የገጠር መንገድ ትስስርን ተደራሽ በማድረግ የዜጎችን የምግብ ዋስትና ማረጋገጠ አለብን ሲሉ የከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ሄለን ደበበ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ በተደረገው መርሀ ግብር ላይ ተናገሩ፡፡
ሚኒስትር ዲኤታዋ ይህን ያሉት ከሁሉም ክልሎች ለተውጣጡ የመንገድና ትራንሰፖርት ዘርፍ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሚኒስቴር መ/ቤቱ አስተባባሪነትና በአለም ባንክ ድጋፍ በ407 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የገጠር ትስስርን በማጠናከር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችለውን አዲሱን ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ ነው፡፡
ሚኒስትር ዲኤታዋ ይህን ያሉት ከሁሉም ክልሎች ለተውጣጡ የመንገድና ትራንሰፖርት ዘርፍ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሚኒስቴር መ/ቤቱ አስተባባሪነትና በአለም ባንክ ድጋፍ በ407 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የገጠር ትስስርን በማጠናከር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችለውን አዲሱን ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ ነው፡፡
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ለመላው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ቤተሰቦች፦
አዲሱ ዓመት የሰላም፤ የጤና እና የብልጽግና እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ!!
ዛዲግ አብርሃ
ፕሬዚደንት
አዲሱ ዓመት የሰላም፤ የጤና እና የብልጽግና እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ!!
ዛዲግ አብርሃ
ፕሬዚደንት
👍2
Forwarded from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
እንኳን ለ2017 የዘመን መለወጫ በዓል ዕንቁጣጣሽ በዓል አደረሳችሁ
ዘመን ዕድል ነው፡፡ ዘመንን መጠቀም ግን የሥራ ውጤት ነው፡፡ ዘመንን ፈጣሪ ለሁላችንም በእኩልነት ሰጥቶናል፡፡ ልዩነት የሚፈጠረው በዘመን በመሥራትና ባለመሥራት ነው፡፡ በታሪካችን ውስጥ የምንኮራባቸው ምእራፎች አሉ፡፡ በሕይወታችን ውስጥም ደስ የሚያሰኙን ጊዜያት አሉ፡፡ እነዚያ ምእራፎችና ጊዜያት ሌላ ነገር አይደሉም፡፡ የተሰጠንን የዘመን ዕድል በሚገባ ተጠቅመን የሠራንባቸው ወቅቶች ናቸው፡፡
እኛ ብንፈልግም ባንፈልግም ዘመን ይለወጣል፡፡ ጊዜ ወደፊት ብቻ የሚሄድ ማሽን ነውና፡፡ ማንም አያስቆመውም፤ አቅጣጫም አያስቀይረውም፡፡ የሚቻለው በጊዜ መጠቀም ብቻ ነው፡፡ “ክረምት ለሰነፍ ገበሬ መዓት፤ ለጎበዝ ገበሬ ምሕረት ነው” ይባላል፡፡ ምሕረትና መዓቱ ከዝናቡ የሚመጣ ሳይሆን ከገበሬዎቹ ዝግጅትና ሥራ የሚገኝ ነው፡፡ በሰነፍ ገበሬ ላይ ዘመን ይለወጥበታል፤ ብርቱው ገበሬ ግን ዘመንን ራሱን ይለውጠዋል፡፡
