አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ስለ ጋብቻ
***
በራህዋ ተስፋዬ ቸርነት (LL B, LL M, የህግ አማካሪ እና ጠበቃ) ( ነገሩን ፍጁት)

ውድ አንባብያን ዛሬም በዚሀ ጽሁፍ ዳግም ለመናኘት ስለበቃን ደስ ብሎኛል። ዞሮ ዞሮ ከቤት፤ ኑሮ ኑሮ ከመሬት አይቀርምና የሞት መልአክ በራችንን ከማንኳኳቱ በፊት ቃላችንን በኑዛዜ እንዴት በተግቢው ማስፈር እንዳለብን ባለፈው ተነጋግረን ነበር። አሁን ደግሞ የህይወታችንን ታላቁን ስምምነት፤ ትዳርን፤ እንዴት ህጋዊ በሆነ መንገድ አስጀምረን፣ በሀገራችን የፍትህ ማእቀፍ መደላደል እንችላለን የሚለውን ጥያቄ በከፊሉ የምትመልስ አንዲት አጭር ጽሁፍ ይዤ ቀርቤያለሁ። የትዳር ጅምሩን ጋብቻን ትዳስሳለች። መልካም ንባብ።
ለመጋባት ወሰናችሁ እንበል። በመጀመሪያ እንኳን ለዚህ ማዕረግ ፈጣሪ አበቃችሁ። ለሶስት ጉልቻ፣ ለስራና ለክብሩ ደርሳችኋል። የፍቅር የትብብር ያርገው። ወይም ውዶችህ/ውዶችሽ እዚህ ስለደረሱ ምን ማድረግ ይኖረባቸው ይሆን ብላችሁ ያሰባችሁ ደግሞ የናንተ ቢጤ ጠባቂ ይቆያችሁ። ስለ ጋብቻ ህጉ ይህን እንደሚል እነግራችኋለሁ።
፩. በመጀመሪያ ለመጋባት ህጉ ብቁ ናቸው የሚለው እነማንን እንደሆነ እንመልከት። ቤተሰብ ማህበረሰቡ የሚደራጅበት መሰረታዊ መገንቢያ ጡብ በመሆኑ ህጉ ጥበቃ እና ክትትል ያደርግለታል። ይህም ጋብቻው ከተፍፀመ በኋላ ብቻ አይደለም፤ ጋብቻው ከመከወኑ በፊት ከሚከሰቱ እና እንዳይፀና ህልውናውን ሊፈታተኑት ከሚችሉ ግድፈቶችም ጭምር ነው። ስለዚህ ወደ ጋብቻ ሊገቡ ያሰቡ ጥንዶች ራሳቸውንም ትዳራቸውንም ለመጠበቅ በእነዚህ መስፈርቶች መመራት ግዴታቸው ነው። ከምንም ነገር በፊት ጋብቻ እንዲጸና ተጋቢዎች ያልተገደበ፣ ሙሉ ፈቃዳቸውን መስጠት አለባቸው። ይህ በመሆኑ በሀይል የተደረገ ጋብቻ ህጋዊ መሰረት እንደማይኖረው ግልፅ ነው። መሰረታዊ ስህተት ተሳስተው የፈፀሙት ጋብቻም ቢሆን እንደሁኔታው ፈራሽ ይሆናል። ቢሆንም የትኛውም ስህተት ትዳር አያፈርስም፤ በህጉ ስር መሰረታዊ ስህተት የሚባሉትም የሚክተሉት ናቸው፡ የሚያገባው ሰው ማንነት አግቢው ከጠበቀው ሌላ ሲሆን፤ ያገባው ሰው ሊድን የማይችል ወይም ወደ ሌሎች ሊተላልፍ የሚችል ከባድ በሽታ ኖሮበት ይህንን ሳያውቅ አግቢው ካገባው፤ ሌላኛው ግለሰብ ግብረስጋ ግንኙነት መፈጸም የማይችል ከሆነና አግቢው ይህን ሳያውቅ ትዳር ከመሰረተ፤ ወይም ተጋቢው ግብረ ሰዶማዊ ግንኙነት የሚፈጽም መሆኑን ሳያውቅ የትዳር አጋሩ ካደረገው ናቸው። እዚህ ላይ አንድ ህጉ በተዘዋዋሪ የሚናገረው ነገር  ስላለ ልብ ሳትሉ እንዳታልፉ ልጠቁማችሁ።  አንድ ሰው ከላይ እንደተገለጸው አይነት ከባድ በሽታ ኖሮበት ወይም ግንኙነት መፈጸም የማይችል ግለሰብ ሆኖ ለተጋቢው ከመጋባታቸው በፊት ካሳወቀው እና ተጋቢው በጋብቻው ለመቀጠል ከወሰነ ጥንዶቹ የመጋባት ሙሉ ህጋዊ መብት አላቸው። ጋብቻ የፍቅር እና የመተጋገዝ ስምምነት ነው። መታመም እና ወሲባዊ ድክመት ይህንን እውነታ ስለማያስቀሩ ተቻችለው አብረው ለመሆን ለቆረጡ ህጉ ጥበቃ አይከለክልም።  
በግለሰቦች ማንነት እና/ወይም ሀጋዊ ሁኔታ ምክንያት የሚሰጡ ከልከላዎችም አሉ። እነዚህም በዘመዳሞች (በወላጆችና ተወላጆች፣ ወንድም እና እህት፣ በአክስቶች እና አጎቶች ወደታች ከሚቆጠሩ ዘመዶቻቸው፣ በትዳር በተፈጠር ዝምደናም፣ ዝምድናው ያልተረጋገጠ ግን በማህበረሰቡ በሰፊው የሚገመት ከሆነ እንኳን) መካክል ጋብቻን መፈጸም፤ በህግ የተከለከለን ሰው ማግባት እና/ወይም ፍቺ ከፈጸመች 180 ቀን ያልሞላትን ሴት ማግባት ህጉ አይፈቅድም። ከፈታች 180 ቀን ያለፋት ሴት ግን በዚህ ጊዜ ውስጥ ከወለደች ከማግባት አትከለከልም።
