#ኢትዮጵያ የፀጥታ እና የደህንነት ተቋማትን እምርታ በማረጋገጥ ላይ መሆኗ ተመለከተ::
#ኢትዮጵያ የፀጥታ እና የደህንነት ተቋማትን እምርታ በማምጣት ላይ መሆኗን ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ #ተመስገን_ጥሩነህ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ በሚሰጠው ስልጠና ላይ አመላከቱ።
ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ የፀጥታ እና የደህንነት ተቋማትን በመገንባት ረገድ የረጅም ጊዜ ባለ ታሪክ መሆኗንም ገልፀዋል።
የዛሬው የሥልጠና ርዕሰ ጉዳይ "የፀጥታና ደህንነት እመርታ" የሚል ሲሆን በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ለኢፌድሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት የጽህፈት ቤቶች አመራሮች የሥልጠናው ገለፃ በክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ ቀርቧል።
ክቡር ም/ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ተመስገን ባቀረቡት ገለፃ ሀገራችን የፀጥታና የደህንነት ተቋማትን በመገንባት ረጅም አመታትን ማስቆጠር ብቻ ሳይሆን እነዚህ ተቋማት የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ከማስጠበቅ አልፈው እንደ ኮሪያ፣ ኮንጎ እና በሌሎች ሀገራት በመሰማራት ሰላም የማስከበር ሀገራዊ ሀላፊነታቸውን መወጣት የቻሉ ናቸው ብለዋል።
ተቋማቱ የየራሳቸው ጥንካሬ ቢኖራቸውም የነበረባቸው ክፍተት ሊያርም በሚችል መልኩ አሁን ላይ በክቡር ጠቅላይ ሚንስትሩ አነሳሽነት ወቅቱን በሚመጥን ደረጃ የሪፎርም ሥራ በመሠራቱ ከፍተኛ አቅም ለመፍጠር ተችሏል ሲሉ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ በሚሰጠው ስልጠና ላይ ተናግረዋል።
#ኢትዮጵያ የፀጥታ እና የደህንነት ተቋማትን እምርታ በማምጣት ላይ መሆኗን ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ #ተመስገን_ጥሩነህ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ በሚሰጠው ስልጠና ላይ አመላከቱ።
ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ የፀጥታ እና የደህንነት ተቋማትን በመገንባት ረገድ የረጅም ጊዜ ባለ ታሪክ መሆኗንም ገልፀዋል።
የዛሬው የሥልጠና ርዕሰ ጉዳይ "የፀጥታና ደህንነት እመርታ" የሚል ሲሆን በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ለኢፌድሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት የጽህፈት ቤቶች አመራሮች የሥልጠናው ገለፃ በክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ ቀርቧል።
ክቡር ም/ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ተመስገን ባቀረቡት ገለፃ ሀገራችን የፀጥታና የደህንነት ተቋማትን በመገንባት ረጅም አመታትን ማስቆጠር ብቻ ሳይሆን እነዚህ ተቋማት የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ከማስጠበቅ አልፈው እንደ ኮሪያ፣ ኮንጎ እና በሌሎች ሀገራት በመሰማራት ሰላም የማስከበር ሀገራዊ ሀላፊነታቸውን መወጣት የቻሉ ናቸው ብለዋል።
