እሁድ:- ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም
ሀገራዊ ለውጡን ተከተሎ በተመዘገቡ ለውጦችና በተፈጠሩ ተግዳሮቶች ዙሪያ ወይይት ተካሄደ!!
ሀገራዊ ለውጡን ተከተሎ በተመዘገቡ ዘርፈ ብዙ ለውጦችና በተከሰቱ ተግዳሮቶች እንዲሁም በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ ከኮሌጁ አሰልጣኞች ጋር ውይይት እየተካሄደ ይገኛል፡፡
"የበቃ አሰልጣኝ ክህሎት የጨበጠ ወጣት ለሀገር ብልፅግና!" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለውን ውይይት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ #ጥራቱ #በየነ ከማዕከል በገለፃ አቅረበዋል።
ክቡር አቶ ጥራቱ በገለፃቸው እንደ ሀገር የመጡ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና የወጪ ግንኙነት ፖሊሲና ዲፕሎማሲ ስኬቶችን እንዲሁም ሀገራዊ ለውጡን የፈተኑ ውስጣዊና ወጫዊ ተግዳሮቶችን አብራርተዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም ብቁ ባለሙያ በማፍራትና የቴክኖሎጂ ሽግግር በማድረግ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ለሀገራዊ ብልፅግና ያላቸው ሚና ትልቅ መሆኑን አውስተዋል፡፡ በገለፃው የመዲናቱ ኮሌጆች ያሉበትን ነባራዊ ሁኔታ በጥንካሬና በክፍተት ማሳየት ተችሏል፡፡
በቀረበው ገለፃ መሰረት ከኮሌጁ አሰልጣኞች የተለያዩ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች እየተነሱ ሲሆን የውይይት መድረኩን በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዝና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ #አቶ #መሀመድ #ልጋኒ እና የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ #መለሰ #ይግዛው እየመሩት ይገኛሉ፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ሀገራዊ ለውጡን ተከተሎ በተመዘገቡ ለውጦችና በተፈጠሩ ተግዳሮቶች ዙሪያ ወይይት ተካሄደ!!
ሀገራዊ ለውጡን ተከተሎ በተመዘገቡ ዘርፈ ብዙ ለውጦችና በተከሰቱ ተግዳሮቶች እንዲሁም በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ ከኮሌጁ አሰልጣኞች ጋር ውይይት እየተካሄደ ይገኛል፡፡
"የበቃ አሰልጣኝ ክህሎት የጨበጠ ወጣት ለሀገር ብልፅግና!" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለውን ውይይት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ #ጥራቱ #በየነ ከማዕከል በገለፃ አቅረበዋል።
ክቡር አቶ ጥራቱ በገለፃቸው እንደ ሀገር የመጡ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና የወጪ ግንኙነት ፖሊሲና ዲፕሎማሲ ስኬቶችን እንዲሁም ሀገራዊ ለውጡን የፈተኑ ውስጣዊና ወጫዊ ተግዳሮቶችን አብራርተዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም ብቁ ባለሙያ በማፍራትና የቴክኖሎጂ ሽግግር በማድረግ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ለሀገራዊ ብልፅግና ያላቸው ሚና ትልቅ መሆኑን አውስተዋል፡፡ በገለፃው የመዲናቱ ኮሌጆች ያሉበትን ነባራዊ ሁኔታ በጥንካሬና በክፍተት ማሳየት ተችሏል፡፡
በቀረበው ገለፃ መሰረት ከኮሌጁ አሰልጣኞች የተለያዩ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች እየተነሱ ሲሆን የውይይት መድረኩን በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዝና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ #አቶ #መሀመድ #ልጋኒ እና የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ #መለሰ #ይግዛው እየመሩት ይገኛሉ፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››