በ2016 ለኢትዮጵያ ምን አሳክተናል? በ2017ስ ለኢትዮጵያ ምን ተዘጋጅተናል? የእነዚህ ጥያቄዎች መልስ የዘመን መለወጥን ትርጉም ይቀይረዋል፡፡ ዘመን እየተለወጠብን ነው ወይስ ዘመኑን እየለወጥነው ነው? የሚለውን ያመለክተናል፡፡ ኢትዮጵያን ዘመን እየለወጣት ብዙ ጊዜ ኖራለች፡፡ አልፎ አልፎ ደግሞ በብርታትና በትጋት ዘመኑን ለውጣው ታውቃለች፡፡ ዘመን ሲለውጠን፣ ከተራራ እንደተፈነቀለ ድንጋይ፣ ወዳሰብነው ሳይሆን ወደ ፈለገው ነው የሚወስደን፡፡
2017 የሚለውጠን ሳይሆን የምንለውጠው ዓመት እንዲሆን ነው ምኞቴ፡፡ ዕቅዶቻችንን ተግብረን፤ ፕሮጀክቶቻችንን በጊዜና በጥራት አጠናቅቀን፤ ግጭቶቻችንን በውይይትና በድርድር ፈትተን፤ የዘመናት ስብራቶቻችንን በምክክርና በሽግግር ፍትሕ ጠግነን፤ በብዙ ነገሮች ራሳችንን ችለን፤ ሪፎርሞቻችንን በብቃት አሳክተን፣ የምንለውጠው ዘመን እንዲሆን ነው ምኞቴ፡፡
2017ን በኢትዮጵያ ታሪክ የሚጠቀስ ዘመን ለማድረግ እንዘጋጅ፡፡ የዘመናት ዕዳዎቻችን የምናወራርድበት፤ የኖሩ ቁስሎቻችን የምናክምበት፤ የዘመናት ሕልሞቻችንን ሥር መሠረት የምናስይዝበት፤ የታሪክን መኪና መሪና ማርሽ የምንቆጣጠርበት ዘመን ለማድረግ እንነሣ፡፡
ወደፊት የሚመጡት ልጆቻችን “ይሄ ታሪክ የተሠራው፣ የዛሬ ስንት ዓመት በ2017 ነው” እንዲሉን እናድርገው፡፡
በወጀብና በዐውሎ ውስጥ አስገራሚ ሥራዎችን እንድንሠራ የፈቀደ ፈጣሪ ዛሬም ከእኛ ጋር ነው፡፡ ነገም ከእኛ ጋር ነው፡፡ መሥራት የእኛ ማከናወንም የእርሱ ነው፡፡ እኛ ከተነሣን ዘመኑን እንድንለውጠው እርሱ ይረዳናል፡፡
በድጋሚ እንኳን ለ2017 የዘመን መለወጫ በዓል ዕንቁጣጣሽ አደረሳችሁ
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ጳጉሜን 5፣ 2016 ዓ.ም
//
ዘመን ዕድል ነው፡፡ ዘመንን መጠቀም ግን የሥራ ውጤት ነው፡፡ ዘመንን ፈጣሪ ለሁላችንም በእኩልነት ሰጥቶናል፡፡ ልዩነት የሚፈጠረው በዘመን በመሥራትና ባለመሥራት ነው፡፡ በታሪካችን ውስጥ የምንኮራባቸው ምእራፎች አሉ፡፡ በሕይወታችን ውስጥም ደስ የሚያሰኙን ጊዜያት አሉ፡፡ እነዚያ ምእራፎችና ጊዜያት ሌላ ነገር አይደሉም፡፡ የተሰጠንን የዘመን ዕድል በሚገባ ተጠቅመን የሠራንባቸው ወቅቶች ናቸው፡፡
እኛ ብንፈልግም ባንፈልግም ዘመን ይለወጣል፡፡ ጊዜ ወደፊት ብቻ የሚሄድ ማሽን ነውና፡፡ ማንም አያስቆመውም፤ አቅጣጫም አያስቀይረውም፡፡ የሚቻለው በጊዜ መጠቀም ብቻ ነው፡፡ “ክረምት ለሰነፍ ገበሬ መዓት፤ ለጎበዝ ገበሬ ምሕረት ነው” ይባላል፡፡ ምሕረትና መዓቱ ከዝናቡ የሚመጣ ሳይሆን ከገበሬዎቹ ዝግጅትና ሥራ የሚገኝ ነው፡፡ በሰነፍ ገበሬ ላይ ዘመን ይለወጥበታል፤ ብርቱው ገበሬ ግን ዘመንን ራሱን ይለውጠዋል፡፡
በ2016 ለኢትዮጵያ ምን አሳክተናል? በ2017ስ ለኢትዮጵያ ምን ተዘጋጅተናል? የእነዚህ ጥያቄዎች መልስ የዘመን መለወጥን ትርጉም ይቀይረዋል፡፡ ዘመን እየተለወጠብን ነው ወይስ ዘመኑን እየለወጥነው ነው? የሚለውን ያመለክተናል፡፡ ኢትዮጵያን ዘመን እየለወጣት ብዙ ጊዜ ኖራለች፡፡ አልፎ አልፎ ደግሞ በብርታትና በትጋት ዘመኑን ለውጣው ታውቃለች፡፡ ዘመን ሲለውጠን፣ ከተራራ እንደተፈነቀለ ድንጋይ፣ ወዳሰብነው ሳይሆን ወደ ፈለገው ነው የሚወስደን፡፡
