አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
አዋጅ ቁጥር ፪፻፲፫/፲፱፻፺፪ ዓ.ም
የ ፲፱፻፺፪ ዓ.ም የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አዋጅ


መግቢያ

ቤተሰብ የሕብረተሰብ የተፈጥሮ መነሻ በመሆኑና በሕብረተሰብና በመንግሥት ጥበቃ ሊደረግለት የሚገባ መሆኑን በማመን፤ የመንግሥት ጥበቃ የሚገለጽበት አንዱ መንገድም የቤተሰብ ግንኙነትን በሕግ መደንገግና መግዛት መሆኑን በመገንዘብ፤

በሥራ ላይ ያለው የኢትዮጵያ ሕግ አሁን ካለንበት የሕብረተሰብ የእድገት ደረጃ፤ በዋነኛነትም ከሕገመንግሥቱ ጋር እንዲጣጣም ማድረግ በማስፈለጉና በተለይም ጋብቻ በተጋቢዎች ነፃና ሙሉ ፈቃድ ላይ ብቻ መመሥረት ያለበት መሆኑንና በጋብቻ አፈፃፀም፣ በጋብቻ ዘመንና በፍቺ ጊዜ የተጋቢዎችን የእኩልነት መብት የሚያስጠብቅ ሕግ ማውጣት አስፈላጊ መሆኑን በመገንዘብ፤

የልጆችን ደህንነት፣ አስተዳደግና አጠባበቅን አስመልክቶ ሕገ መንግሥቱና ኢትዮጵያ ያፀደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች በሚጠይቁት መሠረት የሕፃናትን ደህንነት ቀደምትነት በሚሰጥ መልኩ ሕጉን አሻሽሎ መቅረጽ በማስፈለጉ፤

በቤተሰብ ውስጥ የሚነሱ ክርክሮችን ፍትሐዊ በሆነና በተቀላጠፈ ሁኔታ ብቃት ባለው አካል እንዲዳኙ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤

ይህን እውን ለማድረግም ተጠሪነታቸው በቀጥታ ለፌዴራሉ መንግሥት በሆኑ መስተዳድሮች ተፈፃሚነት የሚኖረው የቤተሰብ ሕግ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መውጣት ያለበት በመሆኑ፤

በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ ፶፭ (፩) መሠረት ከዚህ የሚከተለው ታውጇል፡፡

፩ አጭር ርዕስ

ይህ አዋጅ ‹‹የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር ፪፻፲፫/፲፱፻፺፪›› ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡

፪ ሕጉ የሚፀናበት ጊዜ

ይህ የ፲፱፻፺፪ ዓ.ም የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አዋጅ በተለይ በቁጥር ፩/፲፱፻፺፪ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ የታተመው ከሰኔ ፳፯ ቀን ፲፱፻፺፪ ዓ.ም ጀምሮ የፀና ይሆናል፡፡

 

አዲስ አበባ ሰኔ ፳፯ ቀን ፲፱፻፺፪ ዓ.ም

ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት

https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
ምዕራፍ አንድ

ስለ ጋብቻ አፈጻጸም

ክፍል ፩

ጠቅላላ

አንቀጽ ፩ ልዩ ልዩ የጋብቻ አፈፃፀም ሥርዓቶች


፩. ጋብቻ በአንድ የክብር መዝገብ ሹም ፊት ሊፈጸም ይችላል፡፡

፪. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) የተጠቀሰው ቢኖርም፤ ጋብቻ በተጋቢዎቹ ሃይማኖት ወይም ባህል መሠረት ሊፈፀም ይችላል፡፡


አንቀጽ ፪ በክብር መዝገብ ሹም ፊት የሚፈፀም ጋብቻ


ጋብቻ በክብር መዝገብ ሹም ፊት ተፈፀመ የሚባለው አንድ ወንድ እና አንዲት ሴት ጋብቻ ለመፈፀም ተስማምተው በክብር መዝገብ ሹም ፊት በመቅረብ ፈቃዳቸውን ሲገልጹና የክብር መዝገብ ሹሙም ይህንኑ ፈቃዳቸውን ሲቀበል ነው፡፡

 
አንቀጽ ፫ በሃይማኖት ሥርዓት መሠረት የሚፈፀም ጋብቻ


ጋብቻ በሃይማኖት ሥርዐት መሠረት ተፈጸመ የሚባለው፤ አንድ ወንድና አንዲት ሴት በሃይማኖታቸው ወይም ከሁለቱ በአንዳቸው ሃይማኖት መሠረት የሚፀና ጋብቻ ለማቋቋም የሚያስፈልገውን ሥርዓት ሲፈጽሙ ነው፡፡

 
አንቀጽ ፬ በባህል ሥርዓት መሠረት የሚፈፀም ጋብቻ

ጋብቻ በባህል ሥርዓት መሠረት ተፈፀመ የሚባለው፤ አንድ ወንድ እና አንዲት ሴት በሚኖሩበት አካባቢ ባህል ወይም በሁለቱ ተጋቢዎች ወይም ከሁለቱ ተጋቢዎች በአንዳቸው ባህል መሠረት የሚፀና ጋብቻ ለማቋቋም የሚያስፈልገውን ሥርዓት ሲፈጽሙ ነው፡፡
Forwarded from Arey Bin
''First, we use others as a mere if what we do reflects some maxim to which they could not in principle consent. It means that there is nothing wrong about using someone as a means. However, we may fail in our duty ,even when we do not use anyone as a mere means,if we fail to treat others as ends in themselves''.
Do you memoriased this principle?? It needs deep twig!!!!!!!!!