ተቋማቱ የየራሳቸው ጥንካሬ ቢኖራቸውም የነበረባቸው ክፍተት ሊያርም በሚችል መልኩ አሁን ላይ በክቡር ጠቅላይ ሚንስትሩ አነሳሽነት ወቅቱን በሚመጥን ደረጃ የሪፎርም ሥራ በመሠራቱ ከፍተኛ አቅም ለመፍጠር ተችሏል ሲሉ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ በሚሰጠው ስልጠና ላይ ተናግረዋል።
👍19
ዘመኑ የኢኮኖሚ፣ የቴክኖሎጂ የበላይነት ፉክክር የሚታይበት ብቻ ሳይሆን የጦርነትም በመሆኑ ኢትዮጵያም ከየትኛውም አካል የሚሰነዘርባትን ጥቃት ለመከላከል የሚያስችል የራሷን የፀጥታና ደህንነት ተቋማትን የመገንባትና በሪፎርም የማጠናከር ሥራ ሠርታለች፤ ትሰራለችም፤ ሲሉ አስገንዝበዋል።
በመሆኑም መከላከያን ጨምሮ በፀጥታ ተቋማት፣ በኢትዮጵያ የመረጃና ደህንነት፣ በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት እና በፋይናንስ ደህንነት የተጠናከረ የሪፎርም ሥራ መሰራቱንም ነው ክቡር ም/ጠቅላይ ሚንስትር ተመስገን ጥሩነህ ያብራሩት።
የክቡር ም/ጠቅላይ ሚንስትሩ ገለፃ ዛሬ 6ኛ ቀን ባስቆጠረው ሥልጠና ላይ ቀጥሏል።
በመሆኑም መከላከያን ጨምሮ በፀጥታ ተቋማት፣ በኢትዮጵያ የመረጃና ደህንነት፣ በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት እና በፋይናንስ ደህንነት የተጠናከረ የሪፎርም ሥራ መሰራቱንም ነው ክቡር ም/ጠቅላይ ሚንስትር ተመስገን ጥሩነህ ያብራሩት።
የክቡር ም/ጠቅላይ ሚንስትሩ ገለፃ ዛሬ 6ኛ ቀን ባስቆጠረው ሥልጠና ላይ ቀጥሏል።
👍19
#የአመራር_የሥነ_ምግባር_እመርታ በሀገረ መንግሥት ግንባታ ውስጥ ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ::
የአመራር መልካም ሥነ-ምግባር እመርታ በሀገረ መንግሥት ግንባታ ውስጥ አስፈላጊ በመሆኑ የአመራሩ ሥነ-ምግባር መላበስ ወሳኝ ነው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ክቡር #ጌዲዮን_ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ በሚሰጠው ስልጠና ላይ አሳሰቡ።
የአመራር መልካም ሥነ-ምግባር እመርታ በሀገረ መንግሥት ግንባታ ውስጥ አስፈላጊ በመሆኑ የአመራሩ ሥነ-ምግባር መላበስ ወሳኝ ነው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ክቡር #ጌዲዮን_ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ በሚሰጠው ስልጠና ላይ አሳሰቡ።
👍16
የአመራሩ የሥነ-ምግባር ጉድለት የሀገርን ህልውና አደጋ ላይ ሊጥል እንደሚችል በመገንዘብ ተገቢውን ሥራ መሥራት ይገባል ብለዋል።
ክቡር #ዶ/ር_ጌዲዮን "የስነ-ምግባራዊ እመርታ፤ ከሞራል ብልሹነት ወደ ግብረገባዊ አርኣያነት" በሚል የሥልጠና ርዕስ ላይ ለኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት የጽህፈት ቤቶች አመራሮች ገለፃ አቅርበዋል።
ክቡር ሚንስትሩ ሰለ #ሥነ-ምግባር፣ #ግብረገብ ፣ #ሞራል፣ #ዲሲፒሊን ልዩነትን እና አንድነትን በተመለከተ ፍልስፍናዊ ዳራዎችንና አብነቶችን በመጥቀስ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ በሚሰጠው ስልጠና ላይ አብራርተዋል።
የሥነ-ምግባር ዋነኛ መገለጫዎችን በዝርዝር ያነሱት ክቡር ዶ/ር ጌዲዮን ሥነ-ምግባር #በግለሰብ፣ #በቤተሰብ፣ #በቡድን፣ #በተቋም ደረጃ እንደሚገለፅ ጠቁመዋል።
