General Wingate Polytechnic college-Official channel
9.95K subscribers
3.35K photos
43 videos
204 files
196 links
ራዕይ:- በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆን።

የአይሶ 9001፡2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርተፍኬት ባለቤት።
Download Telegram
#ማስታወቂያ አቅም ማሻሻያ (Remedial )ፕሮግራም የዩኒቨርሲቲ ምርጫን በተመለከተ

በ 2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ የካቲት 10/2015 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ማሳሰቢያ:- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፣ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ና የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲዎች በዚህ ፕሮግራም የማይካተቱ መሆኑን እንገልጻለን።
ትምህርት ሚኒስቴር!
የካቲት 8/2015 ዓ.ም
መረጃዎችን በምስልና ድምፅ ቻናሉን Subscribe አድርጉት
       👇         👇              👇
https://youtube.com/channel/UCw9EUpuNrwP0hLvdmXz-ZBQ
   
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ
@ET_SEBER_ZENA
@ET_SEBER_ZENA

በቻናሉ ማስታወቂያ ለማሰራት  
👇👇 
@Topic_peromotor
ሐሙስ፡- መስከረም 9 ቀን 2016 ዓ.ም

               #ማስታወቂያ

  ለኮሌጃችን የውስጥ ሰራተኞች እና  ለውጪ የተቋማችን አጋር  ማኅበረሰብ በሙሉ

የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተቋማዊዩ የግል ኢንተርፕራይዝ ያደለባቸውን 9 #በሬዎች በከፍተኛ ጥራት እና በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው ማህበረሰብ ለመሸጥ አቅዷል፡፡

ስለሆነም በተዘጋጀው ጥቂት የመሸጫ ቀናት ውስጥ ፈጥነው በመምጣት የመረጡትን ሰንጋ በበሬዎቹ ፎቶ ላይ በተለጠፈው የዋጋ ዝርዝር መሰረት ከፍለው መውሰድ የሚችሉ መሆኑን ስንገልጽልዎት በታላቅ ደስታ ነው፡፡

ለመስቀል በዓል፣ ለተለያዩ ዝግጅቶች ወይም የስጋ አምርዎቶን ቁርጥ ለማድረግ ካሰቡ ወደየትም አይሂዱ፤ የስጋ ፍላግዎቶን ለማርካት እኛ ጋር ኑ  አስር ጊዜ ለክተው አንድ ጊዜ ይመርጡናል እንጂ አያወዳድሩንም ይላል የኮሌጁ ተቋማዊዩ የግል ኢንተርፕራይዝ፡፡

ቀንበር ያልተጫነባቸውና ጅራፍ ያላረፈባቸው የእርድ ቅልብ ሰንጋዎቻችንን መርጠው ለመግዛት ከፈለጉ
#አድራሻ፡-   ቦታ - ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ
             ስልክ - 0991824160

                  የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
አርብ:- ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ∙ም

#የሺያጭ #ማስታወቂያ

ሀ-ብዬ የቆዳ ምርት ውጤቶች ማምረቻ እና ማከፋፈያ ድርጅት ለኮሌጁ ማህበረሰብ በሙሉ ከወዲሁ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ ድርጅቱ በዓሉን ምክኒያት በማድረግ በጥራትና በውበት የሚያመርታቸውን ፋሽን ጫማዎችና ሌዘር ጃኬቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እና በ3 ወር የክፍያ ጊዜ ወስዳችሁ ሽር ብትን በሉ ብሏችኋል፡፡

የሺያጭ ጊዜ ለ10 ተከታታይ ቀናት የሚቆ ሲሆን ቦታውም በሰራተኞች ካፍተሪያ አገልግሎት መግቢያ በር አካባቢ ታገኙናለችሁ ኑና መርጣችሁ ሸምቱ ተብላችኋል፡፡

ሀ-ብዬ የቆዳ ምርት ውጤቶች ማምረቻ እና ማከፋፈያ ድርጅት
ቅዳሜ፡- ታህሳስ 26 ቀን 2017 ዓ.ም

               #ማስታወቂያ

  ለኮሌጃችን የውስጥ ሰራተኞች እና  ለውጪ የተቋማችን አጋር  ማኅበረሰብ በሙሉ

የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተቋማዊዩ የግል ኢንተርፕራይዝ ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ እያለ ለበዓል ያደለባቸውን ምርጥ #በሬዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው ማህበረሰብ ለመሸጥ እንሆ ይላል፡፡

ስለሆነም በተዘጋጀው ጥቂት የመሸጫ ቀናት ውስጥ ፈጥነው በመምጣት የመረጡትን ሰንጋ በተመጣጣኝ ዋጋ መሸመት የሚችሉ መሆኑን ስንገልጽልዎት በታላቅ ደስታ ነው፡፡