ስኬቴን ባንተ ውስጥ እንጅ ባንተ ላይ ማድረግ አልፈልግም፣ስኬትህን በኔውስጥ እንጅ በኔላይ እንድሆን አልፈቅድም፡፡ውስጠት ሲኖር ተግባቦት አለ ይሄ ካለ ደግሞ ቃል ሳይሆን ልብ ምቱ ይደመጣል ህሊና ማሰቡን ሲቀጥል አይን ማስተዋሉን ይካነዋል፡፡ ከዚህ ማፈንገጥ ግን ከድካም ውጪ ምንም የለውም፡፡በነብሳችን ግማድ በእስትንፋሳችን መስመር ነገን ብርሃን እናደርግ ዘንድ አንዳችን ለአንዳችን ሳይሆን ሁላችንም ስለአንዳችን ውስጠት መሆን ያሻል፡፡
.
.
መልካም ቀን ለሁላችን በያለንበት!!!!!!!!
❗️EXIT❗️

የህግ ት/ቤት የመውጫ ፈተና ውጤት ይፋ ተደርጓል በዚህም የአብዛኛዎቹ(በከፊል ) ወይም የሁሉም ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ማለት በሚቻል መልኩ ፈተናውን ማለፋቸው የተረጋገጠ ሲሆን ከዚህ በተቃራኒው ደግሞ የዩኒቨርሲቲያችን ተማሪዎች በአብዛኛው መውደቃቸው ተሰምቷል የዩኒቨርስቲው የህግ ትምህርት ቤት በዚህ ላይ የሠጠበት ማብራሪያ ባይኖርም ፈተናውን የወሠዱ ተማሪዎች
" ይሄ ውጤት እንደሚመጣ መጀመሪያም አውቀን ነበር የጠበቅነውም ነው ያሉ ሲሆን ውጤቱ ሲመጣ ግን ከጠበቅነውም በላይ ብዙ ተማሪ የወደቀበት ሆኖ አግኝተነዋል ብለዋል ለዚህ ውጤት መምጣት የመጀመሪያ ተጠያቂዎች ራሳችንን እያደረግን ሲሆን ከእኛ በመቀጠል ግን ሀላፊነት መውሰድ ያለበት የህግ ትምህርት ቤት መሆኑ ግን ሁሉም ሊገነዘብ ይገባል ብለዋል"

በመጨረሻም እኛ ያመጣነው ውጤት የህግ ትምህርት ቤት አሁን ያለበትን ደረጃ ማሳያ መሆኑ መረሳት የለበትም ዩኒቨርስቲውም ይሄንን ሊያውቅ ይገባል ብለዋል፡፡

#Debremarkos University
ሰላም ውድ የሁልሳ ቤተሰቦች
በትናንትናው እለት የመውጫ ፈተና (exit) ውጤት መውጣቱን ምክንያት በማድረግ ውድ መምህራችን የሆነው መምህር ይርጋለም ለ3 ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ልጆች የማበረታቻ ሽልማት ሰጥቷል። የተሸለሙትም ተማሪዎች
1. ሀምዛ አብዱ 76 ነጥብ
2. ሄዋን ካሱ 69 ነጥብ
3. ዳዊት መልካሙ 68 ነጥብ

ሁልሳ መላ የህግ ተመራቂዎችንና እነዚህን ተሸላሚዎች እንኳን ደስ አላችሁ እያለ እነደዚህ አይነት ሽልማቶችም በተጠናከረ ደረጃ በህግ ትምህርት ቤቶች ላይ ታስቦበት ቢዘጋጅ ለተማሪዎች ልፋት ዋጋ ትንሽም ብትሆን ማበረታቻ ትሆናለች ብለን እናምናለን።
መምህር ይርጋለምን በጣም እናመሰግናለን።
------
ፎቶ 1 ሀምዛ ከመምህር ይርጋለም ሽልማቱን ሲቀበል።
ፎቶ 2 ሄዋን ባለመገኘቷ በተወካይ ተቀብላለች
ፎቶ3 ዳዊት ባለመገኘቱ በተወካይ ተቀብሏል።
ፎቶ 4 እና 5 ዳዊት አርፍዶ ስለመጣ ከሀምዛ እጅ መፅሐፉን ሲቀበል እናም ሲተቃቀፉ ያሳያል
ፎቶ 6 የተሰጣቸው የመፅሐፍ ፎቶግራፍ ነው።
via hulsa

Credit to HULSA (hulsa)
ለተመራቂ #የሕግ ተማሪዎች የሚሆን ምክር#judicial #training
ዛሬ ትንሽ ስለ የፍትህ ማሰልጠኛና ምርምር ማእከል (judicial training) ትንሽ መረጃ ይዘንላችሁ መጥተናል።
መረጃውን ያካፈለን በ2012 ባች ከሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በከፍተኛ ማእረግ የተመረቀው እንዲሁም የሜዳሊያ ተሸላሚ የሆነው ሀብታሙ ቆይታውን እንዲህ በማለት በድምፅ ለሁሉም የህግ ተማሪዎች አጋርቷል።