2017 የሚለውጠን ሳይሆን የምንለውጠው ዓመት እንዲሆን ነው ምኞቴ፡፡ ዕቅዶቻችንን ተግብረን፤ ፕሮጀክቶቻችንን በጊዜና በጥራት አጠናቅቀን፤ ግጭቶቻችንን በውይይትና በድርድር ፈትተን፤ የዘመናት ስብራቶቻችንን በምክክርና በሽግግር ፍትሕ ጠግነን፤ በብዙ ነገሮች ራሳችንን ችለን፤ ሪፎርሞቻችንን በብቃት አሳክተን፣ የምንለውጠው ዘመን እንዲሆን ነው ምኞቴ፡፡
2017ን በኢትዮጵያ ታሪክ የሚጠቀስ ዘመን ለማድረግ እንዘጋጅ፡፡ የዘመናት ዕዳዎቻችን የምናወራርድበት፤ የኖሩ ቁስሎቻችን የምናክምበት፤ የዘመናት ሕልሞቻችንን ሥር መሠረት የምናስይዝበት፤ የታሪክን መኪና መሪና ማርሽ የምንቆጣጠርበት ዘመን ለማድረግ እንነሣ፡፡
ወደፊት የሚመጡት ልጆቻችን “ይሄ ታሪክ የተሠራው፣ የዛሬ ስንት ዓመት በ2017 ነው” እንዲሉን እናድርገው፡፡
በወጀብና በዐውሎ ውስጥ አስገራሚ ሥራዎችን እንድንሠራ የፈቀደ ፈጣሪ ዛሬም ከእኛ ጋር ነው፡፡ ነገም ከእኛ ጋር ነው፡፡ መሥራት የእኛ ማከናወንም የእርሱ ነው፡፡ እኛ ከተነሣን ዘመኑን እንድንለውጠው እርሱ ይረዳናል፡፡
በድጋሚ እንኳን ለ2017 የዘመን መለወጫ በዓል ዕንቁጣጣሽ አደረሳችሁ
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ጳጉሜን 5፣ 2016 ዓ.ም
//
👍4
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ_ፕሬዚደንት_ዛዲግ_አብርሃ በኢቴቪ መዝናኛ ቻናል ላይ ከተለያዩ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጋር ሆነው #የአዲስ_ዓመት #ትዝታቸውን እና #የልጅነት_ትውስታቸውን አጋርተዋል። ፖለቲከኛ እንደሰው ያዝናል፤ ያለቅስማል ይላሉ። ክፍል አንዱን እንድትመለከቱ ጋበዝናችሁ፦
#የአፍሪካ_አመራር_ልህቅት_አካዳሚ #ፕሬዚደንት_ዛዲግ_አብርሃ በፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፀዋል::
ፕሬዚደንቱ ባስተላለፉት የሃዘን መግለጫ፤ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ሰላማዊ የትግል አስተዋፅዖ አበርክተዋል ብለዋል።
#ዛዲግ_አብርሃ በፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ህልፈት ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማቸው ገልፀው፤ ፈጣሪ ነብሳቸውን በአፀደ ገነት እንዲያኖርም ተመኝተዋል፡፡
ፕሬዚደንቱ ባስተላለፉት የሃዘን መግለጫ፤ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ሰላማዊ የትግል አስተዋፅዖ አበርክተዋል ብለዋል።
#ዛዲግ_አብርሃ በፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ህልፈት ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማቸው ገልፀው፤ ፈጣሪ ነብሳቸውን በአፀደ ገነት እንዲያኖርም ተመኝተዋል፡፡
👍4
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ_ፕሬዚደንት_ዛዲግ_አብርሃ በኢቴቪ መዝናኛ ቻናል ላይ ከተለያዩ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጋር ሆነው