በተቃራኒው የአመራሩ የሥነ-ምግባር ብልሹነት #የግል_ጥቅምን_ብቻ_መመልከትን፣ #በዘር_መከፋፈልንና_ፅንፈኝነትን፣ #ሙስናንና_ብልሹ_አሰራርን የሚያስፋፋ ከሆነ እና የመልካም አስተዳደር እጦት የሚኖር ከሆነ #በሕዝብና_በመንግሥት_መካከል_አሉታዊ_ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ ምክንያት እንደሚሆን አስገንዝበዋል።
ለዚህም እንደ ሊባኖስ ያሉ ሀገሮች ከውጭ ሀገሮች ጣልቃገብነት ይልቅ በሀገራቸው የተንሰራፋው ሙስናና በስልጣንን አለ አግባብ መጠቀም 80 በመቶ የሚሆነውን ሕዝብ ለከፋ ድህነት እና ሀገሪቱን ለአደጋ ማጋለጡን በአብነት አንስተዋል። በመሆኑም በአመራሩ ሥነ-ምግባር ላይ ብዙ መሥራት ይገባል ብለዋል።
በመጨረሻም ክቡር ሚንስትር #ጌዲዮን_ጢሞቲዎስ ኢ- ሥነምግባራዊ በሆኑ መንገዶች የሚገኝ ጥቅምም ሆነ ማንኛውም ነገር ዘላቂነት እንደሌለው አስገንዝበው አመራሩ #መልካም_ሥነ-ምግባርን_በመላበስ እና #መርህን_በመከተል ሕዝቡንና ሀገሩን በማገልገል ኢትዮጵያን የማበልጸግ አደራ አለበት ብለዋል።
#በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ እየተሰጠ ያለው ስልጠና ዛሬም ለ7ኛ ቀን ቀጥሏል።
ክቡር #ዶ/ር_ጌዲዮን "የስነ-ምግባራዊ እመርታ፤ ከሞራል ብልሹነት ወደ ግብረገባዊ አርኣያነት" በሚል የሥልጠና ርዕስ ላይ ለኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት የጽህፈት ቤቶች አመራሮች ገለፃ አቅርበዋል።
ክቡር ሚንስትሩ ሰለ #ሥነ-ምግባር፣ #ግብረገብ ፣ #ሞራል፣ #ዲሲፒሊን ልዩነትን እና አንድነትን በተመለከተ ፍልስፍናዊ ዳራዎችንና አብነቶችን በመጥቀስ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ በሚሰጠው ስልጠና ላይ አብራርተዋል።
የሥነ-ምግባር ዋነኛ መገለጫዎችን በዝርዝር ያነሱት ክቡር ዶ/ር ጌዲዮን ሥነ-ምግባር #በግለሰብ፣ #በቤተሰብ፣ #በቡድን፣ #በተቋም ደረጃ እንደሚገለፅ ጠቁመዋል።
በተቃራኒው የአመራሩ የሥነ-ምግባር ብልሹነት #የግል_ጥቅምን_ብቻ_መመልከትን፣ #በዘር_መከፋፈልንና_ፅንፈኝነትን፣ #ሙስናንና_ብልሹ_አሰራርን የሚያስፋፋ ከሆነ እና የመልካም አስተዳደር እጦት የሚኖር ከሆነ #በሕዝብና_በመንግሥት_መካከል_አሉታዊ_ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ ምክንያት እንደሚሆን አስገንዝበዋል።
ለዚህም እንደ ሊባኖስ ያሉ ሀገሮች ከውጭ ሀገሮች ጣልቃገብነት ይልቅ በሀገራቸው የተንሰራፋው ሙስናና በስልጣንን አለ አግባብ መጠቀም 80 በመቶ የሚሆነውን ሕዝብ ለከፋ ድህነት እና ሀገሪቱን ለአደጋ ማጋለጡን በአብነት አንስተዋል። በመሆኑም በአመራሩ ሥነ-ምግባር ላይ ብዙ መሥራት ይገባል ብለዋል።
በመጨረሻም ክቡር ሚንስትር #ጌዲዮን_ጢሞቲዎስ ኢ- ሥነምግባራዊ በሆኑ መንገዶች የሚገኝ ጥቅምም ሆነ ማንኛውም ነገር ዘላቂነት እንደሌለው አስገንዝበው አመራሩ #መልካም_ሥነ-ምግባርን_በመላበስ እና #መርህን_በመከተል ሕዝቡንና ሀገሩን በማገልገል ኢትዮጵያን የማበልጸግ አደራ አለበት ብለዋል።
#በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ እየተሰጠ ያለው ስልጠና ዛሬም ለ7ኛ ቀን ቀጥሏል።
👍17
"ሙስናንና ብልሹ አሰራርን በመታገል ረገድ የምክር ቤት አባላት ሚና ከፍተኛ ነው"
---- የተከበሩ አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ----
የሀገራችንን ህልም እውን ለማድረግ ሙስናንና ብልሹ አሰራርን በመታገል ረገድ የምክር ቤት አባላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ በሚሰጠው ስልጠና ላይ አሳሰቡ።