🔴ወንድማችን ሃብታሙን እጅግ አድርገን እናመሰግናለን ለሌሎችም ይህንን አርዓያ እንድትከተሉ እንመክራለን።

🟢🟡🔴ሁላችንም ሼር በማድረግ ይህንን መረጃ ለሁሉም የህግ ተማሪዎች እንዲደርስ እናድርግ።
Credit to HULSA (@hulsa) and Helina Bekele
via about law (ስለ_ህግ)
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
ለፓስፖርት አገልግሎት መሟላት ያለባቸው ቅድመ ሁኔታዎች!🟢

1. ለአዲስ ፓስፖርት ጠያቂዎች
1.1 እድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ የሆነ ጠያቂዎች
 የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ ወይም፣
 አገልግሎት ጊዜው ያላለፈበት የመንግስት መ/ቤት መታወቂያ ወይም፣
 ውጭ አገር ነዋሪ ሆነው በሊሴፓሴ የገቡ ከሆነ ወደአገር በገቡ በ6 ወራት ጊዜ ውስጥ
ሊሴፓሴውን ይዘው በመቅረብ መስተናገድ ይችላሉ፡፡
1.2 እድሜያቸው ከ18 አመት በታች ለሆኑ አዲስ ፓስፖርት ጠያቂዎች
o ፓስፖርት ሲጠየቅ ህፃኑ በአካል መቅረብ አለበት፣
1.2.1 ወላጆች ይዘው ሲቀርቡ ማሟላት ያለባቸው
 እድሜው ከ6 ወር በታች ለሆነ ህፃን የሆስፒታል የልደት ማስረጃ በማቅረብ የሚስተናገዱ ሲሆን
ከ6 ወር በላይ ለሆናቸው ህፃናት በወሳ„ኩነቶች የተዘጋጀ የልደት ሰርተፊኬት ማቅረብ
ይኖርባቸዋል፣
 መጠኑ ¾ የሆነ የህፃኑ ሁለት ጉርድ ፎቶ ግራፍ፣
 የወላጅ የቀበሌ /የመንግስት መ/ቤት መታወቂያ ወይም ፓስፖርት/፣
ፓስፖርት ለመቀየር በሚቀርብ ጥያቄ መሟላት ያለባቸው ሁኔታዎች
እድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ ለሆኑ፣
1 የአገልግሎት ጊዜው ያበቃ ወይም ገጽቹ ያለቁ ፓስፖርት ለመቀየር o የቀድሞው ፓስፖርት ከነኮፒው ተያይዞ ሲቀርብ፣ 2 የጠፋ ወይም የተበላሸ ፓስፖርት ለመቀየር
- ፓስፖርቱ ከጠፋ የፖሊስ ማስረጃ ወይም ውጭ ሀገር የጠፋ ከሆነ የገቡበትን ሊሴፓሴ፣ - ፓስፖርቱ ከተበላሸ የተበላሸውን ፓስፖርት ከነኮፒው አያይዞ ማቅረብ፣ ያስፈልጋል።
3 ለፓስፖርት እርማት የሚያስፈልጉ ማስረጃዎች
- ስም ለመለወጥ የፍ/ቤት ማስረጃ፣
- ፓስፖርቱ እና ለእርማት የሚያስፈልጉ መረጃዎች (የልደት ሰርትፍኬት) ዋናው ከነኮፒው መቅረብ አለበት፣ - ከ18 አመት በታች ለሆኑ የፓስፖርት እድሳት ጠያቂዎች
- የህፃኑ ፓስፖርት ዋናው ከነኮፒው፣
- ለማስፈፀም የቀረበው አባት ከሆነ የአባት የቀበሌ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ወይም
የመንግስት መ/ቤት መታወቂያ፣
- እናት ከሆነች የህፃኑን የልደት ሰርትፍጄት፣ የእናት የቀበሌ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት
ወይም የመንግስት መ/ቤት መታወቂያ፣ ማቅረብ ያስፈልጋል።
የህጻኑ የፓስፖርት አገልግሎት ጥያቄ ከወላጅ ውጭ በሞግዚት ፣ በተወካይ እና በጉዲፈቻ የቀረበ ከሆነ
የሞግዚትነት የውክልና የአሳዳጊነት ወይም ጉዲፈቻ አድራጊነት የተፈቀደበት ማስረጃ አግባብ ካለው
መንግስታዊ አካል ማቅረብ ያስፈልጋል።
ማሳሰቢያ፡-
- በጊዜያዊ መታወቂያ አገልግሎት አንሰጥም፣
- ማንኛውም ባለጉዳይ የሚያቀርበው ሰነድ ህጋዊ እና ስርዝ ድልዝ የሌለው መሆን አለበት፣
- በተጭበረበረ ሰነድ ለመስተናገድ መሞከር በህግ ያስጠይቃል፡፡
ለግንዛቤዎ
1. በተደጋጋሚ ወደ ውጭ የሚመላለሱ በመሆኑ ምክንያት የፓስፖርቶ ገጾች ከፓስፖርቱ የአገልግሎት
ጊዜ በፊት ቢያልቅብዎ ባለ 64 ገጽ ፓስፖርት በአገልግሎት ላይ ያዋልን ስለሆነ መጠየቅ ይችላሉ።
2 ፓስፖርት በአስቸኳይ ለማግኘት የሚያስገድድ ሁኔታ ቢገጥሞት ተጨማሪ የአገልግሎት ክፍያ
እንዲሁም ከዚህ በታች የተመለከቱትን ማሟላት የጠበቅበታል፦
 ለህክምና ከሆነ የሕክምና ማስረጃ
 የውጭ የትምህርት ዕድል ያገኙ የጀመሩት ፕሮሰስ የሚያሳይና የተምህርት ማስረጃ