ደግሞ አንዳንድ ሁኔታዎች ሲሟሉ ስለሚቀሩ ክልከላዎች እናውራ። በፌደራል ህጉ መሰረት የማግቢያ ትንሹ አመት 18 ነው። ነገር ግን እንደክልሉ ህግ ይህ እድሜ ሊበልጥ ወይም ሊያንስ ይችላል። በፌደራል ህግ ራሱ እድሜው ያልደረሰ አንድ ልጅ ነፃ ወጥቶ ራሱን መቻል ይችላል። ይህ ልጅ ላግባ ቢል አይከለከልም። በተጨማሪም ለፍርድ ቤቶች በሚገባ አቤቱታ ይህንን የእድሜ መስፈርት ከሁለት አመት ላላነሰ ጊዜ ማስቀነስም ይቻላል። ሌላው ክልከላ አስቀድሞ ያገባን ይመለከታል። ዋናው መስፈርት ለአንድ ሰው አንድ አጋር ብቻ ቢሆንም በባህል እና በሃይማኖት በሃገራችን ውስጥ ከአንድ ሚስት በላይ ማግባት እንደሚቻል ይታወቃል። ይህ በህጉ እውቅና ተሰጥቶታል። በመጨረሻም በመርህ ደረጃ ጋብቻን በወኪል ወይም እንደራሴ መፈፀም አይቻልም። ተጋቢዎቹ በአካል ቃላቸውን ለመስጠት መገኘት አለባቸው። ነገር ግን ተጋቢዎች በሁኔታዎች የሚገደዱ ከሆነ እና ወካዩም ተጋቢ ፈቃዱን በማያሻማ ሁኔታ ካሳወቀ ጋብቻ በውክልና መፈጸም ይቻላል።  
፱. ስለዚህ እነዚህ ጉድለቶች እንዳሉ እየታወቀ ጋብቻ ቢፈጸም ምን ይፈጠራል? በመሰረቱ ግድፈት አለበት የተባለ ትዳር እንዲፈርስ ነው የሚደረገው። ይህ ቢሆንም ግን የሚፈርስበት ሁኔታ በግድፈቱ ይወሰናል። በዘመዳሞች መካከል የሚደረግ ጋብቻ በማንኛውም ጊዜ ይህ ለህግ አስፈጻሚ አካላት ግልፅ የተደረገ እንደሆነ አንዲፈርስ ይደረጋል። በአንጻሩ እድሜያቸው ያልደረሰ ስዎች የሚፈጽሙት ጋብቻ፤ ባለ ጋብቻ ላይ የተፈፀመ ጋብቻ፤ በፍርድ የተከለከለ ሰው የሚፈፅመው፤ በሃይል እና/ወይም በስህተት የተፈፀሙ ጋብቻዎች ፈራሽ ቢሆኑም እንኳ ተጋቢዎቹ ወይም በህግ ይህንን አሳውቀው ማስፈርስ የሚችሉ ሁሉ በተወሰነ ጊዜ ግድፈት መኖሩን ካላሳወቁ ቀሪ መሆን የሚችሉት በፍቺ ብቻ ይሆናል ማለት ነው። ህጉ ይህንን የጊዜ ወሰን በስድስት ወር ቢበዛም በሁለት አመት ይወስነዋል። ለምን እነዚህ ግድፈቶች ስለኖሩ ብቻ ጋብቻው ቀሪ አይሆንም ብለን እንጠይቅ ይሆናል። መልሱ ቀላል ነው። ግድፈት አለበት ሰለተባለ ብቻ ጋብቻን የሚያህል ነገር ማስቀረት ተገቢ አይደለም ብሎ ህጉ ስለሚያምን። ለምሳሌ በህግ የተከለከለው ሰው ወንጀል ሰርቶ ይሆናል። ስለዚህ ወንጀለኛ ማፍቀር ማግባት የለበትም? ወይም ሶስት አመት በሰላም ከኖሩ በኋላ አስገድዶ ስላገባት ትዳር የለም ብሎ የሚመጣ ሰው ፍትሃዊ ጥያቄ አነሳ ማለትስ? እዚህ ጋር በምንም መልኩ የህጉ ሚዛን ሳያዘነብል ቆመ እያልኩ አይደለም። ግን በአብዛኛው ከላይ የተጠቀሱት ሁኔታዎች ጋር ተጋቢዎች መኖር ከቻሉ ህጉ ስለእነርሱ ለመወሰን እንደማይፈልግ እየገለጸ ነው እያልኩ እንጂ።
በሌላ ጎኑ ግድፈት ሳይሆኑ ናቸው ተብለው ስለሚታመኑ ጥያቄ የሚፈጥሩ ጉዳዮች አሉ። ስለዚህ ህጉ በግልጹ ይህን ያስቀምጣል፡  የፈታች ሴት ብቻዋን መኖር ባለባት ጊዜ ካገባች፤ የመዝገብ ሹም የተባለ ሰው ስልጣን ሳይኖረው ጋብቻን ካስፈፀመ፤ እና የጋብቻ የፎርም ወይም የይዘት ጉድለት ትዳርን የሚያህል ነገርን የማስቀርት ብቃት የላቸውም።  
፭. አሁን ወደ ገደለው እንዙር። እንዴት መጋባት እንችላለን? ከአንድ በላይ አማራጭ አለላችሁ። በሃይማኖታዊ እና በባህላዊ ስርዓት ወይም አስተዳደራዊ አካል ፊት መጋባት ይቻላል።  ብትሉ በቤተክርስትያን ወይም በሼሁ ፊት ፈጣሪያችሁን እያከበራችሁ፤ በባህላዊ ጭፈራ እና ወግ ደምቃችሁ፤ ሲያሻችሁ ደግሞ ቀለል ባለ መልኩ እናነተ እና ምስክሮቻችሁን ክቡር መዝገብ ፊት አቅርባችሁ በማክሰኞ ከሰዓት እንጋባ ብትሉ የሚገባው ትዳር እኩል ነው። ህጉም ጥበቃ ያደርግለታል። ከኢትዮጵያ ውጭ ተጋብታችሁ መጣችሁ? ችግር የሚባል እንደሌለበት የሚጠፋው ያለ አይመስለኝም።