#አዲስ_ዓመት እንደ #አዲስ_ለመነሳሳት እና #ለመነቃቃት የሚያበረክተውን በጎ ነገር ያካፍሉናል።
#እ_ኤ_አ #2040 ለአሜሪካ፤ ለቻይና፤ ለአውሮፓውያን እና ለአፍሪካውያን ሊኖረው የሚችለውን ገጸ-በረከት እና ዕዳ ያመላክታሉ። እንድትመለከቱ ጋበዝናችሁ፦
#አዲስ_ዓመት እንደ #አዲስ_ለመነሳሳት እና #ለመነቃቃት የሚያበረክተውን በጎ ነገር ያካፍሉናል።
#እ_ኤ_አ #2040 ለአሜሪካ፤ ለቻይና፤ ለአውሮፓውያን እና ለአፍሪካውያን ሊኖረው የሚችለውን ገጸ-በረከት እና ዕዳ ያመላክታሉ። እንድትመለከቱ ጋበዝናችሁ፦
👍4
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ዓለማችን በዘመን የሽግግር ሀዲድ ላይ ተሳፍራለች። በአንድ በኩል #ፈጣን_የለውጥ_ሂደት፤ በሌላ በኩል #የግርታ_ማዕበል ላይ ነን።
የሀገራት ዕጣ-ፈንታ ለጥያቄ ቀርቦ መልስ የሚያስፈልግበት ዘመን ላይ ደርሰናል። #ከጨለማ_ወደ_ብርሀን_የሚያሸጋግር #መሪ የሚያስፈልግበት ጊዜ ላይ ነን።
በተለይ #የሀሳብ_ግልጽነት_ያላቸው_መሪዎች ያስፈልጋሉ። #የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ለዚህ ስራ ራሱን እያዘጋጀ ነው።
የሀገራት ዕጣ-ፈንታ ለጥያቄ ቀርቦ መልስ የሚያስፈልግበት ዘመን ላይ ደርሰናል። #ከጨለማ_ወደ_ብርሀን_የሚያሸጋግር #መሪ የሚያስፈልግበት ጊዜ ላይ ነን።
በተለይ #የሀሳብ_ግልጽነት_ያላቸው_መሪዎች ያስፈልጋሉ። #የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ለዚህ ስራ ራሱን እያዘጋጀ ነው።
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#“ሱሉልታን_እንደ_ዳቮስ” #የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ከቀረጻቸው 13 ፕሮጀክቶች ውስጥ አንዱ ሲሆን #የአመራር_ልማት_ማዕከሉን የዓለምአቀፍ ጉባኤ ማዕከል ለማድረግ የሚያስችል ነው።
አውሮፓውያን ችግር ሲገጥማቸው፤ ችግሮቻቸውን በጋራ ለመመከት፤ #የአውሮፓ_ማኔጅመንት_ኢንስቲትዩትን መስርተው ተሻግረዋል። ይህ ተቋም በጊዜ ሒደት አድጎና በልጽጎ ዳቮስ ላይ አድርሷቸዋል።
#በዳቮስ የማይፈቱ ችግሮች እንደሌሉ ይነገራል።
#አፍሪካዊ_ዳቮስን #በሱሉልታ ላይ ለማቋቋም ያስፈለገበትን ምክንያት #የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ፕሬዚደንት #ዛዲግ_አብርሃ እንዲህ ይገልጻሉ፦
አውሮፓውያን ችግር ሲገጥማቸው፤ ችግሮቻቸውን በጋራ ለመመከት፤ #የአውሮፓ_ማኔጅመንት_ኢንስቲትዩትን መስርተው ተሻግረዋል። ይህ ተቋም በጊዜ ሒደት አድጎና በልጽጎ ዳቮስ ላይ አድርሷቸዋል።
#በዳቮስ የማይፈቱ ችግሮች እንደሌሉ ይነገራል።
#አፍሪካዊ_ዳቮስን #በሱሉልታ ላይ ለማቋቋም ያስፈለገበትን ምክንያት #የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ፕሬዚደንት #ዛዲግ_አብርሃ እንዲህ ይገልጻሉ፦
👍5
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#መሪነት እና #ሀሳብ_ማፍለቅ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች!!
ሀሳብ ማመንጨት እንደስራ የሚቆጠርበት የመሪነት መንገድ!!