---- የተከበሩ አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ----
የሀገራችንን ህልም እውን ለማድረግ ሙስናንና ብልሹ አሰራርን በመታገል ረገድ የምክር ቤት አባላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ በሚሰጠው ስልጠና ላይ አሳሰቡ።
👍13
የምክር ቤት አባላት በሀገራችን የተጀመረው የለውጥ ጉዞ እንዳይቀለበስ እና ዳር እንዲደርስ ሙስናንና ብልሹ አሠራርን ከመታገል ባሻገር በዕውቀትና በሥነ-ምግባር የታነፀ ዜጋ በማፍራት ለሀገራቸው ብልፅግና አሻራቸውን እንዲያስቀምጡም ጥሪ አቅርበዋል።
የተከበሩ አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ይህን ያሉት "የሥነ-ምግባራዊ እመርታ፤ ከሞራል ብልሹነት ወደ ግብረገባዊ አርኣያነት" እና "ሰብአዊ ዕመርታ" በሚሉ ርዕሶች ለኢፌድሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት የጽህፈት ቤቶች አመራሮች በተሰጠው ሥልጠና ዙሪያ ከሠልጣኞች ለቀረቡ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ነው።
የተከበሩ አፈ-ጉባኤ ለለውጡ መምጣት ገፊ ከሆኑት ምክንያቶች ውስጥ የሥነ-ምግባርና ብልሹ አሰራሮችን ተከትለው የመጡ የፍትሕ፣ የፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል ችግሮች እንዲሁም የመልካም አስተዳደር እጦት ተጠቃሽ መሆናቸውን አስረድተዋል።
ከለውጡ በፊት የልማት ባንክን እና የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ በርካታ ፕሮጀክቶ ለሙስናና ምዝበራ ተጋልጠው እንደነበረ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ በሚሰጠው ስልጠና ላይ አስታውሰዋል።
አሁን ላይ መንግስት እነዚህን ተቋማት መልሶ በማደራጀት ከኪሳራ እየታደጋቸው መሆኑንም ነው የተናገሩት። ይህ ሲባል ግን በለውጡ መንግሥት ምንም አይነት የሥነ-ምግባር እና የሙስና ችግር የለም ማለት እንዳልሆነ እና አልፎ አልፎ በአንዳንድ ግለሰቦች፣ በውስን አመራሮችና በተቋማት የሚታዩ ትንንሽ ችግሮች የሉም ለማለት አይቻልም ብለዋል።
ይሁን እንጂ እዚህም እዛም የሚታዩ ትንንሽ ችግሮች ስጋት እንዳይሆኑ የምክር ቤት አባላት በሚያደርጉት የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች ብልሹ አሠራሮች እንዲስተካከሉ መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል።
"እኛም የምክር ቤት አባላት" አሉ የተከበሩ አፈ-ጉባኤ ሙስናንና ኢፍትሐዊ አሠራርን ለመታገል መንግሥት ቁርጠኛ በመሆኑ እንደ አባልና እንደ አመራር በቁርጠኝነት ልንታገል ይገባል ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል ።
ስለዚህም ጥቃቅን ችግርችም ቢሆኑ በእንጭጭነታቸው መቀጨት እንዳለባቸው መንግሥት ስለሚያምንና ቁርጠኛም በመሆኑ በሺህ የሚቆጠሩ ኃላፊዎች ላይ እርምጃ የመውሰድ፣ የሀብት ምዝገባ እና ሙስናን የመከላከል ስትራቴጂ ተቀርፆ ወደ ሥራ መገባቱንም ነው በምላሻቸው ያስገነዘቡት።
በመጨረሻም የተከበሩ አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ይህ የመንግሥት ዕቅድ እንዲሳካ የምክር ቤት አባላት በሕግ ማዕቀፍ፣ በክትትልና ቁጥጥር ሥራቸው ውስጥ በማካተትና በትኩረት በመስራት ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ በሚሰጠው ስልጠና ላይ አሳስበዋል።
