የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ20% ቅናሽ ከአዲስ አበባ ወደ አሜሪካ በሚደረጉ በረራዎች ላይ አድርጓል። ልብ ይበሉ ፤ ይህ ልዩ ቅናሽ እስከ ነሐሴ 25 2016 ድረስ የሚቆይ ሲሆን ጉዞዎን ከጳጉሜ 1 ፣ 2016 እስከ መስከረም 2 ፣ 2017 ዓ.ም ያድርጉ። ይፍጠኑ ይህ አስደናቂ ቅናሽ እንዳያመልጥዎ!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሰኞ ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ከአዲስ አበባ መቐለ እንዲሁም ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ የምሽት በረራ የሚጀምር መሆኑን ለክቡራን ደንበኞቹ ይገልፃል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ከጉዞዎ መጀመሪያ እስከ መዳረሻዎ ድረስ እየተንከባከብን ካሰቡበት እናደርስዎታለን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ኢትዮጵያ! ምድረ ቀደምት!
በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቅርቡ የሚረከበው የኤርባስ A350-1000 የመጨረሻ የቀለም ቅብ እና መለያ ሲደረግለት የሚያሳየውን ተንቀሳቃሽ ምስል እነሆ!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ኢትዮጵያ #ምድረቀደምት
በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቅርቡ የሚረከበው የኤርባስ A350-1000 የመጨረሻ የቀለም ቅብ እና መለያ ሲደረግለት የሚያሳየውን ተንቀሳቃሽ ምስል እነሆ!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ኢትዮጵያ #ምድረቀደምት
የዛሬውን #የመስኮትምልከታ ያጋሩን @Zelalem Alemenew ናቸው፤ እናመሰግናለን! እርስዎም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሲበርሩ ያነሷቸውን ምስሎች ይላኩልን፤ መልሰን እናጋራዎታለን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ልዩ ኢትዮጵያዊ መስተንግዶ እና ልብ የሚያሞቅ ፈገግታ በጉዞዎ ሁሉ ይጠብቅዎታል!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአሜሪካ የትራንስፖርት ደህንነት አስተዳደር (TSA) የተቀላጠፈ የኤርፖርት ውስጥ የደህንነት ፍተሻ (TSA PreCheck®) ፕሮግራም አባል ሆነ። የዚህ ፕሮግራም አባልነት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሚበርባቸው በአሜሪካ ከሚገኙ ኤርፖርቶች የሚነሱ መንገደኞች የተቀላጠፈ፣ ይበልጥ ምቹ እና ደህንነቱ የተጠበቀ የቅድመ በረራ አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላቸዋል። ለበለጠ ንባብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ።
https://rb.gy/59mf4r
https://rb.gy/59mf4r
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አመራሮችና ሠራተኞች የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር ተሳትፏቸውን በመቀጠል በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ በተለምዶው አየር መንገድ ጀርባ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የአረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው አየር መንገዱ የአካባቢ ጥበቃን እንደ አንድ ማህበራዊ ሀላፊነት ይዞ እየሰራ መሆኑን አስታውቀው ከችግኝ ተከላ በተጨማሪም ለአካባቢ ምቹ እና ተስማሚ የሆኑ የአቪዬሽን ቴክኖሎጂዎችን ጥቅም ላይ በማዋል የራሱን አስተዋፅዖ እያደረገ መሆኑን ገልፀዋል። አዳዲስ እና ዘመናዊ አውሮፕላኖችን የበረራ አገልግሎት ላይ በማዋል፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ በአየር መንገዶች በሚደረገው ርብርብ አካል በመሆን የካርበን ልቀትን በከፍተኛ ደረጃ የሚቀንሰውን ዘላቂ የአቪዬሽን ነዳጅ (Sustainable Aviation Fuel) በመጠቀም እንዲሁም ቁሳቁሶችን መልሶ በመጠቀም (Recycling) ለአካባቢ ደህንነት መጠበቅ የራሱን ጉልህ ድርሻ እየተወጣ መሆኑን አስታውሰዋል።
40 ሄክታር በሚሆን ስፍራ ላይ 16 አይነት ሀገር በቀል የሆኑ 50 ሺህ ችግኞች ለመትከል ዕቅድ የተያዘ ሲሆን እስካሁን 27 ሺህ ያህል ችግኞች ተተክለዋል። ። የተቋሙ ሰራተኞች የተተከሉትን ችግኞች በመንከባከብ ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡና በቀጣይም የአረንጓዴ አሻራ ተሳትፏቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #አረንጓዴአሻራ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው አየር መንገዱ የአካባቢ ጥበቃን እንደ አንድ ማህበራዊ ሀላፊነት ይዞ እየሰራ መሆኑን አስታውቀው ከችግኝ ተከላ በተጨማሪም ለአካባቢ ምቹ እና ተስማሚ የሆኑ የአቪዬሽን ቴክኖሎጂዎችን ጥቅም ላይ በማዋል የራሱን አስተዋፅዖ እያደረገ መሆኑን ገልፀዋል። አዳዲስ እና ዘመናዊ አውሮፕላኖችን የበረራ አገልግሎት ላይ በማዋል፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ በአየር መንገዶች በሚደረገው ርብርብ አካል በመሆን የካርበን ልቀትን በከፍተኛ ደረጃ የሚቀንሰውን ዘላቂ የአቪዬሽን ነዳጅ (Sustainable Aviation Fuel) በመጠቀም እንዲሁም ቁሳቁሶችን መልሶ በመጠቀም (Recycling) ለአካባቢ ደህንነት መጠበቅ የራሱን ጉልህ ድርሻ እየተወጣ መሆኑን አስታውሰዋል።
40 ሄክታር በሚሆን ስፍራ ላይ 16 አይነት ሀገር በቀል የሆኑ 50 ሺህ ችግኞች ለመትከል ዕቅድ የተያዘ ሲሆን እስካሁን 27 ሺህ ያህል ችግኞች ተተክለዋል። ። የተቋሙ ሰራተኞች የተተከሉትን ችግኞች በመንከባከብ ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡና በቀጣይም የአረንጓዴ አሻራ ተሳትፏቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #አረንጓዴአሻራ