#የሀሳብ_ግልጽነት_ያላቸው_መሪዎች ሀሳባቸውን የሚያመነጩበት ማዕከል ያስፈልጋል። ለዚህ ደግሞ #የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ መንገድ ጀምሯል።
#ዛዲግ_አብርሃ_የአፍሌክስ_ፕሬዚደንት ይህን ይላሉ፦
#Idea_Generation_center
#Thought_Leadership
#AFLEX_Leadership_Development_Program
#General_Leadership_Development_Program
#Speciallized_Leadership_Development_Program
ሀሳብ ማመንጨት እንደስራ የሚቆጠርበት የመሪነት መንገድ!!
#የሀሳብ_ግልጽነት_ያላቸው_መሪዎች ሀሳባቸውን የሚያመነጩበት ማዕከል ያስፈልጋል። ለዚህ ደግሞ #የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ መንገድ ጀምሯል።
#ዛዲግ_አብርሃ_የአፍሌክስ_ፕሬዚደንት ይህን ይላሉ፦
#Idea_Generation_center
#Thought_Leadership
#AFLEX_Leadership_Development_Program
#General_Leadership_Development_Program
#Speciallized_Leadership_Development_Program
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በሱሉልታ የአመራር ማዕከል ውስጥ ከሚገኙ የቀድሞ ህንጻዎች መካከል የአስተዳደር ህንጻውን በማደስ ለቢሮ አገልግሎት እንዲውል ስራ መጀመሩ ተገለጸ።
#የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ #ለውጥ_Reform #ማስፋት_Scaling_Up እና #ሽግግር_Transformation ስራዎች መካከል አንዱ ሱሉልታ ውስጥ የሚገኙትን የቀድሞ ህንጻዎች በአዲስ መልክ በማደስ ወደ ስራ ማስገባት መሆኑም ተጠቅሷል።
ለአስተዳደር ቢሮው እድሳት የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን (ERA) ወጭውን የሚሸፍን ሲሆን ህንጻውን ለማደስ ደግሞ የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ECC) ውል መግባቱንና ስራ መጀመሩ ተገልጿል።
የአስተዳደር ቢሮው እድሳት ከአምስት እስከ ስድስት ወር ባለው ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ የተገለጸ ሲሆን; አጠቃላይ ወጭውም ወደ 200 ሚሊየን ብር እንደሚሆን ተነግሯል።
የህንጻው እድሳት እንደተጠናቀቀም የአካዳሚው ሰራተኞች ወደ አዲሱ ህንጻ ተዛውረው ስራ እንደሚጀምሩ የተጠቀሰ ሲሆን፤ ይህም አካዳሚው ለቢሮ ኪራይ የሚያወጣውን ገንዘብ ከማስቀረቱም በላይ የአመራር ልማት ስራውን በቅርበት ሆኖ ለማገዝ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ተብሏል።
#የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ #ለውጥ_Reform #ማስፋት_Scaling_Up እና #ሽግግር_Transformation ስራዎች መካከል አንዱ ሱሉልታ ውስጥ የሚገኙትን የቀድሞ ህንጻዎች በአዲስ መልክ በማደስ ወደ ስራ ማስገባት መሆኑም ተጠቅሷል።
ለአስተዳደር ቢሮው እድሳት የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን (ERA) ወጭውን የሚሸፍን ሲሆን ህንጻውን ለማደስ ደግሞ የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ECC) ውል መግባቱንና ስራ መጀመሩ ተገልጿል።
የአስተዳደር ቢሮው እድሳት ከአምስት እስከ ስድስት ወር ባለው ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ የተገለጸ ሲሆን; አጠቃላይ ወጭውም ወደ 200 ሚሊየን ብር እንደሚሆን ተነግሯል።
የህንጻው እድሳት እንደተጠናቀቀም የአካዳሚው ሰራተኞች ወደ አዲሱ ህንጻ ተዛውረው ስራ እንደሚጀምሩ የተጠቀሰ ሲሆን፤ ይህም አካዳሚው ለቢሮ ኪራይ የሚያወጣውን ገንዘብ ከማስቀረቱም በላይ የአመራር ልማት ስራውን በቅርበት ሆኖ ለማገዝ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ተብሏል።
👍4