 ለመንግስት ስራ ክሆነ የመስሪያቤቱ ደብዳቤና የመ/ቤት መታወቅያ
 የውጭ አገር ኗሪ ከሆኑ መኖሪያ ፍቃድ ወይም ቪዛ
 ለDV ደርሶት ፕሮሶስ የጀመሩ
 ኢምባሲ ቀጠሮ ካላቸው የኢምባሲ ቀጠሮ ማቅረብ የሚችሉ ከሆኑ
 መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች የሚሰሩ የድርጅቱ መታውቅያና የሚሄዱበት ምክንያት የሚገልጽ
ደብዳቤ ካቀረቡ፣
ነጋዴ ክሆኑ
o የከፈሉበት LC
o የታደሰ ንግድ ፍቃድ
o ውል ያላቸው ከሆኑ ቅድሚያ መስተናገድ ይችላሉ።
3. መንግስት ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሚደረገው ሕገወጥ ስደት በማስቆም ሕጋዊ የውጭ አገር የስራ
ስምሪት ለማጠናከር ቁጥጥር እና ክትትል እያደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል።
በመሆኑም ፓስፖርት ለማውጣት ወደ ኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ ዋና መምሪያ አገልግሎት
መስጪያ ማእከላት ለምትመጡ ዜጎች የሚከተሉት ቅድመ ሁኔታዎች መሟላት
ይተበቅባቸዋል፦
ዕድሜያቸው ከ18 እስከ 55 ዓመት ለሆኑ ዜጎች ላይ ከተዘረዘሩት መስፈርቶች(ምሳሌ የቀበሌ መታወቅያ)
በተጨማሪ፦
 የመንስግት ሰራትኛ መሆናቸው የመ/ቤት መታወቅያ
 ነጋዴ ከሆኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ
 በግል ድርጅት ተቀጣሪ ከሆኑ የመ/ቤቱ ደብዳቤና መታወቅያ
 መንግስታዊ በልሆኑ ድርጅቶች (NGO) ተቀጣሪ ከሆኑ የድርጅቱ ደብዳቤና መታወቅያ
 ለህክምና ለሚሄዱ የሕክምና ማስረጃ
 ለትምህርት ለሚሔዱ የተጻጻፉበት ማስረጀ
 ለጉብኝት ከሆኑ የግብዣ ደብዳቤ
4. በሕጋዊ መንገድ ለሰራ ወደ ውጭ አገር የሚሄድ ማንኛውም ሰራተኛ ከዚህ በታች የተመለከቱትን ማሟላት የጠበቅበታል፦
ሀ) ቢያንስ የስምንተኛ ክፍል ትምህርት ያጠናቀቀ፣ እና
ለ) በሚቀጠርበት የሥራ መስክ አግባብ ካለው የምዘና ማዕከል (ቴክኒክና ሙያ) የሙያ ብቃት ማረጋገጫ
ማስረጃ የያዘ፣ መሆን አለበት፡፡
ሐ) ዕድሜው ከ21 ዓመት በላይ የሆነ፣
መ) የጤና ምርመራ ያደረገ መሆን እንዳአበት ይደነግጋል።
2. አዲስ አበባ ከሚገኘው የዋና መምሪያው ጽሕፈት ቤት በተጨማሪ ከዚህ ቀጥሎ በተገለጹት
ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶችና እንዲሁም በውጭ ሀገራት በሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች ማግኘት
ይችላሉ።
1 ሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት
2 ደሴ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት
3 ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት
4 ባህርዳር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት
5 መቐለ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት
6 ጅማ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት
7. ጅግጅጋ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት
8. ሳመራ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት
9. አዳማ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት
ለበለጠ መረጃ ወይም ለቅሬታ አድራሻችን
ነጻ ስልክ 8133
መደበኛ ስልክ 0111560167 ወይም 0118287216
website www.ethiopianpassportservices.gov.et
Face book, MDINA Ethiopia
ኢሜይል support@ immigration.gov.et
ፖስታ 5741