(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)
የተከበሩ አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ይህን ያሉት "የሥነ-ምግባራዊ እመርታ፤ ከሞራል ብልሹነት ወደ ግብረገባዊ አርኣያነት" እና "ሰብአዊ ዕመርታ" በሚሉ ርዕሶች ለኢፌድሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት የጽህፈት ቤቶች አመራሮች በተሰጠው ሥልጠና ዙሪያ ከሠልጣኞች ለቀረቡ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ነው።
የተከበሩ አፈ-ጉባኤ ለለውጡ መምጣት ገፊ ከሆኑት ምክንያቶች ውስጥ የሥነ-ምግባርና ብልሹ አሰራሮችን ተከትለው የመጡ የፍትሕ፣ የፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል ችግሮች እንዲሁም የመልካም አስተዳደር እጦት ተጠቃሽ መሆናቸውን አስረድተዋል።
ከለውጡ በፊት የልማት ባንክን እና የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ በርካታ ፕሮጀክቶ ለሙስናና ምዝበራ ተጋልጠው እንደነበረ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ በሚሰጠው ስልጠና ላይ አስታውሰዋል።
አሁን ላይ መንግስት እነዚህን ተቋማት መልሶ በማደራጀት ከኪሳራ እየታደጋቸው መሆኑንም ነው የተናገሩት። ይህ ሲባል ግን በለውጡ መንግሥት ምንም አይነት የሥነ-ምግባር እና የሙስና ችግር የለም ማለት እንዳልሆነ እና አልፎ አልፎ በአንዳንድ ግለሰቦች፣ በውስን አመራሮችና በተቋማት የሚታዩ ትንንሽ ችግሮች የሉም ለማለት አይቻልም ብለዋል።
ይሁን እንጂ እዚህም እዛም የሚታዩ ትንንሽ ችግሮች ስጋት እንዳይሆኑ የምክር ቤት አባላት በሚያደርጉት የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች ብልሹ አሠራሮች እንዲስተካከሉ መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል።
"እኛም የምክር ቤት አባላት" አሉ የተከበሩ አፈ-ጉባኤ ሙስናንና ኢፍትሐዊ አሠራርን ለመታገል መንግሥት ቁርጠኛ በመሆኑ እንደ አባልና እንደ አመራር በቁርጠኝነት ልንታገል ይገባል ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል ።
ስለዚህም ጥቃቅን ችግርችም ቢሆኑ በእንጭጭነታቸው መቀጨት እንዳለባቸው መንግሥት ስለሚያምንና ቁርጠኛም በመሆኑ በሺህ የሚቆጠሩ ኃላፊዎች ላይ እርምጃ የመውሰድ፣ የሀብት ምዝገባ እና ሙስናን የመከላከል ስትራቴጂ ተቀርፆ ወደ ሥራ መገባቱንም ነው በምላሻቸው ያስገነዘቡት።
በመጨረሻም የተከበሩ አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ይህ የመንግሥት ዕቅድ እንዲሳካ የምክር ቤት አባላት በሕግ ማዕቀፍ፣ በክትትልና ቁጥጥር ሥራቸው ውስጥ በማካተትና በትኩረት በመስራት ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ በሚሰጠው ስልጠና ላይ አሳስበዋል።
(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)
👍16
#ዜና_ሹመት
ክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) #ወ_ሮ_መሠረት_ደስታን #የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ_ምክትል_ርዕሰ_አካዳሚ እንዲሆኑ ሹመት ሰጥተዋል።