፮. የቤተሰብ ህጉ የክብር ሹም ብሎ የሚጠራው፣ በፌደራል ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ የውሳኝ ኩነት ኤጅንሲ ቢሮዎች ውስጥ የሚደረግ ጋብቻ ከተጋቢዎቹ አንዱ ሳያቋርጥ ቢያንስ ለስድስት ወር በኖረበት ቀበሌ ውስጥ ባለ ወኪል ቢሮ መፈጸም ይችላል። ተጋቢዎች ለክቡር መዝገቡ ለመጋባት ያላቸውን ፍላጎት ሲያሳውቁ ይሄው ቢሮ እንዳላገቡ ማስረጃ እንዲያቀርቡ ሊጠይቃቸው ይችላል። በዚህ ጊዜ ወይም የስርጋቸው ቀን ተጋቢዎች ጉርድ ፎቶ ይዘው እንዲመጡም ይታዘዛሉ። ማስረጃውን ከያዘ በኋላ ካመለከቱበት ቀን ቢያንስ አንድ ወር የሚቆይ ቀን ቆርጦ ያሰናብታቸዋል። በቀኑ ተጋቢዎች ብቻቸውን መቅረብ የለባችሁም። ሁለታችሁም ሁለት ሁለት ምስክሮች ይዛችሁ ካልመጣችሁ ሂደቱ መቀጠል አይችልም። ይህ ሲሟላ ግን ተጋቢዎች ጋብቻ ለመፈጸም ብቁ እንደሆናችሁ ለክብር መዝገብ ሹሙ በቃለ መሃላ ታሳውቃላችሁ። ለመጋባት ፈቃደኛ እንደሆናችሁ ትገልጻላችሁ። መዝገብ ሹሙ ደግሞ የምትሰጡት ቃል የሚያስከትለውን ውጤት ያስረዳችኋል። ይህን አውቃችሁ ስትቀጥሉ እናንተ እና ምስክሮቻችሁ በሚቀርብላችሁ (ትልቅና ወፍራም) መዝገብ ላይ ትፈርሙና ጋብቻችሁን ትፈፅማላችሁ ማለት ነው። ከዚያ በኋላ ክቡር መዝገቡ አስፈላጊውን መረጃ የያዘውን የጋብቻ ሰርቲፊኬታችሁን ያስረክባችሁና ጨርሳችሁ ትወጣላችሁ ማለት ነው።
፯. በባህል እና በሃይማኖት የሚፈጸሙ ጋብቻዎች እንደሃይማኖቱ ወይም ባህሉ እንደሚወስኑ ግልጽ ቢሆንም ከላይ የተገለጸውን የፈቃድ እና የችሎታ መስፈርቶች ማሟላት ይኖርባቸዋል። በባህላዊ እና ሀይማኖታዊ ተቋማትም ለከወኑት ጋብቻ ሰርቲፊኬት ስለሚሰጡ መጠየቅ ቸል አትበሉ። በተጨማሪም የተፈጸመው ጋብቻ በወሳኝ ኩነቶች መመዝገብ የሚጸናው ከተፈጸመበት ቀን እንጂ ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ እንዳልሆነ አንባቢ ያስተውል።  
፰. ለተጋቢዎች የሚሰጥ ሰርቲፊኬት ምን መርጃዎችን ይይዛል? የተጋቢዎቹ ሙሉ ስም እና የተወለዱበትን ቀን፤ ጋብቻው የተፈጸመበትን ቦታ (ከፍለ ከተማ እና ወረዳ)፤ ጋብቻው የተፈጸመበትን ቀን፣ ወር እና አመተ ምህረት፤ ጋብቻው ሲደረጉ የነበሩ ምስክሮችን ሙሉ ስሞች፤ የተጋቢዎቹ እና የምስክሮቻቸው ፊርማ፤ ሰርቲፊኬቱን ያወጣው ባለስልጣን ስም፤ ሰርቲፊኬቱ የወጣበት ቀን እና የተጋቢዎቹ ፎቶዎች ናቸው። ውሳኝ ኩነቶች ኤጅንሲ የተጋቢዎች መዝገብ የመያዝ ሀላፊነት በህጉ ተጥሎበታል። ይህ በመሆኑ የተጋቢዎች ሰርቲፊኬት በማንኛውም አጋጣሚ ቢበላሽ ወይም በጠፋ ግልባጭ ማውጣት ይቻላል።
፱. ጋብቻ ሊፈፅሙ ያሰቡ ግለሰቦች በትንሹ ከላይ የተዘረዘሩትን ማወቅ ይጠቅማቸዋል አላለሁ። መብትን ማወቅ የመፍትሄ ምንጭ ነውና ስለህጉ ማወቅ ጠቃሚ እንደሆነ እናገራለሁ። ግን ምን አንባቢ ብንሆንም በጉግል ስርች ብቃታችን ሀኪም ሆንን ብለን ከሆስፒታል እንደማንቀረው ሁሉ ከችግር ጋር ስንጋፈጥ የህግ ባለሙያ ጥበቃን እንጠቀምበት። ጠበቃ እና ነገረፍጅ አማክሩ። ይህንን የምታነቡ ግለሰቦች የትዳር ውጤት እና ማግባት ህይወታችን ላይ የሚኖረውን መሰረታዊ እና ዘርፈ ብዙ ውጤት በተገቢው ለመጠቀም ሁለገብ የህግ እውቀት ያለውን ባለሙያ እንደታካትቱበት እመክራችኋለሁ። ይችንም እንደ አንድ ተጨማሪ አውቀት ያዟት።