https://t.me/NegereFej
የአንድ ጥሩ መሪ 10 ዋና ባህሪዎች/10 Key Qualities of a Good Leader🎈

በብዙ ጥናቶች በመመርኮዝ ፣ ምርጥ መሪዎቹ እነዚህን 10 አስፈላጊ የአመራር ባሕርያት በተከታታይ እንደያዙ መለየት ተችሏል።

1. ታማኝነት/Integrity

የቅንነት አስፈላጊነት ግልፅ መሆን አለበት። በሠራተኞች ግምገማዎች ውስጥ የግድ መለኪያ ባይሆንም ፣ ታማኝነት ለግለሰቡ እና ለድርጅቱ አስፈላጊ የአመራር ባህሪ ነው። በተለይም የድርጅቱን አካሄድ ለሚያዘጋጁ እና ስፍር ቁጥር የሌላቸው ሌሎች ጉልህ ውሳኔዎችን ለሚወስኑ ለከፍተኛ ደረጃ ሥራ አስፈፃሚዎች አስፈላጊ ነው። የእኛ ምርምር የሚያሳየው ታማኝነት ለድርጅቶች ዕውር ቦታ ሊሆን ይችላል። ድርጅትዎ በተለያዩ ደረጃዎች ላሉት መሪዎች የሃቀኝነት እና የቅንነት አስፈላጊነትን የሚያጠናክር መሆኑን ያረጋግጡ።

2. የመወከል ችሎታ/Ability to delegate

ውክልና የአንድ መሪ ​​ዋና ኃላፊነቶች አንዱ ነው ፣ ግን ውጤታማ በሆነ መንገድ ውክልና መስጠት ከባድ ሊሆን ይችላል። ግቡ እራስዎን ነፃ ማውጣት ብቻ አይደለም-እንዲሁም ቀጥተኛ ሪፖርቶችዎ እንዲያድጉ ፣ የቡድን ሥራን ለማመቻቸት ፣ ራስን በራስ የማስተዳደር እና ወደ ተሻለ የውሳኔ አሰጣጥ እንዲመሩ ለማስቻል ነው። ምርጡ መሪዎች የበለጠ ውጤታማ በሆነ መንገድ ውክልና ለመስጠት ከሠራተኞች ጋር መተማመንን ይገነባሉ።

3. መግባባት/Communication

ውጤታማ አመራር እና ውጤታማ ግንኙነት እርስ በእርስ የተሳሰሩ ናቸው። ምርጥ መሪዎች መረጃን ከማስተላለፍ ጀምሮ ሌሎችን ከማነሳሳት ጀምሮ ቀጥተኛ ሪፖርቶችን እስከማሰልጠን ድረስ በተለያዩ መንገዶች መገናኘት የሚችሉ የተካኑ የኮሙኒኬተሮች ናቸው። እና በብዙ ሰዎች ሚና ፣ በጂኦግራፊ ፣ በማኅበራዊ ማንነት እና በሌሎችም ላይ ሰፊ ሰዎችን ማዳመጥ እና መገናኘት መቻል አለብዎት። በድርጅትዎ ውስጥ ባሉ መሪዎች መካከል ያለው የግንኙነት ጥራት እና ውጤታማነት የንግድዎን ስትራቴጂ ስኬትም በቀጥታ ይነካል። ውጤታማ ግንኙነት እና የተሻሉ ውይይቶች በእውነቱ የድርጅታዊ ባህልዎን እንዴት ማሻሻል እንደሚችሉ ይወቁ።

4. ራስን ማወቅ/Self-awareness

ይህ ወደ ውስጥ ይበልጥ ያተኮረ ባህርይ ቢሆንም ፣ ራስን ማወቅ እና ትህትና ለአመራር ቀዳሚ ናቸው። እራስዎን በተሻለ ሁኔታ በተረዱት እና የእራስዎን ጥንካሬ እና ድክመቶች በሚያውቁበት ጊዜ እንደ መሪ የበለጠ ውጤታማ ይሆናሉ። ሌሎች ሰዎች እንዴት እንደሚመለከቱዎት ወይም በሥራ ቦታ እንዴት እንደሚታዩ ያውቃሉ? ስለራስ-ግንዛቤ 4 ገጽታዎች እና እያንዳንዱን አካል እንዴት ማጠንከር እንደሚችሉ ለማወቅ ጊዜ ይውሰዱ።

5. ምስጋና/Gratitude

አመስጋኝ መሆን ለራስ ከፍ ያለ ግምት ከፍ እንዲል ፣ የመንፈስ ጭንቀትን እና ጭንቀትን ለመቀነስ እና የተሻለ እንቅልፍን ሊያስከትል ይችላል። ምስጋና እንኳን የተሻለ መሪ ሊያደርግልዎት ይችላል። ሆኖም ብዙ ሰዎች ለአመስጋኝ አለቃ ጠንክረው ለመሥራት ፈቃደኛ እንደሚሆኑ ቢናገሩም በስራ ቅንብሮች ውስጥ አዘውትረው “አመሰግናለሁ” ይላሉ። ምርጥ መሪዎች በሥራ ቦታ ከልብ አመስጋኝነትን እንዴት ማሳየት እንደሚችሉ ያውቃሉ።

6. የመማር ችሎታ/Learning agility

የመማር ቅልጥፍና ምን ማድረግ እንዳለብዎት ሳያውቁ ምን ማድረግ እንዳለብዎት የማወቅ ችሎታ ነው። እርስዎ “ፈጣን ጥናት” ከሆኑ ወይም ባልተለመዱ ሁኔታዎች የላቀ ለመሆን ከቻሉ ቀልጣፋ ትምህርት ይማሩ ይሆናል። ነገር ግን ማንኛውም ሰው በተግባር ፣ በልምድ እና በጥረት የመማር ቅልጥፍናን ሊያሳድግ ይችላል። ለመጀመር ጠንካራ የመማር ችሎታ ያላቸው ታላላቅ መሪዎች እንዴት ታላቅ ተማሪዎች እንደሆኑ ያስሱ።

