General Wingate Polytechnic college-Official channel
9.95K subscribers
3.36K photos
43 videos
204 files
196 links
ራዕይ:- በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆን።

የአይሶ 9001፡2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርተፍኬት ባለቤት።
Download Telegram
እሁድ፡- ሰኔ 8 ቀን 2017 ዓ.ም

ኮሌጁ የፋሽን ሾው ትርኢቱን በዛሬ ዕለት አቀረበ!!

የ15ኛው ቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት ዐውደ ርዕይ አካል የሆነውን የፋሽን ሾው ትርኢት ውድድር የጀነራል ዊንጌት ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዛሬ ሰኔ 8 ቀን 2017 ዓ.ም አቀረበ፡፡

ከትናንት ቅዳሜ ጀምሮ በአዲስ አበባ ኤግዚቪሸን ማዕከል ለጎብኝዎች እይታ ክፍት የተደረገው 15ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ዐውደ ርዕይ የማምረቻ እና የምርት ፈጠራ ስራዎችን ለተመልካቾች ከማቅረብ ባሻገር በልዩ ልዩ ትርኢቶች እና አዝናኝ ውድድሮች እየተከበረ ይገኛል፡፡

በዛሬው ዕለትም በተካሄደው የፋሽን ሾው ትርኢት በኮሌጆች የተሰሩ የፋሽን ዲዛይኖች የተመልካቾችን ቀልብ የሰረቁ አስደማሚ ስራዎች የታዩ ሲሆን የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቴክስታይ ሌዘር ጋርመንት ዲፓርትመንት አሰልጣኞች እና ሰልጣኞች እጃችሁ ይባረክ ያስባለ ፈጠራዎችን ለመድረክ አብቅተዋል፡፡

ዲፓርትመንቱ በጋርመንት እና በሌዘር ዘርፎች ያዘጋጃቸውን ቅንጡ የወንድ እና የሴት ፋሽን ልብሶችን ለታዳሚዎች እና በመድረኩ ለተሰየሙት ዳኞች በማራኪ አቀራረብ አሳይቷል፡፡

ከዲዛይነሮቹ ፍሸና ጋር የሞደሎቹ ውብ አቀራረብ ተዳምሮ የመድረኩን ታዳሚ ቀልብ በመግዛት እውነትም ዊንጌት የከተማይቱ የቴክኒክና ሙያ ድምቀትና ኩራት አስብሎታል።

በቴክኖሎጂ ረገድ በከተማ ደረጃ በዚህ ዐውደ ርዕይ በተለያዩ የሙያ ዓይነቶች ከ150 የማምረቻ፣ የምርት፣ የሀገር በቀል እና የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ፈጠራዎች ተሰርተው ለጎብኝዎች መቅረባቸው ታውቋል፡፡

‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ሰኞ፡- ሰኔ 9 ቀን 2017 ዓ.ም

የኮሌጁ ሰራተኞችና ሰልጣኞች ለኤግዚቪሽን የቀረቡ ቴክኖሎጂዎችን ጎበኙ!!

የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞችና ሰልጣኞች በ15ኛው ቴክኒክና ሙያ ሳምንት ዐውደ ርዕይ ላይ የቀረቡ ቴክኖሎጂዎችን በዛሬው ዕለት ጉብኝት አድርገዋል፡፡

3ኛ ቀኑን ባስቆጠረውና በአዲስ አበባ ኤግዚቪሸን ማዕከል ለጎብኝዎች እይታ ክፍት በተደረገው 15ኛው ከተማ አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ዐውደ ርዕይ ላይ ከ150 በላይ የማምረቻ፣ የምርት፣ የሀገር በቀል እና የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ የፈጠራ ስራዎች ለተመልካቾች ቀርበዋል፡፡

በዛሬው ዕለትም የኮሌጁ ሰራተኞች እና ሰልጣኞች እንዲሁም ከ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የተጋበዙ ተማሪዎች በአሰልጣኞችና በሰልጣኞች የተሰሩ አስደናቂ ቴክኖሎጂዎችን እንዲጎበኙና በአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የተሰሩ ምርቶችን ደግሞ እንዲያዩ ከፈለጉም እንዲሸምቱ ማድረግ ተችሏል፡፡

ከቴክኖሎጂ ጉብኝት ባሻገር ከደጃዝማች ገረሱ ዱኪ /ከቀድሞው አዲስ ከተማ/ ኢንዱስትሪል ኮሌጅ ጋር በመተባበር ለጎብኝዎች የሻይ፣ ቡና ዝግጅት በማድረግ የበዓሉን ድባብ ለማሳመርና የተመልካችን ቀልብ ለመሳብ ተሞክሯል፡፡

ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክነክ ኮሌጅ ከ10 በላይ ቴክኖሎጂዎችን ለዕይታ ያቀረበ ሲሆን በትናንትና ዕለት ደግሞ በቴክስታይ ሌዘር ጋርመንት ዲፓርትመንት አሰልጣኞች እና ሰልጣኞች የተሰሩ ቅንጡ የወንድ እና የሴት ፋሽን ልብሶችን በፋሽን ሾው ትርኢት መድረክ ላይ ለተመልካቾች ማሳየቱ አይዘነጋም፡፡

‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የንግድ ሐሳብ ፈጠራ ውድድር
ሐሙስ፡- ሰኔ 12 ቀን 2017 ዓ.ም

የተመራቂ ሰልጣኞች የስራ ዕድል ሁኔታ መከታተያ ጥናት ግኝት ቀረበ!!

የ2016 ተመራቂ ሰልጣኞች የስራ ዕድል መከታተያ ጥናት ግኝት /graduates tracer study findings/ ቀረበ።

ጥናቱ በኮሌጁ ጥናትና ምርምር ቡድን አባላት ተሰርቶ የቀረበ ሲሆን የተመራቂ ሰልጣኞችን የስራ ሁኔታ በዲፓርትመንት፣ በፆታ እና በስራ ዓይነት ተንትኖ ያቀረበ ነው።

በዚህ ጥናት መሰረት ምን ያህሉ በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች እንደተቀጠሩ፣ ስንቶቹ በራሳቸው ስራ እንደፈጠሩ፣ ምን ያህሉ የሚሰሩት ስራ ከሰለጠኑበት ሙያ ጋር ዝምድና እንዳለውና የትኞቹስ ከስራ ወጪ እንደሆኑ መረጃ የሰጠ ነው፡፡

ጥናትና ምርምሩ ሲቀርብ ሀሳብ ያዋጡ ዘንድ ከፍተኛ ሙያና የካበተ ልምድ ያላቸው የዘርፉ ባለሙያዎችን በመጋበዝ የጥናት ሰነዱን በአስተያየት እንዲያዳብሩ ተደርጓል፡፡

በኮሌጁ የ2016 ዓ.ም አጠቃላይ ተመራቂዎች ዉስጥ ከ91 ፐርሰንት በላይ የሚሆኑት ወደ ስራ የገቡ ሲሆን አብዛኛዎቹ በተማሩት የሙያ መስክ መሰማራታቸው ተረጋግጧል።

ተመራቂዎቹ በመንግስት መስሪያ ቤት እና በኢንዱስትሪዎች በመቀጠር እንዲሁም በግላቸው እና ተደራጅተው በመስራት ወደ ክፍለ ኢኮኖሚው አበርክቶ መግባታቸው ታውቋል።

በሌላ በኩል ጥናቱ በአሰልጣኞች፣ በሰልጣኞች እንዲሁም በትብብር ስልጠና ሰጭ ድርጅቶች ያለውን አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ተንትኖ አሳይቷል።

የተመራቂ ሰልጣኞች የስራ ዕድል ሁኔታ መከታተያ ጥናትና ምርምር በየዓመቱ የሚደረግ ሲሆን የተመራቂ ሰልጣኞች የስራ ዕድል ሁኔታን ለማወቅና ኮሌጁ ለሚሰጣቸው ስልጠናዎች የገበያው ፍላጎትን ለመዳሰስ ነወ፡፡

"በላቀ አገ ልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"