንዱ መፍትሔ ነው !!!
ወርቁ መኮነን
Our Court - Give your verdict!
_______
When a customer returned to collect his property that was to be serviced by a technician and discovered that it was lost, he filed criminal charges for dishonesty against the technician. The technician asserted that he hadn't committed any crime and should instead be held liable for the value of the lost property by the Civil Law.
👨⚖🧑⚖ If you were a judge for this case what would be your judgment, "Is the act a crime?"
Answer here below👇👇👇👇👇
_______
When a customer returned to collect his property that was to be serviced by a technician and discovered that it was lost, he filed criminal charges for dishonesty against the technician. The technician asserted that he hadn't committed any crime and should instead be held liable for the value of the lost property by the Civil Law.
👨⚖🧑⚖ If you were a judge for this case what would be your judgment, "Is the act a crime?"
Answer here below👇👇👇👇👇
If you were a judge for this case what would be your judgment,
"Is the act a crime?"
"Is the act a crime?"
Anonymous Poll
43%
Yes, it's a crime
57%
No, it's not a crime