2015። የፀሃፊዋ መብት በህግ የተጠበቀ ነው።
የህግ ጥያቄዎች አሏችሁ? የህግ ምክር ለማግኘትም ሆነ ጉዳያችሁን እንደራሱ የሚጨርስ ባለሙያ ባስፈለጋችሁ ጊዜ ቫርኒሮ አደባባይ ደንድር ህንፃ በሚገኘው ቢሯችን ብቅ ይበሉ።
Via lawyer Daniel Fikadu
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
አለ_ህግ🔵Ale_Hig:
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ
#Share #ሼር
#አለ_ህግ #Alehig
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties

https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ 
ማስታወቂያ

የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ  ቤት የጥብቅና ፍቃድ ለማግኘት ይቻል ዘንድ ፈተናው ጥቅምት 03 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚሰጥና ፈተናው የሚሰጥበት ቦታና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች በቀጣይ  ማስታወቂያ የሚገለፅ ስለመሆኑ በ23/01/2016 ዓ.ም በማስታወቂያ መነገሩ ይታወቃል፡፡ 

  በዚሁ መሰረት የፈተና ኮድ የሚሰጠው ጥቅምት 01 እና 02 ቀን 2016 ዓ.ም በፍትህ ሚኒስቴር ሲሆን ፈተናው የሚሰጥበት ቦታ ደግሞ ፒያሳ ከጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን  ከፍ ብሎ በሚገኘው በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አዳራሽ በመሆኑ ፈተናው ከሚጀመርበት ከጥዋቱ 3.00 በፊት በፈተናው ቦታ እንድትገኙና ከህግ ኮዶች በስተቀር ምንም አይነት ፅሁፍ ይዞ መገኘትም የተከለከለ መሆኑን እንድታውቁ  በጥብቅ እናሳስባለን፡፡

መረጃውን #share #like በማድረግ ላልደረሳቸው እንድታሳውቁ እንጠይቃለን::

መረጃዎች በፍጥነት እንዲደርሷችሁ የፌስ ቡክ ገፃችንን በሚከተለው መስፈንጠሪያ ይቀላቀሉ::


#ethiopianfederalbarassociation

የኢትዮዽያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር

መስከረም 29 ቀን 2016ዓ.ም
አዲስ አበባ ፤
ለፍትህ አሰጣጥ ተገቢ ሆኖ ሲገኝ ክርክሩ በማናቸውም ደረጃ በሚገኝበት ጊዜ ቀድሞ መስክረው የነበሩትን ምስክሮች ፍ/ቤቱ እንደገና አስጠርቶ ማናቸውንም ተገቢ መስሎ የታየውን ጥያቄ ሊጠይቃቸው ይችላል (ቁ. 266)።

https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ
#Share #ሼር
#አለ_ህግ #Alehig
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties

https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ 
ውድ የ2015 ትምህርት ዘመን ተፈታኞች በሙሉ

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ነገ በ29/01/2016 ዓ.ም ከጥዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ተፈታኞች የሚከተሉትን ሶስት አማራጭ አድራሻዎችን ብቻ በመጠቀም ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ፡፡
• በዌብ ሳይት፡- eaes.et
• በአጭር የጽሁፍ መልዕክት፡- 6284
• ቴሌግራም አድራሻ፡- @eaesbot

ጥብቅ ማሳሰቢያ፡-

ከላይ ከተገለጹት የውጤት መግለጫ አማራጮች ውጪ ሌላ የውጤት መግለጫ መንገዶች የሌሉ መሆኑን እያሳወቅን በማመሳሰል ውጤት እንገልጻለን ከሚሉ ከማንኛውም አጭበርባሪዎች እራስዎን ይጠብቁ። በተጨማሪም ተቋሙ ውጤት ለማሳየት ክፍያ የማይጠይቅ መሆኑን ይወቁ።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