የአካዳሚው አመራር እና ሰራተኛ መልካም የስራ ዘመንን ይመኛል።
ክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) #ወ_ሮ_መሠረት_ደስታን #የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ_ምክትል_ርዕሰ_አካዳሚ እንዲሆኑ ሹመት ሰጥተዋል።
የአካዳሚው አመራር እና ሰራተኛ መልካም የስራ ዘመንን ይመኛል።
👍22
በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የፕሮግራም ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ሆነው የተመደቡት ወ/ሮ መሰረት ደስታ ከዘርፉ ዳይሬክተሮችና ከተቋሙ የሪፎረም ኮሚቴ አባላት ጋር ውይይት አደረጉ።
በውይይቱ ላይ ወ/ሮ መሰረት ደስታ እንደጠቀሱት በግል እና በመንግስት ተቋማት ላይ በብዙ ዘርፎች እንዳገለገሉ ገልጸው ወደዚህ አካዳሚ ከመመደባቸው በፊት በጠቅላይ ሚ/ር ጽ/ቤት በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ እንዳገለገሉም ተናግረዋል፡፡
ምክትል ርዕሰ አካዳሚዋ የአፍሌክስን ራዕይ ከግብ ለማድረስ ከተቋሙ አመራር እና ሰራተኛ ጋር ለመስራት እንደሚተጉ ተናግረው፤ ተቋሙ በህግ የተሰጠውን ተልዕኮ እንዲያሳካ ሰፊ ስራ መስራት እንደሚጠበቅ አስገንዝበዋል።
የአካዳሚው የሪፎርም ኮሚቴ አባላትና የዘርፉ ዳይሬክተሮች በበኩላቸው ለምክትል ርዕሰ አካዳሚዋ መልካም የስራ ዘመን ተመኝተው፤ በተቋሙ ውስጥ የሪፎርም፤ ማስፋት እና ሽግግር ስራዎች ያሉበትን ደረጃ ጠቅሰው፤ ወደፊት መከናወን ያለባቸው ስራዎች ላይ ማብራሪያና ገለፃ አድርዋል፡፡
ወ/ሮ መሰረት ደስታ ከውይይቱ በቂ ግንዛቤ እንደወሰዱ ተናግረው፤ ለሀገረ መንግስት ግንባታ ሂደት አካዳሚው ብዙ መስራት እንዳለበት አስታውቀዋል፡፡
በውይይቱ ላይ ወ/ሮ መሰረት ደስታ እንደጠቀሱት በግል እና በመንግስት ተቋማት ላይ በብዙ ዘርፎች እንዳገለገሉ ገልጸው ወደዚህ አካዳሚ ከመመደባቸው በፊት በጠቅላይ ሚ/ር ጽ/ቤት በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ እንዳገለገሉም ተናግረዋል፡፡
ምክትል ርዕሰ አካዳሚዋ የአፍሌክስን ራዕይ ከግብ ለማድረስ ከተቋሙ አመራር እና ሰራተኛ ጋር ለመስራት እንደሚተጉ ተናግረው፤ ተቋሙ በህግ የተሰጠውን ተልዕኮ እንዲያሳካ ሰፊ ስራ መስራት እንደሚጠበቅ አስገንዝበዋል።
የአካዳሚው የሪፎርም ኮሚቴ አባላትና የዘርፉ ዳይሬክተሮች በበኩላቸው ለምክትል ርዕሰ አካዳሚዋ መልካም የስራ ዘመን ተመኝተው፤ በተቋሙ ውስጥ የሪፎርም፤ ማስፋት እና ሽግግር ስራዎች ያሉበትን ደረጃ ጠቅሰው፤ ወደፊት መከናወን ያለባቸው ስራዎች ላይ ማብራሪያና ገለፃ አድርዋል፡፡
ወ/ሮ መሰረት ደስታ ከውይይቱ በቂ ግንዛቤ እንደወሰዱ ተናግረው፤ ለሀገረ መንግስት ግንባታ ሂደት አካዳሚው ብዙ መስራት እንዳለበት አስታውቀዋል፡፡
👍19
ሚዲያዎች ኢትዮጵያዊያንን አንድ በሚያደርጉ ትርክቶች ላይ ትኩረት አድርገው ሊሰሩ ይገባል ተባለ፡፡
*********************
“የሚዲያ ሚና ለትርክትና ሀገረ መንግሥት ግንባታ” በሚል መሪ ሃሳብ በመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አዘጋጅነት ለሚዲያ አመራሮችና ባለሙያዎች የሚሰጥ ስልጠና ዛሬ ጥቅምት 18/2017 ዓ/ም #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥተጀምራል፡፡
