Ethiopian Airlines የኢትዮጵያ አየር መንገድ
90.5K subscribers
3.78K photos
142 videos
2 files
413 links
ይህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።
Download Telegram
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምንግዜም ለመንገደኞቹ ምቹ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለመስጠት ብሎም የአቪዬሽን ኢንደስትሪው የደረሰበትን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ስራ ላይ ለማዋል ባለው ቁርጠኝነት የቦይንግ አዲስ ምርት የሆኑትን በቅርብ ግዜ እና በሂደት የሚረከባቸውን የ20 ቦይንግ 777-9 አውሮፕላኖችን ለማስገባት የሚያስችለውን ስምምነት ዛሬ ከቦይንግ ጋር ተፈራርሟል። የB777-9 አውሮፕላን የቦዪንግ ስሪት የሆኑትን የB777 እና B787 አውሮፕላኖች ቴክኖሎጂዎችን ቀምሮ የያዘ የቦዪንግ ኩባንያ የቅርብ ጊዜ ምርት ነው። እንደከዚህ ቀደም ሁሉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይህንን አዲስ እና ግዙፍ አውሮፕላን በማዘዝ በአፍሪካ ቀዳሚው ሆኗል። ስምምነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የቦዪንግ ኩባንያ ለአስርት-ዓመታት የገነቡትን የንግድ ስምምነት የሚያጠናክር ነው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሰኔ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በቦትስዋና ሁለተኛ መዳረሻችን ወደሆነችው የማውን ከተማ በሳምንት ሶስት ቀን የመንገደኞች በረራ የሚጀምር መሆኑን ሲያበስር በታላቅ ደስታ ነው። ይህን መልካም አጋጣሚ ተጠቅመው የማውን ከተማን አስደናቂ ውበት ለመጎብኘት ትኬትዎን በመግዛት የመጀመሪያው ይሁኑ!

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ዓመታዊው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ሊከበር እነሆ አንድ ቀን ቀርቶታል። የኢትዮጵያ አየር መንገድም ይህን ቀን በሴቶች ብቻ በሚደረግ በረራ ሲያከብረው ቆይቶ የዘንድሮውንም የሴቶች ቀን በተመሳሳይ መልኩ በድምቀት ሊያከብር ዝግጅቱን አጠናቅቋል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ዓለምአቀፍየሴቶችቀን
ዓመታዊው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በኢትዮጵያ ስካይላይት ሆቴል የመንግስት ሀላፊዎች፣ ዲፕሎማቶችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በደመቀ መልኩ ተከብሯል። የኢትዮጵያ አየር መንገድም ይህን ቀን አስመልክቶ ወደ እንግሊዝ ለንደን በሴቶች ብቻ የሚደረግ በረራ ያደርጋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ዓለምአቀፍየሴቶችቀን
የማይረሳ የበረራ ትዉስታ ከእርስዎ ጋር ለማድረግ ዝግጅታችንን ጨርሰናል። ብሩህ የእረፍት ቀናት ተመኘንልዎ!

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ከአፍሪካ ኩራት ጋር ከፍ ብለን እንብረር!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
በላቀ አገልግሎታችን እየተደሰቱ ከእኛ ጋር በምቾት ይብረሩ። #የኢትዮጵያአየርመንገድ
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለረመዳን ፆም በሰላም አደረሳችሁ። ረመዳን ከሪም!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰሞኑን በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ከመንገደኞች አገልግሎት አሠጣጥ ጋር በተያያዘ በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ቅሬታዎች እየተነሱ መሆኑን ተገንዝቧል።
አየር መንገዱ ከክቡራን ደንበኞቹ ለሚቀርቡ ቅሬታዎች እና አስተያየቶች ከፍተኛ ትኩረት የሚሠጥ በመሆኑ ሂደቱን በጥሞና ሲከታተል ቆይቷል።
በመሆኑም እየተሰሙ ያሉ ቅሬታዎችን መርምሮ መፍትሄ ለመስጠት አየር መንገዱ በአዲስ አበባ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ አገልግሎት ከሚሰጡ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ቅሬታዎችን የማጣራት ስራ እየሠራ መሆኑን ለማሣወቅ እንወዳለን።
ይህንንም ተከትሎ በማጣራቱ ሥራ ላይ በሚገኙ ውጤቶች ላይ በመመርኮዝ ተገቢው የማስተካከያ እርምጃ በፍጥነት እንዲወሠድ ይደረጋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሁልጊዜም ጥረቱ ለውድ ደንበኞቹ ቀልጣፋ እና ምቹ አገልግሎት መስጠት ነው። አሁንም የክቡራን ደንበኞቹን ጥቆማ ተቀብሎ አስፈላጊውን ማስተካከያ በማድረግ ይህንኑ ጥረቱን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በአክብሮት እንገልጻለን።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ‘የኢትዮጵያ ተቋማት የስኬት ሽልማት’ን ተቀዳጀ። ብሔራዊ አየር መንገዱ ሽልማቱን ከክቡር የኢፊዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እጅ ተቀብሏል። አየር መንገዳችን በአህጉር አቀፍ ደረጃ ላሳየው አመርቂ እድገት በተለይም በኮሮና ወረርሽኝ ጊዜ ላበረከተው ዓለም-አቀፍ አስተዋጽኦ ሽልማቱ ተበርክቶለታል። ሽልማቱን አቶ መስፍን ጣሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ ተቀብለዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚው ሽልማቱ ‘የመላው የአየር መንገዱ ሰራተኛ የትጋት ውጤት' መሆኑን ተናግረዋል። #የኢትዮጵያአየርመንገድ
የዛሬውን #የመስኮትምልከታ ያጋሩን shalom.shewamoltot ናቸው፤ እናመሰግናለን! እርስዎም ከእኛ ጋር ሲበሩ ያነሱትን ምስል በመልዕክት መቀበያ ሳጥን በኩል ይላኩልን መልሰን እናጋራዎታለን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
በረራዎን ምቹ እና አስደሳች ለማድረግ ሁልጊዜም እንተጋለን።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ወደ ህልምዎ መዳረሻ በምቾት ልናደርስዎ ተዘጋጅተናል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