Ethiopian Airlines የኢትዮጵያ አየር መንገድ
90.5K subscribers
3.74K photos
140 videos
2 files
410 links
ይህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።
Download Telegram
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው በአፍሪካ አህጉር ሁለንተናዊ ዕድገትና ብልፅግና ላይ አተኩሮ በጋና አክራ በተካሄደው አመታዊው የ “2025 የአፍሪካ ፕሮስፔሪቲ ዲያሎግ” ላይ አፍሪካን በአየር ትራንስፖርት በማገናኘት ረገድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እየተጫወተ ላለው ሚና ላሳዩት የላቀ የአመራርነት ሚና የ “Leadership in Connecting Africa through Transport Award” ተሸላሚ ሆነዋል።
ይህ ሽልማት አፍሪካን እርስ በርስ በማገናኘት ቁርጠኛ የአመራርነት አስተዋፅዖ ላበረከቱ ግለሰቦች ዕውቅና የሚሰጥበት ሲሆን የዘንድሮው የ “2025 የአፍሪካ ፕሮስፔሪቲ ዲያሎግ” የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ የታላላቅ አህጉር ዓቀፍ የንግድ ተቋማት መሪዎች እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች በተገኙበት በጋና አክራ ተካሂዷል። ለተጨማሪ ንባብ ሊንኩን ይጫኑ https://corporate.ethiopianairlines.com/Press-release-open-page/ethiopian-airlines-group-ceo-honored-with-prestigious-leadership-in-connecting-africa-through-transport-award
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የበረራ አድማሱን ከግዜ ወደ ግዜ እያሰፋ የመጣው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ተጨማሪ አዳዲስ አለም ዓቀፍ መዳረሻዎች በረራ ለመጀመር ዝግጅቱን አጠናቅቋል።
እነዚህ አዳዲስ መዳረሻዎቻችንን መገመት ይችላሉ?

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ወደ በርካታ አለም ዓቀፍ መዳረሻዎቻችን አብረውን ይጓዙ!

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ ሰኔ9 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በህንድ 5ኛ የመንገደኛ በረራ መዳረሻ ወደምትሆነው ሀይድራባድ ከተማ በሳምንት ሶስት ቀን የሚደረግ አዲስ በረራ እንደሚጀምር ሲያበስር በደስታ ነው። የዚህ በረራ መጀመር በህንድ የሚኖረንን የበረራ አድማስ ከማስፋቱም በተጨማሪ በአፍሪካ እና እስያ መካከል ያለውን ዘርፈብዙ ግንኙነት ከፍ የሚያደርግ ነው። ትኬትዎን በድረገፃችን www.ethiopianairlines.com አሊያም በተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያችን https://www.ethiopianairlines.com/aa/ethiopian-app በመቁረጥ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሀይድራባድ ይጓዙ።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
አስደናቂ የሆኑትን የኢትዮጵያን የተፈጥሮ መስህቦች ይጎብኙ። የኢትዮጵያ ሆሊደይስ በሚያዘጋጃቸው የተለያዩ የጉዞ ጥቅሎች ተጠቅመው ጥንታዊ የተፈጥሮ መስህቦችንና ማራኪ መልከዓምድሮችን ይጎብኙ። ስለጉዞ ጥቅሎቹ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ድረገፃችንን www.ethiopianholidays.com ይጎብኙ አልያም በኢሜይል አድራሻ ETHolidays@ethiopianairlines.com. ይፃፉልን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ኢቲሆሊደይስ #ምድረቀደምት
ፍፁም ኢትዮጵያዊ መስተንግዶ አለም ዓቀፍ ደረጃውን ከጠበቀ አገልግሎት ጋር በኢትዮጵያ አየር መንገድ! ትኬትዎን በድረገፃችን www.ethiopianairlines.com አሊያም በተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያችን https://www.ethiopianairlines.com/aa/ethiopian-app ይቁረጡ።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የዛሬውን #የመስኮትምልከታ ያጋሩን @BianoAbel ናቸው፤ እናመሰግናለን! እርስዎም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሲበሩ ያነሷቸውን ምስሎች ይላኩልን፤ መልሰን እናጋራዎታለን።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
አፍሪካን እርስ በርስ እና ከተቀረው ዓለም ጋር በማገናኘት ለዘመናት በስኬት የዘለቀ ፓን-አፍሪካዊ አየር መንገድ!

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በአዲስ አበባ ቦሌ አለም ዓቀፍ የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል ውስጥ ከምንሰጣቸው የደንበኞች አገልግሎት መካከል የቢዝነስ ክፍል (Cloud Nine) ላውንጅ ይገኝበታል። በዚህ ላውንጅ ውስጥ ከተለያዩ ሀገራት የመጡ መንገደኞች ዘርፈ ብዙ አገልግሎት ከማግኘታቸውም በተጨማሪ ከኢትዮጵያ ባህልና የቱሪስት መስህቦች ጋር የሚተዋወቁበትም ስፍራ ነው። የዛሬው “የኢትዮጵያ” መርሐግብር በዚህ ላይ ያተኮረ ነው፤ ይከታተሉን!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት መስራች መሪዎች የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን ለመመስረት በሚያደርጉት ያላሰለሰ ትጋት ወደተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ለሚያደርጓቸው በረራዎች የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሚና የላቀ ነበር።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ፓንአፍሪካዊአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ከመስጠት በተጨማሪ የአፍሪካ ሀገራትን በባህል እና በበርካታ እድሎች ያስተሳሰረ እንዲሁም አህጉሪቱን ከሌሎች የአለም ሀገራት ጋር በቀላሉ እንድትገናኝ እንደ ድልድይ ሆኖ እያገለገለ ያለ ፓን-አፍሪካዊ አየር መንገድ ነው።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እውነተኛ የአፍሪካ አቪዬሽን ተምሳሌት የመሆን ርእይ አንግቦ የራሱን የአቪዬሽን አካዳሚ በመመስረት እና ለበርካታ የአፍሪካ ሀገራት ተደራሽ በመሆን ሀገራቱ የራሳቸው አየር መንገድ እንዲያቋቁሙ አስችሏል። ዛሬ ወደ ዩኒቨርስቲ ደረጃ ያደገው ይህ አካዳሚ ከመላው የአፍሪካ ሀገራት ለሚመጡ የአቪዬሽን ሰልጣኞች ተደራሽ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ ነጻ የአየር ትራንስፖርት እንቅስቃሴን ለመፍጠር እንዲሁም የአፍሪካን ቀጠናዊ እና አህጉራዊ ትስስር እጅግ የተቀላጠፈ ከማድረግ ባሻገር በንግድ፣ በቱሪዝም እና በመሰረተ ልማት የተሳሰረች አፍሪካን እውን ለማድረግ በማሰብ በአፍሪካ ህብረት ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን "The Single African Air Transport Market" (SAATM) የተሰኘ አጀንዳ እውን እንዲሆን የአንበሳውን ደርሻ እየተወጣ ይገኛል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ፓንአፍሪካዊአየርመንገድ
የኡጋንዳ ሪፐብሊክ ምክትል ፕሬዝደንት ክብርት ጄሲካ አሉፖ በ38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ስብሰባ ለመካፈል የኢትዮጵያ አየር መንገድን መርጠው ከእኛ ጋር ስለተጓዙ ክብር ይሰማናል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ፓንአፍሪካዊ