አጠቃቀም
በዌብ ሳይት ለማየት

1. eaes.et ብለው ብሮውዘር ላይ ይጻፉ
2. በመቀጠልም በሚመጣው ገጽ ላይ የአድሚሽን ቁጥር (ሬጅስትሬሽን ቁጥር) እና የመጀመሪያ ስም ይጻፉ
3. Check Result የሚለውን በመጫን ውጤትዎን ማግኘት ይችላሉ
በአጭር የጽሁፍ መልዕክት
6284 የአድሚሽን ቁጥር (ሬጅስትሬሽን ቁጥር ) ብቻ ጽፎ አንዴ ብቻ በማላክ መልስ እስኪያገኙ ይጠብቁ
በቴሌግራም ቦት
1. @eaesbot ይፈልጉ
2. የሚመጡ አማራጮችን በመከተል የአድሚሽን ቁጥር (ሬጅስትሬሽን ቁጥር) ያስገቡ በመቀጠልም መልስ እስኪያገኙ ይጠብቁ።
የከርታታው መምህር መልእክት!
*
#ዩኒቨርስቲ_ገነት_አይደለም‼️

ከስር ያያዝኩት የ#Masters_Degreeዬ ውጤት ነው ፤ የዚህ ልጥፍ ዓለማ ራስን ማንቆለጳጰስ ምናምን ሳይሆን ልፋቴ እና የሚከፈለኝ አለመገናኘቱ ሲቀጥል ዩኒቨርስቲ መግባት እና ትምህርት መስቀል ትርጉም አልባነቱን እንዲሁም 12ኛ ክፍል ውጤት ላልመጣላቸው መጽናኛ እንዲሆናቸው ነው።

በአንድ የመንግስት ዩኒቨርስቲ መምህር ነኝ፤ከህይወቴ 17 ዓመት ለመጀመሪያ ድግሪ ሁለት ዓመት ደግሞ ለMasters ድግሪ በአጠቃላይ 19 ዓመታትን ያጠፋሁበት በትምህርት ነው።

በመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም Highschool እና መሰናዶ ጓደኛቼ የነበሩ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያላመጡ እና በተለያዩ የሙያ የንግድ እና የመሳሰሉ ነገሮች ላይ የተሰማሩ በአሁኑ ሰዓት የቤት አከራዮቼ ናቸው ፤ ባለመኪና ባለሆቴል ጽድት ያለ ቡቲክ ብቻ ምን አለፋህ በአጠቃላይ ከእኔ እጅግ በጣም በተሻለ የኑሮ ሁኔታ ነው የሚገኙት!😭

በአሁኑ ሰዓት በመንግስት ዩኒቨርስቲ ሁለተኛ ድግሪ የያዘ የዩኒቨርስቲ መምህር የሚከፈለው ደመውዝ ግብር ሳይቀነስ 12,579 ብር ነው ፤ 35% ግብር እንዲሁ የጡረታ ሲወጣ ኪሴ የሚገባው 9956(ዘጠኝ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሀምሳ ስድስት)ብር ነው።

እንግዲህ በትምህርት ደረጃዬ ሲወራልኝ የዩኒቨርስቲ መምህር ነኝ ፤ ሶስተኛ ድግሪዬን ብሰራ እና ዶ/ር አበባየሁ ጌታ ብባል ወደ 16,000 ብር ከታክስ በፊት እና ወደ 13,000 ብር ገደማ ከታክስ በኋላ እጄ ላይ ይደርሳል።

እና ለምንህ ነው ዩኒቨርስቲ ቀረብኝ ብለህ የምትጨነቀው?

ወዳጄ/ወንድሜ/እህቴ 12 ኛ ክፍል የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት አልመጣልህም?

እሰይ እንኳንም አልመጣልህም! ራስህን ለመቀየር ታትር ፣ አጫጭር ኮርሶችን ከዩቲዩቭ አውርድ ፣ተማር ፣ቪዲዮ ቱቶሪያል ተከታተል ፣ ግራፊክስ እና የመሳሰሉ ገንዘብ ልትሰራ የምትችልባቸው ከምርጥ ኮንተንት ጋር ከመጣህ የዩቲዩብ ስራዎች ብቻ ብዙ ብዙ አማራጮች አሉህ፣ ተስፋ አትቁረጥ! በበሰበሰ ስረዓተ ትምህርት ብዙ ባለድርሻ አካላት ሀላፊነቱን ባልወሰዱበት ከስር ተጀምሮ ባልተሰራ ስራ እና ሰረዓት ተምረህ መጥተህ መጨረሻ ላይ ብትወድቅ(የመስዋዕት በግ ብትሆን) ብቻህን ተጠያቂ አይደለህም! ራስህን ብቻ አትውቀስ! እልፍ በል! ታገል! እመነኝ ታመሰግነኛለህ!

በተመዘገበው ውጤት ልቡ የደማው የአንተው ከርታታው መምህር ወዳጅህ!
#አበባየሁጌታ
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ
#Share #ሼር
#አለ_ህግ #Alehig
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties

https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ 
★ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ0 አመት አዲስ የስራ ማስታወቂያ

Deadline: October 15, 2023.

Commercial Bank of Ethiopia Invites fresh graduates for the following trainee job position.

Professions: LLM in Law, Computer science, Information Science, MIS, Electrical and Computer Engineering or Information Technology and related fields with zero year of experience.

🔻Experience: 0 Years/ Fresh Graduates

🔻Salary Offer: As per Company Scale

How to Apply??
👇👇👇👇👇
https://effoysira.com/commercial-bank-of-ethiopia-vacancy-fresh-graduates/
የፍትሐብሔር ክርክር ሂደት፡-
ከክስ አቀራረብ እስከ ፍርድ አሰጣጥ

.

በዚህ ጽሑፍ የተብራሩ የፍትሐብሔር ክርክር ሂደት ደረጃዎች፡-

👉 የክስ ማመልከቻን መመርመር

👉 ለተከሳሽ መጥሪያ መላክ

👉 የመከላከያ መልስን መመርመር

👉 የጽሑፍ ማስረጃ ስለሚቀርብበት ጊዜና ሁኔታ

👉 የጽሑፍ ክርክር የማቀባበል ሥራን ማጠናቀቅ

👉 ክስን መስማት

👉 የሦስተኛ ወገኖች ጣልቃ ገብነት ወይም ክስ ውስጥ መግባት

👉 ተከራካሪዎችን መመርመር

👉 በመጀመሪያ ደረጃ ክርክር ላይ የሚቀርቡ መቃወሚያዎች

👉 የክርክሩን ጭብጥ መያዝ

👉 ለምስክሮች መጥሪያ መላክ

👉 ምስክሮችን መመርመር

👉 ፍርድ  

https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ
#Share #ሼር
#አለ_ህግ #Alehig
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties

https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ 
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Lawyer Mike 🔊የህግ ባለሙያ)
#እርቅ በወንጀል ጉዳዮች ያለው ፋይዳ!

#አገራችን ኢትዬጲያ የበርካታ ብሄር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ፤ ቋንቋዎች ፣ ባህሎች እና ወጎች ፣ ያላት ሀገር ነች፤የሀገራችን ህዝቦች የየራሳቸውን የሆነ ባህል /ወግ፣ አለባበስ እንዲሁም አገር በቀል የሆነ የዕርቅ፣ የሰላም መጠበቂያ እና የሰላም ግንባታ ስነ-ዘዴዎችም ያሏቸው ህዝቦች ናቸው፤ሀገር በቀል የሰላም መስሪያ ፣ የሰላም መጠበቂያና የሰላም ግንባታ ዘዴ የምንለው ኢ-መደበኛ የሆነው እና ማህበረሰቡ ከአያት ቅድመ አያቶቹ የወረሰው ሰነ-ዘዴ ነው፡፡

#በመሆኑም በእንግሊዘኛው አጠራር non-state based customary institutions የሚያመላክት ሆኖ በዚህ የሰላም እና የፍትህ ስርዓት በዳኝነት የሚቀመጡት መንግስት የሾማቸው ዳኞች ሳይሆኖ ማህበረሰቡ አምኖና ተቀብሎ ለዳኝነት የሾማቸው ባለ ልዪ ተስጦኦ የሆኑ የዕድሜ ባለፀጋ ሽማግሌዎች፤ባህላዊ መሪዎች እና ሀይማኖት አባቶች ሲሆኑ በዚህ ሂደት ውስጥም ትልቅ ሚና ይጫወታሉ፡፡

ይህ መልካም የሆነ ታሪክ እና ባህል በቂ ነው ባይባልም በህጉም እውቅና ተሰጥቶት የነበረ ሲሆን በፍርድ ቤቶችም ጭምር በወንጀል አድራጊው እና ተበዳይ መካከል እርቅ ሲበረታታ ይታያል፡፡ በሁሉም የወንጀል አይነቶች እርቅ መታረቅ ያልተከለከለ ሲሆን ነገር ግን እንደወንጀሉ አይነት እና በጠቅለላዉ እርቁ ፍትህን የማያረጋግጥ በሆነ ጊዜ ከሆነ እርቁ ተፈጻሚ የማይደረግ ሲሆን ነገር ግን ከተፈፀመው ወንጀል ክብደት አንጻር ፍ/ቤቶች ፍርድ ከሰጡ በኀላ ለቅጣት ማቅለያነት ይጠቀሙታል፡፡

#በወንጀል ህጉ በእርቅ ሊያልቁ የሚችሉ ወንጀሎችን በአፈፃፀሙ እና ቅጣቱ ቀላል በመሆኑ የህብረተሰቡን ሰላም እና መልካም ግንኙነት ተጠብቆ ለማቆየት እንደሚጠቅም ተመልክተዋል፡፡
ሌላው በወንጀል ጉዳይ የመታረቅ ጥቅሙ፡ -የመዝገብ ክምችትን ይቀንሳል፣ ከእስራት ይልቅ በእርቅ ማለቁ ለሁለቱም ወገን ዘላቂ ሰላም ያመጣል፣ በወንጀል አድራጊው ላይ የባህሪ ለውጥ ሊመጣ ስለሚችል፣ እንዲሁም የፍርድ ቤቶችን የስራ ጫና እና የተከራካሪዎችን ግዜ ፣ ወጭ እና ጉልበት ያቀላል፡፡

#ከዘህም ባሻገር እርቅ ቀጣይነት ያለውን ሰላም በማስፈን፣የተጎዳን በመካስ ብሎም ሁለንተናዊ የሆነ ማህበራዊ ተግባቦትን በመመለስ ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው፡፡ ነገር ግን እርቅና የተለያዩ አማራጭ የግጭት መፍቻ ሀገር በቀል እውቀቶችና ስርዐቶች እየተረሱና እየተሸረሸሩ በመሄዳቸው በአገራችን በተለያዩ አካባቢዎች በተፈጠሩ ግጭቶችና አለመግባባቶች ምክንያት በርካታ ዜጎች ለመፈናቀል ለሞት እና ለንብረት ውድመት ሰለባ የሆኑባቸው አጋጣሚዎች ተከስተዋል፡፡

#በመሆኑም በአገር በቀል የግጭት አፈታት እና የዕርቅ ሥርዓቶች ላይ ትኩረት በማደረግ ወደ ቦታቸው መመለስ እንዲሁም በህግ ማዕቀፎቻችንም በሰፊው እንዲካተቱና እውቅና እንዲያገኙ ማድረግ ህብረተሰቡን በሰፊው የሚጠቅም ከመሆኑም በላይ በፍትህ ዘርፉ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመሠረታዊነት የሚፈታ በመሆኑ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፡፡

#ድሬዳዋ ፍትህ ፀጥታና ህግ ጉዳዬች ቢሮ
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ
#Share #ሼር
#አለ_ህግ #Alehig
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties

https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ 
Discussion on United Nations Children Right Convection Policy and Current Approach in Ethiopia
When: Thu, Oct 12, 2023
Location: https://maps.google.com/?cid=14199953463616262745&entry=gps
🇺🇸University of Michigan Dearborn Scholarship 2023-24 in USA (Funded)

University: University of Michigan-Dearborn
Degree level: Undergraduate Degree
Scholarship coverage: $40,000
Eligible nationality: All Nationalities
Award country: United States
Last Date: 15 November 2023

👉 Apply Link: http://bit.ly/3T9t5t4
🇺🇸Application Opens for the Fully Funded Community Solutions Program 2024 in the USA

Funding Type: Fully funded
Region in : USA
Deadline: November 1, 2023

💰Financial Support:

1) J-1 visa support
2) Round-trip travel
3) Monthly allowance to cover housing, meals, and other living expenses while in the U.S.
4) Accident and sickness health coverage

👉Apply Link Here :-
https://bit.ly/3PUrpm9
★ በ0 አመት የወጣ የስራ ማስታወቂያ
People in Need (PIN) NGO Career Opportunity

Deadline: October 13, 2023

People in Need is a non-governmental, non-profit organization founded on the ideals of humanism, freedom, equality and solidarity. 

Position: HR intern

🔻Requirements: Minimum BA degree in Management, Human Resource Management, Law other related social science fields of study from a recognized higher education institution

How to Apply??
Click Here to Apply Online
👇👇👇👇👇👇
https://effoysira.com/people-in-need-vacancy-intern/
:
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Lawyer Mike 🔊የህግ ባለሙያ)
መሰረታዊ የሕግ ስህተት በአዲሱ የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
አንድ ጉዳይ የመጨረሻ ፍርድ ከተሰጠው በኋላ መሰረታዊ የህግ ስህተት ተፈፅሞበታል የሚባል ከሆነ መሰረታዊ የህግ ስህተቱ ሳይታረም እንዳይቀር በሰበር ለመታየት ዕድል ይሰጠዋል፡፡ ቀደም ሲል መሰረታዊ የህግ ስህተት ምንነት የህግ ትርጉም ያልተሰጠው የነበረ በመሆኑ ጉዳዮች መሰረታዊ የህግ ስህተት አለባቸው በሚል በብዛት ሲቀርቡ ይስተዋል ነበር፡፡ ይህን ለማስቀረት አዲሱ የፍርድ ቤቶች አዋጅ መሰረታዊ የህግ ስህተትን ምንነት ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ የመሠረታዊ የሕግ ስህተት ምንነትን እና ተያያዥ ጉዳዮችን እንመለከታለን፡፡

የመሠረታዊ የሕግ ስህተት ምንነት

በአዲሱ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀፅ 2(4) መሠረት “መሠረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት” ማለት

. የሕገ-መንግሥቱን ድንጋጌዎች የሚቃረን

ለ. ሕግን አላግባብ የሚተረጉም ወይም ለጉዳዩ አግባብነት የሌለውን ሕግ የሚጠቅስ

ሐ. ለክርክሩ አግባብነት ያለው ጭብጥ ያልተያዘበት ወይም ከክርክሩ ጋር የማይዛመድ አግባብነት የሌለው ጭብጥ የተያዘበት

መ. በዳኝነት ታይቶ ሊወሰን የሚገባውን ጉዳይ ውድቅ የተደረገበት

ሠ. በፍርድ አፈፃፀም ሂደት ከዋናው ፍርድ ጋር የማይገናኝ ትእዛዝ የተሰጠበት

ረ. ጉዳዩን አይቶ የመወሰን የዳኝነት ሥልጣን ሳይኖር ውሳኔ የተሰጠበት

ሰ. የአስተዳደር አካል ወይም ተቋም ከሕግ ውጭ ውሳኔ የሰጠበት

ሸ. የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎትን አስገዳጅ ውሳኔ በመቃረን የተወሰነ
እና ፍትህን የሚያዛባ ጉልህ የሕግ ስህተት ያለበት የመጨረሻ ውሳኔ፣ ፍርድ፣ ብይን፣ ትዕዛዝ ሲሆን መሰል ስህተት ያለባቸው ጉዳዮች በዚህ አዋጅ አንቀፅ 10 መሠረት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሚታረሙ ይሆናል፡፡ የመጨረሻ ውሳኔ ማለት በፍርድ ቤት፣ በህግ የመዳኘት ስልጣን በተሰጠው አካል፣ በተቋማት ወይም በአማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች የተሰጠ እና ለጉዳዩ እልባት የሚሰጥ ፍርድ፣ ብይን፣ ትዕዛዝ ውሳኔ ሲሆን የይግባኝ ሂደቶችን የጨረሰ ፍርድ፣ ብይን፣ ትዕዛዝ ወይም ውሳኔን እንደሚጨምር በአዋጁ አንቀፅ 2(5) ትርጓሜ ተሰጥቶታል፡፡

የጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ስልጣን

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ስልጣን የመነጨው ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 80(3)(ሀ) ሲሆን መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበትን ማናቸውንም የመጨረሻ ውሳኔ ለማረም በሰበር ችሎት የማየት ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡ በዚህም በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/13 አንቀፅ 10 መሰረት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለባቸውን የፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት በይግባኝ አይቶ የመጨረሻ ውሳኔ የሰጠባቸውን ጉዳዮች የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት የመጨረሻ ውሳኔ የሰጠባቸውን ጉዳዮች የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወይም የክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በህገ መንግስቱ በተሰጣቸው የውክልና ስልጣን ፌደራል ጉዳይን አይተው መጨረሻ ውሳኔ የሰጡበት ጉዳይ
የአዲስ አበባ ወይም የድሬደዋ ከተማ ፍርድ ቤት የመጨረሻ ውሳኔ የተሰጠባቸው የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የህገ መንግስቱ ድንጋጌዎች እና የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎቶች አስገዳጅ ውሳኔ ጋር በተያያዘ የመጨረሻ ውሳኔ የተሰጠባቸው ጉዳዮች የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ህግን አለአግባብ ከመተርጎም እና ለጉዳዩ አግባብነት የሌለውን ህግ ከመጥቀስ ጋር በተያያዘ የመጨረሻ ውሳኔ የተሰጠባቸው እና ጉዳዮቹ ለህዝብ ጥቅም ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው ውሳኔዎች በህግ የመዳኘት ስልጣን ተሰጠው አካል ወይም በሌሎች አካላት የተሰጠ የመጨረሻ ውሳኔ አግባብነት ያላቸው የህግ ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆነው በፌደራል ፍርድ ቤት ሊታይ ይችል በነበረ ጉዳይ ላይ በአማራጭ የክርክር መፍቻ ዘዴዎች መሰረት የተሰጡ የመጨረሻ ውሳኔዎች እንዲሁም በሌሎች ህጎች የተጠቀሱ ጉዳዮች በሰበር አይቶ የማረም ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡

አንድ ጉዳይ በሰበር ሲታይ ከአምስት ያላነሱ ዳኞች ሊሰየሙ እንደሚገባ በአዋጁ አንቀፅ 25(2) ተደንግጓል፡፡ ከአምስት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት የሚሰጠው የሕግ ትርጉም በየትኛውም ደረጃ ላይ በሚገኝ የፌዴራል ወይም የክልል ፍርድ ቤት ላይ አስገዳጅነት እንደሚኖረው ከአንቀፅ 10(2) መረዳት ይቻላል፡፡

ይህን አምስት ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት የተሰጠው አስገዳጅ ውሳኔ ሰባት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት በድጋሚ ሊታይ ይችላል፡፡ ይህ የሚሆነው በባለጉዳዮች አመልካችነት ወይም በችሎቱ በራሱ አነሳሽነት ቀድሞ የሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም በተለያዩ ምክንያቶች ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው በሰባት ዳኞች ችሎት እንዲታ በቂ እና አሳማኝ ምክንያቶችን ተንትኖ በመግለፅ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሲያቀርብ እንደሆነ ከአንቀፅ 26(1) መረዳት ይቻላል፡፡ በዚህ መልኩ ጥያቄ ሲቀርብ ፕሬዝዳንቱ ጉዳዩ ሰባት ዳኞች በሚሰየሙበት ችሎት እንዲታይ የሚያደርግ ሲሆን በችሎቱ የሚሰጠው ውሳኔ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በማንኛውም ደረጃ ፍርድ ቤት አስገጃጅ ይሆናል፡፡

በተጨማሪም ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት ቀድሞ የሰጠውን የህግ ትርጉም ከሰባት ባላነሱ ዳኞች በተመሳሳይ ጭብጥ በሌላ ጊዜ ሊሻሻል ይችላል፡፡

ማጠቃለያ

በአጠቃላይ የሰበር ሥርዓት መሰረታዊ ህግ ስህተት ያለበት የመጨረሻ ውሳኔ የተሰጠበት ጉዳይ ለመጨረሻ ጊዜ የሚታይበትና እና የሚታረምበት የዳኝነት ሂደት ነው፡፡ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት ምንነት ደግሞ በአዋጁ የተገለፀ በመሆኑ ለሰበር የሚቀርቡ ጉዳዮች ይህንን ተከትለው መቅረብ አለባቸው፡፡

በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #law https://t.me/lawsocieties
"ማንኛውም የጋራ መኖሪያ ቤት (ኮንዶሚኒየም) የተሰጠው በልማት ምክንያት የተፈናቀለ አርሶ አደር ወይም ቤተሰብ ቤቱ ከተሰጠው ዕለት ጀምሮ እስከ አሥር ዓመት ባለው ጊዜ ውስጥ ለሌላ አካል በማንኛውም መንገድ [ከውርስ ውጭ] ማዛወር አይችልም::"

በልማት ምክንያት ከይዞታቸው ለተፈናቀለ ተጎጂ አርሶ አደሮችና ቤተሰቦቻቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 28/2013 አንቀፅ 10

ዳንኤል ፍቃዱ ተስፋዬ በሁሉም የፌደራል ፍርድ ቤቶች ጠበቃና የህግ አማካሪ
ስልክ - 0913158507
ወይም 0978554559
Daniel Fikadu Tesfaye Certified Attorney of law at all Federal Courts of Ethiopia.
Email- nurotekore@gmail. Com
⚖️⚖️Ethiopian Law by Daniel Fikadu channel ⚖️⚖️⚖️
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ
#Share #ሼር
#አለ_ህግ #Alehig
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties

https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