ዝም ብሎ በሬ አለ በሬ ብሎ ዝምም አለ። የእኛዎቹ በሬ ብሎ ዝም ናቸው ይላል ጀነራል ዊንጌት የግል ኢንተርፕራይዝ።

እንደ ስማችን ዊን_ጌት የሆኑ ሰንጋዎችንን መርጠው ለመግዛት ከፈለጉ ይምጡ ለበዓል ይሸምቱ ተብላችኋል።

#አድራሻ፡-   ቦታ - ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ
             ስልክ - 0991824160

የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ማክሰኞ:- የካቲት 4 ቀን 2017 ዓ∙ም

    #የሰልጣኞች #ምዝገባ #ማስታወቂያ

የ2017 በጀት ዓመት የሁለተኛው መንፈቀ ዓመት ስልጠና ምዝገባ ከየካቲት 17 እስከ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ሲሆን ስልጠና የሚጀምረው የካቲት 26 ቀን 2017 ዓ.ም ነው።

ምዝገባው የ3ቱም መርሃግብር /የቀን፣ የማታ የቅዳሜ እና እሁድ ነባርና አዲስ መደበኛ ሁሉንም ሰልጣኞች ይመለከታል።

ተጨማሪ መረጃዎችን አያይዘናል።
ማክሰኞ፡- ሚያዚያ 7 ቀን 2017 ዓ.ም

               #ማስታወቂያ

  ለኮሌጃችን የውስጥ ሰራተኞች እና  ለውጪ የተቋማችን አጋር  ማኅበረሰብ በሙሉ

የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተቋማዊዩ የግል ኢንተርፕራይዝ ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሣኤ በሰላም አደረሳችሁ እያለ ለበዓል ያደለባቸውን  ምርጥ #በሬዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው ማህበረሰብ ለመሸጥ እንሆ ይላል፡፡

ስለሆነም በተዘጋጀው ጥቂት የመሸጫ ቀናት ውስጥ ፈጥነው በመምጣት የመረጡትን ሰንጋ በተመጣጣኝ ዋጋ መሸመት የሚችሉ መሆኑን ስንገልጽልዎት በታላቅ ደስታ ነው፡፡

ስለዚህ ለመግዛት ከፈለጉ ይምጡ ለበዓል ይሸምቱ ተብላችኋል።

#አድራሻ፡-   ቦታ - ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ
             ስልክ - 0991824160

የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ሐሙስ:- ሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ.ም

#ማስታወቂያ

#ለኮሌጁ #ማኅበረሰብ #በሙሉ

ከሰኔ 7 ቀን 2017 ዓ.ም "ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ቃል 15ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል በቴክኖሎጂ ዐውደ ርዕይ፣ በፋሽን ሾው ትርኢት እና በሌሎች አዝናኝ እና አስተማሪ መርሃ ግብራት ይከበራል።

ስለሆነም ተጠባቂው የጀነራል ዊንጌት ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ፋሽን ሾው ትርኢትን ጨምሮ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች የሚቀርቡት እሁድ ሰኔ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ከሰዓት በመሆኑ ሁላችሁም የኮሌጃችን ሰራተኞችና ሰልጣኞች በቦታው በመገኘት እንድትጎበኙና እንድታበረታቱ እየገለጽን
6:30 ላይ ለትራንስፖርት የተዘጋጁ ባሶች ከግቢ የሚነሱ መሆኑን እንገልፃለን።

የጀነራል ዊንጌት ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ሐሙስ:- ሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ.ም

#ማስታወቂያ

#ለኮሌጁ #ማኅበረሰብ #በሙሉ

ከሰኔ 7 ቀን 2017 ዓ.ም "ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ቃል 15ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል በቴክኖሎጂ ዐውደ ርዕይ፣ በፋሽን ሾው ትርኢት እና በሌሎች አዝናኝ እና አስተማሪ መርሃ ግብራት ይከበራል።

ስለሆነም ተጠባቂው የጀነራል ዊንጌት ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ፋሽን ሾው ትርኢትን ጨምሮ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች የሚቀርቡት እሁድ ሰኔ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ከሰዓት በመሆኑ ሁላችሁም የኮሌጃችን ሰራተኞችና ሰልጣኞች በቦታው በመገኘት እንድትጎበኙና እንድታበረታቱ እየገለጽን
6:30 ላይ ለትራንስፖርት የተዘጋጁ ባሶች ከግቢ የሚነሱ መሆኑን እንገልፃለን።

የጀነራል ዊንጌት ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