7. ተፅዕኖ/Influence

ለአንዳንድ ሰዎች “ተጽዕኖ” እንደ ቆሻሻ ቃል ይሰማዋል። ግን በሎጂክ ፣ በስሜታዊ ወይም በትብብር ይግባኝ ሰዎችን ማሳመን መቻል አነቃቂ ፣ ውጤታማ መሪዎችን አስፈላጊ ባህሪ ነው። ተጽዕኖ ከማታለል ፈጽሞ የተለየ ነው ፣ እናም በእውነተኛ እና ግልፅነት መደረግ አለበት። ስሜታዊ ብልህነትን እና መተማመንን ይጠይቃል። ምን ያህል ውጤታማ ተጽዕኖ ማሳደር የጨዋታ-ለዋጭ ሊሆን እንደሚችል የበለጠ ይረዱ።

8. ርኅራኄ /Empathy

ርህራሄ ከስራ አፈፃፀም ጋር የተዛመደ እና የስሜታዊ ብልህነት እና የአመራር ውጤታማነት ወሳኝ አካል ነው። ወደ ቀጥታ ሪፖርቶችዎ የበለጠ የሚያካትት የአመራር እና ርህራሄ ባህሪዎችን ካሳዩ የእኛ ምርምር በአለቃዎ እንደ የተሻለ አፈፃፀም የመታየት ዕድሉ ሰፊ መሆኑን ያሳያል። በተጨማሪም ፣ በዙሪያዎ ላሉት ሰዎች የሥራ ቦታ ሁኔታዎችን ለማሻሻል ርህራሄ እና ማካተት የግድ አስፈላጊ ናቸው።

9. ድፍረት/Courage

አዲስ ሀሳብ ማሰማት ፣ ለቀጥታ ዘገባ ግብረመልስ መስጠት ፣ ወይም ከእርስዎ በላይ ላለው ሰው አሳቢነትን መጠቆም በስራ ላይ ለመናገር ከባድ ሊሆን ይችላል። ድፍረቱ የመልካም መሪዎች ቁልፍ ባህርይ የሆነው የዚህ ምክንያት አካል ነው። ድፍረትን ችግሮችን ከማስወገድ ወይም ግጭቶች እንዲፈጠሩ ከመፍቀድ ይልቅ መሪዎችን ከፍ ለማድረግ እና ነገሮችን በትክክለኛው አቅጣጫ እንዲያንቀሳቅሱ ያስችላቸዋል። ከፍተኛ የስነ -ልቦና ደህንነት እና ጠንካራ የአሰልጣኝነት ባህል ያለው የሥራ ቦታ እውነትን እና ድፍረትን የበለጠ ይደግፋል።

10. አክብሮት/Respect
በየቀኑ ሰዎችን በአክብሮት መያዝ አንድ መሪ ​​ሊያደርጋቸው ከሚችሉት በጣም አስፈላጊ ነገሮች አንዱ ነው። ውጥረትን እና ግጭትን ያቃልላል ፣ መተማመንን ይፈጥራል ፣ እና ውጤታማነትን ያሻሽላል። አክብሮት አለማክበር አለመኖር የበለጠ ነው ፣ እና በተለያዩ መንገዶች ሊታይ ይችላል። በሥራ ቦታ የመከባበርን የአየር ሁኔታ እንዴት ማልማት እንደሚችሉ ወይም ለሌሎች አጋር ሊሆኑ ስለሚችሉባቸው መንገዶች የበለጠ ይማሩ።
ምንጭ የስኬት አስተሳሰብ
ሼር በማድረግ እውቀት ያጋሩ #Share #Share
https://t.me/NegereFej
.......... Trainee Attorney.............
the_united_insurance_company
#legal_services
#law
#attorney
Addis Ababa

Bachelor's Degree in Law with GPA 2.5 and above

Competence:-
- Excellent communication skill and personality
- Written & Spoken English language proficiency
- Excellent computer skill

Minimum Years Of Experience: #0_years

Deadline: September 27, 2021

How To Apply:

Interested applicants who fulfill the above requirements are invited to submit a non-returnable application, CV and supporting documents in person at The United Insurance Company Office, located on Tewodros Square, at United Insurance Building 9th floor, to HR & Administration Office.