"ሚዲያ ለብሔራዊ ትርክትና ሀገረ መንግሥት ግንባታ" በሚል ርዕስ ላይ ገለጻ ያደረጉት የጠቅላይ ሚኒስተሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙዐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ሚዲያዎች ኢትዮጵያዊያንን አንድ በሚያደርጉን ትርክቶች ላይ ትኩረት አድርገው መሥራት እንደሚጠበቅባቸውና ሃገር የሚገነባው በአዎንታዊ ትርክቶች መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ሥራ ትርክትን እንደሚቀይር የተናገሩት አማካሪ ሚኒስትሩ ባዶ ትርክት እንደማይጸናና ተግባራዊ ሥራ ሲሰራ ትርክቶች ይለወጣሉ ብለዋል። ትላንት የነበረው የአባይ ውሃ ዛሬ ህዳሴ ግድብን ሰርተን ስናጠናቅቅ ትርክቱ ተቀይሯል በማለት ሥራ ተግባርን እንደሚቀር አመላክተዋል፡፡
ትርክቶች አካታች መሆን እንዳለባቸው ፣ልሂቃን የሚገቡ ትርክቶች መቃናት እንዳለባቸው ያነሱት አማካሪ ሚኒስትሩ ትርክት ለነገ ሲባል የትላንቱን የሚተወውን ትተን፣ የዛሬንም ይቅር ብለን ነገን የምንገነባበት ሊሆን ይገባል ብለዋል በገለፃቸው፡፡
ትርክት የአብሮነት ታሪካዊ መሰረት እንደሆነ፣ ሰዎች ከየት ተነስተው እና ወደየት እንደሚሄዱ እና የት እንደሚደርሱ የሚመለከቱበት መሆኑንም ዲያቆን ዳንኤል አክለዋል፡፡
ለመገናኛ ብዙሃን "ሚዲያ ለብሔራዊ ትክርክትና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ" በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ስልጠና ለሶስት ቀናት #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ይቀጥላል፡፡
*********************
“የሚዲያ ሚና ለትርክትና ሀገረ መንግሥት ግንባታ” በሚል መሪ ሃሳብ በመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አዘጋጅነት ለሚዲያ አመራሮችና ባለሙያዎች የሚሰጥ ስልጠና ዛሬ ጥቅምት 18/2017 ዓ/ም #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥተጀምራል፡፡
"ሚዲያ ለብሔራዊ ትርክትና ሀገረ መንግሥት ግንባታ" በሚል ርዕስ ላይ ገለጻ ያደረጉት የጠቅላይ ሚኒስተሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙዐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ሚዲያዎች ኢትዮጵያዊያንን አንድ በሚያደርጉን ትርክቶች ላይ ትኩረት አድርገው መሥራት እንደሚጠበቅባቸውና ሃገር የሚገነባው በአዎንታዊ ትርክቶች መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ሥራ ትርክትን እንደሚቀይር የተናገሩት አማካሪ ሚኒስትሩ ባዶ ትርክት እንደማይጸናና ተግባራዊ ሥራ ሲሰራ ትርክቶች ይለወጣሉ ብለዋል። ትላንት የነበረው የአባይ ውሃ ዛሬ ህዳሴ ግድብን ሰርተን ስናጠናቅቅ ትርክቱ ተቀይሯል በማለት ሥራ ተግባርን እንደሚቀር አመላክተዋል፡፡
ትርክቶች አካታች መሆን እንዳለባቸው ፣ልሂቃን የሚገቡ ትርክቶች መቃናት እንዳለባቸው ያነሱት አማካሪ ሚኒስትሩ ትርክት ለነገ ሲባል የትላንቱን የሚተወውን ትተን፣ የዛሬንም ይቅር ብለን ነገን የምንገነባበት ሊሆን ይገባል ብለዋል በገለፃቸው፡፡
ትርክት የአብሮነት ታሪካዊ መሰረት እንደሆነ፣ ሰዎች ከየት ተነስተው እና ወደየት እንደሚሄዱ እና የት እንደሚደርሱ የሚመለከቱበት መሆኑንም ዲያቆን ዳንኤል አክለዋል፡፡
