11ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት በክላስተር ደረጃ ተካሄደ፡፡
---------------------------------------------
መጋቢት 30 ቀን 2013 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በክላስተር ደረጃ የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአዲስ ከተማ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ እና የኮልፌ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ በጋራ በመሆን ሙያ ሀብት ነው በሚል መሪ ቃል ተካሄዷል፡፡
የኮሌጁ ዋና ዲን #አቶ_መለስ_ይመር በመድረክ የመክፈቻ ንግግር ወቅት እንዳሉት ይህ አንጋፋ ኮሌጅ ከጎኑ የአዲስ ከተማ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅና የኮልፌ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅን በክላስተር አደረጃጀት በመያዝ ብቁ፣ ተነሳሽነት ያለው፣ በራሱ የሚተማመን፣ ተወዳዳሪ የሆነና በመካከለኛ ደረጃ የሰለጠነ የሰው ሃይል በብዛትና በጥራት ለኢንዱስትሪው የማቅረብ ተግባር እያከናወኑ ሲሆን የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ተወዳዳሪነት ለማሳደግና ለወጣቶችና ለሴቶች የስራ ዕድል እንዲፈጥሩ ለማስቻል በየዓመቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢንተርፕራይዞች የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ቴክኖሎጂ ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡
---------------------------------------------
መጋቢት 30 ቀን 2013 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በክላስተር ደረጃ የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአዲስ ከተማ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ እና የኮልፌ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ በጋራ በመሆን ሙያ ሀብት ነው በሚል መሪ ቃል ተካሄዷል፡፡
የኮሌጁ ዋና ዲን #አቶ_መለስ_ይመር በመድረክ የመክፈቻ ንግግር ወቅት እንዳሉት ይህ አንጋፋ ኮሌጅ ከጎኑ የአዲስ ከተማ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅና የኮልፌ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅን በክላስተር አደረጃጀት በመያዝ ብቁ፣ ተነሳሽነት ያለው፣ በራሱ የሚተማመን፣ ተወዳዳሪ የሆነና በመካከለኛ ደረጃ የሰለጠነ የሰው ሃይል በብዛትና በጥራት ለኢንዱስትሪው የማቅረብ ተግባር እያከናወኑ ሲሆን የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ተወዳዳሪነት ለማሳደግና ለወጣቶችና ለሴቶች የስራ ዕድል እንዲፈጥሩ ለማስቻል በየዓመቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢንተርፕራይዞች የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ቴክኖሎጂ ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡
በአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ አስተባባሪነት ሲካሄድ የቆየው ከተማ አቀፍ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድር በጄነራል ዊንጌት ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅ አሸናፊነት ተጠናቀቀ።
ግንቦት 27 ቀን ፤ 2017 ዓ.ም
የአዲስ አበባ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ 14ኛውን የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ምክንያት በማድረግ ከሚያከናውናቸው ሁነቶች አንዱ የሆነው <<ሙያና ክህሎት ለዘላቂ ልማት>>በሚል መሪ ቃል ሲያካሂድ የቆየው የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ከተማ አቀፍ ውድድር በዛሬው ዕለት ተጠናቋል።
በማጠቃለያ ውድድሩ በክላስተር ደረጃ በተካሄደው ውድድር የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ የጥናትና ምርምር ስራዎች የቀረቡ ሲሆን ከፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት የተውጣጡ ምሁራን ደግሞ በዳኝነት ተሳትፈ ውበታል።
በዚህ መሰረት #ጄኔራል ዊንጌት ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ #ተግባረ-ዕድ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና ንፋስ ስልክፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል ።
በማጠቃለያ ውድድሩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የኢንተርፕራይዝና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ኃላፊ #አቶ መክብብ ወልደሃና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች በስልጠና ወቅት የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች እና በማህበረሰቡ የሚስተዋሉ ችግሮችን በጥናት በመለየት እና ችግሮቹ በዘላቂነት እንዲፈቱ ለማድረግ ተግባራዊ ጥናትና ምርምሮች ድርሻቸው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።
#አቶ መክብብ ወልደሃና አያይዘውም ቢሮው በተግባራዊ ጥናትና ምርምር የተገኙ ግኝቶችን በተግባር ለመለወጥ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።
ግንቦት 27 ቀን ፤ 2017 ዓ.ም
የአዲስ አበባ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ 14ኛውን የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ምክንያት በማድረግ ከሚያከናውናቸው ሁነቶች አንዱ የሆነው <<ሙያና ክህሎት ለዘላቂ ልማት>>በሚል መሪ ቃል ሲያካሂድ የቆየው የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ከተማ አቀፍ ውድድር በዛሬው ዕለት ተጠናቋል።
በማጠቃለያ ውድድሩ በክላስተር ደረጃ በተካሄደው ውድድር የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ የጥናትና ምርምር ስራዎች የቀረቡ ሲሆን ከፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት የተውጣጡ ምሁራን ደግሞ በዳኝነት ተሳትፈ ውበታል።
በዚህ መሰረት #ጄኔራል ዊንጌት ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ #ተግባረ-ዕድ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና ንፋስ ስልክፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል ።
በማጠቃለያ ውድድሩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የኢንተርፕራይዝና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ኃላፊ #አቶ መክብብ ወልደሃና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች በስልጠና ወቅት የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች እና በማህበረሰቡ የሚስተዋሉ ችግሮችን በጥናት በመለየት እና ችግሮቹ በዘላቂነት እንዲፈቱ ለማድረግ ተግባራዊ ጥናትና ምርምሮች ድርሻቸው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።
#አቶ መክብብ ወልደሃና አያይዘውም ቢሮው በተግባራዊ ጥናትና ምርምር የተገኙ ግኝቶችን በተግባር ለመለወጥ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።
እሁድ:- ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም
ሀገራዊ ለውጡን ተከተሎ በተመዘገቡ ለውጦችና በተፈጠሩ ተግዳሮቶች ዙሪያ ወይይት ተካሄደ!!
ሀገራዊ ለውጡን ተከተሎ በተመዘገቡ ዘርፈ ብዙ ለውጦችና በተከሰቱ ተግዳሮቶች እንዲሁም በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ ከኮሌጁ አሰልጣኞች ጋር ውይይት እየተካሄደ ይገኛል፡፡
"የበቃ አሰልጣኝ ክህሎት የጨበጠ ወጣት ለሀገር ብልፅግና!" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለውን ውይይት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ #ጥራቱ #በየነ ከማዕከል በገለፃ አቅረበዋል።
ክቡር አቶ ጥራቱ በገለፃቸው እንደ ሀገር የመጡ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና የወጪ ግንኙነት ፖሊሲና ዲፕሎማሲ ስኬቶችን እንዲሁም ሀገራዊ ለውጡን የፈተኑ ውስጣዊና ወጫዊ ተግዳሮቶችን አብራርተዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም ብቁ ባለሙያ በማፍራትና የቴክኖሎጂ ሽግግር በማድረግ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ለሀገራዊ ብልፅግና ያላቸው ሚና ትልቅ መሆኑን አውስተዋል፡፡ በገለፃው የመዲናቱ ኮሌጆች ያሉበትን ነባራዊ ሁኔታ በጥንካሬና በክፍተት ማሳየት ተችሏል፡፡
በቀረበው ገለፃ መሰረት ከኮሌጁ አሰልጣኞች የተለያዩ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች እየተነሱ ሲሆን የውይይት መድረኩን በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዝና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ #አቶ #መሀመድ #ልጋኒ እና የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ #መለሰ #ይግዛው እየመሩት ይገኛሉ፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ሀገራዊ ለውጡን ተከተሎ በተመዘገቡ ለውጦችና በተፈጠሩ ተግዳሮቶች ዙሪያ ወይይት ተካሄደ!!
ሀገራዊ ለውጡን ተከተሎ በተመዘገቡ ዘርፈ ብዙ ለውጦችና በተከሰቱ ተግዳሮቶች እንዲሁም በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ ከኮሌጁ አሰልጣኞች ጋር ውይይት እየተካሄደ ይገኛል፡፡
"የበቃ አሰልጣኝ ክህሎት የጨበጠ ወጣት ለሀገር ብልፅግና!" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለውን ውይይት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ #ጥራቱ #በየነ ከማዕከል በገለፃ አቅረበዋል።
ክቡር አቶ ጥራቱ በገለፃቸው እንደ ሀገር የመጡ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና የወጪ ግንኙነት ፖሊሲና ዲፕሎማሲ ስኬቶችን እንዲሁም ሀገራዊ ለውጡን የፈተኑ ውስጣዊና ወጫዊ ተግዳሮቶችን አብራርተዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም ብቁ ባለሙያ በማፍራትና የቴክኖሎጂ ሽግግር በማድረግ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ለሀገራዊ ብልፅግና ያላቸው ሚና ትልቅ መሆኑን አውስተዋል፡፡ በገለፃው የመዲናቱ ኮሌጆች ያሉበትን ነባራዊ ሁኔታ በጥንካሬና በክፍተት ማሳየት ተችሏል፡፡
በቀረበው ገለፃ መሰረት ከኮሌጁ አሰልጣኞች የተለያዩ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች እየተነሱ ሲሆን የውይይት መድረኩን በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዝና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ #አቶ #መሀመድ #ልጋኒ እና የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ #መለሰ #ይግዛው እየመሩት ይገኛሉ፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ቅዳሜ፡- ሰኔ 7 ቀን 2017 ዓ.ም
15ኛው የቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት ዐውደ ርዕይ ተጀመረ፡፡
15ኛው የቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት ዐውደ ርዕይ ዛሬ ሰኔ 7 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ኤግዚቪሸን ማዕከል ለጎብኝዎች ዕይታ ክፍት ተደረገ፡፡
በመክፈቻ መርሃ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ #አዳነች #አቤቤ፣ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ #ጥራቱ #በየነን ጨምሮ የፌደራል እና የከተማ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
በዕለቱ የመዲናይት ከንቲባ በመልዕክታቸው "ችግር ፈቺ ተኪ ምርቶችን በማምረት ሂደት የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች እያበረከቱት ያለው አስተዋጽኦ የሚበረታታ ነው" ብለዋል።
ክብርት ከንቲባዋ አያይዘውም በቅርቡ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው የክህሎት ውድድር በከተማ አስተዳደሩ አጠቃላይ አሸናፊነት በመጠናቀቁ የዘርፉን አመራሮችና ባለሙያዎች አመስግነዋል።
መንግስት ከለውጡ ማግስት ጀምሮ ለዘርፉ ልዪ ትኩረት በመስጠትና በአዳዲስ እሳቤ በመቃኘት ለሀገራዊ ዕድገትና ብልፅግና መረጋገጥ ዋስትና እየሆነ መጥቷል ያሉት ደግሞ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር #አቶ #ጥራቱ #በየነ ናቸው፡፡
በዚህ ኤግዚቪሽን ላይ በ15ቱ የመንግስት ኮሌጆች በሚገኙ አሰልጣኞች፣ ሰልጣኞች እና ኢንተርፕራይዞች የተሰሩ ከ150 በላይ ችግር ፈቺ የማምረቻ እና የምርት ቴክኖሎጂ ውጤቶች በአውደ ርዕዩ ላይ ቀርቧል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ የተሰሩ 5 የማምረቻ እና 6 የምርት ውጤቶች ለጎብኝዎች ቀርበዋል፡፡
በተጨማሪም በኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ የሚደረግላቸው 2 ኢንተርፕራይዞች የፈጠራ ምርታቸውን ይዘው ተገኝተዋል፡፡
ኤግዚቪሽኑ ''ብሩህ አዕምሮዎች፤ በክህሎት የበቁ ዜጎች'' በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን ለ5 ተከታታይ ቀናት በልዩ ልዩ ሁነቶች እየተስተናገደ ለጎበኝዎች ክፍት ተደርጎ እንደሚቆይ ተነግሯል።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
15ኛው የቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት ዐውደ ርዕይ ተጀመረ፡፡
15ኛው የቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት ዐውደ ርዕይ ዛሬ ሰኔ 7 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ኤግዚቪሸን ማዕከል ለጎብኝዎች ዕይታ ክፍት ተደረገ፡፡
በመክፈቻ መርሃ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ #አዳነች #አቤቤ፣ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ #ጥራቱ #በየነን ጨምሮ የፌደራል እና የከተማ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
በዕለቱ የመዲናይት ከንቲባ በመልዕክታቸው "ችግር ፈቺ ተኪ ምርቶችን በማምረት ሂደት የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች እያበረከቱት ያለው አስተዋጽኦ የሚበረታታ ነው" ብለዋል።
ክብርት ከንቲባዋ አያይዘውም በቅርቡ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው የክህሎት ውድድር በከተማ አስተዳደሩ አጠቃላይ አሸናፊነት በመጠናቀቁ የዘርፉን አመራሮችና ባለሙያዎች አመስግነዋል።
መንግስት ከለውጡ ማግስት ጀምሮ ለዘርፉ ልዪ ትኩረት በመስጠትና በአዳዲስ እሳቤ በመቃኘት ለሀገራዊ ዕድገትና ብልፅግና መረጋገጥ ዋስትና እየሆነ መጥቷል ያሉት ደግሞ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር #አቶ #ጥራቱ #በየነ ናቸው፡፡
በዚህ ኤግዚቪሽን ላይ በ15ቱ የመንግስት ኮሌጆች በሚገኙ አሰልጣኞች፣ ሰልጣኞች እና ኢንተርፕራይዞች የተሰሩ ከ150 በላይ ችግር ፈቺ የማምረቻ እና የምርት ቴክኖሎጂ ውጤቶች በአውደ ርዕዩ ላይ ቀርቧል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ የተሰሩ 5 የማምረቻ እና 6 የምርት ውጤቶች ለጎብኝዎች ቀርበዋል፡፡
በተጨማሪም በኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ የሚደረግላቸው 2 ኢንተርፕራይዞች የፈጠራ ምርታቸውን ይዘው ተገኝተዋል፡፡
ኤግዚቪሽኑ ''ብሩህ አዕምሮዎች፤ በክህሎት የበቁ ዜጎች'' በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን ለ5 ተከታታይ ቀናት በልዩ ልዩ ሁነቶች እየተስተናገደ ለጎበኝዎች ክፍት ተደርጎ እንደሚቆይ ተነግሯል።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››