https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
Forwarded from Qualitymovbot
⚖️ የሕግ መረጃ የሕግ አገልግሎት የሚሠጠው የኢትዮ ሕግ ቻናል ነው
ይቀላቀሉ🚦
⚖️በማንኛውም ፍርድ ቤት ጠበቃና የሕግ አማካሪ
#AddisAbaba #Hawassa #Dilla
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና አመሰራረታቸው
*************
1. መግቢያ
ዜጎች የተለያዩ መብቶችና ነፃነቶች ያሏቸው ሲሆን ከእነዚህ መብቶች መካከል ተደራጅተው መብትና ጥቅማቸውን ማስጠበቅ አንዱ ነው፡፡ ዜጎች ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፤ ማህበራዊና ባህላዊ መብታቸውን በመደራጀት መከወን ይችላሉ፡፡ በሀገራችን ህገ መንግስት አንቀጽ 31 ላይ እንደተደነገገው ማንኛውም ሰው ለማንኛውም ዓላማ በማህበር የመደራጀት መብት አለው፡፡
ነገር ግን ለህገ ወጥ ዓላማ መደራጀት ወይም ህገ መንግስታዊ ስርአቱን በህገወጥ መንገድ ለማፍረስ የተመሰረቱ ወይም የተጠቀሱትን ተግባራት የሚያራምዱ ድርጅቶች የተከለከሉ ይሆናሉ፡፡ እንዲሁም በመደራጀት መብት ምክንያት ሌላ ሶስተኛ ወገንን ለመጠበቅ የወጡ ህጎችን ወይም የሌላ ሰውን መብት በሚጥስ ሁኔታ መንቀሳቀስ የማይችልና የተከለከለ ነው፡፡

2. ሲቪል ማህበሰረብ ድርጅቶች ምንነት፣ አይነት እና የህግ ማዕቀፍ

የመደራጀት መብት ከሚገለጽባቸው መንገዶች መካከል ዜጎች በሙያና በብዙሃን ማህበራት መደራጀት አንዱ ነው፡፡ በሀገራችን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የረጅም ጊዜ ታሪክ ያላቸው ሲሆን ለትርፍ ያልተቋቋሙ ቦጎ አድራጎት ድረጅቶች ከጥንት ጀምሮ በማህበረሰቡ ዘንድ የዳበረ የእርስ በእርስ መረዳጃ ባህላዊ የሆኑ እንደ ደቦ የመሳሰሉ አደረጃጀቶች እንዲሁም እንደ እቁብና እድር ያሉ አደረጃጀቶች ማህበረሰቡ እርስ በእርሱ የሚተጋገዝባቸውና ገንዘብ መቆጠቢያና መበደሪያ መንገዶች ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡ የእርስ በእርስ መረዳጃ ማህበራት ውጭ በኢትዮጵያ መጀመሪያ የተቋቋሙ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ቀይ መስቀልና የስዊዲሽ ሴቭ ዘ ቺልድረን ሲሆኑ በኋላም እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ1990 መጀመሪያ ጀምሮ በርካታ የሲቪል ማህበራት ተመስርተዋል፡፡

በህገ መንግስቱና ሌሎች ህጎች ለመብቱ የተሰጠው ጥበቃ እንደተጠበቀ ሆኖ የመደራጀት መብት ከሚገለፅባቸው መንገዶች አንዱ የሆኑትን በሙያና ብዙሃን የሚደራጁ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የሚገዛ አዋጅ ቁጥር 621/2001 ወጥቶ ሲተገበር ቆይቷል፡፡ ይህ አዋጅ የመደራጀት መብትን ይበልጥ ከማስከበር አንፃር ገደቦች/ውስንነቶች የነበሩበት በመሆኑ አዋጁ ተሻሽሎ አዋጅ 1113/2011 ሆኖ እንዲወጣ ተደርጓል፡፡

በአዋጅ መሰረት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ቢያንስ ሁለትና ከዚያ በላይ በሆኑ ሰዎች በፍቃደኝነት የሚመሰረት፣ የመንግስት አካል ያልሆነ፣ ለትርፍ ያልተቋቋመ፣ ከማናቸውም የፖለቲካ ድርጅት ያልወገነ እና ህጋዊ ዓላማን ለማሳካት ተመዝግቦ የሚንቀሳቀስ አካል ሲሆን የሞያ ማህበራትን፤ የብዙኃን ማህበራት እና የድርጅቶች ህብረቶችን ይጨምራል፡፡

የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሀገር በቀልና የውጭ ድርጅት በሚል በሁለት የሚከፈሉ ሲሆን ሀገር በቀል ድርጅት በኢትዮጵያ ወይም ከኢትዮጵያ ውጭ ህጋዊ ስራ ለመስራት በኢትዮጵያዊያን፤ በኢትዮጵያ ነዋሪ በሆኑ የውጭ ሀገር ዜጎች ወይም በሁለቱም የሚመሰረት ድርጅት ሆኖ መስራቾቹ ሁለትና ከዚያ በላይ መሆን አለባቸው፡፡ የውጭ ድርጅት በውጭ ሀገር ህግ መሰረት የተቋቋመና በኢትዮጵያ ውስጥ ተመዝግቦ የሚንቀሳቀስ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ነው፡፡

በሌላ በኩል አገር በቀል ድረጅቶች በአምስት አይነት አደረጃጀት የሚቋቋሙ ሲሆን እነዚህም ማህበር፣ ቦርድ መር ድርጅት፣ የዘለቄታ በጎ አድራጎት ድርጅት፣ የአደራ በጎ አድራጎት ድርጅት እና የበጎአድራጎት ድርጅት ናቸው፡፤

3. የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምስረታ

የሲቭል ማህበረሰብ ድርጅቶች አመሰራረት በሚከተሉት መርሆች እንደሚመራ አዋጁ ይደነግጋል፡፡ አነዚህ መርሆችም፤-
• ድርጅቶች ለተወሰነ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ ሊቋቋሙ መቻላቸው
• በድርጅቱ ውስጥ አባል ለመሆን ፍቃደኝነት የግድ ሲሆን ከድርጅቱ በፈለገው ሰአት መውጣት ይቻላል
• አግባብነት ያለውን ህግ መሰረት በማድረግ የአባላት መቀበያ ፎርም ማዘጋጀት
• ማንኛውም ሰው መስፈርቱን ካሟላ የድርጅቱ አባል መሆን መብት አለው
• እያንዳንዱ አባል እኩል ድምጽ አለው
• ድረጅቶች ለአባላት ትርፍ በማሰብ ሊቋቋሙ ኤችሉም
• የድርጅቱ አመሰራረትና ውስጣዊ አሰራር ዴሞክራሳዊ መርሆችን የተከተለ፤ ከአድሎአዊነት የጸዳ፤ ነጻና ገለልተኛ ሊሆን ይገባል፡
• ድርጅቱ የሚመራው በመተዳደሪያ ደንቡ ስልጣን በተሰጣቸው አካላት ሙሉ ተሳትፎ በተመረጡሰዎች ነው፤
• ድርጅቱ በመተዳደሪያ ደንቡ ካልሆነ በስተቀር አባላትን ሊቀበልና ሊያሰናብት አይችልም፡፤

3.1. የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምዝገባ እና መስፈርቶች
ማንኛውም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት የፌደራል መስሪያ ቤት በሆነው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ኤጀንሲ መመዝገብ እንዳለበት በህግ ተቀምጧል፡፡ ለሀገር በቀል ድርጅቶች ምዝገባ በድርጅቱ መስራቾች ሰብሳቢ የተፈረመ ማመልከቻ መቅረብ ያለበት ሲሆን ከማመልከቻው ጋር ተያይዘው መቅረብ ያለባቸው ሰነዶች፤-
• የምስረታ ቃለ-ጉባኤ የመስራቾችን ስምና አድራሻ የያዘ፤
• የመስራቾች መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ኮፒ፤
• የድርጅቱ ስም እንዲሁም አርማ፤
• የድርጅቱ አርማና ሊሰራ ያሰበበት የስራ ዘርፍ፤
• የስራ ቦታ፤
• በመስራቾች የጸደቀ መተዳደሪያ ደንብ፤
• የድርጅቱ አድራሻ፡፡
በሌላ በኩል በውጭ ሀገር የተመሰረተ ድርጅት በኢትዮጵያ ለመመዝገብ ከላይ የተዘረዘሩትን ጨምሮ የሚከተሉትን ሰነዶች ማሟላት ይኖርበታል፡
• ድርጅቱ መቋቋሙን የሚያሳይ ከተቋቋመበት አገር የተሰጠው በአግባቡ የተረጋገጠ ሰነድ፤
• ስልጣን ያለው የድርጅቱ አካል ድርጅቱ በኢትዮጵያ ውስጥ እንዲሰራ ያሳለፈው በአግባቡ የተረጋገተ ውሳኔ፤
• በአገር ውስጥ ተወካዩ የተሰጠው በአግባቡ የተረጋገጠ የውክልና ስልጣን፤ ከተቋቋመበት ሀገር ስልጣን ባለው አካል የተሰጠ የድጋፍ ደብዳቤ ወይም በኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተሰጠ የድጋፍ ደብዳቤ፤
• ከሁለት አመት ላላነሰ ጊዜ የሚተገበር የስራ እቅድ ይዞ መቅረብ የግድ ይላል፡፡

ከላይ የተዘረዘሩት ቅደመ ሁኔታዎች አሟልቶ ያቀረበ ሀገር በቀል ድርጅት በኤጀንሲው ማመልከቻውን ባቀረበ በ30 ቀን ውስጥ እና የውጭ ድርጅት የምዝገባ ማመልከቻውን ከስራ እቅድ ጋር ባቀረበ በ45 ቀን ውስጥ ኤጀንሲው መዝግቦ የምስክር ወረቀት መስጠት ይኖርበታል፡፡ የምዝገባ ማመልከቻ አስገብቶ በተባለው ቀን ውስጥ የምስክር ወረቀት ያልተሰጠው ድርጅት ለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ቦርድ በ30 ቀን ውስጥ ቅሬታውን ማቅረብ ይችላል፡፡ ቦርዱ ምዝገባው ያለአግባብ የተከለከለ መሆኑን ከተረዳ ምስክር ወረቀቱ እንዲሰጠው ያደርጋል፡፡

3.2. ምዝገባ ውድቅ የሚሆነበት ሁኔታ

ማንኛውም ሰው በማንኛውም አላማ የመደራጀት መብት ያለው ቢሆንም ህግ በመጣስ መደራጀት ክልክል ነው፡፡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከላይ በተቀመጠው መሰረት ምዝገባ ለማድረግ የሚያስፈልጉ ሰነዶችን ይዞ ለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ኤጄንሲ ካቀረቡ በኋላ ኤጀንሲው የቀረበለትን የምዝገባ ጥያቄ ከሚከተሉት ምክንያቶች አንዱ መኖሩን ካረጋገጠ ድርጅቱ ያቀረበውን ምዝገባ ውድቅ ሊያደርግ ይችላል፡-
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties