አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.83K photos
25 videos
1.86K files
3.55K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ማስታወቂያ

የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ  ቤት የጥብቅና ፍቃድ ለማግኘት ይቻል ዘንድ ፈተናው ጥቅምት 03 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚሰጥና ፈተናው የሚሰጥበት ቦታና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች በቀጣይ  ማስታወቂያ የሚገለፅ ስለመሆኑ በ23/01/2016 ዓ.ም በማስታወቂያ መነገሩ ይታወቃል፡፡ 

  በዚሁ መሰረት የፈተና ኮድ የሚሰጠው ጥቅምት 01 እና 02 ቀን 2016 ዓ.ም በፍትህ ሚኒስቴር ሲሆን ፈተናው የሚሰጥበት ቦታ ደግሞ ፒያሳ ከጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን  ከፍ ብሎ በሚገኘው በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አዳራሽ በመሆኑ ፈተናው ከሚጀመርበት ከጥዋቱ 3.00 በፊት በፈተናው ቦታ እንድትገኙና ከህግ ኮዶች በስተቀር ምንም አይነት ፅሁፍ ይዞ መገኘትም የተከለከለ መሆኑን እንድታውቁ  በጥብቅ እናሳስባለን፡፡

መረጃውን #share #like በማድረግ ላልደረሳቸው እንድታሳውቁ እንጠይቃለን::

መረጃዎች በፍጥነት እንዲደርሷችሁ የፌስ ቡክ ገፃችንን በሚከተለው መስፈንጠሪያ ይቀላቀሉ::


#ethiopianfederalbarassociation

የኢትዮዽያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር

መስከረም 29 ቀን 2016ዓ.ም
አዲስ አበባ ፤