የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአረንጓዴ አሻራ መርሐ- ግብር አንድ መቶ ሺህ ችግኞችን ለመትከል የያዘውን እቅድ ለመተግበር የአየር መንገዳችን አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት የመጀመሪያውን ዙር የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር በዛሬው እለት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 አካሂዷል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ መሰል ተግባራትን በሰራተኞቹ፣ በማኔጅመንት አባላት እንዲሁም በመንገደኞቹ ስም ሲያከናውን የቆየ ሲሆን ፣ ይህ ተግባር አየር መንገዱ ማህበራዊ ሃላፊነቱን ከሚወጣባቸው መንገዶች አንዱ ነው ። በቀጣይ ዙሮችም በንፋስ ስልክ ላፍቶ እና ለሚ ኩራ ክፍለ ከተሞች ተመሳሳይ የችግኝ ተከላ መርሐ- ግብሮችን በተከታታይ ያካሂዳል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #አረንጓዴአሻራ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #አረንጓዴአሻራ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አመራሮችና ሠራተኞች የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር ተሳትፏቸውን በመቀጠል በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ በተለምዶው አየር መንገድ ጀርባ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የአረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው አየር መንገዱ የአካባቢ ጥበቃን እንደ አንድ ማህበራዊ ሀላፊነት ይዞ እየሰራ መሆኑን አስታውቀው ከችግኝ ተከላ በተጨማሪም ለአካባቢ ምቹ እና ተስማሚ የሆኑ የአቪዬሽን ቴክኖሎጂዎችን ጥቅም ላይ በማዋል የራሱን አስተዋፅዖ እያደረገ መሆኑን ገልፀዋል። አዳዲስ እና ዘመናዊ አውሮፕላኖችን የበረራ አገልግሎት ላይ በማዋል፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ በአየር መንገዶች በሚደረገው ርብርብ አካል በመሆን የካርበን ልቀትን በከፍተኛ ደረጃ የሚቀንሰውን ዘላቂ የአቪዬሽን ነዳጅ (Sustainable Aviation Fuel) በመጠቀም እንዲሁም ቁሳቁሶችን መልሶ በመጠቀም (Recycling) ለአካባቢ ደህንነት መጠበቅ የራሱን ጉልህ ድርሻ እየተወጣ መሆኑን አስታውሰዋል።
40 ሄክታር በሚሆን ስፍራ ላይ 16 አይነት ሀገር በቀል የሆኑ 50 ሺህ ችግኞች ለመትከል ዕቅድ የተያዘ ሲሆን እስካሁን 27 ሺህ ያህል ችግኞች ተተክለዋል። ። የተቋሙ ሰራተኞች የተተከሉትን ችግኞች በመንከባከብ ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡና በቀጣይም የአረንጓዴ አሻራ ተሳትፏቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #አረንጓዴአሻራ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው አየር መንገዱ የአካባቢ ጥበቃን እንደ አንድ ማህበራዊ ሀላፊነት ይዞ እየሰራ መሆኑን አስታውቀው ከችግኝ ተከላ በተጨማሪም ለአካባቢ ምቹ እና ተስማሚ የሆኑ የአቪዬሽን ቴክኖሎጂዎችን ጥቅም ላይ በማዋል የራሱን አስተዋፅዖ እያደረገ መሆኑን ገልፀዋል። አዳዲስ እና ዘመናዊ አውሮፕላኖችን የበረራ አገልግሎት ላይ በማዋል፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ በአየር መንገዶች በሚደረገው ርብርብ አካል በመሆን የካርበን ልቀትን በከፍተኛ ደረጃ የሚቀንሰውን ዘላቂ የአቪዬሽን ነዳጅ (Sustainable Aviation Fuel) በመጠቀም እንዲሁም ቁሳቁሶችን መልሶ በመጠቀም (Recycling) ለአካባቢ ደህንነት መጠበቅ የራሱን ጉልህ ድርሻ እየተወጣ መሆኑን አስታውሰዋል።
40 ሄክታር በሚሆን ስፍራ ላይ 16 አይነት ሀገር በቀል የሆኑ 50 ሺህ ችግኞች ለመትከል ዕቅድ የተያዘ ሲሆን እስካሁን 27 ሺህ ያህል ችግኞች ተተክለዋል። ። የተቋሙ ሰራተኞች የተተከሉትን ችግኞች በመንከባከብ ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡና በቀጣይም የአረንጓዴ አሻራ ተሳትፏቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #አረንጓዴአሻራ