ለመገናኛ ብዙሃን "ሚዲያ ለብሔራዊ ትክርክትና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ" በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ስልጠና ለሶስት ቀናት #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ይቀጥላል፡፡
👍12
በመንግሰት የ2017 የመጀመሪያ 100 ቀናት እና በአካዳሚው 1ኛ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ላይ ውይይት ተካሄደ::
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በመንግሰት የ2017 የመጀመሪያ 100 ቀናት እና በአካዳሚው 1ኛ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ላይ ሱሉልታ በሚገኘው የአካዳሚው የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ ውይይት አካሄደ፡፡
በአካዳሚው የኦፕሬሽን ዘርፍ ም/ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) በአለም አቀፍ የፖለቲካ ኢኮኖሚ አዝማሚያና ኢትዮጵያ ላይ የሚኖረው አንድምታ፣ የሪፎርሙ ተጠባቂ ፋይዳዎች የተረጋጋ የማክሮ ኢኮኖሚ፤ የዘርፎች ምርታማነትና ተወዳዳሪነት እና የመንግስስት አገልግሎትና የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ገለፃ አድርገዋል:: ምክትል ርዕሰ አካዳሚው የዋና ዋና ፕሮጀክቶች አፈፃፀም እና ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ላይም ሰፊ ገለፃ አድርገዋል፡፡
በአካዳሚው የአመራር ልማት ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወ/ሮ መሰረት ደስታ በበኩላቸው፣ ተቋሙ እቅዱን በመፈተሸ፣ ተግዳሮትን በመለየት፣ የተቋቋመበት ተልዕኮ ላይ አተኩሮ መስራት እንዳለበትና መሪነት የሚታይበት እና መሪ ፈፃሚ መሆን እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በመንግሰት የ2017 የመጀመሪያ 100 ቀናት እና በአካዳሚው 1ኛ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ላይ ሱሉልታ በሚገኘው የአካዳሚው የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ ውይይት አካሄደ፡፡
በአካዳሚው የኦፕሬሽን ዘርፍ ም/ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) በአለም አቀፍ የፖለቲካ ኢኮኖሚ አዝማሚያና ኢትዮጵያ ላይ የሚኖረው አንድምታ፣ የሪፎርሙ ተጠባቂ ፋይዳዎች የተረጋጋ የማክሮ ኢኮኖሚ፤ የዘርፎች ምርታማነትና ተወዳዳሪነት እና የመንግስስት አገልግሎትና የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ገለፃ አድርገዋል:: ምክትል ርዕሰ አካዳሚው የዋና ዋና ፕሮጀክቶች አፈፃፀም እና ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ላይም ሰፊ ገለፃ አድርገዋል፡፡
በአካዳሚው የአመራር ልማት ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወ/ሮ መሰረት ደስታ በበኩላቸው፣ ተቋሙ እቅዱን በመፈተሸ፣ ተግዳሮትን በመለየት፣ የተቋቋመበት ተልዕኮ ላይ አተኩሮ መስራት እንዳለበትና መሪነት የሚታይበት እና መሪ ፈፃሚ መሆን እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል፡፡
👍17